Translate

Monday, August 31, 2015

ከዊሃ እስከ ኦምሃጀር – አንድ ሰሞን ከአርበኞች ጋር (ኤፍሬም ማዴቦ)

በኤፍሬም ማዴቦ
ቃል የዕምነት ዕዳ ነዉ። አዎ! ማተቡን ላጠበቀና በአምላኩ ለሚታመን በእርግጥ ቃል የዕምነት ዕዳ ነዉ። ሰዉ ነኝና እንደ ፈጣሪ ቃሌ ሁሉ እዉነት ነዉ ብዬ አለተፈጥሮዬ አላብጥም። ግን ሰዉ ብሆንም ፈጣሪዬን የምፈራ ሰዉ ነኝና ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ስል ልቦናዬ እያወቀዉ እንደነ ጋሼ እንደልቡ ዉሸት ደርድሬ ለአንባቢ የማቀርብበት ምንም ምክንያት የለም። ከዚህ ቀጥሎ የማስነብባችሁ እያንዳንዱ ቃል እንደ ዳያስፖራ ተረተኞች የምተርተዉ ‘ሰዉ ሰዉ’ የማይሸተት ተረት ሳይሆን ኢትዮጵያ ድንበር ላይ በየግንባሩ የተሰለፉትንና በስልጠና ላይ የሚገኙትን የኢትዮጵያ አርበኞች ስጎበኝ በአይኔ ያየሁትንና በጆሮዬ የሰማሁትን ቃል ነዉ።Ephrem Madebo with Patriotic Ginbot 7 fighters
ቨርጂኒያ ወደሚገኘዉ “Dulles” አዉሮፕላን ማረፊያ የሄድኩት ከልጄ ጋር ነበር። ከቤቴ Dulles የግማሽ ሰዐት መንገድ ነዉ። ያቺን ግማሽ ሰዐትና አዉሮፕላን ማረፊያ ደርሼ ሻንጣዬን እስካስጭን ድረስ አይኔ እያንዳንዷን ደቂቃ ከልጄ ከቢኒያም አልተለየም። መለየቱን ስላልወደደዉ ልቤ ደንግጧል። ከወያኔ ጋር ለመፋለም በረሃ የሚጓዘዉ ኤፍሬም ከአንድ ልጁ መለየት አቃተዉ። ምነዉ ብዬ እራሴን ጠየኩት- እኔዉ መልሼ ምንም አልኩ። ልጄን አቀፍኩት፤ አሁንም ደግሜ ደጋግሜ አቀፍኩት። እምባ ፊቴን ሞላዉ። ቀና ብሎ ተመለከተኝና ሲከፋዉ ታየኝ።

Friday, August 28, 2015

አርበኞች ግንቦት 7 – መልዕክት በድሆች ድህነት ለመክበር መሯሯጥ ላይ ላሉ የዲያስፓራ ማኅበረሰብ አባላት !

Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracyየግል ኑሮን ለማደላደል ሲባል የወያኔ አባል መሆን “ወይን ለመኖር” የሚል ስያሜ ከተሰጠው ዓመታት ተቆጥሯል። “ወይን ለመኖር” ዜጎች ነፃነታቸውን ለጥቅም አሳልፈው የሚሸጡበት፤ የሰው ልጅ ክብር የሚዋረድበት ገበያ ነው። በወይን ለመኖር “የገበያ ህግ” መሠረት እያንዳንዱ ዜጋ ሊያገኘው መብቱ የሆነውን አገልግሎት እንዲያገኝ የህወሓት፣ የብአዴን፣ የኦህዴግ፣ የደህዴግ፣ የአብዴፓ፣ የቤጉህዴፓ፣ የጋህአዴን፣ የሀብሊ ወይም የኢሶዴፓ አባል መሆን፤ አልያም መደገፍ ግዴታ ነው። እነዚህ ሁሉ ድርጅቶች የህወሓት ተቀጽላ ወያኔዎች ናቸው። የእነዚህ ድርጅቶች አባል ወይም ደጋፊ ያልሆነ እንኳስ የመንግሥት አገልግሎት ሊያገኝ ጥሮ ግሮ ያፈራውንም ይነጠቃል።
በዚህም ምክንያት፣ በገጠር ያለው አርሶ አደር ቁራጭ የእርሻ መሬት፣ የግብርና ባለሙያዎች የምክር እገዛ፣ የማዳበሪያና ዘር ግዢ፣ ብድር ወይም እርዳታ ለማግኘት በአካባቢው ባለ የወያኔ ድርጅት አባልነት መመዝገብ፤ አንድ ለአምስት መደራጀት እና የወያኔን የስልጣን እድሜ የሚያራዝሙ ነገሮችን መሥራት ይጠበቅበታል። በከተሞች ውስጥም ሥራ ለመቀጠር፣ ለደረጃ እድገት፣ የመኖሪያ ቤት (ኮንዶሚንየም) ለመግዛት ሲባል መወየን አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታ ሆኗል:: በንግዱም ዘርፍ የንግድ ፈቃድ፣ የሥራ ቦታ እና የባንክ ብድር ለማግኝት፣ የመንግሥት ጨረታዎችን ለማሸነፍ፣ ከጉምሩክ እቃ ለማስለቀቅ፣ የውጭ ምንዛሪ ለማግኘት መወየን ግዴታ ነው።

Thursday, August 27, 2015

የድህረ-መለሱ ኢሕአዴግ አሰላለፍና የ“አዲሱ” ሥራ አስፈጻሚ የቢሆን ዕድል


tplf eprdf

የአራት ድርጅቶች ስብሰብ የሆነው ኢሕአዴግ፤ በሕወሓታዊ የድርጅት መንፈስ እየተመራ የስልጣን ቆይታ ዘመኑን ከአመታት ልኬት ወደ አስርታት ያሻገረ በመሆኑ፣ ከእንግዲህ የአገዛዝ ዘመኑን በክፍለ ዘመን ክፋይ አገላለጽ መጥራቱ ተራዛሚ የስልጣን ቆይታውን ይበልጥ የሚገልፀው ይሆናል፡፡ እናም ሩብ ክፍለ ዘመን ያህል በስልጣን ላይ ያለው ኢሕአዴግ በሰሜን ኢትዮጵያ የፖለቲካ ተዋረድ አገሪቱን “እየመራ” እዚህ ደርሷል፡፡ ግንባሩ ከፊት ለፊቱ አንደ “ትልቅ” ድርጅታዊ ጉባኤ ይጠብቀዋል፡፡

