Translate

Monday, November 30, 2015

በምህራብ ኦሮሚያ የተጀመረው ተቃውሞ እንደቀጠለ ነው


በምዕራብ ወለጋ በመንዲ እና ጉሊሶ “መንግሥት አድማ በታኞችንና የአግዓዚ ጦርን አሠማርቶ ብዙ ተማሪዎችንና የከተማዪቱን ነዋሪዎች በቁጥጥር ሥር አውሏል” ሲል አንድ ስሙ እንዳይገለፅ የጠየቀ ነዋሪ ከቪኦኤ ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ ገልጿል።
“በተጨማሪም ከላይ በተጠቀሰው ዞን ውስጥ ጉሊሶ በተባለ ከተማም እንዲሁ ዛሬው ተማሪዎች የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ እንደተሰባሰቡ ፖሊስ በአድማ በታኝ ጢስ ሠልፉን በትኗል” ስትል አንዲት ተማሪ ገልፃለች።

ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ቁስለኛ ወታደሮች ዳሽ-6 በተባለ አውሮፕላንና ኤም.አይ-17 ሄሊኮፕተር ከሶማሊያ አየተጫኑ ድሬ ደዋ ላይ በመራገፍ ላይ ናቸው፡፡

Patriotic Ginbot 7's photo.
ራሱን በመንግስትነት ስም የሚጠራው የማፍያው ቡድን ህወሓት የምዕራባዊያንን ቁሳዊና ፖለቲካዊ ድጋፍ በማግኘት ስልጣኑን ለማደላደል ሲል ብቻ ከ10 ዓመታት በፊት ማለትም ከ1998 ዓ.ም ጀምሮ የድሃው የኢትዮጵያ ህዝብ ልጅ የሆኑ የመከላከያ ሰራዊት አባላትን ያለማቋረጥ ወደ ሶማሊያ በረሃማ ምድር እያስገባ እጅግ በጣም አሰቃቂ ለሆነ እልቂት እየዳረጋቸው ይገኛል፡፡ 

ሳዑዲ ዓረቢያና ዩናይትድ ዓረብ ኤምሬትስ በየመን ላይ እያደረጉት ላለው ጦርነት የአሰብ ወደብ ለ30 ዓመታት ተከራዩት

የተባበሩት መንግሥታት የቁጥጥር ቡድን ያወጣቸው መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከሆነ፣ ሳዑዲ ዓረቢያና ዩናይትድ ዓረብኤምሬትስ በየመን ላይ እያደረጉት ላለውጦርነት የአሰብ ወደብ 30 ዓመታት እንደተከራዩት፣ የኤርትራ ወታደሮች በየመኑ ውግያ ላይ እየተሳተፉ መሆናቸውንና የጦር መሣሪያም ወደ ኤርትራ እየገባመሆኑን ይፋ አድርጓል፡፡

Thursday, November 26, 2015

አሜሪካ፡ የሰብአዊያን የመጨረሻ ታላቅ ተስፋ ከኢ-ሰብያዉያን ኪሳራ ማዳን

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
ከናዚ ጀርመን ሰው ልጅ እልቂት የተረፉት እና የኖቤል ተሸላሚ የነበሩት ኤሊ ዊሰል በአንድ ወቅት እንዲህ ብለው ነበር፣ “ኢፍትሐዊነትን ለመከላከል የማንችልበት እና አቅመቢስ የምንሆንበት ጊዜ ሊኖር ይችላል፣ ሆኖም ግን ኢፍትሐዊነትን የምንቃወምበት ጊዜ በምንም ዓይነት ሁኔታ እና በምንም ዓይነት መንገድ በፍጹም ማጣት የለብንም፡፡“America: Saving the Last Great Hope of Humanity
እኔ ደግሞ እንዲህ የሚል አባባል እጨምርበታለሁ፣ ”በቢሮ ተወሽቀው የሚገኙትን የፖለቲካ አስመሳይ እብዶችን እና ምንም ዓይነት ሀሳብ ማመንጨት የማይችሉ እርባና ቢስ የሀሳብ ድሁር ፖለቲከኞችን የምንቃወምበት ጊዜ በምንም ዓይነት መልከኩ እና በምንም ዓይነት መንገድ በፍጹም ማጣት የለብንም፡፡“
የሬፐብሊካን ፓርቲ ዕጩ ፕሬዚዳንት የሆኑት ዶናልድ ትሩምፕ ባለፈው ሳምንት “በዩናይትድ ስቴትስ አሜሪክ የሚገኙ የሙስሊሙን ማህበረሰብ የመረጃ ቁጥጥርን ፍጹም በሆነ መልኩ አካትቶ የሚይዝ የመረጃ ቋት ስርዓት በመንደፍ ተግባራዊ አደርጋለሁ“  ብሎ ነበር፡፡

