Translate

Tuesday, September 29, 2015

አርባ‬ ምንጭ የነበረው የአሜሪካ መንግስት የመከላከያ ኃይል ቡድን አካባቢውን ለቆ እየወጣ ነው

‪አርባ‬ ምንጭ የነበረው የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ መንግስት የመከላከያ ኃይል ቡድን ከባለፈው ሳምንት ሐሙስ ጀምሮ አካባቢውን ለቆ እየወጣ እንደሆነ ታወቀ፡፡ ‪‎ህወሓት‬ በሁመራ የሚገኙ 40 የንግድ ቤቶችን ራሱ በስውር በእሳት አቃጥሎ በአካባቢው በሚንቀሳቀሱ የታጠቁ የነፃነት ድርጅቶች ለማላከክ እየሞከረ እንደሚገኝ ከውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን የተገኘው መረጃ አጋለጠ፡፡

Sunday, September 27, 2015

ነገረ – ኢሕአዴግ

ሥርዓቱ በሁለት ጫፍ የተሳለ አደጋ አፍጦበታል

eprdf two
በብዙ መልኩ ዴሞክራሲያዊ ገፅታን ያልተላበሰው ኢሕአዴግ ራሱን በገዥ መደብነት “አመቻችቶ” አስቀምጧል፡፡ ግንባሩ በቀደመው ዓመት አስረኛ ድርጅታዊ ጉባኤውን በዝግ በማካሄድ እንደተለመደው ባለ ዘጠኝ ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት አጠናቋል፡፡ በዚሁ ጉባኤ፣ ከዚህ ቀደም ከተካሄዱ ጉባኤዎች በተለይም በ1994 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ከተካሄደው አራተኛው የድርጅቱ ጉባኤ ጀምሮ ይነሱ የነበሩ አጀንዳዎች ቅርፃቸውን ብቻ በመቀየር ይዘታቸውን እንደጠበቁ እስከ አስረኛው ድርጅታዊ ጉባኤ ድረስ ዘልቀዋል፡፡

Saturday, September 26, 2015

አቶ ሬድዋን እወቀው (ሄኖክ የሺጥላ)

ሄኖክ የሺጥላ
ሶስት ነገሮች በጣም ሰልችተውኛል ። የአቶ ሬድዋን ሁሴን ዛቻ ፣ የሃይለማርያም ደሳለኝ ደደብነት እና የሰን-ፍራይስ እንጀራ ። ሁሉም መደምደሚያቸው ፈስ ስለሆነ ። የማያባራ ፈስ።
በቀደም አቶ ሃይለማርያም ፣ <<ቁንጮ ሁነህ አንተ ምራን ብለውኛል ብሎ>> ያለ ፕሮግራሜ ሲያስቀኝ ነበር ። ማለቴ መለስን << መላጣ ሁነህ አንተ ምራን >> ብለውት ነበር እንዴ ። ታዲያ በቶፓዝ ምላጭ መቆንጨት ነዋ ፣ ምን ማሳወቅ ያስፈልጋል ። ደሞ ቅጫም ለወረረው ጭንቅላት ቁንጮ መድሃኒት ነው።Redwan Hussein, head of Ethiopia's communication affairs office
ደሞ በቀደም ይሄ ሬዲዋን የተባለ አሽከር ሊያስፈራራን ሞከረ ። << ከአሜሪካ መንግስት ጋ አንድ ላይ ሁነን በመስራት ላይ ነን ፣ ይህ በአሜሪካን ሀገር የሚኖር አሸባሪው የግንቦት ሰባት ቡድን ፣ የአሜሪካ ዜግነቱን ይነጠቃል >> እና ወዘተ ። ላንቺ ቁም ነገርሽ በሶ ብላ ወጥሽ አሉ ። ቆይ ግን ሰውየው ግን እንዴት ነው የሚያስበው ? ለሱ ብርቅ የሆነበት ነገር ሁሉ ለኛም ብርቅ ይመስለዋል ማለት ነው ። ሬድዋን ሆይ ፣ወያኔን የምንታገለው የአሜሪካ ዜግነታችንን ለማስጠበቅ አስመሰልከው እኮ ። እንደው በሞቴ ፣ እኛ የባንዳ ልጆች ስላለመሆናችን ፣ እናም ከኢትዮጵያዊነት ሌላ ፣ ሌላው ብንለብሰውም እንደማይሞቀን እና እንደማያደምቀን አሁን ማን ይሙት ሳይገባህ ቀርቶ ነው በሰው ሀገር ዜግነት መነጠቅ እና መሰጠት እኛን ልታስፈራራ ስትል ትንሽ አታፍርም ? እንደው ትንሽ አይሰቀጥጥህም ። ለነገሩ ለምን ይሰቀጥጥሃል።