Friday, August 21, 2015

የአዲሱ ህውሀት መንግስት መጥፎ አጋጣሚ! (ከኤርሚያስ ለገሠ)

ከኤርሚያስ ለገሠ (ክፍል አንድ )
1 – ደስታ እና ሀዘን
ሰሞኑን ፍቺ በፍቺ ሆነናል። የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን ከፊል አካል ተፈታ። ደስ አለን። የተፈቱት ካልተፈቱት ያላቸው ልዩነት ለብዙዎች ግራ ቢያጋባም!…ዛሬ ደግሞ እነ ሀብታሙ አያሌው ተፈተዋል። ይህም በግለሰብ ደረጃ ደስ የሚል ዜና ነው። ቢያንስ በቅርብ የማውቀው ሀብታሙ (” ሀብትሽ!”) ክፋ ደጉን የማታውቀው ልጁ እጁ ላይ ስታንቀላፋ፣ ወደ አልጋዋ ወስዶ ሲያስተኛት፣ ከእንቅልፏ ስትነቃ አቅፎ ሊያነሳት በመቻሉ ደስ ይለኛል። እንኳን ለዚህ አበቃህም ማለት እፈልጋለሁ።Ermias Legesse former Woyane govt. employee
በሌላ በኩል ገዥው ቡድን በምክንያት እያሰረ በምክንያት የሚፈታበት ሁኔታ ለራሱ ስልጣን መቆያ ትክክል ቢሆንም ለኢትዬጲያ የፍትህ ስርአት ምን ያህል ንቀት እንዳለው የሚያሳይ ተደርጐ ሊወሰድ የሚችል ነው። ሰዎች በህውሀት ላይ አደጋ ሲጋርጡ በፓለቲካ ውሳኔ ይታሰራሉ…ህውሀታዊ ምክንያት !። ገዥው ቡድን ላይ የተጋረጠው አደጋ በሌላ ጐን ሲያጋድል ደግሞ በእጁ ይዞ የሚያሰቃያቸውን ይፈታል…ህውሀታዊ የመፍታት ምክንያት!!

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ ወያኔ እና የሚዘረፈው ሰራዊት (መሳይ መኮንን)

መሳይ መኮንን (የኢሳት ጋዜጠኛ)
ዛሬ ለኢሳት የደረሰው ጥብቅ መረጃ 11ዓመታትን ወደ ኋላ በትዝታ ወሰደኝ:: ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከዋናው ጸሀፊ ቢሮ አፈትልኮ የወጣው መረጃ እንደሚያጋልጠው ለሰላም አስከባሪ 11 ሺህ የኢትዮጵያ ሰራዊት የሚከፈለው ደምወዝ ከ90 በመቶ በላይ የህወሀት ካዝና ውስጥ የሚገባ ነው:: በወር 13 ሚሊዮን ዶላር(500 ሚሊዮን ብር ገደማ) የወታደሩን ገንዘብ ህወሀቶች ይቀራመቱታል:: ይህን ጉዳይ የመንግስታቱ ድርጅት የሚያውቀው ይመስለኛል:: ለዚህም እኔ የተሳተፍኩበትን የሰላም አስከባሪ ዘመቻ አጋጣሚ በአስረጂነት ማሳየት እችላለሁ::Ethiopian peacekeeping troops
እኤአ በ2003-2004 በመንግስታቱ ድርጅት የበላይነት: በአፍሪካ ህብረት አስፈጻሚነት ከተላከው የኢትዮጵያ የሰላም አስከባሪ ሰራዊት ጋር ወደ ቡሩንዲ ሄጄ ነበር:: ወደ 18 የምንሆን አስተርጓሚዎች ከ8 ወር እስከ 1 ዓመትቆይተናል:: ዝርዝሩን ሌላ ጊዜ በሰፊው እመለስበታለሁ:: ከገንዘብ ጋር በተያያዘ የተፈጸመውን የህወሀቶችን ለከት ያጣ ስግብግብነትን ላጫውታችሁ::

Thursday, August 20, 2015

አርበኞች ግንቦት 7 በዋሽንግተን ዲሲ፣ በዳላስ እና በሲያትል የተሳካ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሞችን አካሄደ


Patriotic Ginbot 7 success fundraising Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracyአርበኞች ግንቦት 7 ባለፈው ነሐሴ 10 2007 ዓ.ም በዋሽንግተን ዲሲ በሸራተን ሆተል ባካሄደው የተሳካ የገንዝብ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ቁጥሩ በርካታ ኢትዮጵያዊ መገኘቱን ለማወቅ ተችሏ።
ንቅናቄው በመላው አለም በማካሄድ ላይ ባለው ተመሳሳይ ፕሮግራም በአውስትራሊያ፣ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ የተለያዩ ከተሞች በስደት ነዋሪ የሆነው ነጻነት ፈላጊ ኢትዮጵያዊ ዜጋ በነቂስ በመሳተፍ ለዲሞክራሲ የሚደረገውን ትግል በደጀንነት ለማገዝ ቁርጠኝነቱን እያሳየ ይገኛል።