Wednesday, November 25, 2015

“ረሃቡና ኢህአዴጋዊ እውነታዎች!” (ኤርሚያስ ለገሰ)

ኤርሚያስ ለገሰ

ህወሃት መራሹ መንግስት በኢትዮጵያ ውስጥ ረሃብ በተከሰተ ቁጥር የረሃቡን ዋነኛ ምንጭ “የአየር ንብረት መዛባት” በሚል ውጫዊ ምክንያት ማላከኩ የተለመደ ሆኗል። ለአብነት ያህል የዛሬ ዘጠኝ አመት በኢትዮጵያ ረሃብ በተነሳ ወቅት “የሰሞኑ የረሃብ ፖለቲካ” በሚል ረዕስ የውስጥ ድርጀት ሰነድ ተዘጋጅቶ ነበር ደራሲው ጓድ መለስ ዜናዊ ነበሩ። በማስከተልም የፓርቲው ከፍተኛ ካድሬዎች እና የመንግስት ባለስልጣናት ውይይት እንዲያደርጉበት ተደረገ። በዚህ ሰነድ ገፅ 6 ላይ የረሃቡን ዋነኛ ምንጭ እንደሚከተለው ይገልጻል።Ermias Legesse of ESAT
“ረሃቡ ከምን እንደሚመነጭ በትክክል ማስቀመጥ መፍትሄውን ለማስቀመጥ ወሳኝ ነው። የረሃቡ ቀጥተኛ ምንጭ ከአየር ንብረት መዛባት ጋር ተያይዞ የተከሰተው ድርቅ ነው። የአየር ንብረቱ መዛባትና ድርቁ እኛ ያልፈጠርነው ልናስተካክለው የማንችለው ነባራዊ ሃቅ ነው። በዚህ ነባራዊ ሁኔታ ማዕቀፍ ድርቁን ተቋቁመን ረሃቡን ለማስወገድ ያስቀመጥነው ስትራቴጂ ተዓምር ሰሪነቱ በንድፈ ሃሳብ ደረጃ ብቻ ሳይሆን በተግባር ተረጋግጧል። የረሃቡ ዋነና ምንጭም የአየር ንብረት መዛባትና ድርቅ ነባራዊ ሁኔታን መቋቋም ረሃብን ለማጥፋት የቀየስነው ስትራቴጂ በሚፈለገው ፍጥነት በሁሉም አካባቢዎችን ስላልተፈጸመ ነው” ይላል።

Tuesday, November 24, 2015

“ገበሬው ነፃነት ካላገኘ ችጋር ሁልጊዜ በኢትዮጵያ ይኖራል” ፕሮፌሰር መስፍን

farmer
* “ችጋር የሰው ልጅ እንደ ማገዶ እንጨት ተለብልቦ የሚያልቅበት የውርደት ሞት ነው”
ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ (Institute of Development Research) ሥር ከ1967 ዓ.ም. ጀምሮ ለ10 ዓመታት ያህል በ102 የኢትዮጵያ አውራጃዎች ላይ ምርምር አድርገው ስለ ድርቅ በእርሳቸው አጠራር (ስለ ችጋር) (Rural vulnerability to famine in Ethiopia 1958-1977) የሚል መጽሐፍ ጽፈዋል። የእንቢልታ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል በዛሬው እትማችን ለበርካታ ዓመታት በድርቅ ጉዳይ ያካሄዱትን የምርምር ሥራ መሠረት አድርገን በወቅታዊው የአገሪቱ የድርቅ ሁኔታ ላይ ከጽዮን ግርማ ጋር ቆይታ አድርገዋል። (ዓርብ መጋቢት 26 ቀን 2000 ዓ.ም)

