Translate

Thursday, November 28, 2013

የህዝባችን መከራ የወያኔ የፖለቲካ መጠቀሚያ አይሆንም!


በሳውዲ አረቢያ ውስጥ እጅግ ብዙ ኢትዮጵያውያን አሁንምመከራና ስቃይ ላይ ናቸው። የደረጃ ጉዳይ ነው እንጂ ችግሩ በመካከለኛው ምስራቅ ሀገሮች በሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ የተንሰራፋ ነው። በመላው አለም ተበትኖ የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ካለማቋረጥ ያደረገው ወገንና ሀገር አኩሪ ጩኸትና አቤቱታ ችግሩ በአለም ዙሪያ ትኩረት እንዲያገኝ ባያደረግ ኖሮ የወገኖቻችን መከራ ከዚህም በከፋ መልክ ይቀጥል እንደነበር ጥርጥር የለውም። አንድ ቀን እንኳን ለሚገዛው ህዝብ ሀላፊነትና ተጠያቂነት ተሰምቶት የማያውቀው የወያኔ ጉጅሌ መንግስት እግሩን እየጎተተ ቢሆንም ወደ ችግሩ አቅጣጫ እንዲመለከት የተገደደው በዚሁ የወገን ጩኸት መሆኑ ግልጽ ነው።
ወያኔ ስላልቻለ ነው እንጂ ይህንን ከአለም አጽናፍ እስከ አለም አጽናፍ ያስተጋባ የወገን ደራሽ ድምጻችንን አዲስ አበባ ላይ እንደ አደረገው በሃይል ለማፈን ወደኋላ አይልም ነበር።
ሀፍረት የለሾቹ የወያኔ መንግስት ባለስልጣኖች ይህን የተጋለጠ ሀገርና ህዝብ አዋራጅ ተግባራቸውን እና በውሸት የተበከለ ገመናቸውን ለመሸፈን ከዚያም አልፈው የዋሆችን በማታለል የፖለቲካ ትርፍ ለማትረፍ የተለመደ ቲያትር መስራቱን ተያይዘውታል። ቴዎድሮስ አድሃኖም ችግሩ ባለበት በሳውዲ መሬት ላይ ሳይሆን የሳውዲ አረቢያ መንግስት በራሱ ወጪ አሳፍሮ ቦሌ አውሮፕላን ጣቢያ ባፈሰሳቸው ኢትዮጵያውያን መሃል እየተጎማለለ ያዛኝ ቅቤ አንጓች ቲያትሩን ሲሰራ ትንሽ እንኳን ሀፍረት አይታይበትም።

‹‹ሰው ለሰው›› የቴሌቪዥን ተከታታይ ድራማ በወ/ሮ አዜብ መስፍን ትእዛዝ ስክሪፕቱን እንዲቀይር ተገደደ፡፡

ኢሳት ዜና :-በኢትዩጵያ የቴሌቪዥን ድራማ ታሪክ በረዥምነቱ ቀዳሚውን ቦታ በመያዝ የሚታውቀው ሰው ለ ሰው ተከታታይ ድራማ 109 ክፍሎች ያህል ከተላለፈ በኃላ፣ ሰዎች በማህበራዊ ድህረ ገጾች የድራማው ተዋንያን የሆነውን በትወና ስሙ አስናቀ የተባለውን  ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ባለቤት ከወ/ሮ አዜብ መስፍን ጋር  በማመሳስል ገጸባህሪውና ወ/ሮ አዜብ መስፍን ባለስልጣናትን በገንዘብ ይገዛሉ ፤ ፍትህን ይረግጣሉ ፤ በሰው ህይዎት ይነግዳሉ፡ ፤ ሰው ያስገድላሉ፤ ህዝብን ያስለቅሳሉ ፤ በወንጀል ይነግዳሉ፤ ሰው በላ እና ነፍሰ ገዳይ አምባገነን ናቸው ሲሉ እንደሚተቹዋቸው ይታወቃል፡፡

በሪያድ የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች በወገኖቻችን ስም በእጅ አዙር ገንዘብ ማሰባሰብ መጀመራቸው እየተነገረ ነው ።

በሪያድ መለዝ አካባቢ የሚገኝ፡አሚራ ኑራ ዩንቨርስቲ ግቢ ሜዳ ላይ ያለዳስ ብርድ እና ጸሃይ የሚፈራረቅባቸው ከ 7 ሺሕ የሚበልጡ ወገኖቻችን በመግብ ወሃ እና የመጸዳጃ ቦታ እጦት እየተሰቃዩ ነው ። የተጠቀሰው መጠለያ ውስጥ ያሉት ወገኖቻችን አብዛኛዎቹ ሴቶች ህጻናት እና አረጋውያን እንደሆኑ መረጃዎች ያመለክታሉ።

ከሳዑዲ የተመለሱ 7000 በላይ ኢትዮጵያዊያ በአደገኛ ሁኔታ የመን ውስጥ…

በግሩም ተ/ሀይማኖት 
በባህር ተሻግረው በየመን በኩል ያንን እልህ አስጨራሽ በረሃና ፈተና አልፈው ወደ ሳዑዲ አረቢያ የገቡ ኢትዮጵያዊያን ከአበሀ፣ ከሚስ ምሽት፣ ናጂራንና አሲር… ከመሳሰሉት የመን ድንበር አቅራቢያ ያሉ የሳዑዲ ከተማዎች ላይ ነዋሪ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን ወደ የመን እየገቡ ነው፡፡ ጅዳ ሄደው ወደ ሀገራቸው ለመግባት የማይችሉ በመሆኑ የመን መግባት አማራጭ ሆኖባቸዋል፡፡

Wednesday, November 27, 2013

ከኢትዮጵያ እሳት ወደ ሳውዲ አረቢያ እረመጥ፣ ከድጡ ወደ ማጡ

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

ትርጉም ከነጻነት ለሀገሬ
What “foreign minister” Adhanom said and did not even know he said it
Tedros Adhanom, the malaria researcher-turned-instant-foreign-minster
ባለፉት አስርት ዓመታት በመቶሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎች በአገራቸው ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አህጉር በተለየ መልኩ ተንሰራፍቶ እየተፈጸመ ካለው ጭካኔና ርህራሄ የጎደለው አምባገነናዊ ስርዓት ለማምለጥ ሲሉ እግራቸው ወዳመራቸው አገር በመሰደድ ላይ ይገኛሉ፡፡

የግንቦት7 እና አክራሪ የእስልምና ሀይሎች በኢህአዴግ አባላት ስም ፓርላማውን በመቆጣጠር ኢህአዴግን ሊጎዱት ይችላል ሲሉ የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስትር ተናገሩ

Image

 ኢሳት ዜና :-ሚኒስትር ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም ይህን የተናገሩት ” በክርስትና እና በእስልምና ሃይማኖት ሽፋን የሚካሄደው የፖለቲካ እንቅስቃሴ የመንግስት ቀጣዩ የምርጫ ፈተና” በሚል ርእስ ለኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች ባቀረቡት ጽሁፍ ነው።

ከአቶ ታምራት ላይኔ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ (ከአንድ ጉዳይ በቀር በርካታ ቁምነገሮች አለው)

Former Ethiopian PM Tamrat Layene(ዳዊት ከበደ ወየሳ) – ከአቶ ታምራት ላይኔ ጋር የተደረገው ቃለ ምልልስ አስገራሚ ነው። በአውስትራልያ የ-SBS አማርኛ ፕሮግራም ነው ይህንን ያስደመጠን – ምስጋና ይገባቸዋል። በቃለምልልሱ ውስጥ የምናውቃቸውና የማናውቃቸውን፤ በወሬ የሰማናቸውንም ሆነ በታሪክ ያየናቸውን ጉዳዮች ተካተዋል። ከራሳቸው የግል ህይወት አስተዳደግ እና አስተሳሰብ በመነሳት ስለ ትጥቅ ትግሉ ታሪክ ብዙ ብዙ ነገሮችን ብለዋል። ኢህዴን የተባለው ድርጅት ከጎንደር አካባቢ ተነስቶ ወደ ትግራይ ክልል ከመሄዱ በፊት፤ ከህወሃት ጋር የርስ በርስ ንግግር የተደረገ መሆኑን፤ ያንጊዜ ወደ ትግራይ እንዲገቡ ባይፈቅዱላቸው የርስ በርስ ግጭት ሊኖር ይችል እንደነበር ወይም ወደ ሱዳን ተመልሰው ሃይል አጠናክረው ትግራይ መግባታቸው የማይቀር መሆኑን ያብራራሉ። ከዚህም በተጨማሪ ኢህዴን በኤርትራ ላይ የነበረው አቋም ምን እንደነበረና በኋላም ከህወሃት ጋር ተቀላቅሎ “ኢህአዴግ” የተባለ ግንባር መመስረቱን፤ ከዚያም ይህ ድርጅት ከብሄራዊ ድርጅትነት ወደ ብሄር ድርጅትነት ወርዶ “ብአዴን” ስለመባሉ ይገልጻሉ። ነገር ግን ወደ ዝርዝር ማብራሪያ አልሰጡበትም። “ብዙ ነገር አለ” ብለው ያልፉታል።