አብረሃ ደስታ እና ሀብታሙ አያሌውን ጨምሮ ፍርድ ቤቱ አራት ፖለቲከኞች ነፃ እንዲለቀቁ ወሰነ

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
ዛሬ ነሃሴ 14/2007 ዓ.ም የልደታ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት በዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ የተከሰሱትን 2ኛ ተከሳሽ ሀምታሙ አያሌው፣ 3ኛ ተከሳሽ ዳኤል ሽበሽ፣ 4ኛ ተከሳሽ አብርሃ ደስታና 5ኛ ተከሳሽ የሸዋስ አሰፋ እንዲሁም 7ኛ ተከሳሽ አብሃም ሰለሞን በነፃ እንዲለቀቁ ወስኗል፡፡
Abraha Desta and Habtamu Ayalew to be freeበአንፃሩ አንደኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ ከአሁን ቀደም ተከሶበት በነበረውና ከ15 አመት በላይ እንደሚያሳስር የሚታወቀው የፀረ ሽብር ህጉ አንቀፅ አራት ‹‹ማሴር፣ ማቀድ ተግባረት›› ላይ መረጃ ስላልተገኘበት አንቀፁ 7/1 ላይ በተመለከተው ላይ ተቀይሮ እንዲከላከል ተበይኖበታል፡፡ በዚህ አንቀፅ ለግንቦት ሰባት በመመልመል ተግባር ተሰማርቷል በሚል እንደተከሰሰም ተገልጾአል፡፡ በተመሳሳይ 6ኛ፣ 8ኛ፣ 9ኛ ፣10ኛ ተከሳሾች ከአንደኛ ተከሳሽ ጋር እንዲከላከሉ ተብለዋል፡፡

Tuesday, August 18, 2015

አብርሃም ጌጡ በማዕከላዊ

Legese Weldehana's photo.
የመላው ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ( መኢአድ) የውጭ ግንኙነት ሀላፊ አብርሃም ጌጡ ሰኔ 12 /2007 ልደታ ፓሊስ መምሪያ ታሰረ ብዙም ሳይቆይ ወደ 5ኛ ፓሊስ ጣቢያ ተዛወረ ልደታ ፍርድ ቤት ሚያዝያ 13/2007 ዓም የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ወጣቶችን አደራጅተህ ሚያዝያ 14/2007 ዓም መንግስት የጠራውን ሠልፍ እንዲረበሽ አድርገሃል የሚል ክስ ቀረበበት ጊዜ ቀጠሮ ላይ እያለ ሳይቋጭ ሰኔ 25/2007 ዓም ወደ አዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን (3ኛ) ተወስዶ ታሰረ አ.አ ፓሊስ ኮሚሽን (3ኛ) ድብደባ እንደተፈፀመበት ነግሮናል አራዳ ፍርድ ቤት እያቀረቡ ጊዜ ቀጠሮ እየጠየቀበት ነበር ሀምሌ 17/2007 ዓም አራዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እንዲቀርብ ተወስኖ እያለ የቀጠሮው ቀን ከመድረሱ በፊት ክሱን አቋርጠው ሀምሌ 15/2007 ወደ ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ተወስዶ እየተሠቃየ ይገኛል
አብርሃም በማዕከላዊ የደረሠበት ግፍ
ከሀምሌ 15 ጀምሮ ከባድ ድብደባ ተፈጽሞበታል በነሱ አጠራር 84/3 (ሣይቤሪያ) ተብሎ በሚጠራው ቀዝቃዛ ክፍል ውስጥ ይገኛል ከሀምሌ15 – 19 /2007 ዓም ጀምሮ በተፈፀመበት ከባድ ድብደባ ለ 3 ቀን እራሱን ስቶ እንደነበረ በእስረኞች ድጋፍ እና እንክብካቤ ማገገም ችሏል እንደገና ቆሞ መራመድ ሲጀምር ተጠርቶ እየተወሰደ በድብደባ ብዛት እራሱን በሸክም አምጥተው ጥለውት እንደሚሄዱ ታውቇል
ለ3 ቀን ያክል እህል ውሃ እንዳልቀመሠ እና
በድብደባ ብዛት የሱ ያልሆነ ቃል እራሳቸው ያዘጋጁት
ላይ እንዳስፈረሙትም ተውቇል
በድብደባ ወቅት አፀያፊ ስድብ ይሰድቡት እንደነበረ ተረጋግጧል
በምርመራ ወቅ ት የሚከተሉትን ጥያቄ እየተጠየቀ ተደብድቧል
፠ ትግሬን ትጠላለህ
፠ በትግሬ መገዛት የለብንም ብለህ ትቀሰቅሳለህ
፠ ወጣቶችን ታደራጃለህ የመሣሰሉትን እየተጠየቀ ተደብድቧል
በድብደባ ብዛት በርካታ የሠውነት ክፍሎቹ ተጎድተዋል
ለምሳሌ
፠የግራ ጆሮው አይሰማም
፠ የእጁ 3 ጣቶች አይሰሩም
ተሸካሚውን ሲያገኝ ግፍ ይበረታል ።

እነ ፕሮ/ር ብርሃኑ ከኤርትራ በረሃ መልዕክት አስተላለፉ –


_በፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና በምክትላቸው በአርበኛ መዓዛው ጌጡ የተመራው የአርበኞች ግንቦት ሰባት አመራር በኤርትራ በረሃ በተለያዩ የጦር ካምፖች የሚገኙትን የነጻነት ታጋዮችን ጎበኘ። አቶ ነዓምን ዘለቀና አቶ ኤፍሬም ማዴቦም ተገኝተዋል። ታጋዮቹ ደስታቸውን ገልጸዋል፡፡ ከአመራሮቹም ጋር ተወያይተዋል።

አንድ የወያኔ አባል 5 ሚሊዮን የእንግሊዝ ፓውንድ የሚገመት ጥሬ ገንዘብና ወርቅ በሻንጣው ይዞ ወደ ለንደን ሲገባ ተያዘ

ወደ 150 ሚሊዮን የሚጠጋ ብር በሻንጣ ጠርቆ ለንደን የገባ የሀገራችን ዘራፊ የወያኔ ባልደረባ በእንግሊዝ ፖሊሶች ክትትል እጅ ከፈጅ ተያዘ።ከፍርድ ቤት ጋር በተያያዘ ለጊዜው ስሙ እንዳይገለጽ የጠየቁ ምንጮች እንደገለጹት ፣ አንድ የህወሃት አባል 5 ሚሊዮን የእንግሊዝ ፓውንድ የሚገመት ጥሬ ገንዘብና ወርቅ በሻንጣው ይዞ ወደ ለንደን ሲገባ ጋትዊክ አየር ማረፊያ ላይ በፖሊሶች ተይዟል። ግለሰቡ ፍርድ ቤት ቀርቦአል።
ዳኛው ” ይህን ያክል ገንዘብ እንዴት በሻንጣ ልትይዝ ቻልክ የሚል ጥያቄ ሲያቀርቡ ፣ ግለሰቡ ” ገንዘቡ የመንግስት መሆኑንና ለመንግስት ስራ ለማዋል መያዙን” ገልጻል። ይሁን እንጅ ዳኛው ” ይህን ያክል ገንዘብ በሻንጣህ የያዝከው በአገራችሁ ባንክ ስለሌለ ነው እንዴ? ” በማለት ጥያቄ አቅርበዋል። ግለሰቡ በዋስ የተፈታ ሲሆን፣ መስከረም ላይ በድጋሜ ይቀርባል።
ኢሳት ዜና

