Translate

Thursday, August 20, 2015

አርበኞች ግንቦት 7 በዋሽንግተን ዲሲ፣ በዳላስ እና በሲያትል የተሳካ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሞችን አካሄደ


Patriotic Ginbot 7 success fundraising Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracyአርበኞች ግንቦት 7 ባለፈው ነሐሴ 10 2007 ዓ.ም በዋሽንግተን ዲሲ በሸራተን ሆተል ባካሄደው የተሳካ የገንዝብ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ቁጥሩ በርካታ ኢትዮጵያዊ መገኘቱን ለማወቅ ተችሏ።
ንቅናቄው በመላው አለም በማካሄድ ላይ ባለው ተመሳሳይ ፕሮግራም በአውስትራሊያ፣ በአውሮፓና በሰሜን አሜሪካ የተለያዩ ከተሞች በስደት ነዋሪ የሆነው ነጻነት ፈላጊ ኢትዮጵያዊ ዜጋ በነቂስ በመሳተፍ ለዲሞክራሲ የሚደረገውን ትግል በደጀንነት ለማገዝ ቁርጠኝነቱን እያሳየ ይገኛል።

በየክፍለ አህጉሩ በመደረግ ላይ ባለው ዝግጅት ወያኔ በብዙ ሚልዮን ዶላር ወጭ ከየመን አውሮጵላን ጣቢያ ጠልፎ የወሰዳቸው የቀድሞ ግንቦት 7 ንቅናቄ ዋና ጸሃፊ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌና በቅርቡ የውህድ ድርጅቱን ለመምራት ወደ ትግሉ ሜዳ ያመሩት የንቅናቄው ሊቀመንበር የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ምስሎች ለጨረታ እየቀረበ በውድ ዋጋ መሸጣቸው ታውቋል።
የወያኔ አገዛዝ በህዝባችን ላይ የጫነውን ግፍና መከራ በማስወገድ አገራችን ውስጥ ፍትህ እኩልነትና ነጻነት የሰፈነበት ዲሞክራሲ ሥርዓት ለመገንባት የተጀመረውን ትግል የሚያግዝ የገንዘብና የማቴሪያል ድጋፍ ዝግጅቶች በቀጣዩ ሳምንታት በሰሜን አሜካ፡በካናዳና በአውሮጳ ከተሞች እንደሚደረጉ እየተነገረ ነው።
አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን የሃይማኖት አባቶች፣ አርቲስቶች፣ የፖለቲካ አክቲቪስቶችና የሰብአዊ መብት ተቆርቋሪዎች ኢትዮጵያውያን በየዝግጅቶቹ ላይ በመገኘት ህዝቡን በማበረታታትና በማወያየት ከፍተኛ እገዛ እያደረጉ ይገኛሉ።

No comments:

Post a Comment