Translate

Thursday, September 10, 2015

ሳሞራ ወይስ ሕወሃት “ሕገመንግሥቱን” የጣሱት? ወይስ ሁለቱም?

ሳሞራ ወይስ ሕወሃት “ሕገመንግሥቱን” የጣሱት? ወይስ ሁለቱም?

samora
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር ስብሰባ ባደረገበት ወቅት ሳሞራ የኑስ ህወሃትን ለብሰው፣ ህወሃትን አጥልቀው (ጫማቸውና ሌላው አይታይም እንጂ) ህወሃትን ሆነው ታይተዋል፡፡

“ተጋብዘው ነው” ለማለት ለምትፈልጉ እንትኖች መልሱ ህወሃት ላይ ተጋብዘው ከተገኙ ወደፊት እንደ ሰማያዊ፣ መድረክ፣ ወዘተ ያሉ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች በሚያደርጉት ስብሰባ ላይ የፓርቲዎቹ አርማ ያለበት ባርኔጣ አድርገው ይገኛሉ ማለት ነው – የተነፈሰ ሃሳብ ነው፡፡
ሳሞራ ህወሃትን ሲያይ ዋለ
ተቃዋሚ ፓርቲ የት ነሽ እያለ
ከነጠላው ፉከራ መልስ – “ሕገመንግሥቱ” ያለጥርጥር ተጥሷል፤ ይህ ከሆነ ደግሞ “ሕገመንግሥቱንና ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ …” በሚል ክስ መመሥረት አለበት ማለት ነው፡፡ ይህ ሲሆን ተከሳሽ “አሸባሪ” ሊባል ነው፡፡ ከዚያ ተከሳሽ ወደ …
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር ኢትዮጵያዊ ወንድሞቹን “ጠላት” በማለት የገደለበትን 40ኛ ዓመት ሲያከብር አስቴር በዳኔ “እናንተስ በምርጫ ትወርዱ ይሆን?” በማለት ላነሳችው ጥያቄ ሳሞራ ምንድን ነበር ያሉት? “እኔ ምድብተኛ ወታደር ነኝ”፡፡ ያኔ ግን ባርኔጣ አላደረጉም ነበር፤ ማድረግ አላስፈለጋቸውም፡፡ (የሳሞራ ፎቶና የሕገመንግሥቱ ሃሳብ የተገኘው ከAbenezer B. Yisihak ፌስቡክ ነው)
samora
ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ

No comments:

Post a Comment