Translate

Tuesday, September 30, 2014

በህወሃት “የትግራይ ኩራት ተነክቷል” ባዮች አይለዋል

“ሃይለማርያም በቀጣዩ ምርጫ ሊታቀቡ ይችላሉ”
d t h
የሰሞኑ የጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ካቢኔያቸውን “ከኋላ” አስከትለው ከፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ያካሄዱት የፊት ለፊት ንግግር ያስደሰታቸውና ያስኮረፋቸው ክፍሎች አሉ። “በህወሃት መንደር ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ የመወከል ባለጊዜው ህወሃት ነው። ህወሃት የኢትዮጵያ ምልክትና ተምሳሌት ነው” የሚሉት ወገኖች ቀደም ሲል ሲሰማ የነበረውን “የትግሬ ኩራት ተነክቷል” ስሜት በገሃድ ሲያንጸባርቁ ታይቷል።

የዋሽግተኑ ተቃውሞ ኢሳትን በዓለም ዓቀፍ ስመጥር የዜና አውታሮች ዝናው ገንኖ እንዲወጣ አደረገ፣ኤምባሲው ጉዳዩን ለፖሊስ አሳውቆ እርዳታ ከመጠየቅ ይልቅ አራት ኪሎ ያለ ይመስል ዋሽግተንን በተኩስ መናጡ አሜሪካኖችን ማናደዱ አልቀረም (የዋሽግተኑን የኢትዮጵያ ኤምባሲ በተመለከተ የጉዳያችን አጭር ዘገባ)


ፎቶ www.csnwashigton.com 

''መሣርያውን ወደሚከራከሩት ሰዎች ደገነ እና ተኮሰ'' ''He points the weapon at others who argue with him and fires'' ሮይተርስ ከዋሽግተን ዲሲ ዛሬ የዘገበው። 

ዛሬ መስከረም 19፣2007 ዓም ዋሽግተን ዲሲ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በተቃዋሚ ኢትዮጵያውያን ቁጥጥር ስር ውሎ ባለ ኮከቡ ሰንደቅ ዓላማ በነፃው የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ተቀይሯል። ተቃውሞውን አስመልክቶ ኢሳት ዘግይቶ በለቀቀው ተጨማሪ ዘገባ ተቃዋሚዎቹ በኢምባሲው ውስጥ ዘልቀው የአቶ አንዳርጋቸውን እና የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ ይዘው ''ነፃነት! ነፃነት!'' ሲሉ አሳይቷል።

Monday, September 29, 2014

ለጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ …ከኤርምያስ ለገሰ

በቅድሚያ መጵሀፉን ጊዜ ሰጥተህ በማንበብ አስደማሚ ምልከታ በመስጠትህ ከልብ አመሰግናለሁ ። የተጳፈበትም አንዱ አላማ ይህ ስለሆነ። ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ በእይታህ ላይ እነዚህ ጉድለት ይታይባቸዋል ብለህ ያነሳኸው እና የወደፊት ግምቶችህ ላይ የተወሰነ አስተያየት ለመስጠት የሚጋብዙ ስለሆነ ትንሽ ማለት ፈለኩ። በዚህ አጋጣሚ ሌሎች በመጵሀፉ ይዘት ላይ ዝርዝር ግምገማ ላደረጉ ሰዎች ምስጋናዬ ይድረሳችሁ። ለእያንዳንዱ አስተያየት መስጠት ከጊዜ አኳያ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ የማልዘልቅበትን መንገድ ልጀምረው አልፈለኩም ። የጋዜጠኛ ተመስገንን በልዩ ሁኔታ መመልከት የፈለኩበት የራሱ ምክንያቶች አሉት። ተመስገን ሀገር ቤት ባለ አስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ በድፍረት መጵሀፉን ማንበቡን በአደባባይ ገልጶ በመጵሄት ሳይቀር መክተቡ ልዩ ያደርገዋል ።

Sunday, September 28, 2014

የታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ በአውሮፓ ህብረት ምክርቤት ኮሚሽን ውይይት ተደረገበት፤ በአስቸኮይ እንዲፈታም ጠይቀዋል።

የታጋይ አንደርጋቸው ጽጌ ጉዳይ በአውሮፓ ህብረት ምክርቤት ኮሚሽን ውይይት ተደረገበት፤ በአስቸኮይ እንዲፈታም ጠይቀዋል።

የታጋይ አንደርጋቸው ጽጌ ጉዳይ በአውሮፓ ህብረት ምክርቤት ኮሚሽን ውይይት ተደረገበት፤ በአስቸኮይ እንዲፈታም ጠይቀዋል።
ታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌ በአምባገነኑ ወያኔ እጅ ወድቆ መሰቃየት ከጀመረ 3 ወራት አልፈዋል። ባለፉት ቀናት የአውሮፓ ህብረት የሰበአዊ መብት ም/ቤት በጉዳዩ ላይ ከፍተኛ ውይይት አደርገዋል ። አንዳርጋቸው የፖለቲካ እስረኛ እና ለዲሞክራሲ፣ ለነጻነት፣ ለመልካም አስተዳደር እና ሰበአዊ መብት መከበር የሚታገል የግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር ሲሆን ባስቸኮይ ተለቆ ወደ እንግሊዝ እንዲመለስ ኮሚሸነር ተናግረዋል፡፡

Friday, September 26, 2014

በኦጋዴን ሰሞኑን ለተፈጸመው ጅምላ ግድያ ወታደራዊ ምላሽ ይሆን ዘንድ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በቋራ ወታደራዊ ጥቃት ፈጸመ

ኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በቋራ ወታደራዊ ጥቃት ፈጸመ። ማጥቃቱም በወያኔ አምባገነናዊ አገዛዝ በኦጋዴን ለተፈጸመው ጅምላ ግድያ ወታደራዊ ምላሽ መሆኑን አስታውቋል።timthumb
ሕዝብን ኢ-ፍትሀዊ በሆነ መንገድ እያሰረ፣ እያንገላታ፣ እያሳደደና እየገደለ የሚገኘውን የወያኔ አምባገነናዊ አገዛዝ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ለማውረደ በአርበኝነት ትግል እየተፋለመ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር በተለያዩ ጊዜያት በወያኔ ላይ በሚያካሂዳቸው ወታደራዊ የማጥቃት ዘመቻዎች ለተጨቆነው ሕዝብ ብሶት አፀፋዊ ምላሽ በመስጠት ሕዝባዊ ወገንተኝነቱን እያሳየ እንደሚገኝ የሚታወቅ ነው።
ሰሞኑን ወያኔ በኦጋዴን ወገኖቻችን ላይ ጅምላ ጭፍጨፋ ማካሄዱን ተከትሎ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር የአፀፋ ምላሽ እንደሚሰጥ ማስታወቁ የሚታወስ ሲሆን በዚህም መሰረት መስከረም 8 ቀን 2007 ዓ/ም በቋራ ወረዳ ልዩ ስሙ ደለጎ በተባለው አካባቢ በወያኔ ፀረ-ሽምቅ ኃይሎችና በፌደራል ፖሊሶች ላይ ወታደራዊ የማጥቃት እርምጃ ወስዷል። በዚህም የማጥቃት እርምጃ አስራ ሶስት (13) የወያኔ ታጣቂ ኃይሎች ሙት፣ ዘጠኙ (9) ደግሞ ከፍተኛ የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸው ሲሆን የእጅ ቦምቦች፣ የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች ከነመስል ጥይቶቻቸውና ትጥቆቻቸው ጋር ተማርኳል።