Friday, September 25, 2015

የተናገሩት ከሚጠፋ… (በኤፍሬም ማዴቦ – ከአርበኞች መንደር)

በኤፍሬም ማዴቦ
ባለፈዉ መጣጥፌ “ቃል የእምነት ዕዳ ነዉ” ብዬ ጀምሬ “ቃላችን አይለወጥ” ብዬ ነበር የተለየኋችሁ። አለምክንያት አልነበረም እንዲህ ያልኳችሁ፤ በአንድ በኩለ ቃል መከበርም መከፈልም ያለበት ዕዳ ስለሆነ በሌላ በኩል ደግሞ ቀትር ላይ የገባዉን ቃል ሳይመሽ እንደ ጴጥሮስ ሦስቴ የሚክድ ብዙ ቃላ አባይ ሰላለ ነዉ። አገሬን ከወያኔ አጸዳለሁ ብሎ ቃል የሚገባ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዕዳ አለበት። ዕዳዉ ደግሞ ገንዘብ ወይም ንብረት አይደለም። ቃሉን መጠበቅ ወይም ቃሉን ማክበር ነዉ።Ephrem Madebo with Patriotic Ginbot 7 fighters
ደግሞም አንድ ሰዉ የተናገርዉን ቃል ሰብሮ የእምነት ባለዕዳ ከሚሆን ዕድሜ ልኩን የገንዘብ ባለዕዳ ቢሆን ይሻለዋል። የገንዘብ ዕዳ ቆይቶም ቢሆን ይከፈላል ወይም አበዳሪዉ ሊምረን ይችላል፤ የዕምነት ዕዳ ግን የማይሽር ጠባሳዉ እየቆረቆረን አብሮን ይኖራል እንጂ አይጠፋም። ማንም ሰዉ ለአገሬ ህይወቴን እሰጣለሁ ብሎ ቃል ሲገባ መሃላዉ ከህዝብና ከአገር ጋር ብቻ አይደለም፤ እንዳዉም የሰዉ ልጅ ቃል የሚገባዉ መጀመሪያ ከራሱ ጋር ነዉ። ለራሱ የገባዉን ቃል የማያከብርና ቃሌ ቃል ነዉ ብሎ የገዛ ራሱን የእምነት ዕዳ ያልከፈለ ሰዉ ለህዝብና ለአገር ቃል መግባት አይችልም። ዛሬ ወያኔን እናጥፋ ብሎ ካራ ጨብጦ አብሮኝ የቆመ ሰዉ ነገ ከወያኔ ጋር ሆኖ ካራዉን እኔዉ ላይ አዙሮ ባየዉ እሱ ቀድሞዉንም ካራ የጨበጠዉ ወያኔን ለማጥፋት ሳይሆን ስጋ ሊቆርጥብት ነዉና ብዙ አይገርመኝም። እንዲህ አይነቱን ለቁም ነገር ሲፈልጉት አልሰማ ብሎ ሆዱ ሲሞላለት ግን ሳይጠሩት አቤት የሚል ስጋ ወዳድ ሆዳም ደግሞ ኢትዮጵያ በየዘመኑ አፍርታለችና ብዙ ሊገርመን አይገባም። ከሰሞኑ ከምድረ ኤርትራ የነፈሰዉ ነፋስ ያስተማረን አንድ ትልቅ ቁም ነገር ቢኖር እንዲህ አይነቱን ሞላ ጎደለ የሚባል የካራና የስጋ ጨዋታ ነዉ። አዎ! የካራ ጨወታ – ወዲህ ማዶ ስጋ ሊቆርጡበት ወዲያ ማዶም ስጋ ሊቆርጡበት።

