Translate

Saturday, March 25, 2017

በህወሃት የታፈነው ድርቅ ወደ ረሃብ እያደገ ነው፤ ት/ቤቶች ተዘግተዋል!

በህወሃት የታፈነው ድርቅ ወደ ረሃብ እያደገ ነው፤ ት/ቤቶች ተዘግተዋል!


  • የኢትዮጵያ ሶማሌ ዘጠኙም ዞኖች ሙሉ በሙሉ የድርቁ ሰለባ ሆነዋል!
  • በክልሉ 437 የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ከድርቁ ጋር በተያያዘ ተዘግተዋል፤
  • 183,090 ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቋርጠዋል!
  • የእርስበርስ ዕልቂት ያሰጋል!
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በሁለት ወራት ውስጥ ባወጣቸው ተከታታይ ሪፖርቶች ምስራቅ አፍሪካ የከፋ ድርቅ መከሰቱንና ዓለም የዕርዳታ እጆቹን ለአገራቱ እንዲዘረጋ በተከታታይ ሪፖርቶቹ ተማጽኗል፡፡ እንደ በዘገባው ከሆነ ድርቁ የከፋባቸው ተጠቃሽ አገራት ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኬንያና ኢትዮጵያ ናቸው፡፡

Tuesday, March 21, 2017

በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የአርበኞች ግንቦት 7 መግለጫ

መጋቢት 12 ቀን 2009 ዓ. ም.
ከመጋቢት ወር መጀመሪያ ጀምሮ የአርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሠራዊት አባላት በሰሜንና ደቡብ ጎንደር በህወሓት/ኢህአዴግ የአገዛዝ ሥርዓት ተቋማት ላይ የተቀናጀ የሽምቅ ጥቃት አድርሰዋል። በማክሰኝት፣ በደጎማ፣ በጯሂት፣ በደንቀዝን፣ በበለሳ፣ በአዲስ ወረዳ፣ በደንቢያ፣ አገዛዙ ቀይ ቀጠና ብሎ በሰየመው በመተማ መስመር በጭልጋ ወረዳ፤ በቆላድባ፣ አብራጂራ፣ በቸንከር ቀበሌ በአገዛዙ የፓሊስ ጣቢያዎችና የጦር ሠራዊት ካምፓች እንዲሁም ቀንደኛ የሥርዓቱ አገልጋዮች ላይ ድንገተኛ ጥቃት ሰንዝሯል፤ በሕዝብ ላይ በደል ሲፈጽሙና ሲያስፈጽሙ የነበሩ የሥርዓቱ ቀንደኛ አራማጆች ላይ የማያዳግም እርምጃ ወስዷል። ስለእነዚህ እርምጃዎች በወቅቱ መገናኛ ብዙሃን የዘገቡት ስለሆነ ዝርዝር ውስጥ መግባት አያሻም።Patriotic Ginbot 7
ይህ የፍፃሜው ጅማሮ ነው። አርበኞች ግንቦት 7 ህወሓት/ኢህአዴግን በማስወገድ ሕዝብ የፓለቲካ ስልጣን ባለቤት ለማድረግ በሚደረግ ትግል ውስጥ ራሱን ለመስዋዕትነት በግንባር ቀደምትነት አሰልፏል፤ የትግሉ ባለቤት ግን ሕዝቡ ራሱ ነው።
እስካሁን በጎንደር በተደረጉ ትግሎች የታየው የሕዝብ ንቁ ተሳትፎ አበረታች ነው። የጎንደር ሕዝብ ከአብራኩ የወጡትን የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮችን በመረጃ፣ በስንቅና በቀጥታ በውጊያ በመሳተፍ ረድቷል። ሲራቡ እያበላ፣ ሲቆስሉ እያስታመመ፣ መንገድ እየመራ ግዳጆቻቸውን በስኬት እንዲወጡ ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርጓል። በተለይ እሁድ መጋቢት 03 ቀን በጎንደር አጼ ፋሲለደስ ስታዲዮም የተገኘው ሕዝብ የአገዛዙን ዛቻ ሳይፈራ ለታጋይ አርበኛ ጎቤ መልኬ የህሊና ፀሎት ማድረጉ ለአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮች ትልቅ የሞራል ስንቅ ሆኗል። ሰሞኑን እየተወሰዱ ያሉትን ዓይነት የሕዝባዊ አመጽ እርምጃዎች ከጎንደር በተጨማሪ ወደ ሌሎችም የአገሪቱ ግዛቶች እንዲስፋፋ ማድረግ ይገባል።

Thursday, March 16, 2017

የቆሻሻ ፖለቲካ ተምሳሌት – ቆሼ!! “ድህነት ዋናው ጠላታችን ነው”