ነገረ ኢትዮጵያ – የ‹‹ፍትህ አካላት›› ስብሰባ በአቶ በረከት ማስጠንቀቂያ ተጠናቀቀ

ከሁለት ሳምንት በፊት በአቶ በረከት ስምኦን የተከፈተውና 15 ቀን የፈጀው ባህርዳር ላይ የተደረገው የ‹‹ፍትህ አካላት›› ስብሰባ ትናንት መስከረም 14/2007 ዓ.ም በአቶ በረከት ስምኦን ማስጠንቀቂያ መጠናቀቁን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡
ስብሰባውን የዘጉት አቶ በረከት ስምኦን ‹‹ፖሊስ፣ አቀቤ ህግና ዳኛ ከአስፈጻሚው (ከካቢኔው) ጋር ተስማምቶና እጅና ጓንት ሆኖ መስራ አለበት፡፡ ይህ ነው ልማታዊ የፍትህ ስርዓት፡፡›› ማለታቸውን ምንጮች ገልጸዋል፡፡
በተቃራኒው ተሰብሳቢዎቹ ‹‹ከአስፈጻሚው አካል ጋር እጅና ጓንት ሆናችሁ ስሩ ማለት የፖለቲካ ጣልቃ ገብነት እንዲኖር መፍቀድ ነው፣ ሊሰበስበን ይገባ የነበረው የካቢኔ አካል ሳይሆን የራሳችን ተቋም የሆነው ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው፣ ስልጠናው በራሱ የዳኝነት ስርዓቱን፣ ተቋሙንና ግለሰባዊ መብታችንን የጣሰ ነው፡፡›› ሲሉ ቅሬታቸውን እንደገለጹ ታውቋል፡፡ በአንጻሩ አቶ በረከት ‹‹አሜሪካን ጨምሮ በየትኛውም አገር የፍትህ ስርዓት አስፈጻሚ አካሉ ጣልቃ ይገባል፣ ይህ የምታነሱት ሀሳብ አደናቃፊ ሀሳብ ነው፣ የተባላችሁትን መስራት አለባችሁ፣ ግዴታችሁም ነው›› ማለታቸውን ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡

Thursday, September 25, 2014

ለህወሃት የማስጠንቀቂያ ደወል!

አማራጩ “የተሃድሶ ዕርቅ” ብቻ ነው
bell
የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር ለህወሃት ሊቀመንበር በቀጥታ ወደ ዕርቅ ሊያመጣ የሚችል ደብዳቤ ላኩ፡፡ በደብዳቤው ለህወሃት ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ለትግራይ ተወላጆች በግልጽ ማስጠንቀቂያ የተሰጠ ሲሆን ህወሃት የፈጸመው ወንጀልም በተወሰነ መልኩ ቀርቧል፡፡ መግለጫው ጥፋትን ዘርዝሮ ወደ እውነተኛና ፍትሃዊ የተሃድሶ ዕርቅ ለመምጣት ነው፡፡ ሙሉቃሉ ከዚህ በታች ይነበባል፡፡

Wednesday, September 24, 2014

ESAT Special programme the Massacre in Ogaden | ESATTUBE

ESAT Special programme the Massacre in Ogaden | ESATTUBE

በጎደሬ ወረዳ የዘር ግጭት ተነሳ፤ መከላከያ ገብቷል

የዞንና የወረዳ አስተዳዳሪዎች ከነቤተሰቦቻቸው ተገደሉ

gode-rie

በጋምቤላ ዞን በጎደሬ ወረዳ ነጋዴዎችና ሰፋሪዎች ከአካባቢው ተወላጅ የመዠንገር ጎሳ አባላት ጋር ተጋጩ። በግጭቱ ከ17 ሰባት በላይ ሰዎች ተገድለዋል። በግጭቱ የመዠንገር ዞን አስተዳዳሪና የጎደሬ ወረዳ ዳኛ ከነቤተሰቦቻቸው የግጭቱ ሰለባ መሆናቸው ታውቋል። ግጭቱን ለማብረድ የመከላከያ ሠራዊት የገባ ሲሆን፣ የጋምቤላ ክልል ልዩ ኃይል ግጭቱን ለማብረድ በጉዞ ላይ እንዳለ በተሰጠ መመሪያ እንዲመለስ ተደርጓል

Tuesday, September 23, 2014

የኮብላዩ ሚኒስትር ወጎች

temesgen-desalegn
በዚህ ተጠየቅ ጨርፈን የምንመለከተው በኮሙኑዮኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ የነበረውና ዛሬ በስደት የሚገኘው የአቶ ኤርሚያስ ለገሰን “የመለስ ትሩፋቶች፣ባለቤት አልባ ከተማ” የተሰኘው መጽሐፍን ነው፡፡ የመድብሉ ጻሐፊ ኤርሚያስን በግል
አላውቀውም፤ ለመጀመሪያ ጊዜ በአካል ያየሁት አቶ በረከት ስምዖን እርሱን እና ሽመልስ ከማልን ምክትሎቹ አድርጐ በሚኒስቴር ዲኤታ ማዕረግ መሾሙን በግዮን ሆቴል ለጋዜጠኞች ይፋ ባደረገበት ዝግጅት ላይ ነው፡፡

የህወሓት ትውልድ ገዳይ ስውር መርዝ

አሁን እጅግ በላቀ የዕድገት ደረጃ ሆኖው የሚናያቸው የአለም አገራት መሰረታቸው እውቀት ነው::ያለ እውቀት ፈጠራና ምርምር÷ጥበብና ክህሎት÷ዕድገትና ልማት ሊኖሩ አይችሉም::
ትምህርት የእውቀት ቤት ነው:: እውቀት ካለ ደግሞ ምክንያትነት አለ:: ምክንያትነት ካለ ደግሞ ምርምርና ጥናት አለ::ምርምር ካለ ደግሞ መጠየቅ አለ:: መጠየቅ ካለ ደግሞ መከራከርና መወያየት አለ:: መከራከር ካለ ደግሞ የለውጥ መንገድ አለ:: የለውጥ መንገድ ካለ ደግሞ ዕድገት አለ!!!!
ህወሓት ገና በረኻ ደደቢት እያለች 1973 “የወደፊት የኔ ጠላት ሙሁሩ ክፍል ነው” ማለቷም “የኔ ጠላት ዕውቀት ነው” ከሚል ሐሳብ ጥልቅ የሆነ ግንኙነት አለው::በአሁኑ ዘመን ትምህርት ምላሷ እንጂ ተክለ ሰውነቷ(ቁመናዋ) የለም ማለት ይቻላል:: ይህ ማለት ደግሞ የዕውቀት ግንብ ፈርሷል ማለት ነው::ይህ ማለት ደግሞ የጥበብና የምርምር ቤት ተንዷል ማለት ነው::ይህ ማለትም ምክንያታዊ አስተሳሰብና ግንዛቤ ቀብሮ አገርን ያለ ጠያቂና ተጠያቂ በማስቀረት የለውጥ ድልድይ እንዳይሰራ ያደርጋል::አሁን እያየነው ያለነውም ይህ ነው::

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኤክስፐርቶች ኢትዮጵያ ፀረ ሽብርተኝነት አዋጁን ለሰብዓዊ መብት ጥሰት ትጠቀማለች ሲሉ ከሰሱ

-ተቃዋሚዎች ተገቢ ሪፖርት ብለውታል
United-Nations-01-300x220የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የሰብዓዊ መብት ሁሉን አቀፍ የአቻ ለአቻ ግምገማ የውሳኔ ሐሳቦችን ለመገምገም የተሰበሰበው የተመድ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ኤክስፐርቶች ቡድን መስከረም 8 ቀን 2008 .. በጀኔቭ ስዊዘርላንድ ባደረገው ስብሰባ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የፀረ ሽብረተኝነት አዋጁን ሐሳብን በነፃነት የመግለጽና የመደራጀት መብትን ለመጣስ መጠቀሙን እንዲያቆም አሳሰበ፡፡
ባለፈው ዓመት ኢትዮጵያ ያቀረበችውን ብሔራዊ የሰብዓዊ መብት አፈጻጸም ሪፖርትና የሰብዓዊ መብት ይዞታን በአገሪቱ ለማሻሻል የተወሰዱትን ሕጋዊና አስተዳደራዊ ዕርምጃዎች ተከትሎ፣ አባል አገሮች የተለያዩ የውሳኔ ሐሳቦችን መስጠታቸው ይታወሳል፡፡ ያደጉ አገሮች ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተው እንዲሻሻል ወይም እንዲሰረዝ የጠየቁት ደግሞ የፀረ ሽብርተኝነት አዋጁን ነው፡፡