Tuesday, September 22, 2015

ህወሃት ጦርነት ጀመረ፣ ቁስለኞች ታይተዋል

“ሕዝብ አስፈቅደን ውጊያ እንጀምራለን” ሃይለማርያም

omhajer

በነጻ አውጪ ስም አገር እየገዛ ያለውን የትግራይ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃትን) ለመውጋት ብረት ያነሳው ሌላ የትግራይ ነጻ አውጪ ሃይል /ትህዴን ወይም በትግሪኛ ዴምህት/ መሪ የነበረው “ተጋዳላይ” ሞላ አስገዶም ህወሃትን ከተቀላቀለ ጥቂት ቀናት በኋላ ጦርነት መጀመሩ ተሰማ። የህወሃት ወኪል ሃይለማርያም ደሳለኝ ውጊያው የሚጀመረው የህዝብ ፈቃድ ተጠይቆ እንደሚሆን ተናግረው ነበር።

Wednesday, September 16, 2015

” ከእንካሰላንታው ባሻገር” ኤርሚያስ ለገሰ

የሰሞኑን የኢትዬጲያ ፓለቲካ ለተከታተለ ሰው የትግሉ ጫፍ ወዴት እየሔደ እንደሆነ ለመገመት አያዳግተውም። …በአንድ በኩል ላለፋት ሁለት አስርተ አመታት የበላይነቱን ያስጠበቀው አናሳ እና ዘረኛ ቡድን አሁንም ከማንም በላይ የደም ሀረጉን በመምዘዝ ለመሰባሰብ እየተጋ ያለበት ነው። …በሌላ በኩል ሁሉን አቀፍ ትግል የመረጡ በብሔርም ሆነ በሕብረ ብሔራዊነት የተደራጁ ሀይሎች ሀይላቸውን በማቀናጀት በጋራ ለመስራት እየተመካከሩ ያለበት ሁኔታ ነው። እነዚህ ሁለት እንቅስቃሴዎች ከፓለቲካ ፓርቲ እና የድርጅት ህልውና ባሻገር ከኢትዬጲያ ህዝብ የነጳነት ትግል መቀጠልና ወደ ኃላ መመለስ ጋር የተቆራኙ ናቸው። ርግጥም የእነዚህ ሁለት አካላት የፍልሚያ ውጤት የወደፊቱን የኢትዬጲያ እጣ ፋንታ የመወሰን እድሉ ከፍተኛ ነው።

የሞላ ኣስገዶም ጉዳይ ስርዓቱ የቆመበትን መሰረት ማሳያ ነው

ገለታው ዘለቀ
ከኣመታት በፊት በምርጫ ዘጠና ሰባት ኣካባቢ ኣዋሳ ከተማ ውስጥ የገጠመኝ ነገር ትዝ ይለኛል ። በኣዋሳ ከተማ ቆይታየ ጊዜ ከኣንድ ታዋቂ የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅት ውስጥ እሳተፍ ነበር። በዚህ ድርጅት መሳተፍ እንደጀመርኩ ብዙም ሳልቆይ የወጣቶች ጉዳይና የድርጅት ጉዳይ ሆኘ ተመደብኩ።ታዲያ በዚያ ኣጭር ጊዜ ቆይታየ የመንግስትን የስለላ ስራና ተፈጥሮ እንድረዳ እድል ስለሰጠኝ ያ ጊዜ ኣስተማሪየ ሆኖ ይሰማኛል ። በውነት ለመናገር ያ የኣዋሳ ቆይታየ ስለ ወያኔ ያለኝን መረዳት ኣራምዶት ነበር።
ዛሬ የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (TPDM) መሪ የነበረው ኣቶ ሞላ የተወሰኑ ታጋዮችን ይዞ ወደ ኢትዮጵያ ገባ የሚለው ዜና ከተሰማ በሁዋላ ያ የኣዋሳው ትዝታየ የኋሊት በምናብ ታወሰኝ። በተለይም የኣቶ ሞላ ኣስገዶምን ኢንተርቪው ሳይ “እኛ ከመንግስት ጋር ስንሰራ ቆይተናል። ግንኙነት ነበረን” ሲሉ የኣዋሳ ገጠመኘን በጣም ኣጉልቶ ኣሳየኝ።
እስቲ ኣዋሳ የሆነውን ላውጋችሁ። ኣዋሳ ከተማ ውስጥ እሳተፍበት በነበረው የፖለቲካ ድርጅት ውስጥ ከኮሚቴዎቹ መካከል ኣንዱ ማለትም የህዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊው በጣም ይቀርበኝ ነበር። ኣቶ ኤልያስ ይባላል። ይህ ሰው ትሁት፣ ተቆርቋሪ፣ ለኣገር ኣሳቢ ነው። ኣቶ ሞላን ይመስላል። በስብሰባዎች ወቅት ማስታወሻ መያዝ ይወዳል። ስብሰባዎችን ስንጨርስ ኣቀፍ እያደረገ ወደ ጎን ወሰድ ያደርገንና ለድርጅቱ ያለውን ፍቅር፣ የእኛን ኣስተዋጾ ያደንቃል። እኔም እውነቱን ለመናገር ኣመንኩት። ታዲያ ከእለታት ኣንድ ቀን የተለመደውን ስብሰባችንን ኣጠናቀን ስንጨርስ
“ የማወራህ ብርቱ ሚስጥር ኣለኝና ኣብረን ወጣ እንበል” ኣለኝ ለስላሳው ኣቶ ኤልያስ
በደስታ። እንዴውም እኔም ዛሬ የማካፍልህ ኣሳብ ኣለኝ::

