Translate

Monday, August 28, 2017

ከልሳነ ግፉዓንና ጠለምት የዓማራ ማንነት ጊዜያዊ ድጋፍ ኮሚቴ

ነሐሴ 2 ቀን 2009 ዓ/ም
Welkait Tsegede
ዘረኛውና አምባገነኑ የወያኔ ገዥ ቡድን አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝቧን እጅግ ኋላ ቀር በሆነ የከፋፍለህ ግዛ ዘይቤ ለ26 ዓመት ያደረሰዉንና ዛሬም እያደረሰው ያለው ኢሰብአዊና አምባገነናዊ ተግባር ለኛ ለኢትዮጵያዊያኖች አይደለም ለመላው የዓለም ሕዝብ ገሃድ መሆኑ ግልፅ ነው። ገና ከማለዳው ይህ ዘረኛ፥ ጠባብ፥ ፀረ ኢትዮጵያና ፀረ የኢትዮጵያ ሕዝብ የሆነው ቡድን በአንድና አንድ በሆነ አጀንዳ ብቻ ታውሮ ትግራይን ከቀረው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነጥሎ እንደ ሃገር ለማቆም ከያዘው ቅዥት የተነሳ አጎራባች ከሆኑ ክፍለ ሃገራት በግድና በሃይል ለም የሆኑ መሬቶችን ወደ ትግራይ ማስገባት ቀደም ሲል የፈፀመው ተግባር ብቻ ሳይሆን ዛሬም በስፋት እየጣረበት ይገኛል።

Saturday, August 26, 2017

እንኳንስ ሲሸጡን ሲዋዋሉብን እናውቃለን፣ የመልስ መልስ ለአቶ አብርሃ ደስታ (ከጎሹ ገብሩ)

Abraha Desat, Ethiopian polititian
ለተከበሩ አቶ አብርሃ ደስታ በመጀመሪያ የከበረ ሰላምታየን አቀርባለሁ በአካል ባንተዋወቅም በተጋድሎ ሃርነት ትግራይ ተብየዋ ተዕዛዝ ዘብጥያ በወረዱበት ወቅት የሚያውቅዎትም ሆነ የማያውቅዎት አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ በሙሉ በተሰነዘረብዎት ጥቃት ዘርና አካባባኢ ባልለየ መልኩ ከጎኖ እንደተሰለፈ ይዘነጉታል ብዬ አልገምትም እኔም እንደሌላው ሁሉ ነፃ የሚወጡበት ቀን ስመኝልዎት የነበርኩ ስሆን ህልሙ እውን ሆኖ ይህን ልብ የሚሰብር አጭር ትረካ ለመፃፍ እንኳን አበቃዎት እላለሁ።

የህወሓት/ኢህአዴግ የገጠር መዋቅር ሊፈርስ ይችላል ተባለ

  • ህወሓት በትግራይ ላይ የራሱን አቋም እንዲወስድ ተመክሯል
በኢትዮጵያ ያለማቋረጥ ሲካሄድ ከቆየው ሕዝባዊ ተቃውሞ አኳያ በህወሓት የደህንነት ክፍል የተሰበሰበው መረጃ፤ አሁን ካለው የተቃውሞ ንቅናቄ የተነሳ የኢህአዴግ የገጠር መዋቀር በኦሮሚያና በከፊል የአማራ ክልሎች ሊፈርስ እንደሚችል አስታወቀ። ከሁኔታው አሳሳቢነት የተነሳ ሊወሰዱ የሚችሉ አማራጮች ቢኖሩም ህወሓት ትግራይን አስመልክቶ የራሱን አቋም እንዲወስድ ሃሳብ ተሰጥቶታል።

Friday, August 25, 2017

ሕዝብ “በጠብመንጃ መገዛት በቃን” አለ!! ትውልድ እንዳመጸ ነው!

  • ለፖለቲከኞች እስር እውቅና የሰጡ “ፓርቲዎች” እየተደራደሩ – ሕዝብ እያመጸ ወዴት?
“እንወክለዋለን” በሚሉት ሕዝብ ዘንድ እውቅና ያላቸው ተቀናቃኝ ፓርቲዎች እጅግ አነስተኛ እንደሆኑ ይነገራል። አብዛኞቹ በምርጫ ቦርድ እውቅና ያገኙት የፖለቲካ ፓርቲዎች “ጥቂት” ከተሰኙት ውጪ ስለመኖራቸው እንኳን እንደማይታወቁ በተደጋጋሚ አስተያየት ይሰጣል። እነዚህን ፓርቲዎች ሰብሰቦ ድርድር መቀመጥ የአገሪቱን ችግር ማስተንፈስ እንደማይቻል የሚከራከሩ ወገኖች ድርድሩን አያከብሩትም። በሌላ በኩል ደግሞ ህወሓት/ኢህአዴግ እዚህ ደረጃ መምጣቱ በራሱ አንድ ርምጃ ነው የሚሉና ድጋፋቸውን የሚሰጡ ጥቂት አይደሉም። በውጤቱ ሲታይ ግን አመጹም፣ ቅሬታውም፣ ችግሩም መልኩን ሲቀያይር እንጂ ሲለዝብ ማስተዋል አልተቻለም።

ህወሀት በአዲስ አበባ ህዝባዊ ተዋውሞ ይነሳል በሚል ስጋት ውስጥ ገብቷል

ህወሀት መራሹ መንግስት በኦሮሚያ የተጀመረው ከቤት ውስጥ ያለመውጣት አድማ በአዲስ አበባም ይደገማል በሚል ትልቅ ስጋት ውስጥ መውደቁን ከምንጮቻችን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Wednesday, August 23, 2017

በቤት ውስጥ የመቀመጥ አድማ በመላው ኦሮሚያ ዛሬ ተጀመረ

Image may contain: bus and outdoor

(ኢሳት ዜና –ነሐሴ 17/2009) ለ5 ቀናት የተጠራው በቤት ውስጥ የመቀመጥ አድማ በመላው ኦሮሚያ ዛሬ ተጀመረ።

ይህ ስርዓት በፍጹም አይድንም! (መስቀሉ አየለ)