Thursday, August 13, 2015

አርበኞች ግንቦት 7 – አለቃዎ ሳይሆን ቅን ህሊናዎ የሚያዝዎትን በመፈፀም መልካም ዜጋ ይሁኑ

መልካም ዜጋ ማለት ምን ማለት ነው?

Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracyይህን ጥያቄ ለመመለስ በርካታ መጻሕፍት መፃፍ ይቻላል፤ መሠረተ ሀሳቡን ግን በጥቂት ዓረፍተ ነገሮች ማቅረብ ይቻላል።
መልካም ዜጋ ኢፍትሃዊ ተግባር ሲፈፀም “እኔ ምናገባኝ?” አይልም። መልካም ዜጋ “ያባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ”፤ “እኔ ከሞትኩ ሰርዶም አይብቀል”፤ “እያለህ ካልሆነ ከሌለህ የለህም” እና በርካታ መሰል ምሳሌዎችን አይሰማም። መልካም ዜጋ በማናቸውም ሁኔታ ውስጥ ቢሆን ከነፃና ቅን ህሊናው ጋር ታርቆ ይኖራል።
የህወሓት አገዛዝ፣ መልካም ዜጋ ማለት የመንግሥት ሥልጣን የያዘን ማንኛውም አካል ማክበርና በታማኝነት ማገልገል ተደርጎ እንዲተረጎምለት ይሻል። ፍትህ የሚያዛባ መንግሥትን መቃወም የመልካም ዜጋ አቢይ ተግባር መሆኑ የዘመናችን ወጣት እንዳይገነዘብ ያደርጋል። በተለይ ባለሙያዎች የሚያገለግሉትን አገዛዝ ባህርይ እግምት ውስጥ ሳያስገቡ የተቀጠሩበትን ሥርዓት በታማኝነት ማገልገል የዜግነት ግዴታቸው አድርገው እንዲወስዱት ይወተውታል።

የኤልያስ ገብሩ ቆይታ ከጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጋር (ዝዋይ እስር ቤት)

በኤልያስ ገብሩ
  • ታገሉ! ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ (ከዝዋይ እስር ቤት)
  • ተመስገን ደሳለኝ ስለሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ፍርድም ሀሳቡን ሰንዝሯል
Temesgen Desalegn Fteh newspaper editor
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ
ቦሌ አካባቢ ብርዱ ጠንከር ያለ ነበር፡፡ ከቦሌ ብራስ ወደሚሊኒየም አዳራሽ በሚወስደው ቀጭን መንገድ ላይ ወንዱም ሴቱም በፍጥነት ይራመዳል፡፡ ከታክሲ በሁለቱም አቅጣጫዎች የወረዱ ሰዎች ወደመደበኛ ሥራቸው ለመግባት ብሎም የግል ጉዳያቸውን ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ ነበር – ከትናንት በስትያ ሰኞ (ነሐሴ 04 ቀን 2007 ዓ.ም) ጥዋት 1፡45 ሰዓት፡፡
እኔ እና ወዳጄ አቤል ዓለማየሁ ወደከአዲስ አበባ 160 ኪሎ ሜትር ርቀት ወደሚገኘው ዝዋይ እስር ቤት አምርተን ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬን እና ተመስገን ደሳለኝን ለመጠየቅ በዚህ ቀን ቀጠሮ ይዘን ነበር፡፡ አቤል ከቀጠሯችን 20 ደቂቃ ዘግይቶ፣ ቦሌ ጫፍ ደረሰና ወደቃሊቲ መናሃሪያ ሁለት ታክሲዎችን በመጠቀም ደረስን፡፡ ወደዝዋይ የሚጭኑ ሚኒባስ ታክሲዎች እና ‹‹አባዱላ/ዶልፊን›› የሚል መጠሪያ የተቸራቸው የህዝብ ማመላለሻ መኪኖች ቢኖሩም በተለምዶ ‹‹ቅጥቅጥ›› የሚባለውን መካከለኛ አውቶቡስ ምርጫችን አደረግን – የትራፊክ አደጋን በመስጋት፡፡

Wednesday, August 12, 2015

የኦሮሞ ዲያስፖራ አባላት የመንግስት ባለስልጣናትን በጥያቄ አጨናነቁ

ስብሰባው ከአርባ ሰባት ሃገራት የተሰባሰቡ የኦሮሞ የዲያስፖራ አባላትን የአርባ ሰባቱ ሃገሮች ዲፕሎማቶች በተገኙበት ተካሂዷል ።
መንግስት የኦሮሞ ዲያስፖራ ሳምንት ብሎ የሰየመውን ሳምንት በማስመልከት: ከመላው አለም ያሰባሰባቸውን የኦሮሚያ ዲያስፖራ አባላት: በሚሊኒየም አዳራሽ ጠቅላይ ሚስትሩ በተገኙበት ደማቅ የአቀባበል ስነ ስርዓት ካደረገላቸውና : ለሶስት ቀናት ያክል ሃገሪቷን ካስጎበኛቸው በኃላ : በአዳማ ገልማ አባገዳ አዳራሽ በመሰብሰብ : የተለመደ ፕሮፓጋንዳውን ለመንዛት ቢሞክርም: ከኦሮሚያ የዲያስፖራ አባላት ፍፁም ያልጠበቀው :የጥያቄ ውርጅብኝ ዘንቦበታል ።