  • የግፍ ክምር ናዳው ምን ያህል የሚከፋ ይሆን?
አዲስ አበባ ቃላት የማይገልጹዋት፤ ስሟ ግብሯን የማይወክል የግፍ ከተማ ናት፡፡ በአንድ በኩል ሥጋ በል ለሆኑ የቤት እንሰሳዎቻቸው የዕለት ተዕለት ምግብ ከሱፐርማርኬት የታሸገ ሥጋ ገዝተው የሚመግቡ ባለጠጎች፤ በሚስታቸውና በልጆቻቸው እንዲሁም በደርዘን ውሽሞቻቸው ሥም የተንጣለሉ ቪላ ቤቶችንና ግዙፍ ህንፃዎችን የገነቡ የገዥው ኃይል ማኅበራዊ መሰረት የሆኑ የትግሪኛ ቋንቋ ተናጋሪ የከተማ ዘራፊዎች (Marauders’ city) “ወጋ ትበለይኪ” እያሉ የሚምነሸነሹባት፤ ደሃ-ገፊ መሐል አሟቂ፤ የቁስ ሰቀቀን የተጫናቸው የፖለቲካ-ኢኮኖሚ ዘዋሪ ልሒቃን ከተማ ናት፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የዕለት ምግባቸውን ከቆሻሻ ገንዳ የሚለቅሙ አንጀታቸው በረሃብ የታጠፈ ጐስቋላ ምንዱባን በጐዳና የሚኖሩባት፤ የወር ደመወዛቸውን ለአልቦ-አንጀት (ርህራሄ የለሽ!) አከራዮቻቸው እያስረከቡ ፓስቲ በልተው የረጋ ዘይት የሚያገሱ የኢኮኖሚ ምርኮኛ የመንግስትና የግል ሠራተኞች የሰቀቀን ሕይወት የሚገፉባት፤ ቆሻሻና ሰው ላይና ታች ሆኖ የሚኖርባት ጉራማይሌ ከተማ ናት – አዲስ አበባ!!

Tuesday, March 14, 2017

የኢትዮጵያ አገራዊ ንቅናቄ ጋዜጣዊ መግለጫ

የኢትዮጵያ አገራዊ ንቅናቄ

Sochii Biyyaa Itiyoophiyaa
 Ethiopian National Movement

 ዋሽንግተን ዲሲ – መጋቢት 13, 2017 

ለሃያ ስድስት አመታት የዘለቀው የህወሃት / ኢህአዴግ ጨቋኝ አገዛዝ በወገኖቻችን ላይ ያደረሰውና እያደረሰ ያለው ግፍና መከራ ቅጥ ያጣ መሆኑ ለሁላችንም ግልጽ ከሆነ ቆይቷል። ዕለት ተዕለት በወገኖቻቻን ላይ የሚደርሰው የማዋረድና የሰቃይ ገፈት በተለያየ መልኩ ለስርአቱ ታማኝ በሆኑ የጸጥታ የፖሊስና የሚሊሽያ ኃይሎች ይፈጸማል። ይህ ህዝብን ያለማቋረጥ የማሰቃየትና የመበደል ስራን ዋነኛ ሙያው ያደረገው ዘረኛ ስርአት በአደባባይ በጠራራ ጸሃይ ወገኖቻችንን በጥይት መቁላት አልበቃ ብሎት ዛሬ ደግሞ የሰርአቱ ግፈኞች ጠግበው በሚጥሉት የቆሻሻ ናዳ ህጻናት ሴቶች ወንዶች አዛውንትና ወጣቶች ለሞትና ለአካል ጉዳት እንዲዳረጉ እያደረገ ነው።
Ethiopian garbage dump landslide
 ወገኖቻቻን የሚልሱት የሚቀምሱት አጥተው በረሃብ ሰቆቃ በሚሰቃዩበት በዚህ ወቅት “ታላቅ የኢኮኖሚ እድገት”

Thursday, March 2, 2017

የታጋይ ጎቤ መልኬ ሞት፤ የነፃነታችን ኩራት! (ጎንደር ህብረት ለኢትዮጵያ አንድነት)

ጎንደር ህብረት ለኢትዮጵያ አንድነት
Ethiopian freedom fighter Patriot Melke Gobe

 ለመብትና ለነጻነት የሚደረግ ትግል ከፍተኛ ዋጋ እንደሚያስከፍል የተማርነው፤ የታሪክ ማህደሮችን በማገላበጥ አይደለም። ክቡር ህይወትን፤ ለሕዝብ እና ለአገር ነፃነት አሳልፎ መሥጠት ከቅድመ አያቶቻችን፤ ጀምሮ፤ በኩራት እየወረስን ዘመኑን ዋጀን እንጂ። ለዘለዓለም በባርነት ከመገዛት፤ ለአገርና ለወገን ነጻነት፤ ህወታቸውን ሰጥተው፤ በኩራት እኛም ነፃነታችንን ጠብቀን በመኖር ለቀጣዩ ትውልድ እንድናሥተላልፍ፤ የውጭ ወራሪን፤ የውሥጥ ባፍንዳን አይቀጡ ቅጣት እየቀጡ፤ አሁን ላይ አድርሰውናል።