Translate

Monday, September 24, 2012

የአሜሪካ መንግስት የአቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ሹመት ታሪካዊ ነው አለ


ኢሳት ዜና:-የፕሬዚዳንት ኦባማ አስተዳደር በኢትዮጵያ የታየው የስልጣን ሽግግር ታሪካዊ፣ ሰላማዊና ህገመንግስታ ነው በማለት አወድሶታል።
አሜሪካ ከአቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ጋር ጥሩ የሆነ ግንኙነት መመሰርቷን የገለጠው መግለጫ ፣ በሚቀጥሉት አመታት የኢኮኖሚ ግንኙነቱን ለማጠንከር፣ ሰብአዊ መብቶችንና ዲሞክራሲን ለማጎልበት እንዲሁም የአካባቢውን ጸጥታ ለማስጠበቅ ከእርሳቸው ጋር በጋራ እንደሚሰራ አስተዳደሩ ገልጧል።
የአሜሪካ መንግስት አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው እንዲመረጡ ግፊት ማድረጓን የተለያዩ ድረገጾች መዘገባቸው ይታወሳል። ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ አቶ ሀይለማርያም ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ከመመረጣቸው በፊት ስልክ ደውለው አነጋግረዋቸው እንደነበር መዘገቡ ይታወሳል።
የኦባማ አስተዳዳር በገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ላይ በቂ ግፊት ባለማሳደሩ በኢትዮጵያ ውስጥ ዲሞክራሲ እንዳይዳብር ና የሰብአዊ መብቶች እንዳይከበሩ ምክንያት ሆኗል በማለት ይተቻል።
በእስር ላይ የሚገኙትን ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ አንዱአለም አራጌና ሌሎችንም የህሊና እስረኞች የኦባማ አስተዳዳር ለማስፈታት ያደረገው ጥረት አለመኖር፣ ብዙ ኢትዮጵያውያን በኦባማ አስተዳዳር ላይ ያላቸውን ነቀፌታ ይሰነዝራሉ።

No comments:

Post a Comment