መስቀሉ አየለ
በጌታቸው አሰፋ እና በሳሞራ የኑስ መካከል ያለው ፍጥጫ ከድጡ ወደ ማጡ ሆኗል። በሁለቱ አሽቃባጮች ማለትም በኃይሌ ገብራስላሴና በፕሮፌሰር ይሳሃቅ ኤፍሬም በኩል ተጀምሮ የነበረው የማስታረቅ ጥረት ሚስጥሩ በኢሳት በኩል ሾልኮ ከውቀጣ በኋላ ተቋርጦ የነበረ ቢሆንም አሁን እንደገና በሁለቱም በኩል የተሻለ ተሰሚነት ሊኖራቸው ይችላል ተብለው በሚገመቱ ሙሉ ለሙሉ ከትግራይ በሆኑ የስርአቱ ሰዎች ሌላ የሽምግልና ጥረት እንደቀጠለ ነው።

በአቶ ደመቀ መኮንንና በዶ/ር ደብረጺዮን መካከል የተጀመረው ጥል ወደ ሃይል እርምጃ ተሸጋገረ

(ኢሳት ዜና ነሃሴ 17 ቀን 2009 ዓም)
Image may contain: 2 people
በአቶ ደመቀ መኮንንና በዶ/ር ደብረጺዮን መካከል የተጀመረው ጥል ወደ ሃይል እርምጃ ተሸጋገረ
በም/ል ጠ/ሚኒስትርና የብአዴን ሊ/መንበር ደመቀ መኮንን እና በህወሃቱ ም/ል ሊቀመንበርና የኮሚኒኬሽንና ኢንፎረሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶ/ር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል ያለው አለመግባባት ወደ ሃይል እርምጃ ማምራቱን የኢሳት ምንጮች ገልጻዋል።

Saturday, August 19, 2017

መለኛው ምኒልክና የዘመናዊ ወፍጮ አገባብ

ቋጠሮ ድህረ ገጽ
አጼ ምኒልክ የተወለዱት በ1836 ነኅሴ 12  ቅዳሜ ቀን ነበር። በህይወት ቢኖሩ ትናንት ነሃሴ 12 2009 ዓ.ም የ173 ዓመት ልደታቸውን ያከብሩ ነበር ማለት ነው፡፡ ሰሞኑን አብዛኛው ኢትዮጵያዊው የእኚህን ድንቅና የጥቁር ህዝብ የነጻነት ቀንዲል የሆኑ መሪ ገድል እየዘከረ 173ኛ የልደት ቀናቸውን እያከበረ ይገኛል፡፡ የዚህችም ጽሁፍ ምክንያት ይኽው ነው። የጸሃዩን ንጉስ ዕለተ-ውልደት መዘከር።መለኛው ምኒልክና የዘመናዊ ወፍጮ አገባብ
አጼ ምኒልክ በዘመነ ንግስናቸው በርካታ የስልጣኔ መሰረት የሆኑ ተግባራትን ፈጽመዋል። ስልጣኔን ወደ ሃገር በማስገባትና በማስፋፋት የአጼ ምኒልክን ያህል ተጠቃሽ መሪ የለም። ይሁን እንጂ አጼ ምኒልክ የውጭውን ስልጣኔ ለማስገባት ሲሞክሩ ህዝቡ አልቀበል እያለ ይቸገሩ ነበር፡፡  ለምሳሌ ወፍጮን ለማስገባት በሞከሩበት ወቅት ከመኳንቱና ከቀሳውስቱ ጠንከር ያለ ውግዘትና ተቃውሞ ነበር የገጠማቸው። መለኛው ንጉስ ግን የገጠማቸውን ተቃውሞና ውግዘት በጥበብ አክሽፈውታል። ያከሸፉበት ዘዴ ደግሞ ብልህነታቸውን ከማሳየቱም ባሻገር አስቂኝ ነበር።
ጳውሎስ ኞኞ  “አጼ ምኒልክ” በተሰኘው መጽሃፉ ገጽ 337 ላይ የዘመናዊ ወፍጮን አገባብ ታሪክ እንዲህ ሲል አስፍሮታል፦
የወፍጮ መኪና በኢትዮጵያ ውስጥ ለማቋቋም አስቸጋሪ ነበር። የሸዋው ንጉስ ሳህለ ሥላሴ በ1835 ገደማ አንድ በውሃ የሚሰራ ወፍጮ አስመጥተው ባስተከሉ ግዜ፤ ቀሳውስቱ ወፍጮ የሰይጣን ስራ ነውና በወፍጮው አስፈጭቶ የበላ የሰይጣን አገልጋይ ነውና አውግዘናል በማለታቸው ወፍጭው ፈራርሶ ወደቀ። ከዚያ ዘመን ቀደም ብሎም አቡነ ሰላማ አጼ ቴዎድሮስን ወፍጮ እንዲገባ ባማከሯቸው ግዜ “ የሴቶቹን ክንድ ምን ልናደርግበት ነው?” ወፍጮን ከለከሉ። አጼ ዮሃንስም “በጉዞ ላይ እህል የሚፈጩ ሴቶችን ከማጓጓዝ የሚገላግለን ነው..” ብለው ወፍጮ ቢያስተክሉም በንጉስ ሳህለ ስላሴ እንደደረሰው ሁሉ በእሳቸውም ላይ የሰይጣን ፈጪ ነው ተብሎ ስለተወገዘ ቀረ።

ዘረኝነት የወያኔ መጠባበቂያ ካርድ (ይገረም አለሙ)

ሰሚ ጠፍቶ እንጂ- እዛም እዚህም ሰፈር
ቀድሞ የገባቸው አስጠንቅቀው ነበር፤
Ethiopia, TPLF officials
“Whoever sows injustice will reap calamity.”
ለሁሉም አይቀሬ የሆነውና ክፉ ደግ ሀብታም ድሀ ምንዝር ባለሥልጣን ሳይልና ሳይለይ እኩል የሚወስደው ሞት በቅርቡ የነጠቀን አቶ አሰፋ ጫቦ ከመገናኛ ብዙሀን ጠፋ ብለው ሰነባብተው አላስችል ብሎአቸው  ብቅ ሲሉ ትቼው ረስቼው አንደሚሉት መተው ሆነ መርሳት ይቻል ከሆነ ብዬ ልሞክር ጠፋ አልኩና አላስችልህ ብሎኝ እነሆ ብቅ አልኩ፡፡