የሳዑዲ ጉዳይ የዛሬ አዳዲስ መረጃዎች – በነብዩ ሲራክ (ጋዜጠኛ)

ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከ40 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሃገራቸው ገብተዋል ይሉናል፤ የሳዑዲ ባለስልጣናት ደግሞ 28 ሺህ ኢትዮጵያውያንን ነው ወደ ሃገራቸው የላክነው ይላሉ። ዶ/ር ቴዎድሮስ 13 ሺህ ሰው ከየት ሸቅበው ነው?… ለማንኛውም ሳዑዲ አረቢያ የሚገኘው ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ የሚሰጠንን አዳዲስ መረጃዎች ይመልከቱ…

Tuesday, November 26, 2013

ተዋርደን አንቀርም!! ኢ/ር ይልቃል ጌትነት (የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር)

Interview Eng. Yilkal Getnetሳውዲ አረቢያ በዜጎቻችን ላይ እያደረሰች ያለውን ግፍና በደል በሰላማዊ ሰልፍ ለመቃወም ፓርቲያችን በወሰነው መሰረት ለሚመለከተው ክፍል አሳውቀን ነበር፡፡መቸም ህዝባችን በጭቆና ውስጥ ስለኖረ በመብቱና በግዴታው መሀል ያለውን ድንበር በውል ካለመረዳቱ የተነሳ ሰልፉ እንዲደረግ ስለመፈቀዱ በተደጋጋሚ ስንጠየቅ ነበር፡፡ህጉ የሚለው ግን ማስፈቀድ ሳይሆን ማሳወቅ ብቻ ነው፡፡በተቃራኒው መንግስት በተለያዩ ጉዳዮች ሳቢያ በእለቱ ለሰላማዊ ሰልፉ የደህንነት ከለላ መስጠት የማይችልበት ሁኔታ ከገጠመው ሰልፉን ለጠራው አካል ችግሩን ገልጾ ቀኑ እንዲተላለፍለት ይጠይቃል፡፡በመሆኑም ይህን መሰል ጥያቄ ከሚመለከተው መስሪያ ቤት ለፓርቲያችን ባለመቅረቡ በሙሉ ልብ ቅድመ-ዝግጅት ማድረጉን ተያያዝን፡፡

በደላላ ሃገር ሰትመራ! በታደለ መኩሪያ

በደላላ ሃገር ሰትመራ! በታደለ መኩሪያ
በትግራይ ሕዝብ ነፃነት ግንባር ሽፋን፤ ዛሬ ይህቺን ጥንታዊት ሃገር ኢትዮጵያን እየመራት ያለው ወያኔ የሚባል ቡድን ነው። ይህ የጭንጋፍ ስብስብ  በትግራይ ሕዝብ ልባስ የኢትዮጵያን ለም መሬትና ቡቃቅላ  ልጆቿን በደላላነት ለሳውዲ አረቢያ ሲያቀርብ መቆየቱን ዓለም ያወቀው ፀሐይ የሞቀው ሐቅ ነው። የዚህ ቡድን የጥቅማጥቅም ተቋዳሾችና አልጠብባዮች ጋር በመተባበር ቤሔራዊ ኩራታችንን አደጋ ላይ ጥለውታል።እነዚህ የዕንግዴ ልጆች  ሆድ አደሮች ፤ትውልድም፣ የገዛ ልጆቻቸው የሚያፍሩባቸው ናቸው።

[የሳዑዲው ጉዳይ] ተዋርደን አንቀርም – ከኢንጂነር ይልቃል ጌትነት

ከኢንጂነር ይልቃል ጌትነት
ሳውዲ አረቢያ በዜጎቻችን ላይ እያደረሰች ያለውን ግፍና በደል በሰላማዊ ሰልፍ ለመቃወም ፓርቲያችን በወሰነው መሰረት ለሚመለከተው ክፍል አሳውቀን ነበር፡፡መቸም ህዝባችን በጭቆና ውስጥ ስለኖረ በመብቱና በግዴታው መሀል ያለውን ድንበር በውል ካለመረዳቱ የተነሳ ሰልፉ እንዲደረግ ስለመፈቀዱ በተደጋጋሚ ስንጠየቅ ነበር፡፡ህጉ የሚለው ግን ማስፈቀድ ሳይሆን ማሳወቅ ብቻ ነው፡፡በተቃራኒው መንግስት በተለያዩ ጉዳዮች ሳቢያ በእለቱ ለሰላማዊ ሰልፉ የደህንነት ከለላ መስጠት የማይችልበት ሁኔታ ከገጠመው ሰልፉን ለጠራው አካል ችግሩን ገልጾ ቀኑ እንዲተላለፍለት ይጠይቃል፡፡በመሆኑም ይህን መሰል ጥያቄ ከሚመለከተው መስሪያ ቤት ለፓርቲያችን ባለመቅረቡ በሙሉ ልብ ቅድመ-ዝግጅት ማድረጉን ተያያዝን፡፡
ሁሌም ቢሆን መንግስት ሰበብ ፈልጎ ሊወነጅለንና ከመስመር ሊያስወጣን እንደሚፈልግ በሚገባ እናውቃለንና በጥቃቅን ጉዳዮች ላይ ሳይቀር ጥንቃቄ እናደርጋለን፡፡ለሚመለከተው መስሪያ ቤት ባሳወቅን በአስራ ሁለት ሰአታት ውስጥ ምላሽ ስላልመጣ ሙሉ በሙሉ ህጋዊነታችንን አረጋግጠናል ማለት ነው፣እነሱ ደግሞ ጠብ-መንጃ በእጃቸው አለና የፈለጉትን ሁሉ ማድረግ ይችላል፡፡

ሕዳር 13/2006 ዓ.ም የኢሕአግና የጋህነን ሰራዊት በወሰዱት ድንገተኛ ወታደራዊ ጥቃት የወያኔው 24ኛ ክፍለ ጦር ድባቅ ተመቷል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባርና የጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ ሰራዊት በጋራ ወታደራዊ ጥቃት ፈፀሙ
የጋራ ትግል አስፈላጊ መሆኑን በፅኑ የሚያምኑት የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር /ኢሕአግ/ እና የጋምቤላ ሕዝብ ነፃነት ንቅናቄ /ጋሕነን/ በሕዳር 13/2006 ዓ.ም በሁመራ ሉግዲ ከቀኑ 10፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1፡00 ለሶስት ሰዓት ያህል በወሰደው ውጊያ የወያኔው 24ኛ ክፍለ ጦር ድባቅ ተመቷል። ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሰራዊት በ24ኛው ክፈለ/ ጦር ላይ በተመሳሳይ ሥፍራ ከፍተኛ ድል መቀዳጀቱ ይታወሳል። በሕዳር 13/2006 ዓ.ም የኢሕአግና የጋህነን ሰራዊት በወሰዱት ድንገተኛ ወታደራዊ ጥቃት 66 /ስልሳ ስድስት/ ገድለው 113 /አንድ መቶ አስራ ሶስት/ በማቁሰል እንዲሁም ቁጥራቸው የበዛ የጦር መሳሪያዎችን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ማርከዋል።

ከአቶ ታምራት ላይኔ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ (ከአንድ ጉዳይ በቀር በርካታ ቁምነገሮች አለው)