Monday, September 22, 2014

የዓለም ባንክ ኢትዮጵያ ለብድር ዕዳ አደጋዎች የመጋለጥ ዕድሏ እየሰፋ ነው አለ


ሰሞኑን ለሦስት ቀናት ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩት የዓለም ባንክ ማኔጂንግ ዳይሬክተርና የኦፕሬሽን ዋና ኃላፊ ስሪ ሙሊያኒ ኢንድራዋቲ፣ እያደገ የመጣው የብድር ዕዳ መጠን በኢትዮጵያ ላይ አደጋዎችን ሊያስከትል እንደሚችል ገለጹ፡፡
ስሪ ሙሊያኒ ኢንድራዋቲኢንድራዋቲ ባለፈው ረቡዕ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት፣ ምንም እንኳን የአገሪቱ የብድር ዕዳ መጠን ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት አኳያ ያለው ድርሻ አነስተኛ ቢሆንም፣ የዕዳውን መጠን በግልጽነት ለማስተዳደር የሚችልና ግልጽነት የሰፈነበት አስተዳደር ማስፈን የመንግሥት ግዴታ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ አገሪቱ ያለባት ጠቅላላ የብድር መጠን 20 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል፡፡ ከዚህ ውስጥ 12 ቢሊዮን ዶላር ከውጭ ምንጮች የተገኙ ብድሮችን የሚሸፍን የዕዳ መጠን ነው፡፡ በዚህ መሠረት ከጠቅላላ አገር ውስጥ ምርት አኳያ የዕዳው ድርሻ 44 ከመቶ መድረሱን ይጠቁማል፡፡
ኢንድራዋቲ እንደሚገልጹት፣ ይህ አኃዝ ዝቅተኛ በሚባለው የዕዳ ደረጃ ላይ የሚገኝ ነው፡፡ ነገር ግን የመንግሥት የኢንቨስትመንት ወጪዎች እየተበራከቱ በመምጣታቸው ምክንያት የዕዳ መጠኑን በዚያው ልክ እያደገ በመሆኑ፣ የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን በሚመለከት ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝና ከሚመለከታቸው ሚኒስትሮች ጋር መነጋገራቸውን አስረድተዋል፡፡

ኢህአዴግ ከጠ/ሚኒስትሩ ህልፈት በኋላ ደንግጧል


ከኢትዮጵያ ቴሌኮም ይልቅ ህልሜን አመንኩት!
ባለፈው ሳምንት በህልሜ ያየሁት ነገር አስገራሚ ነው፡፡ በአብዛኛው በህልማችን የምናየው ነገር የግል ህይወታችን ላይ የሚያተኩር ይመስለኛል፡፡ መቼም ናላውን ከሚያዞረው የኑሮ ውድነት ሃሳብ ወጥቶ ስለአገሩ ባለ ሁለት ዲጂት የኢኮኖሚ ዕድገት በህልሙ የሚያይ ሰው ያለ አይመስለኝም፡፡ (ቢያይማ ከኑሮ ውድነት ይወጣ ነበር!) ስለ አገሪቱ የዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መጎልበት ወይም ስለ ስልጡን የፖለቲካ ባህል መዳበር ተኝቶ የሚያልም አለ ብዬ አልገምትም፡፡ (በህልም ዲሞክራሲ ማየት እንዴት ነው? ) በነገራችሁ ላይ ኢህአዴግ በህልሙ ያየውን ነገር ሁሉ እኛም ብናይለት (“ኮፒ ፔስት” ነው ታዲያ!) እንዴት ጮቤ እንደሚረግጥ አልነግራችሁም፡፡ በቃ ሃሳባችን ከሃሳቡ፣ህልማችን ከህልሙ ቢገጥምለት በእድሜው ላይ 40 ዓመት ይጨምር ነበር (ከ30-40 ዓመት በሥልጣን ላይ ለመቆየት ካሰበው ውጭ!) አንዳንዴ ሳስበው “እኔን ምሰሉ!” ማለት ምን ክፋት አለው እላለሁ፡፡

Sunday, September 21, 2014

አስደንጋጭና አሳፋሪ ምስጢር ሲገለጥ፡ Shocking!

በሴቭ አድና

ትላንት ሀይማኖተኛ፣ ፈሪሀ እግዚአብሄር የያዘና ጨዋ የነበረ ህዝብ እንዴት እንዲህ በሙስና፣ የንዋይ ፍቅርና በውሸት እንዲህ ረከሰ?
ባንድ ነገር መስማማት እንችላለን፡፡ የዛሬ አያድርገውና ህዝባችን ሙስናን፣ ስርቆትን፣ ውሸትን፣ ጭቆናን የሚፀየፍ፤ ተካፍሎ መብላትን እንጂ መስገብገብን የማይሆንለት፤ ክብሩን የጠበቀ፣ የሌላ መብትም የማይነካ ኩሩና በራስ መተማመን የተጎናፀና ከፍ ያለ የሞራል እሴቶች የነበሩት ነበር፣ ከአንድ ሁለት ዐስርት ዐመታት በፊት፡፡
አንዳንዶች ጥቂት አባባሎችን (ለምሳሌ “ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል” የሚለውን የአማርኛ ምሳሌ) እያነሱ “ባህላችን ሙስና ያበረታታል” ለማለት ዳርዳር ቢሉም ማለት ይህ ከእውነታ የራቀ ነው፡፡
1. አንደኛ እንዲህ ዐይነቶቹ የስልጣን መባለግን የሚያበረታቱ አባባሎችና አስተሳሰቦች ኢምንቶች ናቸው፤ ከእነዚህ በአስርና ሀያ እጠፍ የበዙ ይህ ዐይነቱ የስነ-ምግባር ዝቅጠት የሚኮንኑ በመቶና በሺህ የሚቆጠሩ ጠንካራ ምሳሌዎች አሉን፤
ደግሞም እንዲህ ዐይነት አባባሎች በአንድና ሁለት ቋንቋዎች ላይ እንጂ ሀገሪቱን አይወክሉም፡፡ ለምሳሌ በኦሮምኛ፣ በትግርኛና በበርካታ ሌሎች የሀገራችን ቋንቋዎች እምብዛም አይገኙም ወይም ጨርሰው የሉም፡፡ ይሀንን የሚያወግዝ ግን በገፍ አለ፡፡ ይሁን እንጂ ያሁኑ የስነምግባር ዝቅጠት በተለይም ሙስና ግን በሀገሪቱ ከጫፍ እስከጫፍ፣ በሁሉም ህዝቦች አለ፡፡

የኢህአዴግ አምባሳደር በስዊዲን ወየንሽት ታደሰ የእንቁላል ድብደባ በከፍተኛ ሁኔታ ደረሰባት።

አባይ ሚዲያ፡- በስዊዲን የሚገኙ ኢትዮጵያኖች ከዚህ በሆላ እንደድሮው በውጪ እየወጡ መዝናናት የለም በማለት አምባሳደሯን እንቁላል በመወርወር ከፍተኛ የሆነ ውርደት እንድተከናነብ አድርገዋል። አብረዋት የነበሩ የወያኔ ጠባቂዎችም ራሳቸውን ከድብድባው ለማምለጥ ሲሉ ጥለዋት ሄደዋል። የስዊድን ፖሊሶች በርካታ የፖሊስ መኪናዎችን በማምጣት ጸጥታውን ለመቆጣጠር የቻሉ ሲሆን ከረጅም እግታ በሆላ በፖሊሶች እርዳታ ከመኪናዋ ወጥታ ለመሄደ ችላለች።