Sunday, November 22, 2015

“የየጁ ደብተራ…” | በኤርሚያስ ለገሰ


ከቅርብ አመታት ወዲህ በአከባበር እየተለወጠ የመጣውን የህውሀት እና ልጆቹን ልደት አጨንቁሮ ለተመለከተ ብዙ ነገሮችን መናገር ይችላል። በልሙጡ ለሚያይ ሰው የብአዴን፣ ኦህዴድ እና ደኢህዴግ የልደት በአላት ” መወድሰ ህወሀት” እየሆኑ መሔዳቸውን በቀላሉ መታዘብ ይችላል። ህውሀቶች የየካቲት 11 እና እሱን ተከትሎ የነበሩት ሳምንታት አልበቃቸው ብሎ ህዳር 11 ( የኦህዴድ እና የሐይለማርያምን ልደት ቀን ረሳሁት) በቤቢ ሻወርነት እየተጠቀሙበት ነው። ርግጥ ነው ህውሀቶች ወገባቸውን ይዘው ” እኛ በልጆቻችን ውስጥ አድረን ቡራኬያችንን ብንወስድ እናንተን ለምን አሳከካችሁ?” እንደሚሉን ይገባኛል። ባያሳክከን ጥሩ ነበር። ፈር የሳተው ቡራኬ በኢትዬጲያ ህዝብ ላይ እያሳረፈ ያለው ጫና በአይናችን ላይ እየሔደ አላሳከከንም ማለት እንደ ብአዴን አባላት ቧልት ስለሚሆንብን ነው። እናም ቢያንስ የብአዴን አባላትን የውስጥ ጩኸት እኛ ብንጮኸው ምስጋናቸው ዘግይቶም ይደርሰን ይሆናል።

Thursday, November 19, 2015

ወንጌል እና ሰይጣን፣ ትግሬ እና ብርቱካን ( ሄኖክ የሺጥላ )

ወንጌል እና ሰይጣን፣ ትግሬ እና ብርቱካን ( ሄኖክ የሺጥላ )
የብርቱካን አሊ ልጅ አብዱ በራ’ብ እንዳልሞተ ወያኔ ነገረን ። በዛ ላይ ቢቢሲ ደሞ እንደ ኢሳት እንደዋሸ ተነገረን ። ይሁን !
እንበልና የብርቱካን ልጅ በራብ አልሞተም ፣ ቀጥሎም የብርቱካን ልጅ በቁንጣን ነው የሞተው እንበል ፣ እንደውም እንደ ወያኔ ባለ ስልጣን ልጆች ሰክሮ መንገድ ላይ ውስኪ እየደፋ ሲሄድ የደፋው ውስኪ አዳልጦት ነው የሞተው እንበል ፣ ከፍ ሲል ለቢቢሲ ጋዜጠኛ ያሳየችው ቅጠል የተሸፈነ የልጇ የአብዱ መቃብር ሳይሆን የእህል ማስቀመጫ ጎተራ ነው እንበል ፣ እነዚህ ሁሉ እውነት ሆኑ እንበል ፣ ከዚያስ ?
እርግጥ ነው ፣ ነገሩን በጥልቀት ከተመለከትነው የብርቱካን ልጅ የሞተው በራብ አይደለም ፣ ራብ ነብሱን ከስጋው የለየው የመጨረሻው ጉዳይ ይሆን ይሆናል እንጂ ፣ የብርቱካን ልጅ የሞተው ፣ እኛ ወንድነታችንን የተቀማን ግዜ ነው ፣ ብርቱካን ልጆቿን የቀበረችው የወለደቻቸው ቀን ነው ፣ እርግጥ ልጇን አፈር ያለበሰችው ዛሬ ነው ፣ መቃብሩ የተቆፈረው ግን ወያኔ ስልጣን ላይ ሲወጣ ነው ። ረሃቡ ሞትን ያስከተለ አንድ ምክንያት ሊሆን ይችላል እንጂ የብርቱካን ልጅ ረሃብ ባይኖርም አያድግም ! ሰው አይሆንም ! ሃገሩን አይጠቅምም ! ባገሩ አይጠቀምም !