ታሪክ የማይረሳው የኮሚቴዎቹ ስቅየት

ከማዕከላዊ እስከ ቂሊንጦ

muslim leaders
የኢትዮጵያን ቀጣይ እጣ ፈንታ አጨልመን እንድናይ ከሚያስገድዱን ሁነቶች ውስጥ ለእስልምና ሃይማኖት የትኞችም አይነት ጥያቄዎች በአገዛዙ በኩል እየተሰጡ ያሉ አሉታዊ ምላሾች አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ በኢትዮጵያ ሙስሊሞች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ ሐምሌ 27/2007 ዓ/ም የተላለፈው “የፍርድ ውሳኔ” ኢሕአዴግ የሚል ገዥ መደብ እስልምናን በምን ያህል መጠን አፍኖ እየገዛ እንዳለ የአደባባይ ማስረጃ ሆኖ ቀርቧል፡፡ በኮሚቴው አባላት ላይ የተላለፈውን “የፍርድ ውሳኔ” ከሃይማኖታዊ መነጸር ባሻገር ጉዳዩን ከፍትህና ከሞራል ልዕልና አኳያ ማየት ተገቢ ነው፡፡ የዚህ አጀንዳ ቀዳሚ ጉዳይ የኮሚቴውን አመሰራረት በማስታወስ የፍርድ ሂደቱን በመጠኑም ቢሆን በመቃኘት የኮሚቴ አባላቱ ቀጣይ እጣ ፈንታ በተመለከተ ሦስት የሚሆን እድል (Scenarios) በማስቀመጥ ማሳየት ይሆናል፡፡

የአብዮቱ አይቀሬነትና ጥቁምታዎቹ!


revolution
በፖለቲካ ሳይንስ መዝገበ ቃላት ውስጥ “አብዮት” የሚለው ቃል “አዲስ ሥርዓትን በመሻት የነባሩን መንግስታዊ ወይም ማህበራዊ ሥርአት በግዳጅ ማስወገድ” በሚል የትርጉም ማዕቀፍ ላይ ሊያርፍ ይችላል፡፡ ‹የሰው ልጅ አብልጦ የሚሻው የተሻለ የፖለቲካ ሥርዓት በየአገራቱ አስካልተመሰረተ ድረስ አብዮት በየትኛውም የዓለም ክፍል አይቀሬ ክስተት› እንደሆነ የፖለቲካ ሳይንስ መምህራኑ አብዝተው ያስተምራሉ፡፡

ለኢትዮጵያዊውስ ማን አለው?

በያሬድ ታዬ መኮንን፤ ቶሮንቶ
ቶሮንቶ ከመጣሁ ሶስተኛ ሳምንቴን ያዝኩኝ፡፡ ቀኑን ሙሉ፤ ከሰሜን ደቡብ፤ ከምስራቅ ምእራብ ሳካልለው ውዬ፤ መጀመሪያ በጓደኛዬ ቤት፤ አሁን ደግሞ መንግስት በሰጠኝ፤ በቶሮንቶ፤ ኦንቴርዮ ጎዳና ላይ በሚገኘውና እኔና ሌላ አንድ ሰው በምንጋራው ክፍል ጣሪያ ስር ሆኜ፤ ወደጣሪያው አንጋጥጬ፤ የኢትዮጵያና የካናዳ ህይወቴን፤ እንዲሁም ነጻነቴን ማሰላሰል ይዣለሁ፡፡ ነጻነት እንዴት ይጥማል፡፡ ድህነት አንድ ነገር ነው፡፡ መራብም አንድ ነገር ነው፡፡ ሰው ግን ነጻነቱንና ክብሩን እንዴት ባገሩ ይነፈጋል፡፡ እነሆ በማያውቁን፤ በማላውቃቸው፤ በሰው አገር የተሰጠኝን ክብርና እንክብካቤ እያጣጣምኩ ሳለሁ፤ የሩቅ ጓደኛዬ የነገረኝ ታሪክ ትዝ አለኝ፡፡ ይህ የሩቅ ጓደኛዬ አውነተኛ ታሪክ ነው ብሎ ያጫወተኝን፤ እኔም የተቀበልኩትን ገጠመኝ ላጫውታችሁ፡፡
እውነት መሆኑን እንዴት ተቀበልከው፤ ያላችሁኝ እንደሆነ ኢትዮጵያ ሃገሬ ውስጥ እንኳን ይሄ ይቅርና፤ ወያኔ “ተቃዋሚዎችም መርጠውኛል” ብሎን ተቀብለነው የለም እንዴ? መቼ ነው ያለው፤ ለምትሉኝ ደግሞ አሁን ባሳለፍነው ምርጫ 2007፤ በአይኔ ያየሁት፤ ምናልባትም ብዙዎቻችሁ በሶሻል ሜዲያ ያነበባችሁ፤ እና ያሰገረማችሁ የምርጫ ውጤት እንደሚያሳየው፤ በአንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች፤ ከ1000 መራጮች መካከል ኢህአዴግ፤ 1000 ከ1000 ተብሎ በምርጫው ጣቢያ ሲለጠፍ፤ አስቡት እንግዲህ፤ ይህ 1000 መራጭ የተቃዋሚ ተመራጭ ተወዳዳሪዎችን ጨምሮ መሆኑን፡፡ እንግዲህ ይህንንም አምነን “አሜን” ብለን ተቀብለን የለም ወይ? እንግዲህ የጓደኛዬንም የህይወት ገጠመኝ አምኜዋለሁ፡፡

Sunday, August 9, 2015

የሰሞኑ ሙዚቃ ጆሮም ኣያነቃ – እኔ ያልለወስኩት ቡኮ እንጀራ ሳይሆን ቂጣ ሆኖ ይቀራል?

