tag:blogger.com,1999:blog-29567523755113587692024-03-13T23:17:36.102-07:00 information for ethiopiaAnonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.comBlogger3284125tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-47117443400740860162019-02-10T10:32:00.001-08:002019-02-10T10:34:17.398-08:00በእስር ቤቱ ውስጥ ኢንተርኔት የለም፤ ኮምፒውተር እንፈልጋለን – በረከት ስምዖን<h1 class="entry-title" style="background-color: white; color: #333333; font-family: Georgia, Times, "Times New Roman", serif; line-height: 30px; margin: 0px 0px 10px; padding: 0px;">
</h1>
<img alt="" class="single-display" src="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2019/01/Bereket-Simon-and-Tadesse-Kassa--620x310.png" height="310" style="background-color: white; color: #333333; display: block; font-family: Verdana, Geneva, sans-serif; margin: 0px auto; padding: 0px 0px 10px;" width="620" /><br />
<div class="entry-content" style="background-color: white; color: #333333; font-family: Verdana, Geneva, sans-serif; overflow: hidden;">
<div class="socialize-in-content socialize-in-content-right" style="float: right;">
<div class="socialize-in-button socialize-in-button-right" style="margin: 5px; min-height: 0px; padding: 0px 0px 5px 5px; text-align: center; width: auto;">
<br /></div>
<div class="socialize-in-button socialize-in-button-right" style="margin: 5px; min-height: 0px; padding: 0px 0px 5px 5px; text-align: center; width: auto;">
</div>
</div>
<div class="pf-content">
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
በሌብነት የተጠረጠሩት በረከት ስምኦንና ታደሰ ካሣ አርብ በባህር ዳርና አካባቢዋ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። በዕለቱ ሁለቱም ግለሰቦች ያሉባቸውን ችግሮች ያስረዱ ሲሆን በተለይ በረከት ስምዖን በእስርቤቱ ውስጥ ኢንተርኔት የለም ሲል ማማረሩን <a href="https://www.bbc.com/amharic/news-47177340" style="color: #0094d2; text-decoration-line: none;">ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል</a>። ኮምፒውተር ያስፈልገናልም ብለዋል።</div>
<a name='more'></a><br />
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
በዕለቱ የአማራ ክልል ፀረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪ ባለፈው በተሰጠው የጊዜ ቀጠሮ ማስረጃዎችን ማየቱንና የምስክሮችን ቃል መቀበሉን አሳውቋል። ሆኖም ጉዳዩ ከባድ፣ ውስብስብና ድንበር ተሻጋሪ ከመሆኑም በላይ ምስክሮች እና ሰነዶች በሃገር ውስጥ እና ከሃገር ውጪ መገኘታቸውን አስታውሶ ምርመራውን ባለማጠናቀቁ ተጨማሪ የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
በወቅቱ የቀረበውን ማራዘሚያ ቀን በረከት የተቃወመ ሲሆን ያቀረበው ምክንያትም የሕግ ሥልጣን በሌለው አካል መከሰሰሱን ነው። ይህ ሕጋዊነት የሌለው አካል እንኳም የማራዘሚያ ቀጠሮ ሊጠይቅ መክሰስም አይችልም የሚል ነበር የበረከት ተቃውሞ።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ከበረከት ጋር በሌብነት ተጠርጥሮ የታሠረው ታደሰ ካሣ ደግሞ የዳሽን ቢራ ሁሉም ሰነዶች ተሟልተው ይገኛሉ በማለት ለፍርድ ቤቱ የተናገረ ሲሆን መንግሥት አስረን አናጣራም፤ አጣርተን ነው የምናስረው እስካለ ድረስ የተሟላ መረጃ እያለ እነሱን ማሰሩና የተጠየቀው የጊዜ ቀጠሮ አነሱን በእስር ለማቆየት ብቻ መሆኑን በመጠቆም ውድቅ አንዲሆን ጠይቋል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
የሌብነት ተከሳሾቹን ቃል ከሰማና የግራ ቀኙን ከተመለከተ በኋላ ፍርድ ቤቱ የጉዳዩን ውስብስብነትና መረጃዎች በሃገር ውስጥም ሆነ በውጭ መገኘታቸውን ከግምት በማስገባት የተከሳሾቹን ቃል ውድቅ በማድረግ የ14 ቀን ጊዜ ቀጠሮውን ፈቅዷል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ከዚህ በተጨማሪ በዕለቱ በነበረው የፍርድ ሒደት ላይ በረከት ስምዖን ስንገባም ስንወጣም አየተሰደብንና ስማችን እየጎደፈ ነው በማለት ማማረሩን <a href="https://www.bbc.com/amharic/news-47177340" style="color: #0094d2; text-decoration-line: none;">ቢቢሲ አማርኛ</a> ጨምሮ ዘግቧል። እንዲሁም ተከሳሾቹ ጠበቃ ማግኘት ባለመቻላቸው ፍርድ ቤቱ እንዲያቆምላቸውና ከቤተሰባቸው ጋር የመገናኘት ዕድል እንዲመቻችላቸው ጠይቀዋል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ተከሳሾቹ ይደርስብናል ላሉት ዘለፋና ስድብ ፍርድ ቤቱ ከፀጥታ አካላት ጋር በመሆን ይህንን ለማስቆም እንደሚሠራ አሳውቋቸዋል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ከዚህ ሌላ ሁለቱ የሌብነት ወንጀል ተከሳሾች በማረሚያ ቤት ለመፃፍ የሚያስችላቸው ኮምፒውተር እንዲገባላቸው ጠይቀዋል። በተለይ በረከት በእስር ቤቱ ውስጥ ኢንተርኔት የለም ሲል መደመጡን ቢቢሲ ዘግቧ።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<a href="http://www.goolgule.com/bereket-and-tadesse-said-our-human-rights-is-abused/" rel="noopener" style="color: #0094d2; text-decoration-line: none;" target="_blank">ባለፈው ፍርድቤት በቀረቡ ጊዜ</a> ተጠርጣሪዎቹ ካለባቸው የጤና ችግር አንጻር በጥንቃቄ የተዘጋጀ ምግብ እንደሚመገቡ ገልጸው፤ ይሁንና በማረፊያ ቤቱ ምግብ በአግባቡ እና በሰዓቱ እንደማይቀርብላቸው የተናገሩ ሲሆን ለአብነትም ትናንት ምሳ በ10፡00 እንደቀረበላቸው ለችሎቱ ማስረዳታቸው ይታወሳል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
በኢትዮጵያ ላለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት ያልፈለገውን ማንኛውንም ሰው አሸባሪ በማለት ሕዝብን ሲገድል፣ ሲያበላሽ፣ ሲያሰቃይ፣ በቃል ሊገለጽ የማይችል ግፍ ሲፈጽም የኖረውን ሥርዓት በታማኝነት ከማገልገል አልፈው መብት ገፋፊ ሕግጋትን በማውጣት ለህወሓት/ኢህአዴግ በትጋት ሲሠሩ የነበሩ ግለሰቦች ይህንን መሰሉ የመብት ጥያቄዎች ሲያነሱ መስማት በእርግጥ በኢትዮጵያ ለውጥ አለ የሚያስብል ነው ተብሎለታል።</div>
</div>
</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com2tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-90206217107905923142018-05-29T08:34:00.000-07:002018-05-29T08:34:10.661-07:00በአዲስ አበባ፣ አውሮፓና አሜሪካ ለ“ዘመቻ ዓቢይ” የስውር ምልመላ ተጀምሯል!<h1 class="entry-title" style="background-color: white; font-family: Georgia, Times, "Times New Roman", serif; line-height: 30px; margin: 0px 0px 10px; padding: 0px;">
<span class="entry-subtitle" style="display: block;"><span style="font-size: small;">የ“ዘመቻ ዓቢይ” - አዝማቾችን ዓቢይ ያውቋቸዋል?</span></span><span style="font-size: small;"><img src="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/05/ESFNA-2-e1527540078448-620x310.jpg" /></span></h1>
<br />
<div class="entry-content" style="background-color: white; font-family: Verdana, Geneva, sans-serif; overflow: hidden;">
<div class="socialize-in-content socialize-in-content-right" style="float: right;">
<div class="socialize-in-button socialize-in-button-right" style="margin: 5px; min-height: 0px; padding: 0px 0px 5px 5px; text-align: center; width: auto;">
<br /></div>
<div class="socialize-in-button socialize-in-button-right" style="margin: 5px; min-height: 0px; padding: 0px 0px 5px 5px; text-align: center; width: auto;">
</div>
</div>
<div class="pf-content">
<ul style="margin: 0px; padding: 0px 0px 15px;">