Wednesday, November 18, 2015

ረሃቡን በሚመለከት የተሰጠ መግለጫ፣ ዓለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት (Global Alliance for the Rights of Ethiopians – GARE)

Global Alliance for the Rights of Ethiopians (GARE)ዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት ከተቋቋመበት ወቅት ጀምሮ ለኢትዮጵያዊያን ወገኖቹ በያሉበት ለሚደርስባቸው ግፍና ችግር ያልተቆጠበ ጥረት በማካሄድ ላይ ይገኛል። በዚሁ መሰረት በሳውዲ አረቢያ፤ በየመን፤ በሊቢያ፤ በኬንያ፤ በሰሜን ሱዳንና በማላዊ ችግር ለገጠማቸው ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች የገንዘብ፤ የዲፕሎማሲ፤ የምክርና ሌሎች ድጋፎች አድርጓል። ይኼ ግዙፍ ድጋፍ ስኬታማ ሊሆን የቻለበት ዋና ምክንያት ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በያሉበት የገንዘብ ድጋፍ ስላደረጉ ነው። ድርጅታችን እነዚህን ደጋፊዎች ያመሰግናል።

“15 ሚሊዮን ህዝብ መደበቅ ሰማይን በመዳፍ ለመሸሸግ እንደ መሞከር ይቆጠራል” (በውቀቱ ስዩም)

Ethiopian author and poet, Bewketu Seyoumባገራችን ኣብዛኛው ዜጋ ለቀን ጉርስና ላመት ልብስ ሲታገል የሚኖር ነው፡፡ ጌቶች ደግሞ ኣማርጠው ይበላሉ፡፡ ኣማርጠው ይለብሳሉ፤በለስ ሲቀናቸው ደግሞ የሃያ ኣምስት ሚሊዮን ብር ቪላ ይቀልሳሉ፡፡ እንዲያም ሆኖ ደግሞ መከበርና መደነቅ ይፈልጋሉ፡፡ ሰው ምንም በስጋው ቢመቸው በሌላው ተመዝኖ እንደቀለለ ሲሰማው ደስተኛ ኣይሆንም፡፡ ስለዚህ ጌቶች ያስንቀናል ብለው የሚያስቡትን ነገር በሙሉ ጠምድው ይይዙታል፡፡ ይዋጉታል፡፡ ኢትዮጵያ- ጌቶች ለኩራታቸው፤ ዜጎች ለራታቸው የሚታገሉባት መድረክ ናት፡፡

Tuesday, November 17, 2015

ለድርቁ አስቸኳይ ብሔራዊ ግብረኃይል ይቋቋም! “ህይወት ለማትረፍ በቅድሚያ መተማመን”

drought and hope





* ከአገዛዝ ለውጥ በፊት ችጋር ይቀድማል?
* “በአሁኑ ጊዜ ችጋሩ እንደ 1977 ሆኗል!”
በኢትዮጵያ ላለፉት ፴ ዓመታት ያለታየ ችጋር ተከስቷል። ድርቁና ረሃቡ ከዚህም በላይ የከፋ ሊሆን እንደሚችል ኢህአዴግን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ተቋማት ይፋ እያደረጉ ነው። “የምግብ ዋስትናን አረጋግጫለሁ” በማለት ሲወተውት የኖረው ህወሃት ተገዶ ያመነው ችጋር ከ፩፱፯፯ ድርቅ በላይ የከፋ እንደሚሆን ስጋት አይሏል። ከዚህ በፊት እንደተከሰቱት ለውጦች ይህኛውም የአገዛዝ ለውጥ ሊያስከትል እንደሚችል ተነገረ። በአስቸኳይ ብሔራዊ ግብረኃይል መቋቋም እንደሚገባ ተገለጸ፡፡

ክፋት በዛ [ረሃብ እንደ ቀይ ሽብር፤ ህወሃት እንደ ደርግ]