Monday, September 14, 2015

ከአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ (ሞላ አስገዶምን አስመልክቶ)

Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracyበኢትዮጵያ የቅርብ ጊዜ የፖለቲካ ትግል ታሪክ ውስጥ ባጠቃላይና በተለይ ደግሞ ህወሓት/ኢህአዴግ የፖለቲካ ስልጣኑን በተቆጣጠረባቸው ባለፉት ሁለት አስርት አመታት ውስጥ ህወሓት/ኢህአዴግን እንቃወማለን በሚለው ወገን ገንነው የመጡ ሁለት አፍራሽና ኋላቀር የፖለቲካ አዝማሚያዎች (trends ) አሉ። ከነኝህ ውስጥ አንደኛው ራስን በፖለቲካ አመለካከት ዙሪያ ከማሰባሰብ ይልቅ በጎጥና በዘውግ ደረጃ የመመልከትና ሀገራዊ ፖለቲካን በደም ቆጠራ የመመንዘር አባዜ ነው። ሁለተኛውና ከዚሁ ያልተናነሰው ችግር የፖለቲካ ድርጅት በመሰረታዊ ያመለካከት መርሆች ዙሪያ ሰፋ ያለ የማህበረሰብ ክፍልን የማሰባሰቢያ ድንኳን መሆኑ ቀርቶ፤ በስራ ሳይሆን ድንገተኛ አጋጣሚን በመጠበቅ ትርፍ ለማጋበስ በሚቋምጡ ሰነፍ “ነጋዴዎች“ የተቋቋሙ ሩቅ የማይሄዱ የንግድ ድርጅቶች ይመስልበ ተግባር ምንም የማይፈይዱ ”የፖለቲካ ድርጅቶች“ እንደ አሸን የመፍላታቸው ፈሊጥ ነው። እነኝህ ሁለቱም አዝማሚያዎች የህወሓት/ኢህአዴግን ህይወት ከማራዘም አልፈዉ ማህበረሰቡን ወደሚመኘው እውነተኛ የዴሞክራሲያዊ ስርዓት አንድ ጋት እንኳን ፈቀቅ አላደረጉትም። ይልቁንም ዴሞክራሲን የሚናፍቁ ታጋዮች ተሰባስበውና ተጠናክረው ስርዓቱን ከመግፋት ይልቅ በግለሰብ ደረጃ ወይንም በትናንሽ ቡድኖች በመሰባሰብ የሚያደርጓቸው እንቅስቃሴዎች በስርዓቱ በቀላሉ እየተመቱ ብዙ ታጋዮች ለሞት፤ ለስቃይና ለእስር ተዳርገዋል። አሁንም እየተዳረጉ ነው።

“ታማኝ ካድሬዎችና አባላት በህወሃት ስብሰባ ላይ ተቃውሞ አሰሙ”