ብርሃኑ ተስፋዬ
ኣሁንስ በየቀኑ የምሰማው ሙዚቃ ቃናው ይለያይ እንጅ እስክስታው ተመሳሳይ መሆኑ ኣግራሞቴን ይስበዋል። ኣንዳንዴ ራሱ ይረጋል የሚል ህሳቤ ብልጭ ቢልብኝም ኣንዳንዴ ሳስበው ደግሞ ሙዚቀኞቹ ሃይ ሊባሉና የሚሰሩትን የማያውቁ መሆናቸው መናገር ግድ ይሆናል። ይህ የሚሆንበትም ምክንያት ኣስበውትም ሆነ ሳያስቡት እየመቱት ያለው ቅላጼ፣ የከበሮው ድምጽ፣ የእስክስታ መቺዎቹ ኣዘላለል ህብረ ብሄራዊ ሳይሆን ለድርጎ ኣዳሪዎች ወያኔ ሰራሾች ኣቀንቃኝ የተደረሰ ድርሰት ላይ መሰረት ማድረጋቸው ነው።Patriotic Ginbot 7 freedom fighters continue attacking TPLF
ለመነሻ የሚሆን ስንቅ
ለረጂም ጊዚያት በዲኣስፖራው የሚነገር ኣንድ ኣባባል ነበር። ወይ ተባበሩ ኣልያም ተሰባበሩ ። ይህ ማለት ግን ውሃና ዘይት ለመቀላቀል የታሰበ ኣልነበረም። ይህ ባለመሆኑም በተለይ ሃይላቸውን ኣስተባብረው በነፍጥ የሚታገሉት ስብስቦች ይህንን ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት የበኩላቸውን በማድረግ ላይ ይገኛሉ። ይህም ይበል የሚባል እንጅ ኣዶ ከብሬ የሚያስነሳ መሆን ኣልነበረበትም።

እየተቃወሙ ለመኖር…!

ይገረም አለሙ
የአርበኞች ግንቦት 7 ቃልን ወደ ተግባር የማሸጋገር እንቅስቅሴ ያሸበረው ወያኔን ብቻ አለመሆኑን ከተቃውሞው ጎራ ከሚሰማው የተቀዋሚ ተቀዋሚዎች ጩኸት እያየን ነው፡፡ ርጥቡ ሬሳ ደረቅ ያስነሳ አንዲሉ ይህ ሰሞነኛ ጩኸት የተረሳ እንዲታወስ የተተወ እንዲቀሰቀስ ምክንያት ሆኖ የአንዳንዶቹ ጯሂዎች የትናንት ማንነት ድብቅ ዓላማና ፍላጎት ጭምር ጸሀይ እንዲሞቀው እየተደረገ ነው፡፡ የማለባባስ አጉል ባህላችንን ተራምደው የይሉኝታ ገመዳችንን በጥሰው ስም እየጠቀሱ መረጃና ማስረጃ እያጠቀሱ አካፋን አካፋ ለማለት ለደፈሩ ወገኖቼ ያለኝን አክብሮት እገልጻለሁ፡፡ እያለባበስን አርባ አመት አልቅሰናልና በቃ ማለት ይኖርብናል፡፡The Patriotic Ginbot 7 attacks factors
አደባባይ ወጥተው የሚጮኹትም ሆኑ ከኋላ ሆነው የሚገፉት የየግል ፍላጎታቸውም ሆነ አንድ የሚያደርጋቸው ምክንያት ምንነትና አንዴትነት በተለያዩ ሰዎች ተጽፋል፡፡ እውነት ናቸውና መስማማቴን እየገለጽሁ ያልተገለጸ የመሰለኝን ልጨምር፡
ስማቸው ብዙ ነው (ፖለቲከኛ ፣ጋዜጠኛ፣ነጻ ማህበር፣ወዘተ) መገኛቸው ሀገር ውስጥም ውጪም ነው፤ዓላማቸው ቢችሉ ምን-ይልክ ቤተ መንግሥት መታየት ካልሆነም በተቀዋሚነት ካባ አንድም ክብር ሁለትም ብር እያገኙ መኖር ነው፡፡ ተባብሮ መስራት አይሆንላቸውም፡ እነርሱ የሚመሩት ወይንም በቀጥታም ሆነ በተዘዋወዋሪ የሚቆጣጠሩት ካልሆነ በስተቀር ማናቸውም ትግል (ሰላማዊውም የጠብ-መንጃውም) አንድ ርምጃ ሲራመድ ማየት አይፈልጉም፡፡

Friday, August 7, 2015

የፕሬዚዳንት ኦባማ የአፍሪካ ኅብረት ንግግርና እንደምታው


def-thumbየዩ ኤስ አሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ሐምሌ 21 ቀን 2007 ዓም አዲስ አበባ ውስጥ በአፍሪካ ኅብረት ጽ/ቤት ያደረጉት ንግግር በርካታ ቁምነገሮችን የያዘ በመሆኑ አንጽዖት ሊሰጠው እንደሚገባ አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ያምናል።
ፕሬዚዳንቱ በዚህ ንግግራቸው የአፍሪቃን በተለይም ደግሞ የአገራችንን ችግሮች ነቅሰው አሳይተዋል። ሰብዓዊ መብቶች ሰው በመሆናችን ያገኘናቸው በመሆኑ በቆዳችን ቀለም፣ በተወለድንበት አካባቢ፣ በምንናገረው ቋንቋ ወይም በሌላ ማናቸውም ምክንያቶች ሊሸራረፉ የማይገቡ መሆኑን በመግለጽ “ሁላችንም እኩል ተወልደናል” በማለት ዘረኞችን አፍ የሚያዘጋ ኃይለቃል ተናግረዋል። “ሁላችንም ከአንድ ግንድ የበቀልን ነን፤ ሁላችንም አንድ ቤተሰብ ነን፤ ሁላችንም አንድ ጎሳ ነን” ካሉ በኋላ በዓለም ያለው አብዛኛው ችግር ይህንን መረዳት አለመቻላችን፤ ራሳችንን በእያንዳንዳችን ውስጥ ማየት አለመቻላችን ነው ብለዋል።

ውድ ቴዲ አድሃኖም – ውሸትም ክብር አለው (ከስንሻው ተገኘ)