ክፋት በዛ

[ረሃብ እንደ ቀይ ሽብር፤ ህወሃት እንደ ደርግ]
birtukan ali


ክፉ ቀን ብዙ ክፉ ምግባሮች ይዞ ይመጣል።
በቀይሽብር ወቅ በመቀሌ ከተማ ያጋጠመ አንድ የክፉ ምግባር ምሳሌ ነበር።
ዘስላሰ የተባለ ወጣት በፀረ ደርግነት ተጠርጥሮ የቀይ ሽብር ሰለባ በመሆን በባዛር እየተባለ የሚታወቀውና አሁን በስሙ ዘላሰ የተሰየመው የአፄ ዮሐንስ ቤተ መንግሥት ፊትለፊት የሚገኝ አደባባይ ይረሸናል። ወላጅ እናቱ በደርግ ወታደሮች ተገድደው እልልል እያሉ፣ እያጨበጨቡ ደስታቸው እንዲገልፁ ተደርገዋል።

ብልግናና እና ስልጣን ( ሄኖክ የሺጥላ )


ባለጌ ብልግናውን በትምህርት ፣ በሥርዓት በተገመደ ባህል ፣ በቤተሰብ እና በሚከተለው ሃይማኖት ካላረቀ ዱርዬ ይሆናል ። ይህ ዱርዬ ወታደር ከሆነ ደሞ ፣ የጠመንጃው አፈሙዝ እና ብልግናው ጥጋብ ይደርብለት'ና የወጣለት አምባገነን ይሆናል ። የኢትዮጵያ ችግር ይሄ ነው ። አመጸኛ ባለጌ ጀግና ሆኖ ፣ የሚፈራው አጣ ፣ የሚያከብረው አጣ ፣ የሚሰማው አጣ ።
ዛሬ ሀገራችን የገባችበት መከራ ምንጩ ፣ የስድ ጓዶች ፣ የመሃይም ጀነራሎች ፣ የባለጌ ሚንስትሮች ፣ የዱርዬ ጳጳሶች እና የወሮበላ ዳኞች ሀገር ስለሆነች ነው ። ባለጌ ብልግናው እሱ ጋ አይቆምም ፣ የ ባለጌ ትውልድ አባወራ ፣ የባለጌ ልጆች አባት ፣ የባለጌ ስርዓት ባለቤት ይሆናል ። ለዚህም ነው ባለጎችን የሚያግባባቸው እና የሚያመሳስላቸው ነገር ሁሉም አለመግባባታቸው ነው የሚባለው ። በባለጌ ስርዓት ውስጥ ይሉኝታ የለም ፣ ሰው ምን ይለኛል የለም ፣ ሀፍረት የለም ፣ ክብር የለም ፣ ታሪክ የለም ፣ ሕዝብ የለም ፣ እምነት የለም ፣ ነገ የለም !
ሕፍረቱን ያጣ ስርዓት ፣ ስርዓቱን የተነጠቀ ሕዝብ ፣ ጨዋነት የራቀው መንግስት ፣ የመዋረድ እና የማጎብደድ ርካሽነት የሚያይበት አእምሮም ነብስም የለውም ። ስለዚህ በሊቢያ መታረድም ሆነ በሱማሊያ ጦር መማገድ ሃገራዊ ውድቀት ሳይሆን እንደ አንድ የማህበረሰብ የለት ተለት ተራ ክንውን ተደርጎ የሚወሰደው ።

Sunday, November 15, 2015

ድርቅ ርሃብና ችጋር ምንና ምን ናቸው? ኢትዮጵያስ ለምን የርሀብ ሀገር ሆነች? (ፈቃደ ሸዋቀና)