ሎተሪ በመግዛት ወገንህን ለመግደል የሚውል ጥይት አትግዛ

Image may contain: one or more people and text

ወያኔ ሀገሪጔቷን ሙሉ በሙሉ ከተቆጣጠረ በኋላ አንዳንድ ከወሰዳችው እርምጃዎች ብዙም ያለተሰማ እና ያልታወቀ ነገር ነበር፡፡ ነገር ግን በቅርቡ በመኣዛ ብሩ መድረክ ላይ ለአንድ ነባር ጋዜጤኛ በቀረበለት ቃለ መጠይቅ የተነገረው አንድ የወያኔ እርምጃ ፈንተው ያደረገልን የወያኔ ድርጊት አለ፡፡

Friday, August 18, 2017

የነጉርሜሳ አያና ምስክሮች ለአራተኛ ቀን መደመጥ ቀጥሏል

የነጉርሜሳ አያና ምስክሮች ለአራተኛ ቀን መደመጥ ቀጥሏል። (11/12/2009) በእነ ጉርሜሳ አያና መዝገብ በዛሬው ቀጠሮ የሚሰሙት ምስክሮች ለ2ኛ ተከሳሽ ጉርሜሳ አያና 4ት ምስክሮች እንዲሁም ለ3ኛ ተከሳሽ አዲሱ ቡላላ የምትመሰክር 1 ምስክር ባጠቃላይ 5ት ምስክሮች የቀረቡ መሆናቸውን ጠበቆች ተናግረዋል።

አልገብርም ሲል እንደመንግስት አላውቅህም ነው (ዳዊት ዳባ)

Small business owners strike in Ethiopia
አገዛዙ የቀረው በቀጣይ የሚለንም “ፋታ ስጡኝ” ነው። ህዘብ እያደረገ ያለው ትግል አገዛዙን ጨርሶ ሽባ አድርጎታል። ፍፃሜውን ለመስራት ድረስ  ጉልበታም ነው።  ከሁለት ከሶስት አመት  በፊት  ቁርጠኝነት፤ ጨዋነትና ውስብስብነት ያለውን ይህን አይነቱን  ትግል የበዛነው ምን አልባት “በተአምር ከሆነ” ብለን ስናስበው የነበረ ነው። የዚህ አባዜ አሁንም ምልከታችን ላይ ጋሬጣ የሆነ ይመስላል። ትግሉ በሚያሻው ሙሉ ትኩረትን፤ እገዛንና ገለፃን እያገኘ አይደለም።

Thursday, August 17, 2017

የመለስ አስከሬን… (አትክልት አሰፋ – ከቫንኩቨር)

አትክልት አሰፋ – ከቫንኩቨር
ye meles zskren
የመለስን ሞት ኢሳት በነገረን ሰሞን ብዙ ውዥንብሮች ነበሩ… ብዙ ብዙ ውጥንቅጥ የበዛበት ወቅት ነበር። አገዛዙ ይይዝ ይጨብጠው አጥቶ በየ መገናኛ ብዙሃኑ የሚወጡ ባለ ስልጣናት መርበትበትና መራወጥ ከትላንት ትዝታነት አልመከነም። ያኔ… የዛሬ አምስት ዓመት አካባቢ…

የክፍለሀገር ነፃነት ጥያቄ በኢትዮጵያ | በዶክተር ዳንኤል ተፈራ፤ የኤኮኖሚክስ ፕ/ር ኤመረተስ | በሚኒሶታ የተደረገ ንግግር

(ዘ-ሐበሻ) ባለፈው ቅዳሜ ኦገስት 12,2017 በሰሜን አሜሪካ የሚኒሶታ ግዛት ውስጥ በጎጃም, በጎንደር, በኦሮሚያና በኮንሶ የተጨፈጨፉትን ኢትዮጵያውያን ለማሰብ ደማቅ የማስታወሻ ምሽት ተዘጋጅቶ ነበር:: በዚህ ሕዝባዊ ዝግጅት ላይ ተገኝተው ሕዝባዊ ንግግር ካደረጉት መካከል ደግሞ ዶ/ር ዳንኤል ተፈራ ይገኙበታል:: ዶ/ር ዳ ኤል በስፍራው ያደረጉትን ንግግር ዘ-ሐበሻ በምስል አስቀርታዋለች – ይታደሙት::

ከያኒ አብዲ ኪያር እግዚአብሄር ይይልህ (ዳዊት ዳባ)

ዳዊት ዳባ
አንድ ሰው ምንድን ነህ? (ብሄረሰብህ ምንድን ነው) ተብሎ ለምን ይጠየቃል። ለምንስ ይናገራል የሚለው ትልቅ ጉዳይ የሆነው አሁን ላይ ፋሽን ተደርጎ እየተቀነቀነ ያለ ፖለቲካዊ አቋም ስለሆነ ብቻ ነው። “ምንድን ነህ የሚለው የሚከብድ ነገር አለው” በሚል ለመጀመርያ ጊዜ   ሲናገር የሰማሁት የምወደው የኪነ ጥበቡ ሰው አብዲ ኪያር ነው። ሀሳቡን ያነሳበት ሆነ ያስረዳበት መንገድ ጠቅላላ መንፈሱ ምንም ስህተት ያለውም አልነበረም።

ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ሆስፒታል በነበሩበት ወቅት በተነሳ የእስር ቤት ቃጠሎ ምስክር ተሰማባቸው

ጌታቸው ሽፈራው
Dr. Fikru Maru
ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ሊፈቱ በተቃረቡበት ወቅት የእሳት ቃጠሎው ተከሰተ። በወቅቱ ታመው ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ገብተው ነበር። ሳንባቸው ተጎድቶ በመሳርያ ተደግፈው ነበር የሚተነፍሱት። ባልነበሩበት ከተከሰሱ በሁዋላ ምስክሮች ቀርበውባቸዋል። ምስክሮቹ በሀሰት አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር ለእስረኛ አከፋፍሏል ብለው መሰከሩባቸው። ይህ የሚባለው ከ200 ብር በላይ በማይፈቀድበት ቂሊንጦ እስር ቤት ነው። ዶ/ር ፍቅሩ ላይ ዛሬ አንድ ምስክር ቀርቧል። ምስክሩ ሀዱሽ ሀይለስላሴ የፌደራለደ ፖሊስ ነበርኩ ያለ ግለሰብ ነው። አሁን እሰረኛ ነው።

Tuesday, August 15, 2017

ሙስና… ሙስና… ሙስና! (በኤልያስ ገብሩ)

ከጭቁን ህዝብ ጉሮሮ ተንገብግቦ መዝረፍ ይብቃችሁ!