ከስንሻው ተገኘ
Ethiopian foreign ministerበምገኝበት አገር አብሮኝ የሚሰራ አፍሪካን-አሜሪካን ወዳጅ አፍርቻለሁ። ስለ ኢትዮጵያ አንዳንድ የታሪክ ግንዛቤዎች እንዲኖሩት ጉጉት ስላለው ደስ እያለኝ ከማውቃት አካፍለዋለሁ። አንዳንድ ጊዜ ግን የምደነግጠው እኔ ከማውቀው በላይ እየሄደ ስለ ኢትዮጵያ አዳዲስ ነገር፣ “ይቅርታ ምጥ ለእናቷ አስተማረች እንዳይሆንብኝ…” ይልና አዳዲስ ክስተቶችን ይነግረኛል። የትናንቱ ጥያቄው ደግሞ ልዩ ነበር። ይኸው ማይክል የምለው ጓደኛዬ “የኢትዮጵያ Gestapo ምን ስም አለው?” ብሎ አፋጠጠኝ። (በነገራችን ላይ ጌስታፖ ትልቁ የሂትለር የአፈናና የግድያ ተቋም ነበር። ይህ ከ 32,000 ሰራተኞች በላይ የነበሩት የስለላ ተቋምና ለአርያን ዝርያ ጠላት ናቸው የተባሉትን አይሁዶች፣ ኮሙኒስቶችና፣ የናዚ ፍልስፍና የሚቃወሙትን ሁሉ በስልት የሚያስወግድ ድርጅት በራሱ ጠንካራ ውስጣዊ መንግስት ነበር።)

Thursday, August 6, 2015

ሰማያዊ ፓርቲ – የሀይማኖት መብታችን የሚከበረው በነፃነት ትግል ነው!

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ
Semayawi party to welcome Andinet membersኢህአዴግ ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ ለስልጣን ለሚያሰጋው ድርጅትና ተቋም ለራሱ ስልጣን የሚበጀውን ሌላ ድርጅትና ተቋም በመፍጠር እንዲሁም ኢትዮጵያውያንን በቋንቋ ልዩነት ከፋፍሎ ሲገዛ ቆይቷል፡፡ ለመምህራን ማህበር ለመምህራን ሳይሆን ለእሱ የሚመች ማህበር፣ ለፖለቲካ ድርጅቶች ለህዝብ የሚቆም ሳይሆን ለአገዛዙ መሳሪያ የሚሆን ድርጅት፣ ለሰብአዊ መብት ድርጅቶችም እንዲሁ ለኢትዮጵያውያን የሚቆሙ ሳይሆን ከእሱ ጋር የሚወግኑ ድርጅቶችን በማቋቋም እውነትና ከእውነተኞችን ሲታገል ኖሯል፡፡ ከዚህም አልፎ አሁን በሀይማኖት ውስጥ ለእሱ የሚመች ሌላ ሀይማኖት በመቋቋም ላይ ነው፡፡

Wednesday, August 5, 2015

በሳውዲ “ድምጻችን ይሰማ” ላይ የተቃጣው ሴራ ከሸፈ


riyadh KSA

ሳውዲ ኢትዮጵያውያን ሙስሊም የትግል አንድነት ላይ የተቃጣው የህወሃት/ኢህአዴግ ሴራ መክሸፉ ተሰማ! ከዕርዳታ አሰባሰብ ጋርም በተያያዘ የተፈጸመው ተግባር ለሕዝብ ይፋ ሆኗል፡፡

የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ለ3ኛ ጊዜ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አላቀረበም

“ቤተሰቦቼ አሸባሪ ተብለው ቤት የሚያከራያቸው አጥተዋል፤ ልጆቼ በረንዳ ላይ ወድቀዋል፤ ቤተሰባችን ተበትኗል” ም/ኢንስፔክተር ሙልዬ ማናዬ ረታ (7ኛ ተከሳሽ)
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በዘመነ ካሴ የክስ መዝገብ ከ2ኛ እስከ 5ኛ ለተከሰሱት አቶ አሸናፊ አካሉ (2ኛ ተከሳሽ)፣ አቶ ደናሁን ቤዛ (3ኛ ተከሳሽ)፣ አቶ ምንዳዬ ጥላሁን (4ኛ ተከሳሽ) እና አቶ አንሙት የኔዋስ (5ኛ ተከሳሽ) ዋስ እንዲሆኑ ለዛሬ ሀምሌ 29/2007 ዓ.ም ፍርድ ቤት እንዲያቀርብ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ የደረሰው የቃሊቲ ማረሚያ ቤት አቶ አንዳርጋቸውን ሳያቀርብ ቀርቷል፡፡Ato Andargachew Tsige, Ginbot 7
ተከሳሾቹ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡላቸው የጠየቁት የፌደራል አቃቤ ህግ ‹‹ከአንዳርጋቸው ፅጌና ፋሲል የኔዓለም እንዲሁም ከሌሎቹ የአሸባሪው ድርጅት አመራሮች ጋር በአካልና በሌሎች የመገናኛ ዘዴዎች በመገናኘት ስለ ሽብር ተግባሩ አፈፃፀም በመግባባት፣ ኤርትራ ወደሚገኘው የግንቦት ሰባት ካምፕ ሄደው ስልጠና በመውሰድ፣ ተልዕኮ ተቀብሎ ወደ ሀገር ውስት በመመለስ፣ ….›› የሚል ክስ ስለመሰረተባቸው ነው፡፡