ፈቃደ ሸዋቀና
ሀገራችን መሬት ላይ እንድ ሌላ ግዙፍ የርሀብና የችጋር ዳመና እያንዣበበ ነው። አንዳንድ ቦታም ግዳይ መጣል መጀመሩን እየሰማን ነው። ይህ ችግር በሰብዓዊMalnutrition hits record high in Ethiopiaዕውቀትና ሀይል የሚፈታ ሆኖ ለምንድነው እንዲህ እየተመላለሰ የሚጎበኘን? ሌሎች ሀገሮች ተመሳሳይ የአየር ሁኔታ ችግር እየገጠማቸው እንደኛ ለአዋራጅ ጉስቁልናና ልመና አልተዳረጉም። እኛ ጋ ምን የተሰወረብን ነገር አለ? የአፍሪካ የውሀ ሰገነት የምትባልና ከማንም የማይተናነስ የተፈጥሮ ጸጋ ያላት ሀገር ይዘን ለምን እንደዚህ አይነት ሕዝብ ሆንን? በጅጉ የሚደንቅ ነገር ብቻ ሳይሆን በንዴት የሚያቃጥል ነገር ነው። እንደሚመስለኝ ችግሩን የልፈታንበት አንዱ ምክንያት ተገቢና የበሰለ ውይይት የማናካሂድ ህዝብ መሆናችንና ይህንንም ለማድረግ የመወያያና መፍትሄ ፍለጋ ሁኔታ እንዳይፈጠር መንግስታቱ ተጠያቂነትን ለማምለጥ ሲሉ የሚፈጥሩት እንቅፋትነት ይመስለኛል። እስከመቼ በዚህ ውርደት እንደምንቀጥል ባሰብኩ ቁጥር የሚያመኝን ህመም ችዬ ነው ይህን ለውይይት የሚሆን ጽሁፍ የጻፍኩት።

Friday, November 13, 2015

የሞቱ ካሉ የሞቱት በረሃብ አይደለም ይላሉ ም/ጠ ሚኒስተሩ – የሚሊዮኖች ድምጽ

8c1e31b24cd68f93e746d072f1231338_XL
የኢትዮጵያ መንግስት 600 ሺህ ሜትሪ እህል አዟል ይሉት አቶ ደመቀ መኮንን 200 የሚሆነው ጅጅቡቲ ወደብ እንደደረሰ ለፋና ራዲዮ ተናግረዋል።ሄ መልካም ዜና ነው። ረፍዷል፤ ቢሆንም ረፍዶም እርምጃዎች መወሰዳቸው ጥሩ ነው።
“የተለያዩ የውጭ መገናኛ በዙሃን በድርቁ የተነሳ የሰው ህይወት አልፏል እያሉ እያሰራጩ ካለው ዘገባ አንጻር በተጨባጭ ያለው እውነታ ምን ይመስላል” በሚል ከፋና ለቀረበላቸው ጥያቄ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲመልሱ፥ “የውጭ መገናኛ ብዙሃን ከተለያዩ አካላት ጋር እንደሚሰሩ ይታወቃል። ከዚያ በላይ ግን፣ አፍ ለማዘጋት አልያም ለማስተባበልና ምላሽ ለመስጠት ሳይሆን፣ ረሃብ የሚባለው ነገር ኢትዮጵያ ውስጥ የለም” ይየሚል ማልሽ ነው የሰጡት።

Wednesday, November 11, 2015

ጉድ በል!!!!! ወገኔ. 15 ሚሊየን ሕዝብ በተራበበት ሃገር ውስጥ አልጠግብ ባይ የወያኔ ሕውሃት ቡድን የሚሰሩትን በራሳቸው ልሳን ስማ. ላረጁና ሕዝብና ሃገርን ሲያደሙ ለኖሩ ለያንዳዳቸው 25 ሚሊየን ብር የሚያወጣ መኖሪያ ቤት እየተሰራላቸው እንደሆነ. .

ጉድ በል!!!!! ወገኔ.  15 ሚሊየን ሕዝብ  በተራበበት ሃገር ውስጥ  አልጠግብ ባይ የወያኔ ሕውሃት ቡድን የሚሰሩትን በራሳቸው ልሳን ስማ.
ላረጁና ሕዝብና ሃገርን ሲያደሙ ለኖሩ ለያንዳዳቸው  25 ሚሊየን ብር የሚያወጣ መኖሪያ ቤት እየተሰራላቸው እንደሆነ. .