በኤልያስ ገብሩ (ጋዜጠኛ)
Flood in Addis Ababa
ይህ ትናንት በአዲስ አበባ በዘነበው ዝናብ የተነሳ የተፈጠረ የጎርፍ ትዕይንት ነበር። ዝናቡ ባልከፋ፣ ነገር ግን ኢብኮ “ሚሊየንና ቢሊየን ብር ወጥቶባቸው ተመረቁ” እያለ በ’ልማታዊ’ ዜና የሚደሰኩርልን የተሽከርካሪና እግረኛ መንገዶች ተሽከርካሪዎችንና እግረኞችን እንዲህ በነጻ ሲያስዋኙት ታይተዋል።

በቀኝ ገዥነት ላይ ንቀትን የደረበው ህወሀት (በያሬድ አውግቸው)

በያሬድ አውግቸው
TPLF ethnic apartheid members
Some of TPLF ethnic apartheid leaders
ህወሀት ከምስረታው ማግስት ጀምሮ የአጎራባች ህዝቦች መሬቶችን ቀምቼ የታላቋን ትግራይ ሉአላዊ መንግስት እመሰርታለሁ የሚል እቅድ አዘጋጅቶ ወደ ጫካ የገባ ድርጅት እንደሆነ ይታወቃል። ጉልበቱን በመጠቀምም ያለቅድመ ሁኔታ መገንጠል የሚያስችል ያልተለመደ አንቀጽ  በህገ መንግስቱ  እንዲካተት አድርጎአል። የእቅዱ ቀሪ ክፍል የሆነውን መሬትና ሀብት  የማሰባሰብ  ስራን  ያለከልካይ ከተያያዘው እነሆ  26 አመታት ተቆጥረዋል። ለአለም አቀፍ ንግድ የሚያግዙ መግቢያና መውጫ አማራጮቹን የማስፋት እንዲሁም ለምግብ ምርት ማምረቻ የሚሆኑ የእርሻ መሬቶች ወደ ክልሉ የማጠቃለል ስራዎች በዚህ የእቅዱ ክፍል ውስጥ ይገኛሉ። ትመጣለች ተብላ ለምትጠበቀው  ሉአላዊ ትግራይ የኢንዱስትሪ ልማት መሰረት ለመጣል ሲል  ገና በልቶ ካልጠገበው የኢትዮጵያ  ህዝብ ጉሮሮ ላይ ካፒታልና ጥሬ እቃ ይዘርፋል፤ ይነጥቃልም።። ይህ እኔና አንተ/ቺ በእለት እለት ህይወታችን የምናየውና የሚሰማን ጸሀይ የሞቀው ሀቅ ነው። ማሳዎች ይቅረቡ ለሚል አካል እስኪ ምልከታችንን መረጃ አዘል እናድርገው፡፡

Monday, August 14, 2017

በመርህ ላይ ተመስርተህ መራሩን እውነት ተጋፈጥ (ኤርሚያስ ለገሰ)

ኤርሚያስ ለገሰ
Ermias Legesse, author and ESAT TV and Radio contributor
ኤርሚያስ ለገሰ
Jim collins “Good to great: why some companies make the leap and others not”በሚለው መጽሐፉ ” መራሩን ሀቅ ተጋፈጥ፣ ሆኖም ተስፋ አትቁረጥ” ይላል። ፀሐፊው እንደሚገልጠው ከሆነ ታላቅ አላማን ለማሳካት መራሩን እውነት መጋፈጥ ግድ ይላል። በሌላ በኩል ይሄንን ትልቅ ግብ ለማሳካት የሚደረገው ጉዞ በየጊዜው መውደቅና መነሳት ስለሚያጋጥመው ጨለምተኝነት እና ተስፋ መቁረጥ ውስጥ መግባት እንደማያስፈልግ ያስገነዝባል።
እርግጥም መራሩን ሐቅ በመርህ ላይ ተመስርቶ ለመጋፈጥ ቁርጠኝነት ይጠይቃል። ፊት ለፊት አገር አፍራሽ አደጋ እየታየ እንደ ሰጐን አንገት መቅበር የሚያዋጣ አይደለም። ዝሆኑ እቤት ውስጥ መኖሩን አምኖ በመቀበል መጋፈጥ ያስፈልጋል። ታዋቂው የአመራር ሳይንስ ምሁር Stephen covey ” The speed of TRUST” በሚለው መፅሐፉ እንዲህ ይለናል፣

Sunday, August 13, 2017

የውስጥ አርበኞች በባህርዳር ህወሃትን እና የብአዴን ተላላኪዎቹን ጭንቅ ውስጥ ከተዋቸዋል

በተፈራ አሳምነው
Bahir Dar City
ነሀሴ 1/2008 ዓ.ም ህወሃት ያሰማራቸው ነብስ ገዳዮች ተቃውሟቸውን በሰላማዊ መንገድ ለማሰማት አደባባይ በወጡ የባህርዳር ነዋሪዎች ላይ ተኩስ ከፍተው ከመቶ በላይ ሰላማዊ ዜጎችን ጨፍጭፈዋል።