እንቁላል አትጨርሱ ዛሬ የባንዳዎች እና የነነዋይ ውርደት በእንቁላል ቢጫ እናድረጋቸዋለን እና እሶ ላይ ብቻ አትጨርሱ፣ መኪናው የእንቁላል ጌጥ በዛበት የሚል አስቂኝ ክስተቶችም ነበሩበት።
በውጪ የሚገኙ ኢትዮጵያኖች በተጠናከረ መልኩ የወያኔን ባለስልጣናት በሄዱበት የማዋረድና እጃቸው ደም የተበከለ መሆኑን በተደጋጋሚ እየተነገራቸው ሲሆን በቅርቡ በተመሳሳይ ሬድዋን ሁሴን በዋሽንግተን ዲዲ የደረሰበት ውርደት ይታወሳል።
በአሁኑ ሰአት በርካታ የወያኔ ባለስልጣኖች ወደ ውጪ መጓዝን እንደማይመርጡ የደረሰን ሪፖርት ያመላክታል።
በስዊዲን የኢትዮጵያ አባሳደር ላይ የገማ አሳና እንቁላል እንዳይወረወርባቸው ሲከላከሉ የሚያሳይ ፎቶ
sewden

Wednesday, September 17, 2014

ኢትዮ ቴሌኮም ሙስሊም ሰራተኞችን አስተዳደሮችን የሚያሸማቅቅ ህገ ደንብ አወጣ።

የኢትዮ ቴሌኮም ስራተኞችና አስተዳደሮች ፂማቸውን እንዳያሳድጉ ተከለከለ!
እንደሚታወቀው የኢህአዴግ መንግስት ከወርሃ ሃምሌ 2003 ሃሮማያ ዩኒቨርስቲ ,ውስጥ ከነበረው አህባሽን በግዳጅ ከመጫን ሂደት ጀምሮ ህዝበ ሙስሊሙ በራሱ ተቋም ላይ የመረጣቸውን የመሳጅድ ኮሜቴዎችና ኢማሞችን በግዳጅ ከቦታቸው ላይ በማንሳት፣ የአህባሽን ሥልጠና አልወሰዳችሁም ተብለን ወደእስር ማጓዝ፣ ኢስላማዊ እውቀት መቅሰሚያዎች የሆኑትም መድረሳዎችንና የሂፍዝ ማዕከላትን መዝጋት፣ የዩኒቭርስቲ ተማሪ ወንድሞችን ፂማቹን ካልቆረጣችሁ፤ ሱሪያችሁን ካላሥረዘማችሁ አትማሩም በማለት ማሸማቀቅ እንዲሁም ሶላተችሁን አትስገዱ ማለት፣ሴት እህቶቻችን ኒቃብ ሂጃብ ጅልባብ እንዳይለብሱ መከልከል(የባህር ዳር ዩኒቭርስቲ ተማሪዎች ሶላትና ሂጃብ ተከልክለው በገፍ ማባረራቸው የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው) ፣ ሙስሥሊም ባለሥልጣናትን ከቦታቸው ማንሳት ወይንም ተፅዕኖ በማይፈጥሩበት ቦታ ካለ ፍላጎታቸው ማስሥቀመጥ፣ በትልልቅ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ተቀጥረው የሚሰሩ ,ሙሥሊም ወንድሞች ሱና እንዳይተገብሩ ማሸማቀቅና መከልከል፣ ሰላማዊ መብት ጠያቂዎችን በገፍ ማሰርና መግደል(የሃምሌ 11ዱ ጥቁር ሽብር የመንግሥትን አምባገነንነት በግልፅ ያየንበት ነው) እንዲሁም የመሳሰሉትን ይህ ነው የማይባል አስከፊ እኩይ ተግባራትን ካለአንዳች ርህራሄና እዝነት ከአንድ ሃገርን ይመራል ከሚባል መንግስት የማይጠበቅ የግፍ መዐት እንዳወረደብን ይታወቃል።

Tuesday, September 16, 2014

እነ አባዱላ ፓስፖርታቸውን ተቀምተዋል- ኦህዴድና ብአዴን ይጠይቃሉ፤ ህወሓት ይመልሳል

negereነገረ ኢትዮጵያ

ከአመታት በፊት የገዥው ፓርቲ አባል ሳይሆን በመንግስት ስራ ላይ ተሰማርቶ ይሰራ ነበር፡፡ 1997 ዓ.ም በኋላ ግን በዚህ አቋሙ አልቀጠለም፡፡ ‹‹አንዴ ቅንጅት ሌላ ጊዜ ደግሞ ኦነግ እያሉ ስም ሲለጥፉብኝ ‹ከዚህ ሁሉ!› ብየ ኦህዴድን ተቀላቀልኩ›› ይላል ካድሬው ለነገረ ኢትዮጵያ፡፡ ከዚህ በኋላ ባሉት ጊዜያት ደመወዝና እድገት በእጥፍ ተጨምሮለታል፡፡ የትምህርት እድል ተሰጥቶታል፡፡ በተቃራኒው ደግሞ ኦህዴድም ሆነ ኢህአዴግ ህዝብ ላይ የሚፈጽሙትን በደል በቅርብ ርቀት ተገኝቶ ተከታትሏል፡፡
ካድሬው እንደሚለው ከእነ አባዱላና መሰል ፖለቲከኞች ውጭ የኦህዴድ ካድሬዎች በፓርቲያቸው እምነት የላቸውም፣ በህወሓት በደል በእጅጉ ተማርረዋል፡፡ የ‹‹ብአዴኖችም ከእኛ የሚለይ ነገር የለውም፡፡ ተመሳሳይ ነው፡፡›› ይላል ካድሬው፡፡
በበርካታ ጉዳዮች ‹‹ፓርቲዬ›› ከሚለው ኢህአዴግ እንደሚለይ ቢገልጽም በአንድ ጉዳይ ግን ይስማማማል፡፡ ‹‹ጥያቄ የሚያቀርብ ካድሬ አንድም ኦነግ አሊያም የድሮው ቅንጅት አካል የነበረ ፓርቲ ወይንም ትምክተኛ ተብሎ ስም ይሰጠዋል፡፡ ኦነግ ወይንም ‹‹ቅንጅትነት/ትምክተኝነት›› ጥያቄ ማንሳት ከሆነ የኦህዴድ ካድሬዎች ሲገለጡ ኦነጎች ናቸው፡፡ ብአዴኖቹ ደግሞ እንደዛው ቅንጅት/ትምክተኛ ናቸው ማለት ነው››፡፡ በዚህ ጉዳይ ካድሬው የድሮው ጠቅላይ ሚኒስትር ‹‹ኦህዴድ ሲገለጥ ኦነግ ነው!›› በሚለው ይስማማል፡፡

Monday, September 15, 2014

የኢትዮጵያ ህዝብ ፍርድህ ምንድነው?

አኝዋክ የፍትሕ (ጀስቲስ) ም/ቤት ኦሞት ኦባንግን ለፍርድ ያቀርባል!!