ወሮበሎች በአሜሪካ ድምጽ የአማርኛው አገልግሎት ዋና መሥሪያ ቤት ውስጥ ሰርጎ መግባት? (ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
ጥንታዊ የሮማ ሰዎች እራሳቸውን ከወሮበላ አደጋ ጣዮች ለመጠበቅ ሲሉ የከተሞቻቸውን በሮች እና ግንቦች ከፍተኛ ጥንቃቄ በማድረግ ይጠብቁ ነበር፡፡TPLF officials and VOA
የሮማ ሰዎች ወሮበላ አደጋ ጣዮች ምንም ዓይነት አደጋ ሳይጥሉ ቅድመ ዝግጅት አድርገው ገና ከበሩ ጋ በመጠበቅ ዓላማዎቻቸውን ያከሽፉባቸው ነበር፡፡
በአሁ ጊዜ ደግሞ የዘመኑ የፕሬስ ነጻነት አደጋ ጣይ ወሮበሎች እ.ኤ.አ መስከረም 26 /2015 በዋሺንግተን ዲ.ሲ የሚገኘውን የአሜሪካ ድምጽ የአማርኛው አገልግሎት ዋና መስሪያ ቤት በድብቅ  ጭለማን ተገን አርገው ሰርጎ ገብተው ነበር ፡፡

አገር ሲያረጅ ጃርት ያፈራል፤ በአክሊሉ ወንበር ቴዎድሮስ ተቀምጧል (ይገረም ዓለሙ)

ይገረም ዓለሙ
Ethiopian foreign ministerበዕድሜአችን የደረስንባቸውንም ሆነ በታሪክ የምናውቃቸውን በዚህች ሀገር በመሪነትም ሆነ በከፍተኛ ሥልጣን ላይ የነበሩ ሰዎች ስናስብ የዘመናችን ባለሥልጣናት በብዙ መንገድ አንሰውና ቀለው ነው የሚታዩት፡፡ በውሸታምነታቸው በዘረኛነታቸውና ለሀገርና ለሕዝብ በአላቸው እኩይ አመለካከት ደግሞ አይደለም ትናንት ከነበሩት ወደ ፊትም ከሚመጡት የሚስተካከላቸው የሚገኝ አይመስልም፡፡ ነገረ ስራቸው ሲመዘን፣ የማይታመን የማይጨበጥ ንግግራቸው ሲሰማ እንዲህ የሚያደርጋቸው ከደደቢቱ እኩይ ዓላማቸው በላይ የተቀመጡበት እነዚያን ታላላቅ ኢትዮጵያውያንን ያስተናገደ ወንበር እያቃዣቸው ሳይሆን አይቀርም ያስብላል፡፡

Monday, November 9, 2015

ረሃብ የመንግሰት ፖሊሲ ብልሹነት እንጂ የዝናብ እጥረት ዉጤት አይደለም! (ኤፍሬም ማዴቦ)

በኤፍሬም ማዴቦ
Malnutrition hits record high in Ethiopia
ደርግ የቀዳማዊ ኃ/ሥላሤን ስርዐት ከደመሰሰ በኋላ ወሎ፤ ትግራይና ሰሜን ሸዋ ዉስጥ ህዝብ እንደ ቅጠል ሲረግፍ እሳቸዉ የልደት በዐላቸዉን ለማክበር ከዉጭ አገር ኬክ ያስመጣሉ ብሎ ነበር ንጉሰ ነገስቱንና ስርዐታቸዉን የከሰሰዉ።

Thursday, November 5, 2015

የኢትዮጵያ ወጣቶች ክልል፣ ቋንቋም ሆነ ሀይማኖት ሳይገድባቸው በጋራ ይቁሙ!