<li style="list-style-type: square; margin: 0px 0px 0px 30px; padding: 0px; text-align: justify;"><strong>ኃይሌ ገብረሥላሴ መልማይ መሆኑ ታወቀ</strong></li>
</ul>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
የሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በዳላስ ሊያካሂድ ያሰበው ሰላሳ አምስተኛ የስፖርት ፌስቲቫል ከወዲሁ እጅግ ጥንቃቄ በሚያሻው ጉዳይ ተወጥሯል። የጎልጉል የመረጃ አቀባዮች እንዳሉት በአገር ውስጥ፣ በአሜሪካና በአውሮፓ የሕዝብ ግንኙነት የሚሠሩ ክፍሎች በምሥጢር እየተመለመሉ ነው። ኃይሌ ገብረሥላሴ አገር ውስጥ ሆኖ ይህንኑ የምልመላ ሥራ እየሠራ ነው። አነጋጋሪ የሆነው ይህንን ዘመቻ የሚያከናውኑት ክፍሎች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ እውቅና ይኑራቸው አይኑራቸው አለመታወቁ ነው።</div>
<a name='more'></a><br />
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ወደ ሥልጣን ከመጡ ጀምሮ <a href="http://www.goolgule.com/esfna-to-approve-abiys-request/" rel="noopener" style="text-decoration-line: none;" target="_blank">በፖሊሲ ጉዳዮች፣ ሕዝብ ባነሳቸው መሠረታዊ ጥያቄዎች፣</a> አፋኝ ህጎችን ከማንሳት አኳያ፣ የፖለቲካ እስረኞችን ሙሉ በሙሉ ከመፍታትና የአስቸኳይ አዋጁን በማንሳት፣ ቀጣዩ ምርጫ ነጻና ገለልተኛ እንዲሆን ምርጫ ቦርድን ከማፍረስ ጀምሮ ተግባራዊ ውሳኔ ያላሳለፉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ <a href="http://www.goolgule.com/esfna-to-approve-abiys-request/" rel="noopener" style="text-decoration-line: none;" target="_blank">ዳላስ በሚካሄደው የስፖርት ፌስቲቫል</a> ላይ ተገኝተው ንግግር እንዲያደርጉ ፈቃድ መጠየቃቸውን ተከትሎ ነው በምሥጢር የሕዝብ ግንኙነት ሥራ የሚሠሩ ሰዎች እንዲመለመሉ የተደረገው።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<a href="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/05/Screenshot-2018-5-28-%E1%8D%8C%E1%8B%B4%E1%88%AC%E1%88%BD%E1%8A%91-ESFNA-%E1%8B%A8%E1%8C%A0-%E1%88%9A-%E1%88%A9%E1%8A%95-%E1%8C%A5%E1%88%AA-%E1%88%8A%E1%8B%AB%E1%8C%B8%E1%8B%B5%E1%89%85-%E1%8A%90%E1%8B%8D2.png" imageanchor="1" style="clear: right; float: right; margin-bottom: 1em; margin-left: 1em;"><span style="color: black;"><img border="0" height="640" src="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/05/Screenshot-2018-5-28-%E1%8D%8C%E1%8B%B4%E1%88%AC%E1%88%BD%E1%8A%91-ESFNA-%E1%8B%A8%E1%8C%A0-%E1%88%9A-%E1%88%A9%E1%8A%95-%E1%8C%A5%E1%88%AA-%E1%88%8A%E1%8B%AB%E1%8C%B8%E1%8B%B5%E1%89%85-%E1%8A%90%E1%8B%8D2.png" width="556" /></span></a>እንደ <a href="http://www.goolgule.com/tplf-on-pr-campaihn-for-abiys-visit-to-the-us-and-europe/" rel="noopener" style="text-decoration-line: none;" target="_blank">ጎልጉል መረጃ ሰዎች</a> ከሆነ ለህወሓት/ኢህአዴግ በአገር ውስጥ፣ በአሜሪካና በአውሮፓ የውስወሳና የሕዝብ ግንኙነት ሥራ እንዲሠሩ የታጩትን የሚያነጋግረው ኃይሌ ግብረሥላሴ ነው። “<a href="http://www.goolgule.com/pm-abiy-to-talk-to-influential-ethiopians/" rel="noopener" style="text-decoration-line: none;" target="_blank">ዳያስፖራውንና ጠቅላይ ሚኒስትሩን ማቀራረብ ነው ዓላማው</a>” በሚል በግል ሰዎችን የሚመለምለው ኃይሌ፣ የማግባባት ሥራውን በስልክ ሲሠራ በተጠቀሱት ቦታዎች የሚዲያ ሥራ የሚሠሩ፣ የሕዝብ ግንኙነት ሥራ የሚያከናውኑና የማግባባት ሥራ የሚሠሩ ሰዎች እየተመለመሉ መሆኑንን አረጋግጧል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ቀደም ብሎም ቢሆን <a href="http://www.goolgule.com/tplf-on-pr-campaihn-for-abiys-visit-to-the-us-and-europe/" rel="noopener" style="text-decoration-line: none;" target="_blank">ጎልጉል በአሜሪካ በምሥጢር</a> ሰዎችን የመመልመልና የማደራጀት ሥራ በኤምባሲው እየተሠራ መሆኑ መረጃ ደርሶት ነበር። ነገሮችን በጥበብ መያዙና የጉዳዩን አካሄድ መከታተል አስፈላጊ በመሆኑ በወቅቱ ይፋ አላደረገም። ይሁን እንጂ ይህ የውስጥ ለውስጥ አሠራር ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ ከተናገሯቸውና አራምደዋለሁ ከሚሉት ጉዳይ ጋር ፍጹም የሚጻረር ሆኖ በመገኘቱ ዜናውን ለማተም ተገድደነናል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ በርሳቸው ስም የተጀመረውን የምሥጢር ምልመላ የሚያውቁት ስለመሆኑ መረጃ የለም። በተመሳሳይ ይህ ድርጊት ከእርሳቸው ዕውቅና ውጪ በስማቸው እየተከናወነ ላለመሆኑም <a href="http://www.goolgule.com/tplf-on-pr-campaihn-for-abiys-visit-to-the-us-and-europe/" rel="noopener" style="text-decoration-line: none;" target="_blank">የጎልጉል ምንጮች</a> ማረጋገጥ አልቻሉም።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ቅቡል ንግግሮችን በማቅረብ፣ ኢትዮጵያዊነትን ከፍ በማድረግ፣ የሴቶችን ሚና በማጉላት፣ በጎረቤት አገራትና በሳዑዲ አረቢያ እስር ቤት ሲማቅቁ የነበሩ ዜጎችን በማስፈታት፣ በሰው በላ ጽንፈኞች ተሰይፈው በረሃ የተጣሉትን ወገኖች አስከሬን እሰበስባለሁ፣ ወዘተ በማለታቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ ተቀባይነትን ያገኙት ጠ/ሚ/ሩ በጁላይ ስድስት የኢትዮጵያ ቀን ላይ እንዲገኙ ያቀረቡት ጥያቄ መልስ ሳይታወቅ በምሥጢር ዳያስፖራውን ለመከፋፈል እየተሠራ ያለው ሥራ ከፍተኛ ቅራኔ እንደሚያስነሳባቸው ይጠበቃል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ከጀርባውም ይሁን ውስጡ ምን እየተሠራ እንደሆነ ያልተረዳው የሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለውሳኔ እንዳይጣደፍ ሲሉ <a href="http://www.goolgule.com/tplf-on-pr-campaihn-for-abiys-visit-to-the-us-and-europe/" rel="noopener" style="text-decoration-line: none;" target="_blank">የጎልጉል የአዲስ አበባ</a> ተባባሪዎች ጠቁመዋል። እንደ ተባባሪዎቹ ከሆነ ፌዴሬሽኑ ሰከን ብሎ ነገሮችን መመርመር ካልቻል በሰላሳ አምስተኛ ዓመቱ የመቀበሪያውን ጉድጓድ ይቆፍራል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
የህወሓት አንደበትና መልዕክት አስተላላፊ የሆነው <a href="https://www.facebook.com/danielberhane.ethiopia" style="text-decoration-line: none;">ዳንኤል ብርሃኔ</a> ማብራሪያ ሳይሰጥ ፌዴሬሽኑ “ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለመጋበዝ ወሰነም አልወሰነም ጉዳዩ የሰሜን አሜሪካውን የተቃውሞ ካምፕ ሁለት ወይም ከዚያ በላይ ቦታዎች እንደሚተረትረው ይጠበቃል” በማለት በፌስቡክ ገጹ ላይ አስፍሯል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ድንገት ከኢትዮጵያዊያን ጫንቃ ላይ በተስፈነጠረው መለስ ትዕዛዝ በሌብነት ተጠርጥሮ በሳዑዲ እስር ቤት የከረመው አላሙዲና የእሱ አስፈጻሚ በሆነው አብነት ገብረመስቀል ምልምሎች አማካይነት ዶላር በትነው ሊንዱት፣ ሊያፈርሱት፣ ሊያከስሙት፣ ሊሰነጥቁት ሁሉ አይነት ሙከራ አድርገውበት በሕዝብ ትግል የተረፈውን ፌዴሬሽን መጠበቅ የዚህ ቦርድና አመራር ኃላፊነት እንደሆነም የመረጃው ባለቤቶች አሳስበዋል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ለህወሓት ስልታዊ አካሄዶች ግንባር በመሆን እያገለገለ ያለው ኃይሌ ገብረሥላሴ በምሥጢር የሚመለምላቸው ሰዎች አድሮ ስለሚታወቁ ከወዲሁ ጥንቃቄ ቢያደርጉ፣ በንግግራቸው የሕዝብን ቀልብ የሳቡት ጠቅላይ ሚኒስትርም ይህ በሳቸው ስም የተጀመረው ዘመቻ እንደማይመጥናቸው፣ በእሳቸው አባባል ካነገሳቸው ሕዝብ ጋር የከፋ ጸብ ውስጥ እንደሚከታቸው በመረዳት ይህንን የድብብቆሽ አሠራር እንዲያስቆሙ የጎልጉል የመረጃ ሰዎች አሳስበዋል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
“አስቡት” ይላል <a href="http://www.goolgule.com/tplf-on-pr-campaihn-for-abiys-visit-to-the-us-and-europe/" rel="noopener" style="text-decoration-line: none;" target="_blank">የጎልጉል የአዲስ አበባ</a> ዘጋቢ ያነጋገረው አስተያየት ሰጪ “አስቡት የአማራን ህዝብ ያዋረደ፣ የሸጠና ለማያባራ መከራ የዳረገው ካሳ ተከለ ብርሃን ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጎን ተቀምጦ ንግግር ሲያደርግ … ነፍሰ በሎች በዲስኩር ብቻ አታለውን ፖለቲካዊ ድል በራሳችን ግብዣ ሲወስዱብን” በማለት ፌዴሬሽኑ ራሱን ከታሪካዊ ስህተት፣ ሊፋቅ ከማይችል ውርደት ሊጠብቅ እንደሚገባ ያሳስባል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