የፌስቡክ ተቃዋሚዎች አብዮታዊ እርምጃ ይወሰድባቸዋል!

facebook blocked


የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በመቀሌ ከተማ ባደረገው ስብሰባ ላይ በጥንቃቄ ተመርጠው የተጠሩ ታማኝ ካድሬዎችና አባላት የተቃውሞ ድምጻቸውን አሰሙ፡፡ የትግራይ ፌስቡክ ተጠቃሚዎች አብዮታዊ እርምጃ ሊወሰድባቸው መሆኑ በአባይ ወልዱ የሚመራው የህወሓት አንጃ አሳወቀ። አንጃው ይህንን አብዮታዊ እርምጃ እንደሚወስድ ያሳወቀው “12ተኛ ጉባኤ እንዴት አለፈ …?” በሚል አጀንዳ በየመንግሥት መስርያ ቤቶች፣ ከመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች፣ የክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች ካድሬዎችና ነዋሪዎች ውይይት በተካሄደበት ጊዜ ነው።

የዴምህት ሊቀመንበር አቶ ሞላ አስግዶም ለምን ከዱ?

(ECADF) – የትግራይ ሕዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ዴምህት) ከአርበኞች ግንቦት7፣ ከአፋር ድርጅቶች የጋራ ንቅናቄ እና ከአማራ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ንቅናቄ ጋር ጥምረት መመስረቱን ባወጀበት ማግስት የጥምረቱ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው የተሾሙትና ዴምህትን ለዓመታት ሲመሩ የኖሩት አቶ ሞላ አስግዶም መክዳታቸው ታውቋል።Former TPDM chairman Mola Asgedom
ኢሳት በአጭር ሰበር ዜና ዘገባው እንደገለጸው ከሆነ አቶ ሞላ አስግዶም ድርጅታቸው ጥምረት እንዲመሰርት ፍላጎት አልነበራቸውም። ይሁንና አብዛኛው የዴህምህት አመራሮች ጥምረቱን በመፈለጋቸው ምክንያት ጥምረቱ እውን ሊሆን ችሏል።
ፋሲል የኔዓለም (የኢሳት ጋዜጥኛ) ወደ ኤርትራ ተጉዞ በነበረበት ወቅት ከአቶ ሞላ አስግዶም ጋር የመወያየት እድል አግኝቶ ነበር። የአቶ ሞላ አስግዶም መክዳት ከተሰማ በኋላ ፋሲል እንዲህ በማለት አስተያየቱን ሰጥቷል፣

Thursday, September 10, 2015

ሳሞራ ወይስ ሕወሃት “ሕገመንግሥቱን” የጣሱት? ወይስ ሁለቱም?

ሳሞራ ወይስ ሕወሃት “ሕገመንግሥቱን” የጣሱት? ወይስ ሁለቱም?

samora
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር ስብሰባ ባደረገበት ወቅት ሳሞራ የኑስ ህወሃትን ለብሰው፣ ህወሃትን አጥልቀው (ጫማቸውና ሌላው አይታይም እንጂ) ህወሃትን ሆነው ታይተዋል፡፡