(ዳዊት ከበደ ወየሳ) – ከአቶ ታምራት ላይኔ ጋር የተደረገው ቃለ ምልልስ አስገራሚ ነው። በአውስትራልያ የ-SBS አማርኛ ፕሮግራም ነው ይህንን ያስደመጠን – ምስጋና ይገባቸዋል። በቃለምልልሱ ውስጥ የምናውቃቸውና የማናውቃቸውን፤ በወሬ የሰማናቸውንም ሆነ በታሪክ ያየናቸውን ጉዳዮች ተካተዋል። ከራሳቸው የግል ህይወት አስተዳደግ እና አስተሳሰብ በመነሳት ስለ ትጥቅ ትግሉ ታሪክ ብዙ ብዙ ነገሮችን ብለዋል። ኢህዴን የተባለው ድርጅት ከጎንደር አካባቢ ተነስቶ ወደ ትግራይ ክልል ከመሄዱ በፊት፤ ከህወሃት ጋር የርስ በርስ ንግግር የተደረገ መሆኑን፤ ያንጊዜ ወደ ትግራይ እንዲገቡ ባይፈቅዱላቸው የርስ በርስ ግጭት ሊኖር ይችል እንደነበር ወይም ወደ ሱዳን ተመልሰው ሃይል አጠናክረው ትግራይ መግባታቸው የማይቀር መሆኑን ያብራራሉ። ከዚህም በተጨማሪ ኢህዴን በኤርትራ ላይ የነበረው አቋም ምን እንደነበረና በኋላም ከህወሃት ጋር ተቀላቅሎ “ኢህአዴግ” የተባለ ግንባር መመስረቱን፤ ከዚያም ይህ ድርጅት ከብሄራዊ ድርጅትነት ወደ ብሄር ድርጅትነት ወርዶ “ብአዴን” ስለመባሉ ይገልጻሉ። ነገር ግን ወደ ዝርዝር ማብራሪያ አልሰጡበትም። “ብዙ ነገር አለ” ብለው ያልፉታል።
እነዚህ ከላይ የገለጽናቸውን ጉዳዮች በክፍል አንድ ላይ ሊያዳምጡት ይችላሉ።

Saturday, November 23, 2013

ኦባንግ – ከዓለምአቀፍ ተቋማት ጋር እየሠራሁ ነው አሉ

የሳዑዲ ልዑል አንጋቾቻቸውን አወደሱ

obang-o-metho-hearing


በሳዑዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውንና እየደረሰ ያለውን ፈር የለቀቀ አስነዋሪ ግፍ ዓለምአቀፍ ይዘት እንዲኖረው ለማድረግ ከሰብዓዊ መብት ተሟጋች እና ሌሎች ዓለምአቀፋዊ ድርጅቶች ጋር እየሠሩ መሆናቸውን አቶ ኦባንግ ሜቶ በተለይ ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ተናገሩ፡፡ የሳዑዲ ልዑል ሰብዓዊነት የረገፈበትንና በግፍ የተሞላ የወሮበላ ተግባር የሚፈጸምበትን አሰቃቂ ተግባር የሚከናውኑትን አንጋቾች አሞካሹ፡፡

ዲፕሎማቱ በትዕዛዝ ኢትዮጵያውያኑን ስደተኞች ወዳልታወቀ ስፍራ ሰደዱ

12ነፍሰ ጡሮችን ጨምሮ 200 ስደተኞች የደረሱበት አልታወቀም

saudi ethio11በሳውዲ አረቢያ ሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒት ግቢ ይገኙ የነበሩ 12 ነፍሰ ጡሮችን ጨምሮ ከ 200 በላይ ስደተኞች በዲፕሎማቱ ትዕዛዝ ወዳልታወቀ ስፈራ ተወሰዱ ።

በሳውዲ ለሚገኙ ወገኖቻችን በአፋጣኝ እንድረስ፤ በወያኔ ላይ በጋራ እንነሳ!!!

በሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለው መጠን የለሽ የመብት ጥሰት ለመቃወም በተለያዩ የዓለም አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን በየአገራቱ የሚገኙ የሳውዲን ኢምባሲዎችን በተቃውሞ እያጨናነቁ ነው። በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ባለው ዘግኛኝ በደል የተሰማቸውን ጥልቅ የመጠቃት ስሜት ኢትዮጵያን በተቃውሞ ሰልፎቹ ላይ በሚያሰሟቸው መሪር የሐዘን እንጉሮችና የቁጭት ንግግሮች እየገለፁ ነው። ከሐዘንና ቁጭት ባለፈም ለበደል ለተጋለጡ ወገኖቻችን አስቸኳይ ሰብዓዊ ርዳታ ለማድረስ እና የዲፕሎማሲ ድጋፍን ለማሰባሰብ ዓለም ዓቀፍ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ሥራውን ጀምሯል።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ይህንን ዓለም ዓቀፍ ጥረት ለመደገፍ በውጭ አገራት የሚገኙ አባላቱ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ መመሪያ አስተላልፏል።
ይህ ሁሉ በውጭ አገራት እየተደረገ ያለ ጥረት ነው። ኢትዮጵያዊያን ባሉበት አገራትና ከተማዎች ሁሉ በዚህ ጉዳይ ላይ በአንድነት መንቀሳቀሳቸው የሚያስደስት ነገር ነው። ሌላው ቀርቶ በሳዉዲ ዋና ከተማ ሪያድ ውስጥ እንኳን ኢትዮጵያውያን የሳውዲን መንግሥት ተቃውመው ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል።
የሳውዲ መንግሥት በኢትዮጵያ ስደተኞች ላይ የያዘውን ጨካኝ አቋም እና በመንግሥት እውቅና በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን በደል መቃወም ያልተቻለው በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ!!! ይህ እጅግ ያማል፣ ልብን ያደማል።
ወያኔ የሳውዲ የንግድ ሸሪኮቹን ለማስደሰት የፈንሳይን ግማሽ የሚያህል ለም መሬት በነፃ መስጠቱ በቂ አልመሰለውም። በአገራቸው ኢትዮጵያዊያንን ሲጨፈጭፉ፣ ሲገሉና ሲደፍሩ በቸልታ መመልከቱ በቂ የወዳጅነት ስጦታ መስሎ አልተሰማውም። እናም ሸሪኮቹ የበለጠ እንዲደሰቱና ከእስከዛሬ በበለጠ ገንዘብ እንዲደጉሙት ለማበረታታት አዲስ አበባ በሚገኘው ኤምባሲያቸው ፊት ለፊት ኢትዮጵያንን ደበደበላቸው።

Thursday, November 21, 2013

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማሪያም ደሳለኝ ከቁራና ከዳዊት የቱን ይመርጣሉ?

ከተከበሩ ግርማ ሠይፉ 

girmaseifu32@yahoo.com
አልፎ አልፎ ጠዋት የማገኛቸው የማኪያቶ ቡድን አለ፡፡ በፓርላማ ሰለነበረው ውሎ መሠረት አድርገው የግል አሰተያየት ይሰጣሉ በዚህ መሃል አንዱ ምሳሌያዊ ንግግር አደረገ ወደድኩትና ላካፍላችሁ ወደድኩ፡፡ ቁራ ታውቃላችሁ በተለይ መሬት ላይ በእግሯ ስትሄድ አታምርም ይህ ችግር እንዳለባት ታውቃለች፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የእርግብ አካሄድ ይማርካታል፡፡ አካሄዷን ለማሳመር እንደ እርግብ መሄድ ይኖርብኛል ብላ ወሰነችና ልምምድ ጀመረች፡፡ አስር ዓመት ሙሉ ቤት ዘግታ ስትለማመድ ቆይታ ሳይሳካላት ይቀርና ተስፋ በመቁረጥ አንድ ውሣኔ ላይ ትደርሳለች ቢያስጠላም በራሷ በቀድሞ አካሄድ እንደ ቁራ ለመሄድት ወስናለች፡፡የሚያሳዝነው ነገር ግን የእርግብንም ሳትለምድ የራሷም የቁራ አካሄድ ጠፋባት፡፡

የኃይሌ ገ/ሥላሴ ‘‘ታላቁ ሩጫ’’ ለሳዑዲ አረቢያ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች መታሰቢያ ሯጮች ሪቫን እንዳያደርጉ ከለከለ

በዘሪሁን ሙሉጌታ
Haile
በመጪው እሁድ በታላቅ ድምቀት በሚካሄደውና በአፍሪካ በግዙፍነቱ ቀዳሚ በሆነው ‘‘ታላቁ ሩጫ” ላይ የሚሮጡ ተሳታፊዎች በሳዑዲ አረቢያ ኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውን ጉዳት በሐዘን ለመግለፅ ጥቁር ሪቫን አድርገው እንዲሮጡ ሲል ሰማያዊ ፓርቲ ያቀረበውን ጥሪ የ‘‘ታላቁ ሩጫ” አስተባባሪዎች ተቃወሙ።
የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ አባላት በሳዑዲ አረቢያ የተፈናቀሉ ዜጎች ላይ የደረሰውን ግፍና በደል ለዓለም አቀፍ ህብረተሰብና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ለማስገንዘብ በሩጫው የሚካፈሉ ተሳታፊዎች ጥቁር ሪቫን በማድረግ ሐዘናቸውን እንዲገልፁ ሲል ወስኗል። የታላቁ ሩጫ አስተባባሪዎች በጉዳዩ ላይ እንዲተባበሩና አጋርነታቸውን እንዲገልፁ ለማድረግ በደብዳቤ ጥያቄውም እንደሚያቀርብ የፓርቲው ህዝብ ግንኙነት አስታውቋል።

ኢትዮጵያ፣ በህዳርና በ… ሁልጊዜ አስታውሳለሁ!! (ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገ/ማርያም)