በቀጣዩ ምርጫ በግል ከሚወዳደሩት ምልምሎች መካከል አንዱ የሆነው ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ ያወቀ መስሎት እዛም እዚህም ጥልቅ ማለቱ፣ እጅግ ለሚተላው የህወሓት ጎሰኛ ቡድን ተላላኪ መሆኑ አድሮ ዋጋ እንደሚያስከፍለው ከወዲሁ እንዲረዳ በተደጋጋሚ ሲነገረው መቆየቱ አይዘነጋም።<a href="http://www.goolgule.com/tplf-on-pr-campaihn-for-abiys-visit-to-the-us-and-europe/" target="_blank">http://www.goolgule.com/tplf-on-pr-campaihn-for-abiys-visit-to-the-us-and-europe/</a></div>
</div>
</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-83075485168563046502018-04-04T09:11:00.000-07:002018-04-04T09:11:31.360-07:00ቀጣዬ 100 ቀናት!(ኤርሚያስ ለገሰ)<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px;">
<img alt="Ermias Legesse, author and ESAT TV and Radio contributor" src="https://i2.wp.com/ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2016/10/Ermias-Legesse2.jpg?resize=620%2C330" /></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">መንደርደሪያ</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">የትግራይ ነፃ አውጪ በገጠመው ሕዝባዊ ማእበል፣ እንዲሁም የሕዝቡን ተቃዉሞ በተከተለበት ጫና ዶክተር አቢይን ወደ ጠቅላይ ሚኒስትርነት አምጥቷል። የዶክተር አቢይ ወደ ፊት መምጣት በብዙ መልኩ የተደበላለቀ ስሜቶችን ፈጥሯል። በህውሓት ደጃፍ ከፍተኛ ቁዘማና ንዴት የፈጠረ ሲሆን በለውጥ ፈላጊው ዘንድ የተከፋፈለ አስተያየቶች በመስተናገድ ላይ ናቸው። በተለይም ዶክተሩ በበአለ ሲመቱ እለት ያቀረበው ንግግር የብዙ ኢትዬጲያውያንን አንጀት ቅቤ ያጠጣ ነበር። በታሪካዊነቱም ተመዝግቧል።</span></div>
<a name='more'></a><br />
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">በአጭር ጊዜ ውስጥ በስልጣን ኮርቻው ላይ የወጣው ዶክተር አቢይ እጅግ ውስብስብ የሆኑ ችግሮችን ለመፍታት፣ መንፈሱ የተበታተነውን የኢትዬጲያ ህዝብ ለማረጋጋት፣ ኢትዬጲያን ወደ ፊት ሊያራምዱ የሚችሉ ሁሉንም ኃይሎች ለማስተባበር፣ የኢኮኖሚ እና ፓለቲካ እቅዶችን ለማስተዋወቅ ጥረት አድርጓል።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ይህንም ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቀጣይ ቀናት ወደ ተግባር ሊመነዝራቸው ይገባል የተባሉ ስፍር ቁጥር የሌላቸዉ ድርጊቶች መዘርገፍ ጀምረዋል። ሰውየው ለወደፊቱ ያለበትን ተልእኮ የሚያሳስበውም ብዙ ነው። እኔም እንደ አንድ ኢትዬጲያዊ ዶክተር አቢይ በኦሮሚያ የጀመረውን ስራ ሳይጨርስ ወደ ፌዴራል መምጣቱ ልቤ አልተቀበለውም። ተቃውሞዬን በአደባባይ ገልጫለሁ። በጠላቶቹ ሜዳ ላይ ከመጫወቱ በፊት የራሱን ሜዳ በብረት እንዲያጥረው ፍላጐቴ ነበር።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">አሁንም ቢሆን ከትላንት አቋሜ የተለወጠ ነገር የለኝም። በስልጣን ላይ ያለው ሽፍታ አገዛዝ አሁንም የስለላና ወታደራዊ መዋቅሩን የተቆጣጠረው ነው። ወደድነውም ጠላነውም የኢኮኖሚ መዋቅሩን የተቆጣጠረው ይህ ከፋፋይ ቡድን ነው። ሌላው ቀርቶ የአሁኖቹ የዶክተር አቢይ የግልና የቤተመንግስት ጠባቂዎች የሟቹ መለስ ዜናዊ ጠባቂዎች ናቸው።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">በመሆኑም ሰውየው በአምባገነኖች፣ በዘረኞች፣ በማይማን፣ ኢትዬጲያን በሚጠሉና በሚያሳፍሩ ሰዎች መዳፍ ውስጥ መግባቱን ስመለከት መንፈሴ ይረበሻል። የትግራይ ነፃ አውጪ ካድሬዎች እና ባለሟሎች እንዳይሰራ መውጪያ መግቢያውን እንደሚዘጉበት ሳውቅ ልቤ ይደማል። በፈላ ውሃ እንደምትቀቀለው እንቁራሪት እየሆኑ ያሉት ህውሓቶች የተካኑበትን አጥፍቶ መጥፋት ፓሊሲ እንዳይፈፅሙበት እሰጋለሁ።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">በሌላ በኩል አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ለኢትዬጲያ ህዝብ ያቀረበው ራዕይ አስደስቶኛል። የኢትዬጲያ ተስፋና የኢትዬጲያችን መቀጠል ሲያስጨንቀው አብሬ ተጨንቄያለሁ። ዶክተር አቢይ የሕዝብ አሽከር ሆኖ ሕዝብን ለማገልገል ቆርጦ መነሳቱን ሳይ በምን ልደግፈው እችል ይሆን የሚል ጥያቄ አንስቻለሁ። የጠላት ሜዳ ላይ አሸንፎ ለመውጣት እንዴት ቢጫወት ያዋጣዋል የሚለውን አስቤያለሁ።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">እናም ዶክተር አቢይ የኢትዬጲያ ህዝብ ትግልና እምቢተኝነትን እንደ ነዳጅ እየወሰደ የተቆጠረ ግቦችን በተቆጠረ ጊዜ ቢፈፅም አሸናፊ ሆኖ ሊወጣ ይችላል። ባለፈው መጣጥፌ በተራዘመ ጊዜ ሊፈፅማቸው የሚችሉትን አላማዎች ጠቆም አድርጌ ነበር። ለዛሬው በመቶ ቀናት ሊፈፅማቸው ይገባል ያልኳቸውን የአደረጃጀትና የፓለቲካ ግቦች ጠቁሜያለሁ። እነዚህ አራት ግቦችና በስራቸው ያሉ የተቆጠሩ ተግባራት ከአረጃጀት፣ በመንግስትና በፓርቲ መካከል መኖር ስለሚገባው ግንኙነት፣ ስልጣንን እና ሌብነትን እንዲሁም የዲሞክራሲ እሴቶችን ለመገንባት የተዘረዘሩ ናቸው። ግቦቹና ዝርዝር ተግባራቱ ያለቀላቸው ሳይሆኑ ለውይይት መነሻ ሆነው የሚያገለግሉ ናቸው።<br />***</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#<a class="_58cn" data-ft="{"tn":"*N","type":104}" href="https://www.facebook.com/hashtag/%E1%8C%8D%E1%89%A5?source=feed_text" style="cursor: pointer; font-family: inherit; text-decoration-line: none;"><span class="_5afx" style="direction: ltr; font-family: inherit; unicode-bidi: isolate;"><span aria-label="hashtag" class="_58cl _5afz" style="font-family: inherit; unicode-bidi: isolate;">#</span><span class="_58cm" style="font-family: inherit;">ግብ</span></span></a> አንድ:-</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">በሕገ መንግስቱ መሰረት በኢትዬጲያ ህዝብ አመኔታ እና ተቀባይነት የላቸውን በመለየት የሚኒስትሮች ምክር ቤትና ሌሎች ከፍተኛ የስልጣን እርከኖች ማዋቀር።<br />*</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;"><a class="_58cn" data-ft="{"tn":"*N","type":104}" href="https://www.facebook.com/hashtag/%E1%8B%A8%E1%8C%8D%E1%89%A5?source=feed_text" style="cursor: pointer; font-family: inherit; text-decoration-line: none;"><span class="_5afx" style="direction: ltr; font-family: inherit; unicode-bidi: isolate;"><span aria-label="hashtag" class="_58cl _5afz" style="font-family: inherit; unicode-bidi: isolate;">#</span><span class="_58cm" style="font-family: inherit;">የግብ</span></span></a> አንድ ተግባር አንድ:-</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ሕገ መንግስቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከህዝብ ተወካዬች ምክር ቤት አባላት እና ከምክር ቤት አባላት ውጪ ሚኒስትሮችን በመመልመል በፓርላማው ያፀድቃል በሚለው መሰረት እጩዎችን ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች መመልመል።