Wanted omot obang olum


ከአኝዋክ ጀስቲስ ካውንስል የተሰጠ መግለጫ  
Anuak-Justice-Councilየህወሃት ፍጹም ታማኝ ነበር። በተለያዩ ሃላፊነቶች በህጻናት፣ በወንድሞቹ፣ በእህቶቹ፣ በእናቶቹ፣ በአባቶቹ አጠቃላይ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ በሰራው ወንጀል በህግ ይፈለጋል፣ በህግ የሚፈልጉት ኢትዮጵያዊያን ብቻ ሳይሆኑ ዓለም አቀፍ የፍትህና የመብት ተሟጋቾች ናቸው። ህወሃትን ክዶ በስደት ከሚገኝበት አገር እጁን እንዲሰጥ ጥሪ ቀርቦለታል። ይህ “ሰው” በጋምቤላ ክልል የፖሊስና የጸጥታ ሃላፊ የነበረ። የደህንነት አመራር ነበረ። ክልሉን በፕሬዚዳንትነት ለዓመታት የመራ፣ በጅምላ ለተጨፈጨፉት የአኝዋክ ንጹሃን ደም ቀዳሚ ተጠያቂ ነው – ኦሞት ኦባንግ !!

በጎደሬ ወረዳ የዘር ግጭት ተነሳ፤ መከላከያ ገብቷል

የዞንና የወረዳ አስተዳዳሪዎች ከነቤተሰቦቻቸው ተገደሉ

goderie


በጋምቤላ ዞን በጎደሬ ወረዳ ነጋዴዎችና ሰፋሪዎች ከአካባቢው ተወላጅ የመዠንገር ጎሳ አባላት ጋር ተጋጩ። በግጭቱ ከ17 ሰባት በላይ ሰዎች ተገድለዋል። በግጭቱ የመዠንገር ዞን አስተዳዳሪና የጎደሬ ወረዳ ዳኛ ከነቤተሰቦቻቸው የግጭቱ ሰለባ መሆናቸው ታውቋል። ግጭቱን ለማብረድ የመከላከያ ሠራዊት የገባ ሲሆን፣ የጋምቤላ ክልል ልዩ ኃይል ግጭቱን ለማብረድ በጉዞ ላይ እንዳለ በተሰጠ መመሪያ እንዲመለስ ተደርጓል

በህወሀት እና በአጋር ፓርቲዎቹ መካከል አለመተማመን እየተፈጠረ ነው


1231607_10151872226524743_661233572_nእስከ ጳጉሜ 4 2006 ዓ.ም ድረስ የተካሄደው የኢህአዴግ ምክር ቤት ስብሰባ በርካታ እንግዳ ክስተቶችን ይዞ የተገኘ እንደነበር ውስጥ አዋቂ ምንጮች ገልጸዋል:: በአንድ ወር ውስጥ ብቻ ለሶስተኛ ጊዜ በተካሄደው በዚሁ የድርጅቱ ስብሰባ ብአዴን እና ኦህዴድ ድርጅታዊ ተልእኮዎችን የማስፈጸም ውስንነት እንደታየባቸው አልፎ ተርፎም የኦሮሚያ እና የአማራ ክልሎች በተለይም ከኦሮሚያ ክልል ወለጋ ኢሊባቡር እና አምቦ የኦነግ ምሽግ የሆኑ ሲሆን በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር በአርበኞች ግንባር ቁጥጥር ስር ለመዋል እንደተቃረበ፣ በአመራሩ እንዝህላልነት ህዝቡ ከኢህአዴግ እየራቀ እና ለድርጅቱ ጀርባውን እንደሰጠ ከመድረክ ተገልጽዋል:: በዚህ ጉዳይ ላይ የተናገሩት የብአዴን እና የኦህዴድ አመራሮች የተቀሰው አካባቢ ገብቶ ለመስራት ፍቃደኛ የሚሆኑ አባላት እጥረት እንዳለ፣ ህዝቡ በተደጋጋሚ በአካባቢው አመራሮች ላይ ዛቻ እና ማስፈራሪያ እንደሚያደርስ ገልጸው ይህም ሊሆን የቻለው በአካባቢው ያለው የሀይል እጥረት እንደሆነ ገልጸዋል::

Sunday, September 14, 2014

የግንቦት 7 ላንቺ ነው ኢትዮጵያ የተሰኘው ህዝባዊ ስብሰባ በሲውዘርላንድ እየተካሄደ ነው።

zemene

ታጋይ ዘመነ ካሴ እና ታጋይ ግርማቸው ንግግር በማድረግ ላይ ናቸው

በ አሁን ሰአት ታጋይ ዘመነ ካሴ በስካይፒ ከ ኤርትራ በቀጥታ ሰለ ህዝባዊ ሃይሉ ማብራሪያ በመስጠት ላይ ነው ይህው አለው እንደምታዩኝ ምንም አልሆንኩም ብልዋል በመቀጠል በሲውዘርላድ ሉዘርን ከተማ ነዋሪ የነበረው አርበኛ ግርማቸው የ አውሮፓ ኑሮውን በመተው ህዝባዊ ሃይሉን መቀላቀሉ የሚታወስ ነው ይህ አርበኛ ታጋይ ግርማቸው ከዘመነ ካሴ በሃላ ይናገራል
በሴወዝርላንድ በራካታ የሆነ ኢትዮጵያዊ በአሁኑ ሳት የግንቦት 7 ላንች ነው በተሰኘው ህዝባዊ ስብሰባ ላይ ተገኝቶል። ግንቦት 7 አሁንም የሚያደርገውን እልህ አስጨራሽ ትግል በድል ሳያጠናቅቅ ለአንዳፍታም አይተኛም። የተጀመረው ትግል ይቀጥላል። ኢትዮጵያም አሸናፊ ሁና ትቀጥላለች።  ታዳሚው በከፍተኛ ስሜት ስብሰባውን እየተከታተለ ነው። የክብር እንግዳው ተናጋሪ ታጋይ ዘመነ እና ታጋይ ግርማቸው በስካይፒ ከትግል ሜዳ አካባቢ ሆነው ንግግር በማድረግ ላይ ናቸው። ዝርዝሩን ይዘን እንመለስበታለን።
ታጋይ ዘመነ ለታዳሚው ንግግር በማድረግ ላይ እያለ።
# አባይ ሚዲያ live

Saturday, September 13, 2014

የ2007 ዓ/ምን አዲስ አመት በማስመልከት ከኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር የተሰጠ ድርጅታዊ መግለጫ


url
አምባገነኖች የጭቆና ቀንበር ለመላቀቅ ከግማሽ ምዕተ-ዓመት በላይ ለነፃነቱና ለመብቱ ሲታገል ለኖረውና የትግሉ ባለቤት ለሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ ፣
- በአርበኝነት ትግል በዱር ገደሉ ህይወታችሁን፣ ጉልበታችሁን፣ ጊዜያችሁንና ዕውቀታችሁን ሳትሰስቱ ለተቀደሰው ዓላማ በማበርከት ላይ ለምትገኙ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሠራዊት፣

Thursday, September 11, 2014

ህወሃት “በህወሃት ወዳጆች” ለእርቅ እንዲነሳሳ እየተሸመገለ ነው!

ራስ መንገሻ ስዩም ጉልህ ሚና ይዘዋል

tplf recon

በኢትዮጵያ ከቀን ወደ ቀን እየከረረ የሚሄደው የጥላቻ ደረጃ ያሳሰባቸው “የህወሃት ወዳጆች” ህወሃት ለእርቅ እንዲነሳሳ የማግባባት ስራ እየሰሩ መሆናቸው ተሰማ። የአቶ መለስና “የህወሃት ወዳጅ” ወይም ቅርብ ናቸው የሚባሉት ራስ መንገሻ ስዩም ጉልህ ሚና ይዘዋል።

2007 ወሳኝ የትግል ዓመት!!!

2007 ወሳኝ የትግል ዓመት!!!