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገ/ማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
የህዳር ወር በኢትዮጵያውያን በአሰቃቂነቱ ሁልጊዜ ሲታወስ ይኖራል፡፡
Ethiopia November Victims never again, Alemayehu G. Mariamእ.ኤ.አ ኖቬምበር 2013 ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በቃላት ለመግለጽ በሚዘገንን መልኩ በኢትዮጵያውያን/ት ላይ ሰቆቃ የተፈጸመበት ወር ነው፡፡ ላለፉት ጥቂት ዓመታት በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ፣ በሚሰሩና የፖለቲካ ጥገኝነት ለመጠየቅ ጥረት በማድረግ ላይ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን/ት ላይ ስልታዊ የሆነ ጥቃት ሲሰነዘር ቆይቷል፡፡ እንዲያውም በግል በሚኖሩበት ቤት እምነታቸውን በማራመዳቸው ብቻ ኢትዮጵያውያኑ/ቱ ዜጎች ላይ የወንጀል ድርጊት ተፈጽሞባቸዋል፣ እንዲጋዙም ተደርጓል፡፡

በ1997ቱ የኢትዮጵያ ምርጫ ታዛቢ የነበሩት አና ጐሜዝ አዲስ አበባ ሊመጡ ነው


Photo: © Europen Parliament/P.Naj-Olearipietro.naj-oleari@europarl.europa.eu


በ1997 ዓ.ም. በኢትዮጵያ በተካሄደው አገር አቀፍ ምርጫና ምርጫውን ተከትሎ ተከስቶ በነበረው የፖለቲካ ውዝግብ አካል የነበሩት የአውሮፓ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ አና ጐሜዝ ወደ ኢትዮጵያ ሊመጡ ነው፡፡

በህገወጥነት ሽፋን ለወገኖቻችን መጭፍጨፍ ግባር ቀደም ተጠያቂው በሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ እና አለቆቻቸው ናቸው !

በሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ ዛሬ በተለምዶ መንፉሃ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በተቀሰቀሰ ሁከት ቁጥራቸው በውል ለማይታወቁ ወገኖቻችን አስቃቂ ግድያ እና በ10 ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በሳውዲ አረቢያ እየደረሰባቸው ላለው ስቃይ እና መከራ ግንባር ቀደም ተጠያቂ የሚያደርገው የተዝረከረከ አሰራሩ ሲቃኝ።

Wednesday, November 20, 2013

በግብታዊነት የተደራጀ የልማት ሰራዊት ውጤቱ ጥፋት ነው -ከአስገደ ገ/ስላሴ ወ/ሚካኤል መቐለ

ህ.ወ.ሃ.ት ትግራይን በመልካም አስተዳደር ፣ በፍትህ፣ በነፃነት፣ በልማት፣ በግብር አሰባሰብ ፣ በባለሃብቶች ፍሰት የኢንቨስትመንት ግበአት፣ በከተማ ልማት በጥቃቅንና አነስተኛ ተቋማት እድገት በእርሻ እድገት በአርሶ አደሩ ሞዴልነት በኢንዱስትሪ በጤና ፣ በትምህርት፣ ጥራት፣ በማህበራት ኣደራጃጀት በሁሉም አይነት ዲሞክራሲ መብት አጠባበቅ ሞዴል፤ ለሁሉም ክልሎች እንደሰርቶ ማሳያ ተደርጎ ነዉ የሚቀርበው የህ.ወ.ሃ.ት መሪዎች ሲደሰኩሩበት የቆዩና ያሉት ። ሃቁ ግን በሚከተሉት ፅሁፍ አንቀፅ በአንቀፅ ላስቀምጣቸዉ እሞክራለሁ።
በትግራይ ክልል ብዙ ብቁ ምሁራኖች ከዲፕሎማ እስከ ዶክትረት ደረጃ የተማሩ ሊቃኖች በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በእርሻ ምርምር በጤና ፣ በትምህርት፣ በመአድን፣ በኢኮኖሚክስ ፣ በሂሳብ፣ በመሃንዲስነት በአስተዳደር ወ.ዘ.ተ የተሰማሩ አሉ። እነዚህ ግን በሞያቸዉ ተሰማርተዉ ቢሰሩ ኖሮ በክልላችን ያሉ እጅግ ብዙ የተበላሹ ነገሮች ማስተካከል ይችሉ ነበር። ነገር ግን በክልላችን እየተሰራ ያለዉ ሙሁሩን በማግለል ምንም ሞያ የሌላቸዉ በህ.ወ.ሃ.ት መሪዎችና በፖለቲካ ታማኝነት መሆናቸዉ ተብሎው የታመነባቸዉ አዛዥነት ነዉ የሚሰራዉ ምንም ሞያ የሌለዉ የማሌሊት ካድሬ ከክልል እስከ ቀበሌ ቢዘረጋ ደግሞ የክልሉ ሃብት ከማባከን በሙስና ከመዝረፍ አልፎ ምንም ለውጥ ሊያመጣ አልቻለም።በህ.ወ.ሃ.ት መንደር ሙሑሩ ቦታ የለውምና።

‘‘ታላቁ ሩጫ’’ የሰማያዊ ፓርቲን ጥሪ ተቃወመ

በዘሪሁን ሙሉጌታ
 
በመጪው እሁድ በታላቅ ድምቀት በሚካሄደውና በአፍሪካ በግዙፍነቱ ቀዳሚ በሆነው ‘‘ታላቁ ሩጫ’’ ላይ የሚሮጡ ተሳታፊዎች በሳዑዲ አረቢያ ኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውን ጉዳት በሐዘን ለመግለፅ ጥቁር ሪቫን አድርገው እንዲሮጡ ሲል ሰማያዊ ፓርቲ ያቀረበውን ጥሪ የ‘‘ታላቁ ሩጫ’’ አስተባባሪዎች ተቃወሙ።
የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ አባላት በሳዑዲ አረቢያ የተፈናቀሉ ዜጎች ላይ የደረሰውን ግፍና በደል ለዓለም አቀፍ ህብረተሰብና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ለማስገንዘብ በሩጫው የሚካፈሉ ተሳታፊዎች ጥቁር ሪቫን በማድረግ ሐዘናቸውን እንዲገልፁ ሲል ወስኗል። የታላቁ ሩጫ አስተባባሪዎች በጉዳዩ ላይ እንዲተባበሩና አጋርነታቸውን እንዲገልፁ ለማድረግ በደብዳቤ ጥያቄውም እንደሚያቀርብ የፓርቲው ህዝብ ግንኙነት አስታውቋል።

Tuesday, November 19, 2013

ኢትዮጵያውያን ሰቆቃ ምክንያትና መፍትሄዎች ዶ/ር ያቆብ ኃ/ማሪያም



Image

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) :- 
ባለፈው እሁድ ህዳር 8 ሰማያዊ ፓርቲ በሳውዲ አረቢያ የሚገኙት ኢትዮጵያውያን ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ ለመቃወም ያወጣውን መርሃ ግብር መዝጊያ ላይ እውቁ የዓለም አቀፍ ህግ ምሁር ዶክተር ያቆም ኃ/ማሪያም በታጋባዥ እንግዳነት ተገኝተው ነበር፡፡ በወቅቱ ዶ/ክተሩ ያደረጉትን ንግግርም በስነ ስርዓቱ ላልተገኙት ይደርስ ዘንድ እንዲህ አቅርበነዋል፡፡ ምንም እንኳ ያለፉት 20 አመታት የሰቆቃና የውርደት አመታት ቢሆኑም ሳውዲ ውስጥ በሚገኙት ወገኖቻቸን የደረሰው ግን በ1977 በኢትዮጵያውያን ላይ ከደረሰው ርሃብና ውርደት በኋላ የመጀመሪያው ነው፡፡(ምንሊክ ሳልሳዊ)በዚህ ችግር ሳውዲ አረቢያ ያሉት ብቻ ሳይሆን አገር ውስጥም ሆነ በሌላው አለም ያለነው ኢትዮጵያውያን ተደፍረናል፡፡

ጭንቁን ቀን እንዴት እንለፍ!?