<br />*</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#የግብ አንድ ተግባር ሁለት፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ከተመለመሉት ውስጥ በብቃታቸው፣ በስነምግባራቸውና ተቀባይነታቸው የላቁትን ለሽግግር ጊዜው በሚኒስትርነት መመደብ። በዚህ መሰረት የሚከተሉት ግለሰቦች ለሽግግር ጊዜው ለእጩነት ቢቀርቡ በምክረ ሃሳብ የቀረቡ ናቸው፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">° ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት: አቶ ደመቀ መኮንን<br />° ውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት: ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና<br />° ኢኮኖሚና ፋይናንስ ሚኒስትር: አቶ ስዩም ተሾመ<br />° ፍትሕ ሚኒስትር: አቶ ተማም አባቡልጋ<br />° ደህንነት ሚኒስትር: አቶ ገዱ አንዳርጋቸው<br />° ኮሙዩኒኬሽን ሚኒስትር: አቶ ንጉሱ ጥላሁን<br />°የአገር ደህንነት ሚኒስትር: አቶ አንዷለም አራጌ<br />° ገቢዎች ሚኒስትር: - አቶ አስራት አብርሃም<br />° አርብቶ አደር ሚኒስትር: ዶክተር አብርሃ ተከስተ<br />° መገናኛ ሚኒስትር: አቶ የሺዋስ አሰፋ<br />° መከላከያ ሚኒስትር : አቶ በቀለ ገርባ<br />° ትምህርት ሚኒስትር:- አቶ ሬድዋን ሁሴን<br />° አሳ ሐብት ሚኒስትር: ወ/ት ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር<br />° የጡረታ ሚኒስትር: አቶ አስመላሽ ወልደስላሴ ( አባይ ነብሶ)<br />° ቱሪዝም ሚኒስትር:- ዶክተር አዲሳለም ባሌማ<br />° የኢንቨስትመንት ሚኒስትር:- አቶ ግርማ ሰይፉ<br />° ወጣቶች ሚኒስትር: - አብርሃ ደስታ<br />° ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር: - አርቲስት አስቴር በዳኔ<br />° ኤታማዦር ሹም: - ጄነራል ተፈራ ማሞ<br />° ፌዴራል ፓሊስ ሹም:- ኮረኔል ደመቀ ዘውዴ<br />° ሴቶችና ህፃናት ሚኒስትር:- ወይዘሮ የትነበርሽ<br />° የጽህፈት ቤቱ ሚኒስትር:- አቶ ደግፌ ቡላ<br />° የንግድ ሚኒስትር:- ተስፋዬ በጅጋ<br />° የግብርና ሚኒስትር: - አቶ ሲራጅ ፈርጌሳ<br />*</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#ግብ አንድ ተግባር ሁለት፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">የመንግስት የልማት ድርጅቶች፣ ኮርፓሬሽን፣ ባለስልጣናት እና ተቋማት ስራ አስኪያጅ፣ ዋና ስራ አስፈፃሚና ዴሬክተሮች ሹመት የየትኛውም የፓለቲካ ድርጅት አባላት ካልሆኑ ኢትዬጲያውያን ውስጥ ብቃት ያላቸውን መሾም። መመዘኛዎቹ በሚዲያ ተቋማት በግልፅ እንዲነገሩ ማድረግ። ሂደቱን ሕዝቡ በቀጥታ በሚከታተለው መልኩ እና ተወዳዳሪዎች ተቋማቱን እንዴት እንደሚመሩ እና የት ማድረስ እንደሚፈልጉ በሚገልፁበት ሁኔታ እንዲፈፀም ማድረግ። በውጭ የሚኖሩ ከፍተኛ ሙያተኛ የሆኑ ኢትዬጲያውያን እና ትውልደ ኢትዬጲያውያን የውድድሩ አካል እንዲሆኑ ማድረግ።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ከእነዚህ የስልጣን ቦታዎች መካከል ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ይሆናሉ፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">• የብሔራዊ ባንክ ገዥ<br />• የልማት ባንክና ንግድ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ<br />• የኢትዬጲያ መድን ድርጅት<br />• የኢትዬጲያ አየር መንገድ<br />• የኢትዬጲያ ቴሌ ኮሙዩኒኬሽን<br />• የመንግስት ሆቴሎች<br />• የኢትዬጲያ ቴሌቪዥን እና ሬዲዬ<br />• የመንገዶች ባለስልጣን<br />• ምርት ገበያ ( ECX)<br />• ዋና ኦዲተር ጄኔራል<br />• ሁሉም የአምባሳደርነት ቦታዎች<br />• አደጋና ዝግጁነት ዴሬክተር ( አመዝኮ)</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">*<br />#የግብ አንድ ተግባር ሶስት:-<br />በመንግስት በጀት የሚተዳደሩ አላስፈላጊ የሚኒስቴር መስሪያቤቶች፣ ባለስልጣናት ፣ ተቋማት እና የሐላፊነት ቦታዎችን ማፍረስ። ከእነዚህ ውስጥ ቅድሚያ የሚሰጣቸው፣<br />• ፌዴራል ጉዳዬች ሚኒስትር<br />• የመንግስት ዋና ተጠሪ ፅህፈት ቤት<br />• የብሮድካስት ባለስልጣን<br />• የኢትዬጲያ ዜና አገልግሎት እና ፕሬስ ድርጅት<br />• የእምባ ጠባቂ ኮሚሽን<br />• የሰብአዊ መብት ኮሚሽን<br />• ምርጫ ቦርድ<br />• የብረታ ብረት ኮርፓሬሽን ( ሜቴክ)<br />• ብሔራዊ መረጃ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ(ኢንሳ)<br />• የፓሊሲ ምርምር፣ ጥናትና አማካሪ ቢሮ</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">*<br />#የግብ አንድ ተግባር አራት፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ጠቅላይ ሚኒስትሩን በቋሚነት የሚያሟክሩ በኢትዬጲያ ሕዝብ ተቀባይነት ያላቸው ከ25 እስከ 30 የሚጠጉ ምስጉን የአገር ሽማግሌዎች፣ የሐይማኖት አባቶችና አገራችንን በአለም ደረጃ ያስተዋወቁ አባላት የያዘ “ አማካሪ ምክር ቤት” ማቋቋም።<br />• አማካሪ ምክርቤቱ በሁለት ሳምንት አንዴ ( ቅዳሜ ከሰአት) ለግማሽ ቀን የሚሰበሰብ ይሆናል።<br />• አማካሪ ምክር ቤቱ ዋነኛው ተልእኮ የሽግግር ሂደቱን ለማፋጠን ድልድይ ሆኖ የሚያገለግል ይሆናል። የፓለቲካ ፓርቲዎችን ድርድር በይፋና በሚስጥር ያደርጋል። ፓርቲዎቹ የሚያቀርቡትን የሽግግር ሰነድ እየመረመረ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀርባል። የዲሞክራሲ ተቋማት ተአማኒነት ባለው መልኩ የሚዋቀሩበትን ሐሳቦች በማመንጨት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀርባል።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">• የአማካሪ ምክር ቤት አባላት የገዥው ፓርቲ አባላትም ሆነ ደጋፊዎች መሆን የለባቸውም።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">• ለአማካሪ ምክር ቤት አባልነት ለመነሻ እንዲሆን አቶ እየሱስ ወርቅ ዛፋ፣ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ፣ ዶክተር ነጋሶ ጊዳዳ፣ አቶ ክቡር ገና፣ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ፣ አቶ ገብረየስ ቤኛ፣ ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ፣ ዶክተር በድሉ ዋቅጅራ፣ አቶ አርአያ ገ/ እግዚአብሔር፣ አቶ ገብሩ አስራት፣ ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም፣ ዶክተር ያዕቆብ ሐይለማርያም፣ ዶክተር በፍቃዱ ደግፌ፣ አርቲስት አሊ ቢራ፣ አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን፣አርቲስት አረጋኸኝ ወራሽ፣ አትሌት ሐይሌ ገብረስላሴ፣ አቶ አስገደ ገ/ ስላሴ፣ አቶ ገብሩ ገብረማሪያም፣ አቶ ቆስጠንጢኖስ በርሄ፣ ፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ የመሳሰሉት አባል የሚሆኑበት ይሆናል።<br />*</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#የግብ አንድ ተግባር አምስት፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">የቀድሞ የሕውሓት/ ኢህአዴግ ባለስልጣናትን በሶስት ዙር በጡረታ ማሰናበት። ከጡረታ በኃላ በየትኛውም የሚዲያ ተቋም ፣ብሔራዊና ድርጅታዊ በአላት፣ ስብሰባዎች፣ ምርቃቶች እንዳይገኙ ማድረግ። አቶ ተፈራ ዋልዋ ልምዱን እንዲያካፍላቸው መድረክ ማዘጋጀት። በመጀመሪያው ዙር የሚሰናበቱት አቶ ስዩም መስፍን፣ አቶ በረኸት ስምኦን፣ አቶ አርከበ እቁባይ፣ አቶ ስብሃት ነጋ፣ አቶ አባይ ፀሀዬ፣ አቶ ግርማ ብሩ፣ ዶክተር ካሱ ኢላላ ፣ ኩማ ደመቅሳ ፣ አዲሱ ለገሰ፣ ሳሞራ የኑስ፣ ጌታቸው አሰፋ፣ አለማየሁ ተገኑ ይሆናሉ።<br />***</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#ግብ ሁለት፣<br />የመንግስት እና ፓርቲ ስራ እንዲለያዩ ማድረግ። ፓርቲ መንግስትን ተክቶ አመራር አይሰጥም። መንግስት በቀጥታ በፓርቲው እየተመራ አመራር አይቀበልም።<br />*</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#የግብ ሁለት ተግባር አንድ፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">የመንግስት አካላት የሚከተሉትን አጠቃላይ የፓለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማህበራዊና የባህል ፓሊሲዎች የሚቀየሱት በሚኒስትሮች ምክር ቤት ብቻ ይሆናል።<br />*</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#የግብ ሁለት ተግባር ሁለት፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">በሕዝብ ምርጫ ከሚደራጁ ምክር ቤቶችና ካቢኔዎች ( እስከ ቀበሌ) ውጭ የሚሞሉ የመንግስት ሐላፊነት ቦታዎች የየትኛውም የፓለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆኑ ኢትዬጲያውያን እንዲያዝ ማድረግ።<br />*</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#የግብ ሁለት ተግባር ሶስት፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">በሲቪል ሰርቪስ ውስጥ ተቀጥረው የሚሰሩ ሰራተኞችም ሆነ በቀጣይ የሚቀጠሩ ሰራተኞች የትኛውም የፓለቲካ ፓርቲ አባል እንዳይሆኑ ማድረግ። በሲቪል ሰርቪስ ውስጥ እየሰሩ አስቀድሞ አባል የሆኑ ሲቪል ሰርቫንቶች ለነበሩበት ፓርቲ በይፋ መልቀቂያ እንዲያስገቡ ማድረግ። የፓርቲ መልቀቂያ ለማስገባት ፍቃደኛ ያልሆኑ የመንግስት ሰራተኞች በፍቃደኝነት ስራቸውን እንዲለቁ ማድረግ።<br />*</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#የግብ ሁለት ተግባር አራት፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">በመንግስት የስራ ሰአት፣ በመንግስት ፅህፈት ቤት ውስጥ የየትኛውም የፓለቲካ ድርጅት የፓለቲካ ስራ( ማደራጀት፣ መሰብሰብ፣ ካድሬ መመልመል) እንዳይካሄድ ማድረግ። የመንግስት ንብረት ለመንግስት ስራ ብቻ ማዋል። ይሄን ተላልፎ የሚገኝ ማንኛውም ሰራተኛ ከስራ እንዲሰናበት እና የትኛውም የመንግስት መስሪያ ቤት በድጋሚ እንዳይቀጠር ማድረግ።