Untitled g7
ሁለት ሺህ ስድስት ዓመተ ምህረት ለኛ ለኢትዮጵያዊያን በአብዛኛው በመጥፎ የሚታወስ ዓመት ነው። 2006፣ በመካከለኛው ምስራቅም ሆነ በአፍሪቃ በስደት ላይ የሚገኙ ወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው ስቃይ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰበት ዓመት ነበር። 2006፣ ቀደም ባሉ ዓመታት አገራቸዉን ለቅቀዉ የተሰደዱ ሳይደላቸው በርካታ አዳዲስ ስደኞች ከአገር ወጥተው በበረሃዎችን ቀልጠው፤ በባህር ሰጥመው ያለቁበት አሳዛኝ ዓመት ነው። 2006፣ ጥንቃቄ በተሞላበትና በተቆጠበ መንገድም ቢሆን የተቃውሞ ድምጽ ያሰሙ ወገኖቻችን ወደ እስር ቤቶች የተጋዙበት ዓመት ነው። 2006፣ በአምቦ፣ በለቀምት፣ በጅማ በሀረር በርካታ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የተገደሉበት፤ በአስር ሺዎች የሚገመቱት ደግሞ የታሰሩበት ዓመት ነው። 2006፣ በአፋር፣ በኦሮሚያ፣ በደቡብ፣ በቤንሻንጉል፣ በጋምቤላ፣ በአዲስ አበባና አካባቢው በ100 ሺዎች የሚገመት ኢትዮጵያዊ የተፈናቀለበት ዓመት ነው። 2006 ቁጥራችው ቀላል ያልሆኑ የነፃነት ታጋዮች ከጎረቤት አገራት ታፍነው ወደ እስር ቤቶች የተጋዙበት ዓመት ነው። 2006 የንቅናቄዓችን ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በጉዞ ላይ እያለ በትራንዚት አውሮፕላን ለመቀየር ባረፈበት በየመን ዋና ከተማ ሰንዓ በየመን መንግሥት ወንበዴዎች ታፍኖ ለሸሪካቸው ህወሓት በህገወጥ መንገድ አስተላልፈው ለስቃይ እንዲዳረግ የተደረገበት ዓመት ነው። በእነዚህ ሁሉ ምክንያቶች ነው 2006 “ጥቁር ዓመት” የሚል ስያሜ ያገኘው።

አዲሱን ዓመት በማስመልከት ከነጻነት ታጋዮች ጋር በቂሊንጦ እስር ቤት

አዲሱን ዓመት በማስመልከት ከነጻነት ታጋዮች ጋር በቂሊንጦ እስር ቤት

kiliminto jail
ባለፈው ሳምንት በማህበራዊ ሚዲያው ‹‹ጥቁር ሳምንት›› (black week) በሚል ለአምስት ቀናት ዘመቻ (campaign) መካሄዱ ይታወሳል፡፡ በዚያ የጥቁር ሳምንት ዘመቻ ወቅት በመጨረሻው ቀን አስተባባሪዎቹ አዲስ አመትን በማስመልከት ‹አዲስ አመት በዓልን ከነጻነት ታጋዮች ጋር› በሚል የታሰሩ የነጻነት ታጋዮች እንዲጠየቁ ጥሪ መተላለፉ አይዘነጋም፡፡ በመሆኑም የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ ዝግጅት ክፍል ጳጉሜ 5 ቀን 2006 ዓ.ም በቂሊንጦ የሚገኙ የዞን 9 የጡመራ ቡድን አባላትንና የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን በመጠየቅ የዘመቻውን አካል አከናውነዋል፡፡

ሚሊየነሩ ጄ/ል (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

ሚሊየነሩ ጄ/ል (ከኢየሩሳሌም አርአያ)
የሕወሐት ታጋይ ጄ/ል ዮሃንስ ገ/መስቀል ቦሌ ቴሌ መድሃኒያለም ባለ6 ፎቅ ህንፃ እንዳስገነቡ የቅርብ ምንጮች አጋለጡ።
ሚሊየነሩ ጄ/ል (ከኢየሩሳሌም አርአያ)
Sep11,2014

የሕወሐት ታጋይ ጄ/ል ዮሃንስ ገ/መስቀል ቦሌ ቴሌ መድሃኒያለም ባለ6 ፎቅ ህንፃ እንዳስገነቡ የቅርብ ምንጮች አጋለጡ።

ከ95ሚሊዮን ብር በላይ በሚደርስ ወጪ እንደተገነባ የተነገረለት ይኸው ባለ6 ፎቅ ዘመናዊ ህንፃ ለተለያዩ የግልና የመንግስት ባንኮች፣ ኢንሹራንስ ድርጅቶች፣ ንግድ ቤቶችና የተለያዩ ድርጅት ቢሮዎች እንደተከራየ የጠቆሙት ምንጮቹ በወር ከ2.1 ሚሊዮን ብር የሚገመት ኪራይ ጄኔራሉ እንደሚሰበስቡ አስታውቀዋል።

ሌ/ጄ ዮሃንስ በግላቸው ባለ6 ፎቅ ዘመናዊ ህንፃ በከፍተኛ ወጪ በማስገንባትና ከፍተኛ የኪራይ ሂሳብ በየወሩ በመሰብሰብ ከሌሎቹ በቢዝነስ ከተሰማሩ የሕወሐት/ኢህአዴግ ጄኔራል መኮንኖች የተለየ እንደሚያደርጋቸው ምንጮቹ አመልክተዋል። በአገር መከላከያ ሚኒስቴር የመረጃ ዋና መምሪያ ሃላፊ ሆነው ለረጅም አመታት ሲሰሩ የቆዩት የህወሐቱ ጄኔራል ዮሃንስ ገ/መስቀል ከ1995ዓ.ም ጀምሮ ከጄ/ል ሳሞራ የኑስ ጋር የከረረ ቅራኔ ውስጥ ገብተው እንደቆዩና በሁለቱ የህወሀት ጄኔራሎች መካከል የተፈጠረው ቅራኔ እየተባባሰ ሄዶ ጄ/ል ዮሃንስ ከሃላፊነት እንዲነሱ መደረጉን ያስታወሱት ምንጮቹ የሁለቱ ቅራኔ ሙስናን መሰረት ያደረገ እንደነበረ አስረድተዋል። (በወቅቱ ስለግጭታቸውና መለስ ዜናዊ ዘንድ ቀርበው ስለተነጋገሩት በኢትኦጵ ጋዜጣ መረጃው ይፋ ተደርጐዋል)  ጄ/ል ዮሃንስ ከመከላከያ ሃላፊነታቸው እንዲነሱ የተደረጉት በጄ/ል ሳሞራ መሆኑን ያስታወሱት ምንጮቹ በወቅቱ “ጡረታ” በሚል እንደተነሱና ሲነሱም በሜ/ጄኔራል ማእረግ እንደነበሩ አስታውቀዋል።

በሙስና ባገኙት በመቶ ሚሊዮን የሚገመት ገንዘብ ሕንፃ ወደማስገንባት የግል ቢዝነስ የተሰማሩት ጄ/ል ዮሃንስ ከአራት አመት በኋላ በመከላከያ የሌተና ጄኔራልነት ማእረግ ባሳለፍነው ሰኔ ወር ተሰጥቷቸው በደቡብ ሱዳን የሚሰማራውን የተመድ ሰላም አስከባሪ ሰራዊት በጦር አዛዥነት እንዲመሩ መመደባቸው አስገራሚ ነው ያሉት ምንጮቹ ምክንያቱም ጡረታ ተብለው የተሰናበቱት ዮሃንስ የሌተና ጄኔራል ማእረግ እድገት ተሰጥቷቸው መመለሳቸው በመከላከያ ታሪክ የመጀመሪያው ሊያደርጋቸው ስለሚችል ግርምት ሊፈጥር ችሏል ብለዋል። ዮሃንስ የአገር መከላከያ ሚ/ር የሌ/ጄኔራል ማእረግ እንዲሰጣቸውና በተመድ እንዲመደቡ የተደረገው በአሜሪካ ትእዛዝ መሆኑን ምንጮቹ አመልክተዋል። በቦሌ ለንደን ካፌ ፊት ለፊት ዘመናዊ መኖሪያ ካስገነቡት ጄኔራሎች አንዱ ናቸው።