def-thumb
ከ1950ዎቹ ጀምሮ የተደረጉ ሕዝባዊ ንቅናቄዎች በሙሉ የተጠነሰሱትና የተመሩት እድሜያቸው ከሠላሳ አምስት ዓመት በታች በሆኑ ወጣቶች ነው። የ1997 ምርጫ ታሪካዊ እንዲሆን ያደረጉ፤ የሚያዝያ 30 ቀን 1997ን ታላቅ ሰልፍ ያደራጁ፤ ሕዝብን አደፈፍረው ለምርጫ በማሰለፍ ግንቦት 7 ቀን 1997 ታሪካዊ ዕለት እንድትሆን ያደረጉ፤ በኋላም “ድምፃችንን አናስነጥቅም” በማለት የአግዓዚ ፋሽስቶችን በድንጋይና ዱላ የገጠሙ የኢትዮጵያ ወጣቶች ናቸው። በዚህ ትግል ሽብሬ ደሳለኝን ጨምሮ በርካታ ወጣቶች ሕይወታቸውን ሰውተዋል፤ በቁጥር የበዙት ደግሞ አካሎቻቸውን አጥተዋል፤ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች አሁንም በአገዛዙ እስር ቤቶች ሰቆቃ እየተፈፀመባቸው ነው። ጥቃቱ ቢበዛም ትግሉ ደግሞ የዚያኑ ያህል ተጠናክሮ ቀጥሏል። የኢትዮጵያ ወጣት ጥቃትን አሜን ብሎ አይቀበልም።

‹‹የመጣነው የሚላስ የሚቀመስ ስለሌለ ነው፡፡ ከብቶቻችን አልቀዋል፡፡ አዝመራ የሚባል የለም፡፡ ሰው በርሃብ እያለቀ ነው፡፡››››




‹‹የመጣነው የሚላስ የሚቀመስ ስለሌለ ነው፡፡ ከብቶቻችን አልቀዋል፡፡ አዝመራ የሚባል የለም፡፡ ሰው በርሃብ እያለቀ ነው፡፡››››
መንግስት በርሃብ ለተጠቁት ዜጎች እርዳታ እየሰጠ እንዳልሆነ ታወቀ
• በርሃብ የተጠቁት ዜጎች ቀያቸውን ለቀው እየተሰደዱ ነው
• ‹‹ሰው በርሃብ እያለቀ ነው››
• ‹‹የሚላስ የሚቀመስ የለም፡፡ ቤተሰባችን ፈርሷል››
• ‹‹እርዳታ ቢሰጥማ ከዚህ ድረስ አንመጣም ነበር፡፡››

Tuesday, November 3, 2015

የታማኝ እዳ

እንግዳ ታደሰ – ኦስሎ
በቃል የምነት እዳ ሸክፎ ሸክሙን 
እንደ ሴባስቶፖል ሽቅብ ቁልቁለቱን
ሲወጣና ሲወርድ ቋጥኝ አቀበቱን 
እስቲ እንካፈለው የሃገር እዳውን ፡፡
Ethiopian activist Tamagne Beyene
እዳው በግል የናት አባት እዳ አይደለም ፡፡ የርሱ እዳ የዕምነቱ እዳ ነው ፡፡ ለሸክም የከበደ ፥ የሰው ፊት የሚያስገርፍ፥ ዕረፍት የሚነሳ ፥ ከወለዳቸውና ከሚወዳቸው ቤተሰቡ ለወራት የሚያቆራርጥ፣ እንደ አጼ ቴዎድሮስ መድፍ ሴባስቶፖል ሽቅብና ቁልቁል የሚያስሮጥ፣ ኢሳትን በግሩ ለማቆሞ የሚደረግ ትግል ፡፡

ለጥቅምት 22 ሰማዕታት የመታሰቢያ ፕሮግራም ተካሄደ (ነገረ ኢትዮጵያ)

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

The Ethiopian police massacre 2005
ምርጫ 1997 ዓ.ምን ተከትሎ ጥቅምት 22/1998 ዓ.ም በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ቀጥታ ትዕዛዝ በ‹‹ፀጥታ ሀይሎች›› በጭቃኔ ለተገደሉት ሰማዕታት እና ለቆሰሉት ኢትዮጵያውያን በሰማያዊ ፓርቲ ፅ/ቤት መታሰቢያ ተደረገ፡፡ የፕሮግራሙ ተሳታፊዎች ጥቅምት 22/1998 ዓ.ም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የገጠማቸውን በተለይም ኢትዮጵያውያን ሲገደሉ ያዩትንና የራሳቸውን ገጠመኝም አካፍለዋል፡፡