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">*<br />#የግብ ሁለት ተግባር አምስት፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">በዩንቨርስቲዎች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ቴክኒክና ሙያ እንዲሁም በአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ማንኛውም የፓለቲካ ፓርቲ በይፋም ሆነ በግልፅ የድርጅት ስራ ( ምልመላ፣ ማደራጀት፣ ስብሰባ፣ መሰረታዊ ድርጅት) የመሳሰሉትን እንዳይሰራ ማድረግ። የትምህርት ተቋማቱ አመራሮች ምደባ የፓለቲካ ፓርቲ አባል አለመሆንን እንደ ቅድመ ሁኔታ በመውሰድ መመዘኛው ብቃት እና ብቃት ብቻ እንዲሆን ማድረግ። በየትኛውም ደረጃ ያሉ መምህራት እንደ ሲቪል ሰርቪስ ሰራተኝነታቸው ከየትኛውም የፓለቲካ ድርጅት አባል አይሆኑም። ህሊናቸው ካልፈቀደ በፍቃደኝነት ስራቸውን እንዲለቁ ይደረጋል።<br />***</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;"># ግብ ሶስት፣<br />ስልጣን የሐብት ምንጭ የማይሆንበት ሁኔታ መፍጠር።<br />*</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#የግብ ሶስት ተግባር አንድ፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ሚኒስትሮች፣ ምክትል ሚኒስትሮች፣ ዋናና ምክትል ስራ አስፈፃሚዎች፣ ስራ አስኪያጆች፣ ዴሬክተሮች፣ መምሪያ ሐላፊዎች፣አምባሳዳሮች፣ ዲፕሎማቶች፣ ከኮረኔል እስከ ጄኔራል ባለ ማእረግ የጦር አዛዦች ንብረታቸውን በመመዝገብ ለሕዝብ ይፋ ማድረግ። የወር የገቢና ወጪ መጠናቸውን፣ የልጆች ትምህርት ቤት ወጪ ወዘተ በምዝገባው እንዲካተት ማድረግ። ለምዝገባ ፍቃደኛ የሆኑትን እና ለመደበቅ ጥረት የሚያደርጉትን ለሕዝብ በማጋለጥ ለህግ ማቅረብ። በአርአያነት ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና የካቢኔው አባላት በአንድ ወር ውስጥ ንብረታቸውን ይፋ እንዲያደርጉ ማድረግ።<br />*</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#የግብ ሶስት ተግባር ሁለት፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">በግብ ሶስት ተግባር ሁለት የተገለጡት ባለስልጣናት ከአንድ በላይ የቦርድ አመራርም ሆነ የቦርድ አባል እንዳይሆኑ ማድረግ። በቦርድ የሚተዳደሩ ተቋማት ውስጥ ቢያንስ ሁለት ከተፎካካሪ ፓርቲ፣ አንድ ከባለስልጣንም ሆነ ከሲቪል ሰራተኛ ውጭ ማድረግ። በቦርድ ውስጥ የማገልገል ስራ በፍላጐትና ያለምንም ክፍያ እንዲሆን ማድረግ።<br />*</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#የግብ ሶስት ተግባር ሶስት፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">በግብ ሶስት ተግባር ሁለት የተጠቀሱት ባለስልጣናት የቅርብ ዘመዶች ባለቤት የሆኑበት ቢዝነስ ከባለስልጣኑ ስራ ጋር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚገናኝ ከሆነ ባለስልጣኑ ሐላፊነቱን በፍቃደኝነት እንዲለቅ አሊያም ሌላ ቦታ ተዘዋውሮ እንዲያገለግል ማድረግ። በተጨማሪም ባለስልጣናቱ ከመንግስት ተቋማት ውጪ ባሉ ድርጅቶች የቦርድ አባልነትም ሆነ የአማካሪነት ስራ መስራት አይችሉም።<br />*</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#የግብ ሶስት ተግባር አራት፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">የፓለቲካ ፓርቲዎች የሚያስተዳድሩት ንብረትም ሆነ ቢዝነስ እንደማይኖራቸው በሕጉ የተገለፀውም ተፈፃሚ ማድረግ። በዚህ ሕግ መሰረት የኤፈርት፣ የትልማ፣ ረስት፣ ጥረት፣ ዲንሾ፣ ወንዶ ንብረቶች ለግል ባለሀብት እንዲሸጡ ማድረግ። ከሽያጭ የሚገኘውን ገቢ ለአንደኛ ፣ሁለተኛና ዩንቨርስቲዎች ማከፋፈል።<br />*</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#የግብ ሶስት ተግባር አምስት፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">የግሉ ዘርፍ በነፃ ገበያው መርህ እየተመራ በኢኮኖሚው ላይ የበላይነቱን እንዲያረጋግጥ ምቹ ሁኔታ መፍጠር። በመንግስት የተያዙ ተቋማት በነፃ ገበያ ህግጋት መሰረት በሂደት ወደ ግል የሚዞሩበት ጥናቶችን ሰርቶ ማጠናቀቅ።<br />***</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#ግብ አራት፣<br />በኢትዬጲያ ህዝብ ውስጥ ዲሞክራሲያዊ ባህልና እሴቶች እንዲጠናከሩ ማድረግ።<br />*</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#የግብ አራት ተግባር አንድ፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">የፀረ ሽብርተኝነት ፣ የመንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና የፕሬስ ህጉን በገለልተኛ ወገን እንዲጠና ማድረግ። የሚኒስትሮች ምክርቤት እና የአማካሪ ምክር ቤት አባላት በጋራ በመሆን በገለልተኝነት አጥንተው የሚያመጡ ሙያተኞችን በስምምነት እንዲመድቡ ማድረግ። ጥናቱ ተጠናቆ እስኪመጣ ድረስ አዋጆቹ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅራቢነት በፓርላማ እንዲታገዱ ማድረግ። በህውሓት ፓርላማ “ ሽብርተኛ!” ተብለው የተፈረጁ አገራዊ ድርጅቶች በአስቸኳይ እንዲሰረዙ ማድረግ።<br />*</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#የግብ አራት ተግባር ሁለት፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">በሕግ መልኩ በፓርላማ ሊወጣ የተዘጋጀውን “ የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ሕግ” ሙሉ ለሙሉ ሂደቱ እንዲቋረጥ ማድረግ። እንደዚህ አይነት ከፀረ ሽብርተኝነት የባሰ ጨቋኝ ህግ እንዲወጣ በመታሰቡ ለወጣው የሕዝብ ገንዘብ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይቅርታ ጠይቀው እንደማይደገም ቃል መግባት።<br />*</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#የግብ አራት ተግባር ሶስት፣</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ሬዲዬ ፋና፣ ዋልታ፣ ENN ፣ ድምፀ ወያኔ የመሳሰሉ የፓርቲ ሚዲያዎችን ማገድ። በግልፅ ጨረታ ወደ ግል ይዞታ የሚዞሩበትን ሁኔታ ማመቻቸት። ሂደቱ በሚኒስትሮች ምክርቤትና በአማካሪ ምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ እየቀረበ አበረታች ምርመራ እንዲካሄድ ማድረግ።<br />*</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">#የግብ አራት ተግባር ሶስት፣</span></div>
<div style="background-color: white; display: inline; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-top: 6px;">
የሽግግር ሰነድ ካዘጋጁ ተፎካካሪ የፓለቲካ ድርጅቶች ጋር ሚኒስትሮች ምክር ቤትና አማካሪ ምክር ቤቱ ይፋዊ ውይይቱን መጀመር። ውስጣዊ ድርድሮቹ ካለቁ በኃላ ለህዝብ ይፋ በሆነ መንገድ ውይይቱን መጀመር።<br />-----//----</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-38701210068677240062018-03-18T03:48:00.000-07:002018-03-18T03:48:00.210-07:00ዛሬ ልወቅስ ነው፣ ራሴን ጨምሬ…<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መሳይ መኮንን</em></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<a href="https://ecadforum.com/Amharic/archives/18728/waldeba-prisoners3/" rel="attachment wp-att-18729" style="border: 0px none; color: #0f06ba; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px; text-decoration-line: none; transition: all 0.2s ease-in-out;"><img alt="Waldeba monastery priests, political prisoners in Ethiopia." class="aligncenter size-full wp-image-18729 jetpack-lazy-image--handled" data-lazy-loaded="1" height="330" sizes="(max-width: 620px) 100vw, 620px" src="https://i2.wp.com/ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2018/03/Waldeba-prisoners3.jpg?resize=620%2C330" srcset="https://i2.wp.com/ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2018/03/Waldeba-prisoners3.jpg?w=620&ssl=1 620w, https://i2.wp.com/ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2018/03/Waldeba-prisoners3.jpg?resize=300%2C160&ssl=1 300w" style="border: 1px solid rgb(203, 205, 204); clear: both; display: block; height: auto; list-style: none; margin: 2px auto; max-width: 100%; outline: none; padding: 4px;" width="620" /></a></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ዛሬ ልወቅስ ነው። ራሴን ጨምሬ በጽሁፍ ጅራፍ ልጋረፍ ነው። በእውነት ይህን ጽሁፍ ስሞነጫጭር ውስጤ በእልህና ቁጭት ድብን እያለብኝ ነው። በዚህም አሰብኩት። ወደዚህም ወሰድኩት። አገለባብጬ ተረጎምኩት። ዝምታችን ከፍርሃት በቀር ምክንያታዊ አልሆንልህ አለኝ። መቼም የትግራዩ አገዛዝ ስልጣን ላይ ከወጣ በኋላ የሞራል ልኬታችን ፈሩን ስቷል። የህሊና ፍርዳችን ተዛብቷል፡፡ ሰው የመሆን ሚዛናችን ጎድሏል።</div>