(በፎቶው ጄ/ል ዮሃንስ ገ/መስቀል)ከ95ሚሊዮን ብር በላይ በሚደርስ ወጪ እንደተገነባ የተነገረለት ይኸው ባለ6 ፎቅ ዘመናዊ ህንፃ ለተለያዩ የግልና የመንግስት ባንኮች፣ ኢንሹራንስ ድርጅቶች፣ ንግድ ቤቶችና የተለያዩ ድርጅት ቢሮዎች እንደተከራየ የጠቆሙት ምንጮቹ በወር ከ2.1 ሚሊዮን ብር የሚገመት ኪራይ ጄኔራሉ እንደሚሰበስቡ አስታውቀዋል።
ሌ/ጄ ዮሃንስ በግላቸው ባለ6 ፎቅ ዘመናዊ ህንፃ በከፍተኛ ወጪ በማስገንባትና ከፍተኛ የኪራይ ሂሳብ በየወሩ በመሰብሰብ ከሌሎቹ በቢዝነስ ከተሰማሩ የሕወሐት/ኢህአዴግ ጄኔራል መኮንኖች የተለየ እንደሚያደርጋቸው ምንጮቹ አመልክተዋል። በአገር መከላከያ ሚኒስቴር የመረጃ ዋና መምሪያ ሃላፊ ሆነው ለረጅም አመታት ሲሰሩ የቆዩት የህወሐቱ ጄኔራል ዮሃንስ ገ/መስቀል ከ1995ዓ.ም ጀምሮ ከጄ/ል ሳሞራ የኑስ ጋር የከረረ ቅራኔ ውስጥ ገብተው እንደቆዩና በሁለቱ የህወሀት ጄኔራሎች መካከል የተፈጠረው ቅራኔ እየተባባሰ ሄዶ ጄ/ል ዮሃንስ ከሃላፊነት እንዲነሱ መደረጉን ያስታወሱት ምንጮቹ የሁለቱ ቅራኔ ሙስናን መሰረት ያደረገ እንደነበረ አስረድተዋል። (በወቅቱ ስለግጭታቸውና መለስ ዜናዊ ዘንድ ቀርበው ስለተነጋገሩት በኢትኦጵ ጋዜጣ መረጃው ይፋ ተደርጐዋል) ጄ/ል ዮሃንስ ከመከላከያ ሃላፊነታቸው እንዲነሱ የተደረጉት በጄ/ል ሳሞራ መሆኑን ያስታወሱት ምንጮቹ በወቅቱ “ጡረታ” በሚል እንደተነሱና ሲነሱም በሜ/ጄኔራል ማእረግ እንደነበሩ አስታውቀዋል።

Wednesday, September 10, 2014

የዌብሳይትን ትራፊክ በአዲስ አመት ለማጨናነቅ እና ኪስን ለመሙላት ትግሉን መጉዳት ተገቢ አይመስለኝም

eliyas
ኢትዮ ሪቪው በጉጉት ስንጠባበቅ የነበረውን “የፖሊስ ምርመራ ይፋ አደረገልን” ። በይሆን ይሆናል ማስረጃ የተደገፈው ይሄው “ሪፖርት” ታላቅ ሆኖ ሰሞኑን ይነበብ ዘንድ እና ወያኔን እንድንታገለውም ይላል። ሁሌም ታጋዮች በጠላት እጅ ሲወድቁ አደርባዮች ትግሉ እየሞተ ይመስላቸውና ከወዲሁ ካባ መቀየር በኢትዮጵያኖች ዘንድ የተለመደ ቢሆንም ይሄኛው ደግሞ የወረደ ነው።

በወያኔ ስር የሚገኘው የመከላከያ ሰራዊት፣ የወያኔ አገልጋይ ኢሕአዴግ፣የአፋኞችና የነፍሰ ገዳዮች ምሽግ- የወያኔ ደህንነት

ነዓምን ዘለቀ,        

ዋና ጸሃፊያችንና  የትግል ዳችን  አንዳርጋቸው ጽጌ
g7-logo
የንቅናቄአችን ዋና ጸሃፊና የትግል ጓዳችን  አንዳርጋቸው ጽጌ  በየመን ትብብር በፋሽስታዊ ወያኔ አፋኞች  እጅ መውደቅ ያስቆጣው የኢትዮጵያ ሕዝብ ባሳየው ወገናዊነት ልባችን ተነክቷል። የአንዳርጋቸው መታሰር ይቆጨናል፤ እየደረሰበት ያለው ስቃይ ያንገበግበናል፤ የሱን አይነት ብርቱ፣ ቆራጥ፣ አስተዋይና ብቃት ያለው ታጋይ ትግሉ ማጣቱ ይጎዳናል:: አንዳርጋቸው በሳል የፖለቲካ ሰውና ቆራጥ የተግባር ታጋይ ብቻ አይደለም። በግል ለማታውቁት በበርካታ የእውቀት ዘርፎች በጥልቀት ያነበበ፤ ፍልስፍና፣ ሊትሬቸር፣ ሲኒማ የሚወድና ህሊናው በዕውቀት በከፍተኛ ደረጃ የበለፀገ ነው። የሰው ልጅ መከራ፣ በደልና ስቃይ እስከ አጥንቱ ይሰማዋል። ዱባይ ላይ ከአመት በፊት ስላገኛት ኢትዮያዊት የነገረኝ ሲቃ እየተናነቀው ነበር።ልጅቷ ሲያገኛት ያለማቋረጥ ታለቅሳለች፤ ምን እንደሆነች ቢጠይቃት ለመናገር ባትፈቅድም አጥበቆ ሲይዛት እንደተናገረችው፤ ተቀጥራ በምትሰራበት  የቤቱ ባለቤት ሽማግሌ አረብና አራት ወንድ ልጆቹ በየገዜው ተራ በተራ ደፍረዋታል። የሚያስነባት ይህ ነበር። አንዳርጋቸው “የኢትዮጵያውያን መከራና ውርደት መቼ ነው የሚያበቃው” በሚል ነበር ሲቃ እየተናነቀው ያጫወተኝ።

Tuesday, September 9, 2014

የቀድሞው የጋምቤላ መሪ በክልሉ ለደረሰው ጭፍጨፋ የህወሃት ባለስልጣናትን ተጠያቂ አደረጉ

የቀድሞው የጋምቤላ መሪ በክልሉ ለደረሰው ጭፍጨፋ የህወሃት ባለስልጣናትን ተጠያቂ አደረጉ

666Umod_Ubong
ጳጉሜን ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አቶ ኦሞድ ኦባንግ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ 400
ሰዎች የተገደሉበት የጋምቤላወኢ ጭፍጨፋ እንዴት እንደተከናወነ በዝርዝር አስረድተዋል።
የህወሃት ከፍተኛ ባለስልጣን የሆኑት አቶ አባይ ጸሃየ ግድያውን በተመለከተ ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል።
በክልሉ ስለሚፈጸመው ሙስናና የመሬት ወረራ የቀድሞው ባለስልጣን በዝርዝር ገልጸዋል። አቶ አዲሱ ለገሰ
በቅርቡ ባወጡት ጽሁፍ በጋምቤላ ለኢህአዴግ ታማኝ የሆነ ሰው ለማግኘት እንዳልተቻለ ገልጸው ነበር።
አቶ ኦሞድ ውጭ አገርከወጡ በሁዋላ ጋዜጣዊ መግለጫ ሲሰጡ ይህ የመጀመሪያ ጊዜያቸው ነው። የቀድሞው ባለስልጣን ከክልል ፕሬዚዳንትነታቸው ከወረዱ በሁዋላ የፌደራል ጉዳዮች ም/ል ሚኒስትር ሆነው ሰርተዋል።