ጥላቻው እያደገ ሔዷል፣ ሳውዲ አሰሪዎች ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞቻቸውን ድሮ ድሮ በአረቦች ዘንድ የተከበርን፣ የታፈርን የእኛን የሃበሻ ልጆች “ጨካኞች ፣ የማይታመኑ!” እያሉ ጥላቻቸውን መገልጽ ጀምረዋል። November 14,2013 የወጣው አረብ ኑውስ Recent clashes make Saudis wary of Ethiopian maids በሚል ርዕስ ስር ሳውዲ አሰሪዎች ኢትዮጵያን ሰራተኞችን ለማባረር እየዛቱ ነው! ይህ የአረብ ኒውስ ዘገባ በሹክሹክታ የምንሰማው ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
የሪያድ መንፉሃን ግጭት ተከትሎ ደም እድገብሮም ለኢትዮጵያን ተሰጠው ወደ ሃገር ቤት የመግባትን እድል ለመጠቀም ከሃያ ሽህ በላይ ኢትዮጵያውያን የሪያድ መጠለያዎችን አጨናንቀዋል። እንዲውም በሪያድ የኢትዮጵያ አምሳደር ቁጥሩን ወደ ሃያ ሶስት ሽህ እንደሆነ ረቡዕ November 14,2013 ለወጣው አረብ ኒውስ አስታውቀዋል። አሁንም በሽዎች የሚቆጠሩ ወደ መጠለያ ለመግባት እየጎረፉ ነው። በመጠለያው የምግብና የሚጠጣ ውሃ እጥረቱ ደግሞ ኢትዮጰያውያኑ አጥር ሰብረው እንዲወጡ እያስገደደ ነው ተብሏል።

Stupid Numbers or Growth?

ወደ ገደለው ከመግባቴ በፊት ይችን እውነተኛ ታሪክ ልንደርደርባት።
በዛሬይቱ ኢትዮጵያ የንግድ አሰላለፍ – ወተት ከገበሬ ጀምሮ ተጠቃሚው ጋር እስኪደርስ ልክ ጎል እንደምትገባ እንደፕሪሜር ሊግ ኳስ ብዙ አማካኞች፣ ተከላካዮችና በረኛ ማለፍ አለበት። አንድ ገበሬ ላም አልቦ ለሰፈሩ ነጋዴ የሸጣል፤ ያ ነጋዴ ከሱ ከፍ ለሚል ነጋዴ ይሸጣል፤ ያም ነጋዴ (ላሳጥረውና) ለመጨረሻው ነጋዴ ይሸጣል፤ የመጨረሻው ነጋዴ በመጨረሻም ለተጠቃሚ። በሀገራችን የንግድ ደንብ መሰረት ወተት ከአንዱ እጅ ወደ ሌላው ሲያልፍ ውሃ ተጨምሮበት ነው። እናም አንድ ቀን ሁሉም በየእርከኑ ያሉ ነጋዴዎች በራሳቸው ግምት “የማይታወቅ ያክል” ትንሽ ትንሽ ውሃ እየጨመሩ የመጨረሻው ነጋዴ ጋር በብዙ ውሆች የታጀበ ወተት ይደርሰዋል። እሱም እንደለመደው ውሃ ሲጨምርበት ወተቱ ከወተትነት ወደ ውሃነት ይቀየራል። በዚያም “እንዴት ውሃ እንደጨመሩ ለኔ አይነግሩኝም?” በማለት በጣም ይናደድና ላስረከበው ነጋዴ ደውሎ “እንዴት ነው ጎበዝ – እየተነጋገርን እንጂ” አለው አሉ።

በዜጎች ሰቆቃ ፕሮፓጋንዳ ለምን? በፕሮፓጋንዳ የተለከፈ ፓርቲና መንግስት

ግርማ ሠይፉ ማሩ 
በኢትዮጵያ ሀገራችን ፓርቲና መንግሰት መለያየት አሰቸጋሪ እንደሆነ ከተረዳን ውለን አድረናል፡፡ ለዚህም ነው
መንግሰት የሚባለው አካል ሁል ጊዜ ግዴታውን በሚወጣበት ጊዜ አብሮ ፕሮፓጋዳ የሚጨምርበት፡፡ ሰሞኑን ግን
ቅጥ ያጣ የፕሮፓጋዳ ርዕስ ሆኖ ያገኙሁት ደግሞ በሳውዲ ሀረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ላይ በደረሰው ግፍ፣
ሰቃይ፣ መከራና ሞት ጎን ለጎን የኢትዮጵያ መንግሰት ችግሩን ለመፍታት ከሚያደርገው ጥረት የገዘፈ የፕሮፓጋንዳ
ዘመቻና ነውረኝነት የተሞላበት ዘገባ ነው፡፡

የኢትዮጵያውያን ከሳውዲ አረቢያ መውጣት ያስከተለው ችግር

Foreign workers wait for a taxi as they leave the Manfuhah neighbourhood of the Saudi capital Riyadh on November 10, 2013, after two people have been killed in clashes between Saudi and other foreign residents the previous day, according to the Saudi police. On November 4, the authorities began rounding up thousands of illegal foreign workers following the expiry of a final amnesty for them to formalise their status. AFP PHOTO/FAYEZ NURELDINE (Photo credit should read FAYEZ NURELDINE/AFP/Getty Images)

እአአ ከ 610 ዓ ም ጀምሮ የእስልምና ኃይማኖት መገኛ እና ማስፋፊያ ማዕከል በመሆን ትታወቃለች። በማዕከላዊው ምስራቅ በፋርስ ባህረ ሰላጤ እና በቀይ ባህር መካከል በተንጣለለው የዓረቢያ በረሃ ላይ ጆርዳን ኢራቅ ኩዌት የመን ኦማን ቀጠር እና የተባበሩት ኣረብ ኢማራት በምድር ያዋስኗታል።

Monday, November 18, 2013

በገዛ ሀገራችን መንግስታዊ ሽፍቶችም ሆነ በተሰደዱበት ሀገር ሰዎች መደፈሩ ፣ መዋረዱ መቼ ይሆን የሚቆመው ?

“… በየምሽቱ ሁላችንንም ወደ ምርመራ ክፍል ይወስዱናል ፡፡ ከዚያም እያንዳችንን ለያይተው ይገርፉናል ፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ ስጠራ ሶስት ወንዶች በክፍል ውስጥ ይጠብቁኝ ነበር ፡፡ ወዲያዉኑ ሶስቱም በየተራ እየተፈራረቁ ደፈሩኝ ፡፡ ወደነበርንበት ጉድጓድ ስመለስ በከፍተኛ ህመም እየተሰቃየሁ ነበር ፡፡ አሁን ድረስ ህክምና ማግኘት አልቻልኩም ፡፡

የስደት ውርደት በዛ! ኢትዮጵያዊነትም ረከሰ

በሳዑዲ ዓረቢያ በኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ላይ እየተፈጸመ ያለውና እየተስተጋባ ያለው አሰቃቂ ግድያና ድብደባ ይዘገንናል፣ ይሰቀጥጣል፣ ያቅለሸልሻል፡፡ አረመኔያዊ ነው፡፡ 
የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት የራሱን ሕግ ማስከበር እንዳለበት እናምናለን፡፡ በሕገወጥ መንገድ አገሪቱ ውስጥ የገቡትን ሰዎች ወደ አገራቸው ቢመልስ ወይም ቢያባርር ተቃውሞ የለንም፡፡ ጥያቄያችንና ተቃውሞአችን ግን በሕገወጥ መንገድ የገቡትን ኢትዮጵያውያን ለምን መለስካቸው?ለምን አባረርካቸው?የሚል አይደለም፡፡ ሕገወጦችን መቆጣጠርና ሕግን ማስከበር የማንም አገር መብትና ኃላፊነት ነውና፡፡

Friday, November 15, 2013

አዲስ አበባ ላይ በሳዑድ አረቢያ ኤምባሲ አጠገብ ሊካሄድ የነበረ የተቃዉሞ ሰልፍ በፖሊስ ተበተነ። አሶሲየትድ ፕረስ እንደዘገበዉ ፖሊስ በመቶዎች የሚቆጠሩን ሰልፈኞች ለመበታተን ኃይል ተጠቅሟል።

0,,17229922_303,00
የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት እርማጃና ተቃዉሞዉ
አዲስ አበባ ላይ በሳዑድ አረቢያ ኤምባሲ አጠገብ ሊካሄድ የነበረ የተቃዉሞ ሰልፍ በፖሊስ ተበተነ። አሶሲየትድ ፕረስ እንደዘገበዉ ፖሊስ በመቶዎች የሚቆጠሩን ሰልፈኞች ለመበታተን ኃይል ተጠቅሟል።

መንግሥት አልባ አገር!

ህወሃት ፈቀደ እኛም ተዋረድን

tplf addis mexico square


የብዙ ሺህ ዘመናት የመንግሥትነት ታሪክ የነበራት አገራችን ኢትዮጵያ ዛሬ መንግሥት አልባ አገር ናት ብሎ ደፍሮ መናገር የሚቻልበት ወቅት ላይ ደርሰናል።

ጭንቁን ቀን እንዴት እንለፍ!?