<a name='more'></a> አገዛዙ ይዞብን የመጣው እሴት አልባ፡ ራዕይ የለሽ፡ ክብረ ነክ ወረርሽኝ ውስጣችንን ገዝግዞ፡ እንደምስጥ ስጋችንን በልቶ፡ ዝም ብለን የምንከላወስ፡ በልቶ ማደር፡ ጠጥቶ መነሳት መኖር የሚመስለን ሆነን ቀርተናል። ስንቱን በጎነታችንን፡ የሞራል ልዕልናችንን አራግፈን ጥለን ፡ በፍርሃት ቆፈን በተቀፈደደ፡ በእንጭፍጫፊ ሰበብና ምክንያቶች በተለበጠ፡ ኢትዮጵያዊ ክብርና ሞገሱን በተገፈፈ ማንነት ደረታችንን ነፍተን፡ ልክ ነን ብለን ልክ አጥተን የምንኖር ዜጎች ሆነናል።<br />
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
አዎን! ለሃይማኖቱ ቀናዒ፡ ለእምነቱ ክብር አንገቱን ለሰይፍ ከመስጠት ወደኋላ አይልም በሚባልለት ኢትዮጵያዊ አፈር ላይ በዚህ ዘመን የሃይማኖት አባቶች ተዘቅዝቀው አርባ ይገረፋሉ። የነጭ ወራሪ ባንዳ ሶላቶ ባህር ተሻግሮ ሊወረን በመጣ ጊዜ ታቦት ተሸክመው፡ በማርያም ምለው ዘምተው፡ በጊዮርጊስ ቀን ድል አድርገው ለመላው ጥቁር ህዝብ የነጻነት አክሊል ያጎናጸፉ ኢትዮጵያውያን በበቀሉባት ምድር ላይ ዘንድሮ መነኮሳት፡ ወፌ ላላ እየተገረፉ፡ መሬት ለመሬት እየተጎተቱ፡ ሰውነታቸው ደም እስኪያዥ በኤሌክትሪክ ሽቦ እየተጠበሱ፡ ታላቁን ስቃይና ሰቆቃ ይጋታሉ። ለሀገር ነጻነት ደረታቸውን ለጥይት ሰጥተው፡ መራሯን ሞት በአደባባይ ተጎንጭተው ሃይማኖቷንም፡ ሀገራቸውንም አስከብረው፡ በክብር የተሰዉትን የታላቁን ፓትርያርክ አቡነ ጴጥሮስን አጽም በተሸከመችዋ የአሁኗ ኢትዮጵያ መስቀልና መጽሀፍ ቅዱስ ብቻ ይዘው ዓለምን ተጠይፈው ገዳም የገቡ መናኞች የክህነት ልብሳቸውን አውልቁ ተብለው ግፍ ይፈጸምባቸዋል።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ይሄ ሁሉ ጉድ ይሰማል። ድብቅ አይደለም። መሀል ኢትዮጵያ፡ ከአዲስ አበባ እምብርት እየተፈጸመ ያለ ሰቆቃ ነው። ኸረ ለመሆኑ የታላቁ መንፈሳዊ አባት<br style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;" />ልጆች ይህን መከራ አልሰሙም? እነዚያ ለእምነታቸው ክብር እስከሞት ዋጋ የሚከፍሉ ናቸው የሚባልላቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናን ከማዕከላዊና ቂሊንጦ በመናኞች ላይ እየተፈጸመ ያለውን ስቃይ እንዴት በዝምታ ተመለከቱት? ምን ነካቸው? ከነክህነት ልብሳቸው እጆቻቸው በብረት ካቴና ተቆላልፎ በአጋዚ ቅልብ ወታደሮች ተከበው በአደባባይ የሚታዩ የመንፈስ አባቶቻቸው ሁኔታ ምን ስሜት ሰጣቸው? በእውነት የኢትዮጵያ የተዋህዶ ልጆች ከየት ነው ያላችሁት? እነዚህ የዋልድባ መነኮሳት ታላቅ ግፍ እየተፈጸመባቸው እንዴት አስቻላችሁ? እንዴትስ እንቅልፍ ይወስዳችኋል? የእምነት ትርጉሙ ምንድን ነው? መንፈሳዊ ህይወት ሲባል እንዲህ ነውን? ግፍ እያዩ ዝም። አባቶች ሲዋረዱ ጸጥ። ቋርፍ በልተው የሚኖሩ፡ ስጋቸውን ለመንፈሳዊ ዓላማ ሲሉ ያደከሙ መናኞች ተዝቅዝቀው ሲገረፉ እንዳላየ፡ እንዳልሰማ ሆኖ ማለፍ።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
የኢትዮጵያ ኦሮቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፈተናዋ በዝቷል። የቤተመንግስት አጋንንት ከቧታል። በቅጥሯ የተሾሙት አባትና በየሀገረ ስብከቱ የተሰገሰጉት የትግራይ ገዢ ቡድን አባላት ቤተክርስቲያኒቱን አፍነው ይዘዋል። ለስለላ ብለው ገብተው ቆብ ደፍተው በዚያው እስከ ጵጵስና የደረሱ የትግራይ ገዡ ቡድን አባላት የአባይ ጸሀዬንና ስብሃት ነጋን ቃል እንጂ የመጽሀፍ ቅዱስን መንፈሳዊ ህግ የሚያከብሩ እንዳልሆነ ይታወቃል። ይህ በመሆኑም ከቤተክህነት የሚጠበቅ አንዳች ተስፋ የለም። በጉልበት የተሾሙት ፓትርያርክ አቡነ ማቲያስ የዋልድባ አባቶች መከራና ስቃይ ሲደርስባቸው፡ ቤተክርስቲያኒቱን የሚያዋርድ ተግባር ሲፈጸምባቸው፡ አንዲትም ቃል ሳይተነፍሱ ስልጣን አልባው ጠቅላይ ሚኒስትር ስልጣን ሲለቅ ቤተመንግስት ድረስ ዘልቀው ውዳሴና ቡራኬ የሚያቀርቡ፡ ከንቱ አባት በመሆናቸው ከእሳቸውም የሚጠበቅ ነገር የለም። ምዕመኑ ግን ምን ነካው? ከዚህ ልቆ የሚያስፈራ ምን አለ?</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ማህበረ ቅዱሳን የት ነው ያለው? የቤተክርስቲያኒቱን ገዳማትና ነዋየ ቅድሳት ከትውልድ ትወልድ ተጠብቆ እንዲቆይ እስከ ገጠር ቀበሌ ድረስ የዘለቀ መጠነ ሰፊ ተግባራትን በመከወን የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ዘብ ጠባቂ እንደሆነ የሚነገርለት ማህበረ ቅዱሳን የእነዚህን መናኞች ግፍና ስቃይ አልሰማ ይሆን? ወይስ ለመናኞች፡ ለመነኮሳት ደህንነትና ክብር እንዲጮህ መተዳደሪያ ደንቡ አይፈቅድለትም? ቢያንስ ክሳቸው በአግባቡ እንዲታይ፡ ሰብዓዊ መብታቸው እንዲከበር ለመጠየቅ የሚያስችል ወኔ ማህበረ ቅዱሳን ዘንድ እንዴት ሊጠፋ ቻለ? ገዳማት ያለመናኞች ምንድን ናቸው? ለገዳማት ተጨንቆ ለመንፈሳዊ አባቶች ግድ ማጣት ምን የሚሉት መንፈሳዊ መስመር ነው?</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
በእውነቱ እነዚህ አባቶች በማዕከላዊና ቂሊንጦ የደረሰባቸው ግፍ ለሃይማኖታቸው እስከመጨረሻው ዋጋ ይከፍላሉ በሚባሉ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ በሆኑ ኢትዮጵያውያን መኖሪያ በሆነችው ኢትዮጵያ መፈጸሙ ያስደነግጣል። አንድም ቀን በዚያ የግዞት ስፍራ ማደር አልነበረባቸውም። እንኳን ተዘቅዝቀው ሊገረፉ፡ ሰውነታቸው ላይ አንዲትም ዱላ ማረፍ አልነበረባትም። ምን ጉድ እንደመጣብን አላውቅም። እንዲህ ዓይነት ሰቆቃ እየተፈጸመ ዝምታችን ግራ ያጋባል። ለምን አባቶቻችን ታሰሩ ብሎ መጠየቅ እንዴት አልተቻለም? ለምን እንዲህ ክብራቸው ይነካል የሚል ድምጽ እንዴት ለጆሮአችን ይናፍቀናል? አባቶቹ እኮ አይደሉም የተዋረዱት። ማዕከላዊ ተዘቅዝቅው የተገረፉት መናኞቹ አይደሉም። እጆቻቸው በካቴና የተቆላለፈባቸው የዋልድባ መነኮሳት እኮ አይደሉም። አዎን! የተዋረደችው ቤተክርስቲያኒቱ ናት። ወፌ ላላ የተገረፈችው የአቡነ ጴጥሮስ ቅጥር የሆነችው የኦርቶዶክስ ቤት ናት። እጆቿ የታሰሩት እናት ቤተክርስቲያናችን ናት። ይህ ካላመመን፡ ይህ ካልቆጨን፡ ይህ ካልተሰማን በእውነት እኛ የተዋህዶ ልጆች ነንን?</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ድምጽ ይሰማል። የአባቶች የሲቃ ጩኸት።አብያተ ክርስቲያናት በየጸሎታቸው ሊያነችሷቸው ይገባል። ምዕመናን ዘውትር ከጸሎት ባሽገር የእምነት አባቶቻቸው ላይ ጫና በመፈጠር ስለተዋረደችው ቤተክርስቲያን ሲሉ ከፍርሃት ቆፈን ተላቀው ተቃውሞአቸውን ሊያሰሙ ግድ ይላል። እያሪኮም በጩኸት ፈርሳለች። እንጩህ! የግፈኞች ግምብ መፈረሱ አይቀርም። የቤተመንግስት አጋንንት ይለቀን ዘንድ በአንድነት እንጩህ። ልቦና ይስጠን።</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-10374213069966992682018-03-13T07:53:00.000-07:002018-03-13T07:53:22.280-07:00የነዳጅ አቅርቦት ማስተጓጎል ዘመቻ()<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px;">
<a href="https://i1.wp.com/ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2017/12/Mesay-Mekonnen-Articles.jpg?resize=300%2C160&ssl=1" imageanchor="1" style="clear: right; float: right; margin-bottom: 1em; margin-left: 1em;"><img alt="Mesay Mekonnen, ESAT journalist" border="0" src="https://i1.wp.com/ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2017/12/Mesay-Mekonnen-Articles.jpg?resize=300%2C160&ssl=1" /></a></div>
<div style="background-color: white; display: inline; margin-top: 6px;">
</div>
<div>
<div style="background-color: white; display: inline; margin-top: 6px;">
<span style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif;">መሳይ መኮንን</span></div>
</div>
<span style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif;">ቄሮ ቃሉን አያጥፍም። ባለፉት ሁለት ዓመታት በቄሮ ተጠርቶ ያልተሳካ የአድማም ሆነ የተቃውሞ ሰልፍ ከነበረ አላስታውስም። ከሁሉ የሚደንቀኝ በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት፡ የኦሮሚያን ክልል ከዳር እስከዳር ባናወጠው ህዝባዊ እምቢተኝነት በቄሮዎች እጅ ህይወቱን ያጣ ሰላማዊ ሰው አለመኖሩ ነው። የሚጠራው አድማ፡ የሚካሄደው ዘመቻ፡ የሚወሰደው እርምጃ የአገዛዙን የማፈናና የመግደል አቅም ከማላሸቅ ያለፈ የትኛውንም የህብረተሰብ ክፍል ለጉዳት የዳረገበት አጋጣሚ አልተፈጠረም። በእውነት የቄሮዎች ትግል እነመሀተማ ጋንዲ የእንግሊዝ የቅኝ ግዛት ዘመን እንዲጨልምና ከነግሳንግሱ ከምድር ገጽ እንዲጠፋ ያደረጉበትን አስደናቂ የእምቢተኝነት ትግል የሚያስታውስ ነው።</span><br />
<div>
<div style="background-color: white; display: inline; margin-top: 6px;">
<br /></div>
<div>
<div style="background-color: white; display: inline; margin-top: 6px;">
<span style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif;">በእርግጥ ቄሮዎች ዛሬ ላይ ላቀጣጠሉት እምቢተኝነት እርሾው ቀደም ተብሎ የተዘጋጀ መሆኑን እዚህ ላይ መጥቀስ ያስፈልጋል። ኢትዮጵያ ውስጥ የትግራይ አገዛዝ ቤተመንግስት ከገባ ጀምሮ ትግል ነበር። በተለያዩ አካላት ሲደረግ የነበረው እልህ አስጨራሽ የነጻነት ተጋድሎ በቅብብሎሽ እዚህ ዘመን ላይ ደርሷል።</span></div>