Saturday, August 12, 2017

በርካታ ፖሊሶች የሥራ መልቀቂያ እያስገቡ ነው

(ትንሳኤ ራድዮ እንደዘገበው) በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት መልቀቂያ እንዳያስገቡ ላለፉት አሥራ አንድ ወራት ተከልክለው የነበሩ የመከላኪያና ፖሊስ አባላት አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተነስቶአል ከተባለበት ማግሥት ጀምሮ አገዛዙን እጅግ በሚያስደነግጥ ሁኔታ መልቀቂያ እያስገቡ መሆናቸውን ለአገዛዙ ቅርበት ያላቸው ምንጮች እየገለጹ ነው።
FilePhoto
በአብዛኛው የአገሪቱ ክፍሎች መልቀቂያ በማስገባት ላይ ካሉ የሠራዊቱና የፖሊስ አባላት መካከል በአዲስ አበባ የሚገኙ ፖሊሶች ከፍተኛውን ቁጥር እንደያዙ ተገልጾአል። ይህ ዜና እስከተጠናከረበት የዛሬው ቀን ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ መልቀቂያ ካስገቡ አባላት
መካከል ከ20 በላይ ከፍተኛ የፖሊስ መኮንኖችና ኤክስፔርቶች እንደሚገኙ ታውቋል።
ብዛት ያላቸው የመከላኪያ ሠራዊትና የፖሊስ አባላት በጥቂት ቀናት ውስጥ ባቀረቡት መልቀቂያ የተደናገጠውና ግራ የተጋባው የህወሃት አገዛዝ በደመወዝ ጭማሪና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች እንዴት አድርጎ መልቀቂያ ያቀረቡትን አባላት ማስቀረት እንደሚቻልና ወደፊትም ሊቀርቡ የሚችሉ የመልቀቂያ ጠያቄዎችን ቁጥር እንደሚቀንስ ማስጠናት እንደጀመረ ከውስጥ ምንጮች ለትንሳኤ ሬዲዮ ዝግጅት ከደረሰው መረጃ ለመረዳት ተችሏል። አገዛዙ እያስጠና ካለው ጥቅማ ጥቅም በተጨማሪም አንድ የሠራዊት አባል መልቀቂያ
ለማቅረብ ማበርከት ያለበት የ7 አመት አገልግሎት ጊዜን ወደ አሥር ወይም አሥራ ሁለት ከፍ ለማድረግ እየታሰበ እንደሆነም ተገልጿል።

Friday, August 11, 2017

የኢትዮጵያዊቷ አትሌት አሳዛኝ የባህር ማዶ ኑሮ ሲፈተሽ – “እንደ አሮጌ ቁና ተጣልኩኝ” (ልዩ ዘገባ) በታምሩ ገዳ


የኢትዮጵያዊቷ አትሌት አሳዛኝ የባህር ማዶ ኑሮ ሲፈተሽ – “እንደ አሮጌ ቁና ተጣልኩኝ” (ልዩ ዘገባ) በታምሩ ገዳ

የሜቴክ ውንብድና….በአዲስ አበባ ትራንሰፖር አውቶቢስ ግዢ ላይ (ጥብቅ መረጃ)

በበዛብህ ሲሳይ (2009) ሀይድራባድ ህንድ
ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ ሰሞኑ በቀድሞ የስርዓቱ ልሳን በነበረው በአቶ ኤርሚያስ ለገሰ ሜቴክ ከንግድ መርከብ ስለገዛቸው ሁለት መርከቦችና ሊያቋቁመው ስላሰበው የውሃ ትራንስፖርት ንግድ ስራ እንዲሁም በአገሪቷ ላይ ያደረሰውን ኪሳራ ካይሁ በኃላ ነው፡፡ እውነት ነው ተቋሙ ሲቋቋም ጀምሮ ለገዢው ጉጅሌ ኢኮኖሚያዊ ትርፍ እንዲያመጣ ተብሎ ብቻ አይደለም የትግራይ ተወላጆችን ከሰሜን ኤርትራዋኖች ላይ እንዲሁም ከደቡብ ደግሞ ሰፊው የኢትዮጰያ ህዝብ ላይ የፖለቲካዊ ልእልና እንዲያመጣ ጭምር እንጂ፡፡ ስለዚህ አቶ ኤርምያስ እንደ አስቀመጠው የሜቴክ መሪዎቹ ሲጋራን በቄንጥ ሚያጨሱ ብቻ ሳይሆኑ በዚህ እኩይ አላማቸው ላይ የሚሳተፉትን ሆድ አደር “ሙሁራን” ወይም ባለሰርተፊኬቶችን ወይም እንዴት ማስተዳደርና መጠቀም እንዳለባቸው ስለሚያውቁ ይሄው ይሄ ሁሉ ጉዳት በአገሪቱ ላይ ሊያደርሱ ቻሉ፡፡ አንዳንዴ የፈረንጅንም ጫማ ላሾችንም (Bootlikers) ይጠቀማሉ፡፡ በዚህ ጽሁፍ ዋና አላማ ሜቴክ ተልዕኮውን እንዴት እንደሚያሳካ ለማሳይት የታሰበ ሲሆን ፅህፉ ያለውን ነባራዊ ሁኔታን ብቻ የሚያሳይ ነው..ፍርዱን ደግሞ እናነተ ስጡ… መልካም ንባብ !!

Wednesday, August 9, 2017

ትልቁ ሰውዬና የጅጅጋ ሕዝብ ሰቆቃ

ከሙክታር ኦማር የእንግሊዝኛ መጣጥፍ በግርድፉ የተተረጎመ
(ምንጭ፣ የአርበኞች ግንቦት7 ድረገጽ)
Abdi Mohamoud Omar
Abdi Mohamoud Omar
በድህረ ቅኝ ግዛት ዘመኗ አፍሪካ የገባችበትን የአስተዳደር ብልሹነትና የፖለቲካ ቀውስ አስመልክቶ  እንደ ካሜሩናዊው የማህበረሰብ ጥናት ተመራማሪ አቺሌ ሜምቤ  በትክክል የተረዳና የጻፈ ምሁር  ጥቂት ነው። ” የብልግና ውበት” በተባለው ድንቅ ጥናታዊ ጽሁፉ የነጮቹን ጌቶቻቸውን ቦታ ተረክበው አፍሪካን እየተጫወቱባት ያሉት “ጌቶቹ አምባገነን መሪዎቻችንና ባለስልጣናቱ” የፈጠሩት ስርዓት ጥቂቶቹን ጨቋኞችና ብዙሃኑን ተጨቋኝ ህዝብ በአንድ ላይ ጠፍንጎና አቆላልፎ አስከፊ ወደሆነ የስብዓና ዝቅጠትና ሕይወት አልባ ወደሆነ የደመ ነፍስ ጉዞ እንደሚጎትታቸው በሚያስደንቅ ብዕሩ ገልጾታል።