Wednesday, September 9, 2015

ቴዲ “የፍቅር ነብዩ”ን ተውት ስለ ፍቅር ደግሞ ደጋግሞ ይዘምር… (ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
እረ ተዉኝ ባትነኩኝ ምናለበት
አባካችሁ ሰዎች ስራዬን ልስራበት።
ታላቁ ጥላሁን ገሠሠ
ፍቅር ሁሉንም ድል ያደርጋል !
ሸክስፒር “አስራሁለተኛው ሌሊት“ በሚለው የትያትር ፁሁፋቸው ላይ የኦርሲኖ መስፍን በአዳራሹ ተሰባስበው ለነበሩት ድምጻውያንና ሙዚቀኞች  እንዲህ በማለት ተናግረው ነበር፣ “ሙዚቃ የፍቅር ምግብ እስከሆነ ድረስ አሁንም ዘምሩ፣ በርካታ ሙዚቃዎችን ደግማችሁ ደጋግማችሁ ዘምሩልኝ…“Teddy Afro, Ethiopian popular singer
እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ የሚጠራው የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ በቅጽል ስሙ ቴዲ አፍሮ እየተባለ የሚጠራውን ቴዎድሮስ ካሳሁንን በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ከብዙ ጊዜ በፊት ጀምሮ ለመንፈሳቸው እርካታ ምግብ የሆነውን የህዝቦች የፍቅር ሙዚቃ እንዳይጫወት እገዳ ሲጥልበት ቆይቷል፡፡
የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የቴዲን ህይወት እንደ እነርሱ በመከራ የታጀበ እንዲሆን አጥብቀው ይሰራሉ፡፡ እንደ እነርሱ “የመከራ ፍቅር ኩባንያ“ እንዲሆን ይፈለጋል፡፡
ቴዲ ግን ስለሰው ልጆች ፍቅር ደስታ እንጅ በምንም ዓይነት መልኩ ስለመከራ አይዘምርም፡፡
ቴዲ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብን ለማገልገል የተፈጠረ ድምጻዊ ከያኒ አይደለም፡፡ ስለመከራ እና ስቃይም አይዘምርም፡ መዘመርም አይችልም።
ቴዲ መቸውንም ጊዜ ቢሆን ለወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ባዶ ፕሮፓጋንዳ ማድመቂያ የሆኑትን የጥላቻ፣ የበቀል፣ ኢፍትሀዊ እና ጥልቅ ጥላቻዎችን የሚያነግሱ ሙዚቃዎችን በምንም ዓይነት መልኩ አያቀነቅንም፡፡

ሻዕቢያ ህወሃትን አስጠነቀቀ

የጦርነት አታሞ እየተመታ ነው፤ “ሳንጃም ተስሎብኛል” ብሏል

melesna isayas
ቀደም ሲል የአባትና ልጅ “አፈጣጠርና ግንኙነት” የነበራቸው ወዳጆች ሻዕቢያና ወያኔ ያልተጠናቀቀውን የባድመን ጦርነት ካካሄዱ በኋላ ለዳግም ግጥሚያ ዝግጅት እያደረጉ ነው። “የጦርነቱ ሁኔታ” ያሳሰበው ሻዕቢያ በማስታወቂያ መ/ቤቱ በኩል ለህወሃት ማጠንቀቂያ ሰጥቷል። ከጥቂት ሳምንታት በፊት ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በዘገበው መሠረት መግለጫው ህወሃት ኤርትራን እንዲወጋ የአሜሪካንን ይሁንታ አግኝቷል ብሏል።

Monday, September 7, 2015

ከዝምታው በስተጀርባ (ይገረም አለሙ)

ይገረም አለሙ
አንዳንድ ወገኖች የወያኔ አገዛዝ መቶ በመቶ አሸነፍኩ ያለበት ደረጃ መድረሱ እያበገናቸው፣በሀገርና በሕዝብ ላይ የሚደርሰው ጥፋት እያስቆጫቸው የሕዝቡን ዝምታ በፍርሀት ሲገልጹት ይሰማል፡፡ አንዳንዶች እንደውም ገፋ አድርገው በቅርብ ግዜ የታየውን የአረብ አብዮት እያነሱና ተኒዚያና ግብጽን እየጠቀሱ ኢትጵያዊ በምን ያንሳል በማለት በምሬት ይናገራሉ ይጽፋሉ፡፡
የአረብ አብዮት አይነት ሰላማዊ የሕዝብ ተቃውሞና አምቢተኝነት ወያኔ አጥብቆ የሚፈራው፣ ተቀዋሚው ቢሆን የሚሻው፣ የኢትዮጵ ሕዝብ ሊያደርገው የማይችለው ነው፡፡ ሁሉም የየራሳቸው ምክንያት አላቸው፡፡ ወያኔ በሕዝብ አለመወደዱን ማወቁ፣ ለሥልጣኑ መስጋቱና ፍርሀቱ ሲሆን ፤ተቀዋሚው ለውጥ መሻቱ፣ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን መናፈቁ ነው፡፡ ሕዝቡ የማያደርገው ደግሞ ከጥንት እስከ ዛሬ የኖረበት ወግ ልማዱ ስላልሆነ፣ ትናንት ንጉሶች በቅርቡ ደግሞ አብዮተኞች ሥልጣን ሲነጣጠቁ ያየው በጠብ-መንጃ እንጂ በሰልፍ ስላልሆነ፣ በውርስ የተቀበለውም ሆነ በልማድ ያዳበረው ባለመሆኑ ነው፡፡