<a name='more'></a><span style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif;"> በተናጠልና በጋር የተደረጉ ንቅናቄዎች ያበሰሉት የኢትዮጵያውያን ትግል ለቄሮዎች መንገዱን በመጥረግ ረገድ አስተዋጽኦው በታሪክ በደማቁ የሚመዘገብ ነው። በተለይም የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ትግል ምንጊዜም የሚታወስ፡ በሰላማዊ እምቢተኝነት የኢትዮጵያውያንን የነጻነት ትግል አንድ ምዕራፍ ወደ ፊት የወሰደ ታላቅ ተጋድሎ መሆኑን መጠቀስ ግድ ይላል። እናም ቄሮዎች እንደዱላ ቅብብል የተጀመረውን የነጻነት ተጋድሎ አድምቀው ተያይዘውታል።</span></div>
<div>
<div style="background-color: white; display: inline; margin-top: 6px;">
<span style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif;"> </span><br /><span style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif;">የቄሮዎች ትግል በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መስመሩን በትክክል ይዞ ሌላውን ኢትዮጵያዊ ከሚጋብዝበት መድረክ ላይ ወጥቷል። ክልላዊ ስሜት ያጠላበት፡ ለሌላው የሚጎረብጥ የሚመስለው፡ በመልዕክቱና በእንቅስቃሴው ሁሉን አሳታፊ ያልነበረው የቄሮዎች ትግል ወሳኝ ለውጥ አድርጓል። አዳማ፡ ጂማ፡ አምቦ በቄሮዎች የተላለፉት የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች የሌላውን ኢትዮጵያዊ ልብ የሚከፍቱ፡ ለአብሮነት ትግል መደላድል የሚፈጥሩ በመሆናቸው በቄሮዎች ትግል ብዥታ ውስጥ ለነበረ፡ በጥርጣሬ የዳር ተመልካች ሆኖ ለሰነበተ ምላሽ የሰጠ የትግል አቅጣጫን ይዟል። እንግዲህ ሜዳውም ፈረሱም አለ። አብሮ ከመታገል ውጪ ምርጫ የለም። ለጋራ ድል በእኩል መስዋዕትነት መክፈሉ ለቀጣዩ አብሮነታችንም ዋስትናው እንደብረት የጠነከረ ይሆናል።</span></div>
</div>
<div>
<div style="background-color: white; display: inline; margin-top: 6px;">
<span style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif;"><br />ለነገ የተጠራው ዘመቻ በቄሮውች እስከዛሬ ከተደረጉት አድማዎች የበለጠ ውጤታማና አገዛዙን ሽባ በማድረግ ረገድ ክፍተኛ ተጽዕኖ የሚፈጥር እንደሆነ ይሰማኛል። የቄሮዎች ትግል እያደገ፡ እየተመነደገ፡ በዕውቀትና ብልሃት እየተመራ ለመሆኑ የነገው ዘመቻ ትልቅ ማሳያ ነው። ነዳጅ ላይ የሚጠራ አድማ ውጤቱ የአገዛዙን የስልጣን ወንበር እስከመፈንቀል የሚደርስ ሊሆን እንደሚችል ይታመናል። ነዳጅ ያልገባበት የህይወታችን እንቅስቃሴ የለም። ነዳጅ ደምስር ነው። የአንድ ሀገር የጀርባ አጥንት፡ የሁለንተናዊ መዘውር አንቀሳቃሽ ሞተር ነው። እናም የነገው ዘመቻ ሀገሪቱን ቀጥ አድርጎ፡ ከየትኛውም እንቅስቃሴ ገድቦ፡ የሚያስቀር እንደሚሆን ይታመናል። በተለይ ለአገዛዙ ብርቱ ፈተና ከመሆን ባለፈ ሀገሪቱን ለመቆጣጠር የሚያስችለውን አቅም የሚያሳጣው፡ ከቆየና ከጠነከረ ደግሞ እስከወዲያኛው የሚያሰናብተው ስለመሆኑ ከቶም አልጠራጠርም።</span></div>
</div>
<div>
<div style="background-color: white; display: inline; margin-top: 6px;">
<span style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif;"><br />ነገ ተጀምሮ ለሳምንት የሚዘልቀውን የነዳጅ ዝውውርን የማስተጓጎል ዘመቻ እንዲሳካ የቄሮዎች ጥረትና መስዋዕትነት ብቻውን በቂ አይደለም። ውጤታማም አይሆንም። ከመቀሌ እስከ ሞያሌ፡ ከከቤንሻንጉል ጉምዝ እስከ ሀረር የተዘረጋ፡ ሁሉን ያሳተፈ፡ በሁሉም ክልል ተግባራዊ እንዲሆን ማድረግ ያስፈልጋል። የነዳጅ አቅርቦቱ በአብዛኛው በሱዳን በኩል የሚገባ በመሆኑ ከመተማ ጀምሮ ያለው የኢትዮጵያ ህዝብ የነገውን ዘመቻ በባለቤትነት ሊመራው ይገባል። በመተማ መስመር ከዚህ በፊት ከ5በላይ የነዳጅ ቦቴ ተሽከርካሪዎች እንደጧፍ የነደዱበትን አደጋ የጣሉት የሰሜኖቹ ፋኖዎች የነገውን ዘመቻ ተፈጻሚ ለማድረግ የሚገድባቸው ነገር ይኖራል ብዬ አላምንም። ከመተማ ጎንደር፡ ከመተማ ሁመራ የሚወስዱትን መንገዶች ለነዳጅ አመላላሽ ተሽከርካሪዎች ዝግ ማድረግ፡ ለባለንብረቶችም መልዕክት በማስተላለፍ እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ ከማስጠንቀቂያ ጋር ማሳወቅ ይገባል። ተደርጓልም ብዬ አምናለሁ።</span></div>
</div>
<div>
<div style="background-color: white; display: inline; margin-top: 6px;">
<span style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif;"> </span><br /><span style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif;">የነገው ዘመቻ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስር በወደቀችው፡ ደም በጠማቸው የአጋዚ ወታደሮች በታፈነችው፡ የትግራይ አገዛዝን የዕልቂት አዋጅ ለማስፈጸም በተሰማራው የመከላከያ ሰራዊት ማንቁርቷን በተያዘችው ኢትዮጵያችን የሚከናወን በመሆኑ መስዋዕትነቱ ከባድ ሊሆን ይችላል። ቄሮዎች ዘመቻውን በትንሽ መስዋዕትነት፡ በግዙፍ ስኬት ለማጠናቀቅ የሚያስችል ዕቅድ እንዳላቸው ስለማምን በዚህ በኩል ብዙም ስጋት አይኖረኝም። በዚህ ላይ የነዳጅ አመላላሽ ተሽከርካሪ ባለቤቶች ቢያንስ ንብረቶቻቸውን ከአደጋ ለመጠበቅ ሲሉ፡ ገፋ ካለም ለነጻነት የሚደረገውን ትግል ለመደግፍ ብለው ተሽከርካሪዎቻቸውን ከስምሪት ውጭ ያደርጋሉ የሚል ተስፋም ውስጤ አለ።</span></div>
</div>
<div>
<div style="background-color: white; display: inline; margin-top: 6px;">
<span style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif;"><br />ጥንቃቄም ያስፈልጋል። የትግራይ አገዛዝ ከቄሮዎች ጥሪ ጋር ተመሳሳይ የሆነ ነገር ግን የእርስ በእርስ ግጭትንና ጥፋትን የሚጋብዝ መልዕክት አሰራጭቷል። በቄሮ ስም የተበተነው መልዕክት የነዳጅ ማደያዎችን በእሳት ማጋየት፡ በትግራይ ተወላጆች ንብረቶች ላይ ጥቃት መፈጸምና ሌሎች እርምጃዎች እንዲወሰዱ የሚጠይቅ ነው። ቄሮዎች እንዲህ ዓይነት ጥሪ አላደረጉም። እውነተኛው ጥሪ ግልጽና ጥርት ያለ ነው። የነዳጅ ተሽከርካሪዎች እንዳይዘዋወሩ ማድረግ ብቻ ነው። ወደ ሀገር ቤት የሚገቡና በውስጥም ነዳጅ የሚያመላልሱ ተሽከርካሪዎች ለአንድ ሳምንት ከእንቅስቃሴ ውጭ ሆነው እንዲቆሙ የተጠራ ዘመቻ ነው። ከዚህ የሚጨምርም የሚቀንስም ዓላማ የለውም። </span></div>
</div>
<div>
<div style="background-color: white; display: inline; margin-top: 6px;">
<span style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif;"><br />ከደህንነት አከባቢ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተውም በአዲስ አበባና በአንዳንድ የሀገሪቱ አከባቢዎች በተለይ በነዳጅ ማደያ አከባቢዎች ፍንዳታ ለመፈጸም አገዛዙ በስውር ተዘጋጅቷል። ይህን ሴራ ማክሸፍ የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው። አጥፍቶ ለመጥፋት ቆርጦ የተነሳው የትግራዩ አገዛዝ የቄሮውችን ትግል ጥላሸት ለመቀባትና የነገውን ዘመቻ በኢትዮጵያውያን ዕልቂት እንዲጠናቀቅ ሃላፊነት የጎደለው እርምጃ ሊወስድ መሆኑ ሾልኮ የወጣ መረጃ ላይ ተመልክቷል። በመሆኑም ህዝባችን ይህን አውቆ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርበታል። </span><br /><span style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif;">ነገ ሁላችንም ቄሮዎች ነን!!!!!!</span></div>
</div>
</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-84076480334123697882018-03-10T06:46:00.000-08:002018-03-10T06:46:12.038-08:00“የክርስቲያን አገር በሆነችው ሙስሊሞች ሊነግሡባት ነው” ህወሓት ለአሜሪካ እንደራሴዎች<img src="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/03/1-more-chance-e1520602937879-620x310.jpg" /><br />
<div class="entry-content" style="background-color: white; font-family: Verdana, Geneva, sans-serif; overflow: hidden;">
<div class="pf-content">
<ul style="margin: 0px; padding: 0px 0px 15px;">
<li style="list-style-type: square; margin: 0px 0px 0px 30px; padding: 0px; text-align: justify;"><strong>የአስራ ሰባት ታዋቂ ኦሮሞ ሙስሊሞችን ስም ለማስረጃነት አቅርቧል</strong></li>
<li style="list-style-type: square; margin: 0px 0px 0px 30px; padding: 0px;"><strong>ከዝርዝሩ ውስጥ የዶ/ር አቢይ አህመድ ስም ይገኝበታል</strong></li>
</ul>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ህወሓት ከፊቱ የተጋረጠበትን የፖለቲካ ቀውስና ቀውሱን ተከትሎ ከጌቶቹ የተነሳበትን ተቃውሞና ግፊት አቅጣጫ ለማስቀየር ሃይማኖትን የተንተራሰ ስልት ተግባራዊ ማድረጉ ተሰማ። የሚካሄደው ህዝባዊ ተቃውሞ አገሪቱን ለእስልምና አክራሪ አሳልፎ ለመስጠት ያለመ እንደሆነ ህወሓት በወኪሉ በኩል ስም ዘርዝሮ አቅርቧል።</div>