የመረጃው ክፍተት የለያየን ግፉአን ዜጎችና ዲፕሎማቶች

ethsaudi
ጥላቻው እያደገ ሔዷል፣ ሳውዲ አሰሪዎች ኢትዮጵያውያን የቤት ሰራተኞቻቸውን ድሮ ድሮ በአረቦች ዘንድ የተከበርን፣ የታፈርን የእኛን የሃበሻ ልጆች “ጨካኞች ፣ የማይታመኑ!” እያሉ ጥላቻቸውን መገልጽ ጀምረዋል። November 14,2013 የወጣው አረብ ኑውስ Recent clashes make Saudis wary of Ethiopian maids በሚል ርዕስ ስር ሳውዲ አሰሪዎች ኢትዮጵያን ሰራተኞችን ለማባረር እየዛቱ ነው! ይህ የአረብ ኒውስ ዘገባ በሹክሹክታ የምንሰማው ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ከሳውዲ አረቢያ መንግሥት ጐን በመቆም ዋና ተባባሪ መሆኑን በዛሬው እለት አስመስክሯል! (ሰማያዊ ፓርቲ)

በሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለው በደል እና ስቃይ መጠኑ ከመጨመር አልፎ ሕይወትን እስከማሳጣት መድረሱ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህን በደል እና ስቃይ ለመቃወም እና ሀዘናችንን ለመግለፅ በዛሬው ዕለት ማለትም ህድር 6 ቀን 2006 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው በሳውዲ አረቢያ ኢምባሲ ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ የተጠራ ቢሆንም በመንግሥት ታጣቂዎች በተወሰደ በአሰቃቂ እርምጃ ሰልፉ ሊካሄድ አልቻለም፡፡

Ethiopia's Semayawi party (blue party)
እኛ ኢትዮጵያን በውጭ በሚገኙ ዜጐቻችን ላይ የሚደርሰው በደልና ግፍ እንዲቆም፣ ይህንንም ድርጊት የፈፀሙት ለሕግ እንዲቀርቡና የተጐዱ ዜጐች ተገቢውን ካሳ እንዲያገኙ፤ የኢትዮጵያ መንግሥትም በዜጐቹ ላይ ያሳየውን ቸልተኝነት በአስቸኳይ በማቆም ተገቢ የሆነውን የመንግሥት ኃላፊነት እንዲወጣ ቢጠየቅም፤ ሰልፉ በተቃራኒው በመንግሥት ታጣቂዎች በተወሰደ አሰቃቂ እርምጃ ተጠናቋል፡፡

መቋጫ ያጠው የወገኖቻችን ስቃይ እና ሞት በሳውዲ አረቢያ ፡አሁንም ቀጥሏል !

ትላንት አመሻሹ ላይ ሪያድ ከተማ በተለምዶ መንፍሃ እየተባለ የሚጠራ አካባቢ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን አገርሽቶ በዋለው ተቃውሞ የተጓዳ የሞተ ባይኖርም ኢትዮጵያውያኑ ድምጻቸውን ከፍ አድረገው አንድነን አንድነን … መብታችን ይከበር ….እኛም ሃገር አለን ወዘተ… በሚል መፈክር ታጅበው ብሷታቸውን ሲያሰሙ መዋላቸውን የሚገልጹ የአይን እማኞች የሳውዲ የጸጥታ ሃይሎች ተቃውሞውን ለመብተን በከፈቱት ቶክስ ይሰማ በነብረው የጥይት ድምጽ አካባቢውን ወደ ጦርነት አውድማ ለውጦት ማምሸቱን የገልጻሉ። 

ሰበር ዜና ወያኔ የሰማያዊ ፓርቲ መሪዎችን አሰረ ሰልፉም እንዳይደረግ ከለከለ

ህዝብ መንግስት ከሳውዲ ጋር አበረ እያለ እያማረረ ነው፡፡
የስዑዲ ፖሊስ በጅዳ ከተማ የሚገኙ ኢትዮዽያውያን ስደተኞች ‘ሕገ ወጥ ኗሪዎች’ በሚል ሰበብ እያሰረና እየደበደበ ይገኛል። የኢህአዴግ ፖሊስም በአዲስ አበባ ከተማ የሚኖሩ ኢትዮዽያውያን ዜጎች ‘ሕገወጥ ሰልፈኞች’ በሚል ሰበብ እየገረፈና እያሰረ ይገኛል።

አዜብ መልቀቂያ አስገቡ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

ወ/ሮ አዜብ መስፍን ለሕወሐት ማ/ኮሚቴ የመልቀቂያ ደብዳቤ ማስገባታቸውን ምንጮች አስታወቁ። ከባለቤታቸው ህልፈት በኋላ በፓርቲው የነበራቸው ተሰሚነትና የበላይነት እየተሸረሸረ በመምጣቱና ከኤፈርት ሃላፊነታቸው በመነሳታቸው እንዲሁም ጓጉተውለት የነበረው የአዲስ አበባ ከንቲባነት ስልጣን በማጣታቸው፣ ተስፋ መቁረጥ ውስጥ በመግባታቸው ምክንያት ለፓርቲው የመልቀቂያ ጥያቄ ማቅረባቸውን ምንጮቹ አስረድተዋል። በተጨማሪ አዜብ ይተማመኑባቸው የነበሩት ሹማምንት ከስልጣን እየተገፉ ገሚሶቹም እስር ቤት መወርወራቸው እንዲሁም በስብሃት ነጋ ቡድን እየተወሰደባቸው ያለው ፖለቲካዊ የበላይነት መቋቋም ስለተሳናቸው ከፓርቲው በግዜው መሰናበት እንደመረጡ ከምንጮቹ መረዳት ተችሏል። አዜብ መስፍን ላቀረቡት የመልቀቂያ ጥያቄ ፓርቲው በቅርቡ ምላሽ ይሰጣል ተብሎ እንደሚጠበቅ ያመለከቱት ምንጮች፣ አያይዘውም ጥያቄው ተቀባይነት ካገኘ አዜብ በሲውዲን ወይም አሜሪካ ቨርጂኒያ በገዙት መኖሪያ ቤት ጠቅልለው ሊገቡ እንደሚችሉ አመልክተዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ጄ/ል ሳሞራ የኑስ ከኢታማጆር ሹመታቸው በማስነሳት በምትካቸው በቅርቡ ሌ/ጄ ተደርገው የተሾሙትን ጄ/ል ዮሃንስ ገ/መስቀልን ለመተካት መታቀዱን ምንጮች ጠቁመዋል።

Thursday, November 14, 2013

“ለኢትዮጵያውያን በችግሩ ዙሪያ ማብራሪያ እንዲሰጥ እንጠይቃል”

“ለኢትዮጵያውያን በችግሩ ዙሪያ ማብራሪያ እንዲሰጥ እንጠይቃል”

saudi ethio3


ሰሞኑን በሳውዲ አረቢያ በተለይ በኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ እየተፈፀመ ያለው እንግልት፣ ድብደባ፣ ግድያና ለህይወት አስጊ በሆነ ሥፍራ ማጎር ከኢሰብአዊነትም በላይበኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ላይ የተሰነዘረ ጥቃት ነው፡፡

ከካሌብነት ወደ ከልብነት

በእውቀቱ ሥዩም

ethio saudi6
ኢትዮጵያ እመ-መከራ
የግዜር መመራመሪያው የስቃይ ቤተ-ሙከራ
መውደቅማ ነበር ያባት
እንደ ያሬድ እስከ ሰባት
እንደ በላ ብላቴና፣ የእንክርዳድ ሙልሙል እንጎቻ
የትውልዴ እጣ ፋንታ ፣ መውድቅ መውድቅ መውድቅ ብቻ…

“Are Ethiopians without a country?”

SMNE holds KSA and EPRDF accountable!

ethio saudi


Press Release
Washington, DC, November 11, 2013
SMNE Calls on the Saudi government to stop this brutal and inhumane treatment of the Ethiopian migrant workers immediately And on the TPLF/ERPDF regime to Protect Ethiopian Citizens in Saudi Arabia

Wednesday, November 13, 2013

ብሄራዊ ውርደት፤ የምንመጻደቅበት ‘ሌጋሲ’

ብሄራዊ ውርደት፤ የምንመጻደቅበት ‘ሌጋሲ’


ክንፉ አሰፋ 
The suffering of Ethiopians in Saudi Arabia
ወገናችንን በጥይት ሲደፉት በራሱ ላይ አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ባንድራችንን ጠምጥመውበታል[1]። ጭካኔ በተሞለበት መንገድ የተገደለው ይህ ኢትዮጵያዊ አስከሬኑም በሰላም አላረፈም። በአካሉ ላይ ያረፈውን ጨርቅ በሴንጢ እየቆራረጡ በሰብአዊ ፍጡር ላይ ሊደረግ የማይገባውን ሁሉ አደረጉበት። ድርጊቱ ናዚዎች በኦሽዌትስ ይፈጽሙት የነበረውን አሰቃቂ ግፍ ያስታውሰናል። በ21ኛው ዘመን እንዲህ አይነቱ ክስተት ይደገማል ብሎ የሚያስብ የለም። እነሆ ሳውዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ እየፈጸመችው ነው። በስውር ሳይሆን በግልጽ። እንደ ኦሽዊትስ በታጠረ የማጎርያ ካምፕ ሳይሆን በአደባባይ።

Tuesday, November 12, 2013

ታላቅ ሀገራዊ የተቃውሞ ጥሪ!! ሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ጠራ!!!