“ለውጥ ያረገዙ መልካም አጋጣሚዎች፣ የአዋላጅ ያለህ እያሉ ነው!” – የአማራ ሕልውና ለኢትዮጵያ አንድነት በወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ የበተነው ጽሁፍ ደርሶናል | ይዘነዋል


ነሃሴ ፪ ቀን ፪ሺ፱ ዓ.ም ቅጽ ፩ ቁጥር ፭
በየትኛውም መልኩ በሕዝብ ላይ የተጫነን አምባገነንና ዘረኛ አገዛዝ ለመጣል፣ ለውጥን አስፈላጊ የሚያደርጉ አጋጣሚዎች አሉ። ካሉት የለውጥ አዋላጅ መልካም አጋጣሚዎች ውስጥ የአገዛዙ የኢኮኖሚ ሥርዓት መናጋት አንዱና መሠረታዊው ነው። የአንድ አምባገነን ሥርዓት የኢኮኖሚ መሠረቱ ሲናጋ የሚከተሉት ሁኔታዎች በማኅበረሰቡ ውስጥ ጎልተው ይታያሉ። የሥራ አጡ ሕዝብ ቁጥር ከምንጊዜውም በላይ ይጨምራል። የኑሮ ውድነት ከሚጠበቀው በላይ ይንራል። የገንዘብ የመግዛት አቅም ይቀንሳል። የማኅበራዊ ሰላም ይናጋል። ሕጋዊ ሥርዓቱ ቦታውን ለሕግ-አልባው ይለቃል። መተማመን በጥርጣሬ ይዋጣል። ሕይዎት ዋጋ ያጣል። የአምባገነኑና የዘረኛው የአፈና የመንግሥታዊ ተቋሞችና ቢሮክራሲ እንደ ጥንቱ የአፈናና የዕመቃ ተግባራቸውን ለማከናወን አቅም ብቻ ሳይሆን ፣ ወኔና የማድረግ ፍላጎቱ ይከዳቸዋል። በነዚህም ምክንያቶች የአገዛዙ ቁንጮዎች በመካከላቸው መተማመን ያቅታቸዋል። ለሚከሰቱ ችግሮች አንዱ በሌላው ላይ ጣቱን ይቀስራል። በዚህም ትልቁ ዓሣ ትንሹን እንደሚውጠው፣ እርስ በራሳቸው ይዋዋጣሉ። የአገዛዛቸው ዕድሜ እያጠረ መምጣቱንም ስለሚገነዘቡ ኅሊናቸው ውጭ ያማትራል። በዚህም ልጆቻቸውንና ሚስቶቻቸውን በተለያዩ ምክንያቶች ወደውጭ ይልካሉ። ገንዘባቸውን ያሸሻሉ። ተፈርተው ይከበሩ የነበሩት፣ ክብራቸውን ያጣሉ። ሲያልፉና ሲያገድሙ ይሽቆጠቆጥላቸው የነበረው ሕዝብ ይንቃቸዋል፣ ያዋርዳቸዋል።

Saturday, August 5, 2017

ኃይሌ ገብረሥላሴ ምን እያለ ነው? (ደረጀ ሀብተወልድ)

ደረጀ ሀብተወልድ
ይህ ኃይሌ ገብረሥላሴ ዛሬ ጧት የሰጠው አስተያዬት ነው፣
“ሞ ፋራህን ወደ ኋላ ሄጄ ቪዲዮውን ብመለከት እንዲህ የሚባል ሰው የለም:: እኔም ስሮጥ አልነበረም ቀነኒሳም ሲሮጥ የለም:: ለማሸነፍ ሲሮጥ እንጂ ሰአት ሲያሻሽልም አታየውም:: ይሄን ስታይ ትጠራጠራለህ ከየት መጣ? የምጠረጥረው ነገር አለ ግን በአደባባይ መናገሩ ክስም ሊያመጣ ይችላል”
Mo Farah is the UK's finest ever distance runner
ሞ ፋራህ በአዲስ አበባ፣ ከቴዲ አፍሮ ጋር
ይህ አስተያዬት ከሌላ ሰው ቢሰነዘር ምንም አልነበረም። ሆኖም በሱ ዘመን ሲያሸንፍ አድናቆት ሲጎርፍለት የነበረ አትሌት ዛሬ ባለስልጣን ሆኖ ተሹሞ በቡድኑ ላይ ሽንፈት ሲደርስበት ተራው የሌላ አትሌት መሆኑን አምኖ ከመቀበል ይልቅ ወደ ስም ማጥፋት መሮጡ ያሳዝናል።

አቶ ዛይድ ወልደገብርኤል ሃጎስን ያሳሰረ የስኳር ፋብሪካ ጦስ! (ዳዊት ከበደ ወየሳ)

የመንገድ ስራዎች ባለስልጣን ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ዛይድ ወልደገብርኤል ሃጎስ በትላንትናው እለት በሙስና ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ውለዋል። አቶ ዛይድ የመንገድ ስራዎችን ኮንትራት ለቻይና ድርጅቶች በመስጠት፤ ምናልባትም ከዚሁ ጋር በተያያዘ ሙስና ውስጥ እንደገቡ ተደርጎ በተደጋጋሚ ስማቸው ሲነሳ ቆይቷል። ትንሽ ውስብስብ የሚመስለውን የሙስና እንቆቅልሽ ለመፍታት ግን፤ ይህን በአገር ላይ የሚደረግ ድራማ ከስር መሰረቱ መፈተሽ ያስፈልጋል።
ዝርዝር ጉዳዮችን ወደጎን በመተው በቀጥታ ወደ ኩራዝ ስኳር ፋብሪካ እንሄዳለን። የስኳር ፋብሪካው የግቤ ግድብን ተከትሎ የተሰራ፤ በአቶ አባይ ጸሃዬ የሚመራ ፕሮጀክት ነው። ለአቶ አባይ ጸሃዬ እንደጉዳይ አስፈጻሚ ሆነው፤ የሚወከሉት ደግሞ የስኳር ፋብሪካው ምክትል ዳይሬክተር አቶ ኪሮስ ደስታ ነበሩ። (ባለፈው አመት ከስልጣናቸው ከተነሱ በኋላ፤ ትላንት ምሽት ላይ በሙስና ተጠርጥረው መታሰራቸው ተሰምቷል)
አቶ ዛይድ ከስራ እንዲሰናበቱ አስተዋጽኦ እንዳደረጉ፤ የሚነገርላቸው አቶ ወርቅነህ ገበየሁ፤ ከአቶ ዛይድ ጋር ሞቅ ያለ ንትርክ ላይ እያሉ የተነሱት ፎቶ።