ሁለቱ ትግሎች፤ አንዳርጋቸው ጽጌ፤ የዶክተር ቴዎድሮስ አድሀኖም የማስቀየስ ስልት

እርቀ ሰላም (ከደቡብ አፍሪቃ )
ብርሁኑ ነጋ ዱር ገባ!
አንዳርጋቸው ጽጌ መፅሀፈ ሰ ጨረሰ!
ኦባማ በዴሞክራሲያዊ መንገድ መመረጣችንን አውቅና ሰጠ!
እነዚህ እንግዲህ የሰሞኑ ፖለቲካዎች ናቸው።
ያለወትሮዋቸው በአሜሪካ ድምፅ ላይ ለቃለመጠይቀ የቀረቡት ዶ/ር ቴዎድሮስ አድኅኖም ያልበላቸውን ሲያኩ ተደምጠዋል። አድማጭ ልብ ሊሊው የሚገባ ጉዳይ አለ። ዶፍተሩ ስለ ብርሀኑ ነጋም ሆነ ስለ አንዳርጋቸው ጽጌ የተናገሩት ሳይጠየቁ ነበር ይኼ እንግዲህ “ማርያምን … ምን የበላ ..” እንዲሚባለው ነው።Tedros Adhanom interview
ሲጀመር ዶፍተሩ ቪኦኤ ላይ የቀረቡት ስለ ኦባማ መምጣትና መሄድ ላይ አስተያየት ይሰጡ ዘንድ ነበር። ማርሻቸውን ቀየሩት!
የተጠየቁት “ከአንበሳና ነብር ማን ያሸንፋል?” ተብለው ሲሆን፣ የእርሳቸው መልስ ግን
“ዝሆንን ማን አህሎት!” እንደሚባለው ፈሩን የለቀቀ ምላሽ ሰጥተዋል። የዚህ ጽሁፍ አቅራቢ ወያኔ ሸገር ሰተት ብሎ ሲገባ ግፋ ቢል የአምስት አመት ልጅ ነበርኩ፤ ሀያአራት አመት ግን የወያኔ ባህሪ ለመረዳት እጅግ በጣም ብዙ ነውና ይህንን መሳት አይኖርብንም የሚል ሀሳብ አለኝ።

Tuesday, August 4, 2015

ቴድሮስ አድሃኖም “ኢህአዴግ ቂመኛ አይደለም” አሉ

አማርኛ ተናጋሪዎች ላይ በቂም ስለሚፈጸው ወንጀል አልተጠየቁም

tedros a voa


የኢህአዴግ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቴድሮስ አድሃኖም “ኢህአዴግ ቂመኛ አይደለም” ሲሉ ከቪኦኤ አማርኛው ክፍል ባልደረባ ትዝታ በላቸው ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ አስታወቁ። ሚኒስትሩ ድርጅታቸውን ከደርግ ጋር በማነጻጸር ከቂም የጸዳ እንደሆነ ሲያስረዱ ጋዜጠኛዋ አማርኛ ተናጋሪዎች ላይ በቂም በቀል ስለተፈጸመውና እየተፈጸመ ስላለው ግፍ ጥያቄ አላቀረበችም። ሚኒስትሩ ኢህአዴግ በህግ የበላይነት ስለማመኑ በመረጃ አልተሞገቱም

Monday, August 3, 2015

በአፍሪካ ገንዘብ የሚሰባሰበው ኋላቀርነትን ለማራመድ ነው እንዴ?

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
የምዕራቡ ዓለም አፍሪካን እንዴት ኋላቀር እንዳደረጋት እና በአሁኑ ጊዜ ገንዘብ ለማሰባሰብ እያደረገ ያለው ጥረት፣
ባለፈው ሳምንት “ገንዘብ ለልማት 3ኛው ዓለም አቀፍ ጉባኤ” በሚል ርዕስ በኢዲስ አበባ ዓለም አቀፋዊ ጉባኤ ተካሂዶ ነበር፡፡ በዚህ ጉባኤ ላይ በከፍተኛ የኃላፊነት ደረጃ ላይ የሚገኙ የፖለቲካ ተወካዮች፣ ርዕሳነ ብሄሮች እና መንግስታት፣ የገንዘብ ሚኒስትሮች፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና የልማት አጋሮች፣ የንግድ ዘርፉ እንዲሁም ሌሎች ከጉባኤው ጋር አግባብነት ያላቸው ተቋማት፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና የንግድ ዘርፉ ተወካዮች የተሳተፉበት ጉባኤ ተካሂዶ ነበር፡፡Financing for (Under)development in Africa?
ጉባኤው የተካሄደበት ዋናው ዓላማ “በዶሃ መግለጫ መሰረት ተደርሶበት የነበረውን የገንዘብ ስምምነት አፈጻጸም ለመገምገም እና እ.ኤ.አ ከ2015 በኋላ በመንግስታት መካከል ለልማት የሚውል ገንዘብ የማሰባሰብ አጀንዳ በማቅረብ እና ይህንኑ ስምምነት በማጽደቅ ጠቃሚ የሆነ ገንዘብ ማሰባሰብ“ የሚል ነበር፡፡

የናትናኤል ፈለቀ ማስታወሻ – ጥቂት ስለ ማዕከላዊ (ከቂሊንጦ እስር ቤት)

ናትናኤል ፈለቀ (ከቂሊንጦ እስር ቤት) – ምንጭ ዞን9 ፌስቡክ ገጽ
An economist by training and a human right activist by interest.
ናትናኤል ፈለቀ
ይህንን ጽሁፍ ስጽፍ ዓላማዬ ማዕከላዊ ያሉ ሥራቸውን አክብረው የኢትዮጵያውያንን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ የሚሰሩ ጥቂት ፖሊሶችን (ምናልባትም በአንድ እጅ ጣቶች ተቆጥረው የሚያልቁ መርማሪዎችን) ለማበረታታት አይደለም፡፡ ይህን ዓላማ በሌላ ጽሁፍ እመለስበት ይሆናል፡፡ ለነገሩ ሥራቸውን አክብረው የሚሰሩ ባለሙያ ፖሊሶች የኔ ማበረታታትን የሚፈልጉ አይደሉም፡፡ ያሉበት ደረጃ ላይ ለመድረስ በኃላፊነት ማሰብ የቻሉ ስለሆኑ፡፡
ስለዚህ የዚህ ጽሁፍ ዓላማ በተቋሙ ውስጥ ኢትዮጵያ የምትተዳደርባቸውን ሕጎች ለማክበር (የተላለፉትን ለይቶ ለማስቀመጥና በስህተት የተጠረጠሩትን ነጻ ለማውጣት) ሳይሆን የአገዛዙን ዕድሜ ለማርዘም የሚሰሩትን አብዛኞቹን ሙያቸውን የማያከብሩ ፖሊሶች ‹‹ምርመራ›› ሴራቸውን እንዴት እንደሚፈትሉ ለማሳየት፣ ቢያንስ ሌላ ስልት እስኪፈጥሩ ድረስ በሀገሪቷ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ ኢትዮጵያውያን አንዴ በተቋሙ ውስጥ ከገቡ በኋላ ሊገጥማቸው የሚችለውን የተንኮል መረብ ለማስረዳት እና ቀድሞ ለማዘጋጀት ያሰበ ነው፡፡