ከወገኖቻችን ጐን በመቆም ብሄራዊ ክብራችንን እናስመልሳለን

Ethiopia's Semayawi party (blue party)ሰሞኑን የሳውዲ አረቢያ መንግሥት በኢትዮጵያዊያን ላይ እየፈፀመ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት በመቃወም ሰማያዊ ፓርቲ ታላቅ የተቃውሞ ጥሪ አስተላልፏል፡፡በመሆኑም በዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን ኢሰብዓዊ ድርጊት ለማስቆምና የዜጐችን ህይወት ለመታደግ እንዲሁም ዜጐቻችን በአፋጣኝ ወደ ሀገራቸው የሚመለሱበትን ሁኔታ መንግሥት እንዲያመቻች እና በተጨማሪም በዜጐቻችን ላይ ለደረሰው የአካል መጉደል፣ እንግልት፣ ድብደባ፣ አስገድዶ መድፈርና የህይወት መጥፋት ኃላፊነቱን የሚወስዱ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ፤ ለተጐዱ ወገኖቻችንና ቤተሰቦቻቸውም አስፈላጊው ካሳ እንዲደረግላቸው ፓርቲያችን አበክሮ እያሳሰበ፤ የብሄራዊ ክብርና የወገኖች ስቃይ የሚያሳስባቸው አካላት በሙሉ በዚህ ታላቅ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ላይ እንዲሳተፉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡
የተቃውሞ እንቅስቃሴ አፈፃፀም፡-

በሳዑዲ አረብያ የመከራ ማጥ ውስጥ ላሉት ወገኖቻችን ሲባል ፈጥነን እንነሳ!

ዳኛቸው ቢያድግልኝ

Protest at Saudi Arabia Mission to United Nations!
እንደ ሰው አንድ የሚያደርገን ባሕርይ፣ እንደ ኢትዮጵያዊነትም ሁላችንንም የሚመለከተንና የፖለቲካም ሆነ የሃይማኖት ልዩነት የማይነጣጥለው በደል በሳዑዲ አረብያ ግዛት እየተፈጸመ ነው።

ወያኔ ማለት ቁምጣ ለብሶ የመጣ ደርግ ነው ፡፡

http://www.facebook.com/photo.php?v=286230021510610
ጥቁር ሽብር ወያኔ ቁምጣ የለበሰ ደርግ ነው ! እመኑኝ በየትኛውም የታሪክ ገጠመኝ የሳወዲ መንግስት የዚህ አይነት ድፍረት ያውም በአደባባይ በዜጎቻችን ላይ አሳይቶ አያውቅም ፡፡ ነገሮችን ተመልሰን ከተመለከትን ይህ ግፍና በደል የእኛው ባለስልጣናት ሳውዲወችን አደፋፍረው ያስፈፀሙት ጉዳይ ነው፡፡

Monday, November 11, 2013

የኢሕአዴግ መንግሥት አሳምሮ ይፈራል!

በኃይሉ አርአያ (ዶ/ር) - የአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት አባል

ሰሞኑን የኢሕአዴግ መንግሥት ይፈራል አይፈራም የሚል ጉዳይ ከፓርላማ ተነስቶ ወደ መገናኛ ብዙኃንም ደርሷል። ጉዳዩ
 የተነሳው የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ አዲሱ ፕሬዚዳንታችን በፓርላማ ያደረጉትን ንግግር አስመልክቶ

ባቀረቧቸው የማማሻሻያ ሐሳቦችና ጠቅላይ ሚኒስትራችን በሰጡት ምላሽ ዙሪያ ነው። ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዝ ሪፖርተር ጋዜጣ ጥቅምት 13 ቀን 2006 ዓም በአወጣው ዕትሙ ‹‹'ፈሪ' መንግሥት?›› በሚል ርዕስ ጋዜጠኛ የማነ ናግሽ ጥሩ ትንተና አቅርቧል። የፍርኃት ነገር ከተነሳ ጋዜጠኛው ያነሳውን ለማዳበር በእኔም በኩል የምለው አለኝ። የኢሕአዴግ መንግሥት አሳምሮ ይፈራል። የኢሕአዴግ መንግሥት አሳምሮ ይፈራል ስል ግን በደፈናው አይደለም። በርካታ የማይፈራቸው ነገሮች አሉ። ለምሳሌ ጦርነትን አይፈራም። በተለይ ሕወሓት/ኢሕአዴግ ጥርሱን ነቅሎ ያደገበት ጉዳይ ነው። ሕግ መጣስን አይፈራም። ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን መጣስን አይፈራም። መዋሸትን አይፈራም።

የኢሕአዴግ መንግሥት ይፈራል ስል በተለይ የማተኩረው በአንድ ጉዳይ ላይ ነው። እውነት ላይ። የኢሕአዴግ መንግሥት እውነትን ይፈራል። እውነትን ስለሚፈራ እሱ ራሱ በሚፈልገው መንገድ እንዲታወቅ ከሚፈልገው ውጪ ሕዝቡ እውነቱን እንዲያውቅ አይፈልግም። ይህ ደግሞ የአምባገነን አውራ ፓርቲዎች መንግሥታት አንዱና ዋናው የደባቂነትና የሸማቂነት መገለጫ ባህሪ ነው። የኢሕአዴግ መንግሥት እውነትን ለመፍራቱ በርካታ ማስረጃዎችን መጥቀስ ይቻላል። ለጊዜው ግን አራቱን ብቻ በምሳሌነት እንደሚከተለው ልጥቀስ።

Friday, November 8, 2013

ሕወሓት አለማቀፍ አሸባሪ መዝገብ ላይ በአሸባሪነት የሚታወቅበት ፕሮፋይል::

ምንጭ :- START – UNIVERSITY OF MARYLAND – የአሸባሪዎች አጥኚ ቡድን
የአሸባሪ ድርጅቶች መዝገብ
በሃገሩ ቋንቛ መጠሪያው .. አልተገለጸም
የድርጅቱ ስም …..የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (TPLF)
የሚንቀሳቀስበት አከባቢ … ኢትዮጵያ
የተቋቋመበት ጊዜ ….. አልተገለጸም
የአባላቶቹ ቁጥር/ጥንካሬው … አይታወቅም
መለያው ….. ኮሚኒስት/ሶሻሊስት/ብሄርተኛ/ተገንጣይ
የገንዘብ ምንጩ …. አይታወቅም
የተነሳበት የፖለቲካ ፍልስፍና
ራሱን የትግራይ ንቅናቄ ወይንም ወያኔ በማለት በ1970ዎቹ መጀመሪያ በመንግስቱ ሃይለማርያም አገዛዝ ላይ የተጀመረ ተቃውሞበ1975 አከባቢ የትግራይ ነጻ አውጪ በማለት ተመስርቶ በኤርትራ ነጻ አውጪ ስር እየተዳደረ ውጊያ የከፈተ ድርጅትነው::አላማቸው የአልቤንያን ሞዴል የተከተለ የኮሚኒስት ስርኣት በማስፈን የታለመ…የትግራይን ህዝብ ከደርግ አገዛዝ ነጻ ለማውጣትየተነሳ ነበር::በሜይ 1989 የደርግን ሰራዊት በማሸነፍ ሙሉ ትግራይን መቆጣጠር ችሎ ነበር::በተለያየ ጊዜ ከሻእቢያ ጋር እና በተናጠልበተለያዩ አከባቢዎች የአሸባሪነት ድርጊት ፈጽሟል::

Breaking news የግንቦት 7 መሪዎችን ለመግደል የተጠነሰሰው ሴራ ከሸፈ

xx
በኢትዮጵያ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት ዋና ሃለፊ በአቶ ጌታቸው አሰፋ እና በጠቅላይ ሚኒስትሩ የብራዊ ደህንነት አማካሪ በአቶ ጸጋየ በርሄ ቁጥጥር የተመራና በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌና በግንቦት7 ህዝባዊ ሀይል መሪዎች ላይ የተቀነባበረው የግድያ ሙከራ ከሸፈ።
ከግንቦት7 ህዝባዊ ሀይል ለኢሳት የደረሰው መረጃ እንዳመለከተው ለግድያ የተላከው ሙሉቀን መስፍን የተባለው ግለሰብ በትናንትናው እለት በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን፣ በእየደረጃው ከሚገኙ የደህንነት ሀላፊዎች ጋር በስልክ ሲያደርግ የነበረው የስልክ ለውውጥ በህዝባዊ ሀይሉ የመረጃ ክፍል ሲቀዳ ቆይቷል።
ወያኔ-ኦ-ሚሊኒየም በሚል የተመራው የግድያ ዘመቻ -በነገው እለት ጥቅምት 30/2006 ዓም ሊካሄድ ታቅዶ እንደነበር የድምጽ መረጃው ያመለክታል።

ትግል በመሰዋትነት ይሰፈራል!!!