የመንገድ ስራዎች ባለስልጣኑ መስሪያ ቤት ሌሎች አስቸኳይ ስራዎች ቢኖሩበትም፤ በ2014 ዓ.ም ግን አስቸኳ ትዕዛዝ፤

ክቡር ጠ/ሚኒስትር: “የእርስዎ ከሥልጣን መውረድ ለኢትዮጲያ ትልቅ ውለታ ነው!

ስዩም ተሾመ
ባለፈው ባወጣነው ፅሁፍ የፖለቲካ አመራር ብቃት የሌላቸው መሪዎች ለሀገር ሰላም፥ ልማትና ዴሞክራሲ “እንቅፋት” እንደሚሆኑ በዝርዝር ተመልክተናል። በመጨረሻም፣ በሀገራችን ወቅታዊ ፖለቲካ ላይ በግልፅ የሚስተዋለው ችግር የመልካም አስተዳደር ወይም የኪራይ ሰብሳቢነት ችግር ሳይሆን የፖለቲካ አመራር ብቃት ማነስ እንደሆነ በፅሁፉ ተጠቁሟል። ከዚህ አንፃር፣ “የኢህአዴግ መንግስት የፖለቲካ አመራር ብቃት እንዴት ይታያል?” የሚለውን በዚህ ፅሁፍ በዝርዝር እንመለከታለን።

በእርግጥ በሀገራችን ፖለቲካዊ ሁኔታ ላይ የሚሰጥ ማንኛውም ሃሳብና አስተያየት ከጭፍን ድጋፍ ወይም ተቃውሞ ስለሚቆጠር በአንድ ነገር ላይ በግልፅ ተነጋግሮ መግባባት አስቸጋሪ ነው። አሁንም ቢሆን ስለ ጠ/ሚ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ አመራር ብቃት የግል አስተያየቴን ስሰጥ “የመንግስት ተቃዋሚ ስለሆነ ነው” መባሉ አይቀርም።

Thursday, August 3, 2017

አዜብ መስፍን እና ስብሃት ነጋ በደህንነቱ ሹም ተጋለጡ | ሊታይ የሚገባው




<...በሕወሃት ሙስና ወንጀል አይደለም። በጋራ ዘርፈው የኢኮኖሚ የበላይነት ለማግኘት ወስነው ነው ሲዘርፉ የኖሩት።የሰሞኑ የይስሙላ የሙስና ዘመቻ ዋናዎቹን ሙሰኞች የሕወሓት ባለስልጣናት፣ጄኔራሎች ፣የእነሱን ኢንቨስተሮች አይነካም .

የማላውቀው ሲሳይ አጌና! (ኤርሚያስ ለገሰ)

ኤርሚያስ ለገሰ
Ethiopian journalist Sisay Agena
ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና
ባለፋት ወራት ” ሲሳይ አጌና!” በሚል የፌስቡክ ስም የተሳሳቱ መረጃዎች መዛመታቸው ይታወቃል። በዚህ ፌስቡክ ስም ከተስተናገዱት መረጃዎች መካከል አንጋፋው ኢትዬጲያዊ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ማረፋቸው፣ አንጋፋው ድምፃዊ አሊ ቢራ ማረፋ፣ የኢትዮጵያ ሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊዎች በሳኡዲ አረቢያ የሞት ፍርድ እንደተፈረደባቸው ይገኙበታል። ሰሞኑን ደግሞ በብዙ ኢትዬጲያውያን ዘንድ የፅናት ተምሳሌት ተደርጐ የሚወሰደው ታማኝ በየነ በመኪና አደጋ ህይወቱ እንዳለፈ የተገለጠበት ነበር።

ወያኔ በአምሳሉ የፈጠረው የአየር ሃይል ሲፈተሽ (የአርበኞች ግንቦት 7 ድምጽ ሬድዮ)

Ethiopian air forceአየር ሃይል ለአንዲት አገር መከላከያ የሚያበረክተው አስተዋጽኦ እጅግ የላቀ ነው። በዚህም አገራችን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ደረጃ የራሷን የአቪየሽን ተቋም በመመስረት ግንባር ቀደምት ነች።ወይንም ነበረች ሳይሻል አይቀርም።ያኔ የአፍሪካ አገራት በቅኝ ግዛት ቀንበር ስር ወድቀው በሚማቅቁበት ዘመን ኢትዮጵያ የራሷ ጠንካራ የአየር ሃይል ተቋም ነበራት።በኢትዮጵያ የአቪየሽን ታሪክ የሚጀምረው በ1921 ዓ/ም እንደጀመረ ታሪክ ይነግረናል።የኢትዮጲያን አየር ሃይል በዘመናዊ መልኩ ማደራጀት የተጀመረው ደግሞ በ1936 ዓ/ም ከፋሺስት ኢጣሊያ ወረራ በኋላ ነው። አየር ሃይሉ ከሌሎች የሃገሪቱ መከላከያ ተቋማት ጋር በመጣመር የሃገሪቱን ዳር ድንበርና ሉአላዊነትን ለማስከበር በተደረጉ ተጋድሎዎች  እስከደርግ ወድቀት ድረስ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል። በተለይም የኢትዮጵያን የአየር ክልል በማስከበር ረገድ የማይተካ ሚና ነበረው።

ግፍ ያልገታው፣ ያልተንበረከከው መንፈስ !