Wednesday, September 2, 2015

መለስን የገደለው መለስ ነው (ይገረም አለሙ)

ይገረም አለሙ
PM Meles Zenawiስለ ቀድሞው ጠቅላይ ምስትር መለስ ዜናዊም ሆነ በአንድ ቅኝት ሲያዘፍኑዋቸው ስለነበሩ ፓርቲዎች እንዲሁም ከተከታይነት ያለፈ ምንም ፋይዳ ስላልነበራቸው ሹማምንት ብዙ የተባለ ቢሆንም ዛሬም አድናቂ ነን ባዮች እወደድ ባዮች በመንግሥታችሁ አትርሱን ባዮች ወዘተ ታላቁ ባለ ራዕዩ ወዘተ ከማለት አልፈው አቶ መለስ ለኢትዮጵያና ለህዝቧ ሲሰሩና ሲባትሉ እንደሞቱ ሊነግሩን ይዳዳቸዋል፡፡
አቶ መለስ ሀገር ከማስገንጠል ህዝብ እሰከ መነጣጠል (ያውም እንደ አሰቡት አልሆነላቸውም) ወደብ አልባ ከማድረግ ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት እስከ መጣር የደረሱ ለዛሬው ብቻ ሳይሆን ለመጪው ትውልድም ነቀርሳ የሆኑ እኩይ ድርጊቶቻቸው እንኩዋን ኢትዮጵያዊ አለም ያወቃቸው ናቸው፡፡ጥቅም ማስተዋልን ነስቶአቸው ዛሬ ስለ አቶ መለስ ተቃራኒውን የሚነግሩን ሰዎች አንድ ቀን የአቶ መለስ ትሩፋት ሲደርሳቸው ከእኛ ብሰውና ልቀው ሲኮንኗቸው እንሰማ ይሆናል፡፡
እኔ ዛሬ በትንሹ ማንሳት የምፈልገው አቶ መለስ የሞቱት ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን ሲለፉና ሲደክሙ ሳይሆን ስልጣናቸውን ለማስጠበቅ ሲማስኑ እንደሆነና ራሳቸውን የገደሉት ራሳቸው መሆናቸውን ነው፡፡

የመሐል ሀገር ሰው መልዕክት ለትግራይ ሰው! (በፍቃዱ ኃይሉ)

ማስታወሻ፡- ቀጥሎ የምታነቡት ጽሑፍ በፍቃዱ ኃይሉ ከቂሊንጦ እስር ቤት ለነገረ ኢትዮጵያ የላከው ነው፡፡
Fekadu Hailu zone9 bloggerበፍቃዱ ኃይሉ
ትግራይ የኢትዮጵያ ገናና ታሪክ መሬቷ ላይ የተጻፈባት ክልል ናት፡፡ ብዙዎች ‹‹የኢትዮጵያ ራስ ናት›› የሚሉት ለዚህ ነው፡፡ የኢትዮጵያን ታሪክ ወደኋላ 3000 ዓመት የሚያደርሰው የአክሱም ስልጣኔ አሻራውን ትቶ የሄደው በትግራይ ክልል፣ አክሱም ከተማ ነው፡፡ ከአረቦች ተቀድቷል የሚባለውን የንግስተ ሳባ ታሪክ ‹‹ክብረ ነገስት›› በሚባለው መጽሐፍ ተርጉመው ለዚህ ትውልድ ያኖሩልን የትግራይ ሊቃውንት ናቸው፡፡
ሌላው ቀርቶ ህብረ-ብሄራዊ ቅርስ የሆነንን የሳባ ፊደል ለመላው ኢትዮጵያዊ ያወረሱት የትግራይ ሊቃውንት ናቸው፡፡ ከኢትዮጵያዊነት ቀለሞች አንዱ የሆነው ያሬዳዊው ዜማ የተቀዳው ከትግራይ ምድር ነው፡፡ እነዚህና ሌሎች ያልጠቀስኳቸው እውነታዎች ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚኮራባቸው ናቸው፡፡