ከተስፋዬ ዘበነ(ኖርዌይ በርገን)

ሃገርና ሕዝብ በውጥረት በታመሰበት አምባገነን የህውሃት/ኢአዴግ/ ዘረኛ ስርዓት ከምስራቅ እስከ ምህራብ ከሰሜን እስከ ደቡብ ሃገሪቱን እንደ ብራና ወጥሮ የሕዝቡን ኑሮ ሲያከብድበት እያየንና እየተመለከትን ስርኣቱን ለመታገል በየትኛውም መልኩ የተዋቀርን ድርጅቶች ሳንጀምር እየጨረስን ወይም እራሳችን ስላዋቀርነው ፓርቲ፣ ድርጅት ወይም ሸንጎ ሳንመረምር ሌሎች ስለሚደክሙበትና ስለሚለፉበት ትግል መፃዪ እድል እየተነበይን እርስ በእርስ ስንናከስና ስንጣረዝ የዘረኛውን የህውሃት እድሜ አበርክተን እዚህ አድርሰነዋል፡፡
በዚህ እኩይ የህውሃት ስርዓት መጀመሪያ ጀምሮ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል በራስ ተነሳሺነት ተዋቅረው እየተንቀሳቀሱ ያሉት የፖለቲካ ድርጅቶች አላማና ግባቸውን ለማስፈፀም የሰላማዊ ትግል መርሆችን ተግባራዊ ለማደረግ አንድም በራሳቸው የውስጥ ችግር ምክንያት፣ በዋነኝነት ግን ስርዓቱ ካለው ተፈጥሮዊ ባህሪ አንፃር ከሕዝብ ጋር ያለው ትስስርና በሕዝብ ላይ የሚፈፅመው የመልካም አስተዳደር ችግርም ሆነ የሰብሃዊ መብት አያያዝ እንዲሁም ሌሎች ዘርፈ ብዙ ችግሮች ስላሉበት በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ለተደራጁ  ፓርቲዎች  ነፃነት ሰጥቶ ሞቱን ማፋጠን አይፈልግም፡፡

Thursday, November 7, 2013

ኢትዮጵያ፣ የቦምብ ፍንዳታ እና ማስጠንቀቂያው

ኢትዮጵያ ውስጥ የሽብር ጥቃቶች ሊደርሱ ይችላሉ በሚል የጸጥታ ኃይሎች በተጠንቀቅ እንዲቆሙ በታዘዙበት በኣሁኑ ወቅት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኣንድ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ላይ በፈነዳ ቦምብ አራት ሰዎች መሞታቸው ተዘገበ።
ከሶስት ሳምንታት በፊት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ላዓለም ዋንጫ ማጣሪያ አዲስ ኣበባ ላይ ከናይጄሪያው ቡድን ጋር በሚጫወትበት ዕለት ጥቃት ለማድረስ ሲዘጋጁ ነበር የተባሉ ሁለት የሶማሊያ ኣጥፍቶ ጠፊዎች በራሳቸው ቦምብ መሞታቸው ይታወሳል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ ህብረተሰቡም ጥንቃቄ እንዲያደርግ መንግስት እያሳሰበ ሲሆን የጥንቃቄ ማስጠንቀቂያውን ተከትሎም በተለያዩ አካባቢዎች የጸጥታ ቁጥጥሩ መጠናከሩም ተሰምቷል።

አብዮት እና ወጣትነት – በወጣት ሃብታሙ አያሌው (የአንድነት ፓርቲ ም/የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ)

ክፍል 1
ሰሞነኛ
አዲሱን አመት ተቀብለን ሁለት ወራት ሳንሻገር ጥቅምት 11 ቀን የኢትዮ ምህዳር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ እና ሥራ አሥኪያጁ ጋዜጠኛ ሚሊዮን ደግነው ክስ ተመስርቶባቸው ፍርድ ቤት ቀረቡ፤ በዳግም ቀጠሮ ዕረቡ ጥቅምት 20 ቀን በሐዋሳ ከተማ ጋዜጠኞቹ ለፍርድ ቤት ቀጠሮ ሄደው በስልት የተቀናበረ በሚመስል ሆኔታ ለመኪና አደጋ ተዳርገው ጋዜጠኛ ኤፍሬም የከፋ አደጋ ሲደርስበት ዋና አዘጋጁ ጌታቸው እና ሥራ አስኪያጁ ጋዜጠኛ ሚሊዮን በመለስተኛ ጉዳት መትረፋቸው ተሰማ፤ ጥቅምት 13 ቀን እኔን ጨምሮ ሌሎች ሦስት ጓዶቼ አንድ አመት በተጓተተ ክስ ፍርድ ቤት ቀርበን ክሱ ለህዳር 24 ተቀጠረ፡፡
ጥቅምት 15 ቀን የኢትዮጵያ ህዝብ አብዝቶ የሚሳሳለት ጋዜጣኛ ተመስገን ደዳለኝ ፍርድ ቤት ቀርቦ አንደ ገና በድጋሚ ቀጠሮ ጠቅምት 21 ውሎው ፍርድ ቤት ሆነ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስተር ኃይለማርያም ደሳለኝ በበኩላቸው መንግስታዊ ስልጣናቸውን በመጠቀም በሀሣብና በአመለካከት ጎራ ለይተው በሚታገሏቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ ፍረጃ አና ዛቻ ሲሰነዝሩ ከረሙ፤ ፕሬዝዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ ቤተ መንግስቱን ለቅቀው በየወሩ ግማሽ ሚሊዮን ወደ እሚከፈልበት ቤታቸው ሲያመሩ ዶ/ር ሙላቱ ፕሬዘዳንት የሚል ስያሜ በመያዝ ሰተት ብለው ወደ ቤተ መንግስቱ መግባታቸው ተሰማ፡፡

ሀገራዊ ውርደት እንዲያበቃ ወያኔን ከሥልጣን ማስወገድ!!!

የወያኔ ገዢ ጉጅሌ በባህርዩ ኢትዮጵያ ከዚህ በፊት አጋጥሟት የማያውቅ ፍጹም ኢሰብዓዊና ነውረኛ ስብስብ እንደሆነ ለመረዳት ኢትዮጵያዊያንን ለማዋረድ የሚጠቀሟቸውን ተግባራትና ቃላትን ማጤን ይበቃል።
በሶማሌ ክልል የኦብነግን ታጣቂዎች ቅስም ለመስበር ልጃገረዶችንና እናቶችን ብቻ ሳይሆን ወንዶችንም ጭምር በቤተሰብ ፊት በደቦ የሚደፍሩ፤ ለዚህ ተግባር የሠለጠኑ የልዩ ጦር አባላት መኖራቸው በስፋት የሚታወቅና በተደጋጋሚም የተዘገበ ጉዳይ ነው። ወያኔ፣ የኦጋዴን ወገኖቻችን በዚህ ጥቃት ተሸማቀው ያነገቡትን መሣሪያ ጥለው ፀጥ-ለጥ ብለው ይገዛሉ ብሎ ተስፋ ያደረገ ቢሆንም እየሆነ ያለው ግን የዚህ ተቃራኒ ነው። ዛሬ የሶማሌ ክልል ወንዱም ሴቱም፤ ወጣቱም አዛውንቱም በፀረ-ወያኔ አቋም የጋራ መግባባት ላይ ደርሷል። በኦጋዴን የወያኔ አስነዋሪ ጥቃት የፈጠረው ምሬት በውጭ አገራትም በሚደረጉ የፀረ ወያኔ ትግሎች የኢትዮጵያ ሶማሌ ተወላጆች ተሳትፎ እንዲጎለብት አድርጎታል። በሶማሌ ወገኖቻችን ላይ የደረሰው ጥቃት በሁላችንም ላይ የደረሰ ነውና ቁጭታቸውን እንጋራለን። በሶማሌ ወገኖቻችን ላይ የደረሰው ጥቃት ሀገራዊ ውርደት ነው።