ክምሩን የሀገር ሀብት ስርቆት ፣ ብክነት ሳስበው  …
ክምር በቢሊዮን የሚቆጠር የሀገር መዋዕለ ንዋይ ከመቶ ባልበለጡ የሀገሪቱ ባለስልጣናት የመዘረፉን ወንጀል እየሰ ማን ነው ። ጥሎብኝ ገንዘቡን ወደ አባይ ግድብ አስጠጋውና የሳውዲ ነዋሪ ለአመታት ካጠራቀመው ጋር አወዳድረዋለሁ። አልገናኝህ ይለኛል … ገንዘቡ ከፍ ሲል ሌላ ማወዳደሪያ እፈልጋለሁ ። .. ውጭ ያለው በሚሊዮን የሚቆጠር ዜጋ ወደ ሀገር ከሚልከው ገንዘብ የተገኘውን ገቢ አስበውና እንደገና የተሰረቀው ከባድ የመሆኑን ክብደት ያስደነግጠኛል ፣ እደነግጣለሁ ። “ጠፋ ፣ ተሰረቀ” የተባለው የዚህች ድሃ ሀገር ገንዘብ ስንት አውሮፕላን እንደሚገዛ ሳሰላ ውዬም አውቃለሁ፣ የሞኝ ነገር ትሉኝ ይሆናል። ግን አይደለም። የገንዘቡን ክብደት ለማወቅ እንጅ … እንዲህ ሲቆጨኝ ስዳክር ነው የሰነበትኩት

የህወሓት “መከላከያ ሰራዊት” በበቃኝ ጥያቄ ተወጥሯል፤ ጄኔራሎች አሉበት!

ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው ህወሓት የሚመካበትን የታጠቀ ሰራዊት የሚመሩ ከፍተኛ መኮንኖችና ጄኔራሎች በጡረታ ለመሰናበት ጥያቄ ማቅረባቸው ተሰማ። የአስቸኳይ አዋጁ ሲነሳ መልስ እንደሚያገኙ ቃል የተገባላቸው እንዳሉም ታውቋል።
የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ለደህንነት ሲባል መረጃውን ያገኘበትን ሳይገለጽ እንደጠቆመው “መከላከያ ሰራዊት” የሚባለውን የህወሓት ሥልጣን አስጠባቂ የታጠቀ ኃይል ከሚመሩት ጄኔራሎች መካከል “በቃኝ” ያሉት ጄኔራሎች ከሰባት በላይ ሲሆኑ፣ በከፍተኛ መኮንን ደረጃ ያሉት ግን ቁጥራቸው በርከት ያለ ነው።

Tuesday, August 1, 2017

የሱሌይማን ደደፎ ደብዳቤ! – ከኤርሚያስ ለገሠ

በሕውሓቱ ጄኔራል ክንፈ ዳኘው ስለሚመራው የመከላከያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፕሬሽን ( ሜቴክ) ሌብነት እና ዝርፊያ ብዙ ተብሏል። እድሜ ይስጠን እንጂ ለወደፊቱም እጅግ በጣም ብዙ ይባላል። በትክክልም ይህ በእውቀት አልቦነት እና ማን አለብኝነት የሚንቀሳቀስ ኮርፖሬሽን በአንድ በኩል የአገሪቱ መፃኢ እድል እያጨለመ፣ በሌላ በኩል የሕውኃት የግል ንብረት የሆነውን ኤፈርት የፋይናንስ አቅም እያደለበ እንዲሄድ በማድረጉ ምክንያት ጊዜ አጥፍቶ መነጋገሩ ቢያንስ ከህሊና ተጠያቂነት የሚያድን ይሆናል። ዘለግ ባለ ሁኔታ መነጋገሩ ፍሬ ካፈራ ደግሞ የህውሓቶችን የዘረኝነት አምድ ለማፈራረስ ፣ የአገር መግደያ ሃይላቸውን ለመደምሰስ እና የአፓርታይድ መሰል ፓሊሲና አካሄዳቸውን ለመግታት የሚረዳ ይሆናል።
እርግጥ ለሁላችንም የማይካድ አንድ ሐቅ አለ። ሲጋራን በቄንጥ ከማጨስ ውጭ ሌላ ዘመናዊ እውቀት የሌላቸው የሜቴክ ጄኔራሎች ገደብ የለሽ በሆነው ዝርፊያቸው ታውቀዋል። በተለይ ዋና ዴሬክተር የሆነው ጄኔራል ክንፈ ዳኘው የመቶ ፐርሰንት የሕውኃት/ ኢህአዴግ ፓርላማ ላይ ቀርቦ ያቀረበው ማስፈራሪያ የአመቱ አስገራሚ ንግግር ተደርጐ የተወሰደ ነው።

ደባርቅ፦ጎንደር ግብር አንከፍልም ብሏል * ለማይወክለን መንግስት ግብር አንከፍልም

ከአስናቀው አበበ
የሠሜን ተራሮች መገኛ የሆነችው ደጋማዋ ከተማ ደባርቅ ወገብ በሚሰብር የግብር ጭማሬ ውሳኔ እየተረበሸች ትገኛለች፡፡ የዳባት ከተማን ጨምሮ ብዙ የወረዳ ከተሞች ተመሳሳይ ትርምስ አለ። ደባርቅ ዓመቱን ለነፃነት የተሰው ልጆቿን እያሰበች፣ ከቱሪስት የምታገኘውን ገቢ እንኳን ቅጥ ባጣው የወያኔ ኮማንድ ፖስት እንዳታገኝ የተደረገች፣ የዕለት ጉርሳቸውን ከበቅሎ ኪራይ፣ ከቱሪስት አስጎብኝነት እንዲሁም ከመኪና ኪራይ የሚያገኙ ልጆቿ ተጨማሪ እሴት ታክስን ጨምራችሁ ክፈሉ ተብሎ ተወስኖባቸዋል።

ከአምባሳደሮቹ ሹመት በስተጀርባ ያሉት ምስጢሮች ሲተነተኑ




ከአምባሳደሮቹ ሹመት በስተጀርባ ያሉት ምስጢሮች ሲተነተኑ