የለውጡ አካል መሆኛው ግዜው አሁን ነው

የለውጡ አካል መሆኛው ግዜው አሁን ነው

እኔም አንዳርጋቸው ነኝ የሚል ድምፅ ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ እያሰተጋባ ነው። ይሄን ድምፅ የሚያቆመው አንዳችም ምድራዊ ኃይል አልተገኘም። ኢትዮጵያዊ ባለበት ሥፍራ ሁሉ ይሄ ድምፅ ከፍ ብሎ እየተሰማ ነው። ይህንንም ተከትሎ “ላንቺ ነው ኢትዮጵያ፤ ላንቺ ነው ኢትዮጵያ” የሚለው መዝሙር በኢትዮጵያ ተራሮች እናት ላይ እየተዘመረ ነው። ፍትህ ተዋርዳለች፤እኩልነት ጠፍቷል፤ ነፃነት የለም ያሉ ምርጥ ኢትዮጵያዊያን ሳያቅማሙ አያቶቻቸው በተመላለሱበት ተራሮች ላይ ተሠማርተዋል። ሞትንም ንቀው ጋሻ አንስተዋል፤ ሰይፋቸውንም መዘዋል። ለፍትህ፤ ለዕኩልነት እና ለነፃነት የተመዘዘው ሰይፍ ከእንግዲህ ወደ ሰገባው እንደማይመለስ ህወሃቶች እንዲያውቁት እንፈልጋለን።
በኢትዮጵያችን ፍትህ ከጠፋ ብዙ ዘመን ሁኖታል። ከሁሉም ዘመን የህወሃቶች ዘመን ግን የተለየ ነው። ህወሃቶች ህግን ዜጎችን የማጥቂያ መሣሪያ አድርገው መጠቀማቸው ከሌሎች እንዲለዩ ያደርጋቸዋል። እነዚህ ቡድኖች ሥፍር ቁጥር የሌላቸው ቂም መወጣጪያ ህጎችን አውጥተዋል። እንዲህ በማድርጋቸውም ሠላም እናገኛለን ብለው ያስባሉ። የህወሃቶች አስተሳሰብ ደካማና እርባና ቢስ መሆኑን ከሚያሳዩ ተግባሮቻቸው መካከል አንዱ ይሄው በፍትህ ሳይሆን በህግ ብዛት ሠላም እናገኛለን ብለው ተስፋ ማድረጋቸው ነው። የህግ ብዛት ሠላምን አያስገኝም፤ ፍትህንም ማስፈን አይችልም። እንዲያውም ህግ በበዛ ቁጥር ፍትህ እየጎደለች እንደምትሄድ የህወሃቶች ድርጊት ደህና ምስክር ነው። እነርሱ ዜጎችን ለመበቀያ ብለው የሚያወጧቸው ጥቃቅን ህጎች እነርሱ “ህገ መንግስት” ብለው የሚጠሩትን የሚንዱ እና ፍትህን ዋጋ የሚያሳጡ ሁነው እያየናቸው ነው። የፀረ ሽብር ህጉ በህገ መንግስቱ የተቀመጠውን የዜጎችን የመናገር የመደራጀትና በሰላማዊ መንገድ የመንግስትን እኩይ ተግባራት የመቃወምን መብት የገፈፈ ነው።

Sunday, September 7, 2014

የዓመቱ አነጋጋሪና አወዛጋቢ ክስተቶች

በዓመቱ መጀመሪያ በመስከረም ወር 2006 ዓ.ም ለ12 ዓመታት የአገሪቱ ፕሬዚዳንት በመሆን ያገለገሉት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ፤ ከስልጣናቸው የወረዱ ሲሆን በቦታቸውም ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ ተተክተዋል፡፡ በአምባሳደርነት ዘመናቸው የውጭ አገር ኢንቨስተሮችን ወደ ኢትዮጵያ በማምጣትና አገር ውስጥ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ በማግባባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸው የሚነገርላቸው ዶ/ር ሙላቱ፤ የፕሬዚዳንትነት ስልጣናቸውን ከተረከቡ በኋላም ሥራቸው በቤተመንግስት አካባቢ የተገደበ አልሆነም፡፡ በተለያዩ አገራት እየዞሩ የውጭ ኢንቨስተሮችን የማግባባት ሥራቸውን ቀጥለውበታል፡፡

Thursday, September 4, 2014

ወጣቱን ለማደንቆር ያለመው ስልጠና ህወሓትን ለመቅበሪያነት ይዋል!

ወጣቱን ለማደንቆር ያለመው ስልጠና ህወሓትን ለመቅበሪያነት ይዋል!

Untitled g7
ህወሓት፣ ከሶስት መቶ ሺህ በላይ የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን በየቦታው ሰብስቦ እያሰለጠነ ነው። ይህ ሲያልቅ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ስልጠና ይቀጥላል ተብሏል። በድምሩ ወደ ግማሽ ሚሊዮን የሚጠጋ ወጣት አንድ አይነት ሰነድ አንብቦ ለ2007 ትምህርት ይዘጋጃል ማለት ነው። ስልጠናው ወደ መንግሥት ሠራተኞችና ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎችም ይስፋፋል ተብሎ ይገመታል።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በዚህ ሥልጠና ላይ ያለውን እይታ በነሐሴ 16 ቀን 2006 ዓም ቁጥር 328 ርዕሰ አንቀጹ መግለጹ ይታወሳል። ግንቦት 7 የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በወያኔ ስልጠናዎች ላይ ተቃውሞ ለማሰማት መድፈራቸው ወጣቱ ለለውጥ የተዘጋጀ እንደሆነ አመላካች መሆኑን ተገንዝቦ ይህ የለውጥ ፍላጎት በድርጅት እንዲታገዝ ወጣቱ በትናንሽ ሕዋሶች ራሱን እንዲያደራጅ መክሯል። ሆኖም ግን ህወሓት ለስልጠናው የሰጠው ትኩረት ቀድሞ ከታሰበው በላይ በመሆኑ ንቅናቄዓችን በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ላይ እንደገና ሊመለስበት ወስኗል።
ህወሓት፣ ይህንን ያህል መጠነ ሰፊ ስልጠና ማድረግ ለምን አስፈለገው? የዲሞክራሲ ኃይሎችስ ይህንን ስልጠና እንዴት ለራሳቸው ጥቅም ሊያውሉት ይችላሉ?
ህወሓት ይህንን ትርጉም የለሽ ስልጠና በአሁኑ ሰዓት ለመስጠት የፈለገበትን በርካታ ምክንያቶች ማቅረብ ቢቻልም የሚከተሉት ሁለቱ ግን ዋነኛዎቹ ናቸው ብለን እናምናለን።

Wednesday, September 3, 2014

ግንቦት 7 ንቅንቄ ቅዳሜ ኦገስት 30, እሁድ ኦገስት 31, እና ሰኞ ሴፕቴምበር 1, 2014 በመላው አለም ያደረጋቸው ህዝባዊ ስብሰባዎች ማሳካቱን ገልጿል።

ግንቦት 7 ንቅንቄ ቅዳሜ ኦገስት 30, እሁድ ኦገስት 31, እና ሰኞ ሴፕቴምበር 1, 2014 በመላው አለም ያደረጋቸው ህዝባዊ ስብሰባዎች ማሳካቱን ገልጿል።
በአለም 26 ከተሞችና በኖርዝ አሜሪካ በሚገኙ 6 ታላላቅ ከተሞች የተደረጉት ውይይቶች በርካታ ኢትዮጵያኖች በቦታው በመገኘት ድጋፋቸውን ያሳዩበትና የገለጹበት ሲሆን፣ ዝግጅቱ በአትላንታ፣ ቦስተን፣ቴክሳስ፣ በዋሽንግተን ዲሲ እንዲሁም በካናዳ ቶሮንቶና ካልጋሪ ተካሂዷል።
DcWashington Dc