<a name='more'></a><br />
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<span style="color: black;"><a href="http://www.goolgule.com/a-christian-land-to-be-invaded-by-muslims-tplf-to-us-congress/" rel="noopener" style="text-decoration-line: none;" target="_blank">የጎልጉል ዲፕሎማት የመረጃ</a> አቀባዮች ከዋሽንግቶን ዲሲ እንዳስታወቁት ህወሓት አሁን የተነሳበትን ዙሪያ ገጠም ተቃውሞ ከእስልምና አክራሪነት ጋር በማቆራኘት የአስራ ሰባት ኦሮሞ ሙስሊም ታዋቂ ፖለቲከኞችን፣ የመብት ተሟጋቾችን፣ ወዘተ ስም ዘርዝሮ ነው ያቀረበው።</span></div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ዙሪያው ገደል የሆነበት ህወሓት የስም ዝርዝሩን ባቀረበ ጊዜ ራሱን የክርስቲያን መንግሥት አድርጎ ለማሳየት ሞክሯል። ይህቺ አገር የክርስቲያን ደሴት ነች፤ እስካሁን ኢትዮጵያን ከመሩት ሁሉ ለሃይማኖት ነጻነት የሰጠነው እኛ ነን፤ የክርስትና እምነታችንን በመጠበቅም ከሆነ እንደ እኛ እስካሁን በትጋት የሠራ የለም፤ ሙስሊሞች ይህችን የክርስቲያን አገር ሊቆጣጠሯት ቆርጠው ተነስተዋል፤ ይህ ካልተገታ አገሪቱ ትበታተናለች – ሃይማኖቱም ያከትምለታል የሚሉ አቅጣጫ የማስቀየሪያ ማስፈራሪዎችን የሎቢ (ውስወሳ) ሥራ በሚያከናውንለት ድርጅት አማካኝነት ህወሓት አቅርቧል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
እነዚህን በአገር ውስጥና በውጪ የሚገኙ ታዋቂ ኦሮሞ ሙስሊሞችን ስም በመዘርዘር፤ የማምለጫ ሰነድ በማዘጋጀት፤ በቀጠራቸው ሎቢስቶች አማካይነት የውስወሳ ሥራ የጀመረው ህወሓት ጉዳዩ በጣት በሚቆጠሩ እንደራሴዎች (የኮንግሬስ አባላት) ዘንድ ይሁንታ እንዳገኘለት የመረጃ ምንጮቹ አመልክተዋል። ህወሓት የፕሮፓጋንዳ ዒላማውን ያነጣጠረው ወግአጥባቂ በሆኑ፣ በኢትዮጵያ ለዘመናት ሙስሊምና ክርስቲያን እንዴት በሰላምና ፍቅር እንደኖሩ ጠለቅ ያለ ግንዛቤ በሌላቸው እንደራሴዎች ላይ መሆኑን የጎልጉል መረጃ አቀባዮች አረጋግጠዋል። በግምባር ቀደምትነትም <a href="http://www.goolgule.com/inhofe-on-a-rescue-mission/" style="text-decoration-line: none;">የህወሓት ወዳጅ የሆኑት ሴናተር ኢንሆፍ ህወሓት/ኢህአዴግን ለመታደግ</a> ኢትዮጵያ ድረስ እስኪሄዱ ያደረሰ የውትወታ መካሄዱ የሚታወስ ነው።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
እነዚሁ ክፍሎች እንዳሉት ለጠቅላይ ሚኒስትርነት ተስፋ የተጣለባቸውና የክርስትና (የፕሮቴስታንት) እምነት ተከታይ እንደሆኑ የሚነገርላቸው አቢይ አህመድም (ዶ/ር) በስማቸው ብቻ ሙስሊም ከሆኑ ታዋቂ ኦሮሞዎች ጋር በመቆራኘታቸው ለኃላፊነት እንደማይበቁ ከአስራ ሰባቱ ስም ዝርዝር ጋር ተካትተው ቀርበዋል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
የዋልድባን ገዳም ከማፍረስ ጀምሮ መንኩሴዎችን፣ የጸሎት ሰዎችን፣ የእምነት መሪዎችንና ህዝብ የሚያከብራቸውን የእምነት እሴቶች እያወደመ ያለው ህወሃት፣ አሁን ለክርስትና ተቆርቋሪ ሆኖ መቅረቡ ያስገረማቸው፣ “አሁን የተመዘዘው የነፍስ አድን ካርድ ነገሮችን እጅግ ሊያወሳስብ ይችላል። አርፈው የተቀመጡና በዜግነታቸው ብቻ ለውጥ የሚጠይቁትን የኅብረተሰብ ክፍሎች ወደማይሆን መንገድ እንዳይገፋቸው እንፈራለን” ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። ከዚህ አኳያ ትግሉን እየመሩ ያሉ ይህንን የህወሓት መሠሪ አስተሳሰብ አስቀድመው ተረድተው አንድነት፣ ኅብረት፣ አብሮነት፣ መደመር ላይ አበክረው እንዲሠሩ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<span style="color: black;"><a href="http://www.goolgule.com/tplfs-threat-hr-128-and-the-global-magnitsky-act/" style="text-decoration-line: none;">ከማግኒትስኪ ሕግ ጋር ተጋብቶ የቀረበው HR 128</a> በሕዝብ ላይ አስከፊ ግፍ ሲፈጽሙ የነበሩትንና በጠራራ ፀሐይ ሕዝብን ሲዘርፉ የኖሩትን የህወሓት <a href="http://www.goolgule.com/hr-128-a-threat-to-tplf-and-their-cronies/" style="text-decoration-line: none;">ሹሞችና ቤተሰቦች መግቢያ ያሳጣ ሆኗል</a>። ይህ ረቂቅ ሕግ በአዋጅ እንዳይወጣ ሲከላከል የነበረው ህወሓት፤ በቅርቡ <a href="http://www.goolgule.com/workinehs-campaign-to-be-pm-exposed/" style="text-decoration-line: none;">በወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ”</a>አማካኝነት አልሸባብን ማስፈራሪ አድርጎ ለአሜሪካ ፖሊሲ አውጪዎች ማቅረቡ ይታወሳል። እኛ <a href="http://www.goolgule.com/tplf-suspected-as-partner-of-al-shabab/" style="text-decoration-line: none;">ሥልጣኑን ካልቀጠልን አልሸባብ መላውን</a> የአፍሪካ ቀንድ ባጭር ጊዜ ውስጥ ይቆጣጠራል በማለት በመለስ ስልት ለመጫወት ያቀደው ሳይሳካለት ወደመጣበት መመለሱ የሚታወስ ነው።</span></div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
በቅርቡ ለውይይትና ለድምፅ ይቀርባል የተባለውን HR 128 የህግ ረቂቅ <a href="http://www.goolgule.com/somalia-car-bomb-and-tplf-who-works-to-thwart-hr-128/" style="text-decoration-line: none;">ለማምለጥ ሁሉንም ዓይነት ካርድ ሲስብ</a> የኖረው ህወሃት፣ <a href="http://www.goolgule.com/ethiopia-to-be-under-a-total-military-rule/" style="text-decoration-line: none;">ስልታዊ መፈንቅለ መንግስት</a> ካካሄደ በኋላ በአስቸኳይ አዋጅ ስም ከውስጥ በጥይት፣ አፈናና የጅምላ እስር፤ ከውጭ በፍረጃ ለማምለጥ በወስዋሾቹ አማካይነት ድጋፍ እያሰባብሰበ መሆኑን ጎልጉል ከሌሎች ለጉዳዩ ቅርብ ከሆኑ ክፍሎች አረጋግጧል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ከዚህ ጋር በተያያዘ በቡድን ለማ ሥር የአቢይ አህመድ ለጠ/ሚ/ር ሥልጣን ይበቃል የሚለው አስተሳሰብ እያየለ በመምጣቱ በተለይ በአገር ውስጥ በህወሓት በጀት በሚቆረጥላቸው ደጋፊ የማኅበራዊ ገጽ ሚሊሺያዎችና ካድሬዎች የአቢይን ስም የማጥፋት ዘመቻ መክፈታቸው ከሰሞኑ እንቅስቃሴያቸው ለመረዳት ይቻላል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ህወሓት እገዛዋለሁ የሚለው ሕዝብ ከከዳው በኋላ ባለቀ ሰዓት የከፈተው ይህ አጀንዳ እንደጠበቀው የበርካታ እንደራሴዎችን አመኔታ አላገኘም። በተለይ ከ“ድምጻችን ይሰማ” የሙስሊሞች የመብት ጥያቄ ጀምሮ የኢትዮጵያን ጉዳይ በቅርብ የሚከታተሉ ነባር እንደራሴዎች፤ ጥያቄያቸውን በሰለጠነና ሰላማዊ በሆነ መልኩ ሲቀርቡ በነበሩ ሙስሊሞች ላይ የህወሓት ታጣቂዎች የፈጸሙትን ኢሰብዓዊ ግፍ በማስታወስ ይህንን የህወሓት ማምታቻ ከመስማት ባለፈ ለመደገፍ የማይቻልና በቂ ማስረጃ ያልቀረበበት መላምት አድርገው በመውሰድ ይበልጡኑ <a href="http://www.goolgule.com/hr-128-a-threat-to-tplf-and-their-cronies/" style="text-decoration-line: none;">በHR 128</a> ላይ እየሠሩ መሆናቸውን ጎልጉል ያገኘው መረጃ ይጠቁማል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<a href="http://www.goolgule.com/a-christian-land-to-be-invaded-by-muslims-tplf-to-us-congress/" target="_blank">http://www.goolgule.com/a-christian-land-to-be-invaded-by-muslims-tplf-to-us-congress/</a></div>
</div>
</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-69215288202646708792018-03-01T06:21:00.000-08:002018-03-01T06:21:12.563-08:00ህወሓት፡ የHR 128 ፍርሃቻ እና የማግኒትስኪ ሕግ<div class="post-info" style="background-color: white; color: #333333; font-family: Verdana, Geneva, sans-serif; font-size: 11px; margin: 0px 0px 15px;">
<span class="date published time" style="background: url("images/icon-time.png") left top no-repeat; padding: 2px 0px 2px 21px;" title="2018-02-27T22:49:38+00:00"><img src="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/02/tplf-and-Magnitsky-Act-e1519797187533-620x310.jpg" style="background-color: transparent;" /></span></div>
<div class="entry-content" style="background-color: white; font-family: Verdana, Geneva, sans-serif; overflow: hidden;">
<div class="pf-content">
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ከዚህ በፊት በአሜሪካ ምክርቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በረቂቅ ሕግነት ከቀረቡት መካከል ህወሓት/ኢህአዴግ HR 128 እጅግ ፈርቶታል። ይህንን ረቂቅ ሕግ ለማክሸፍም የውትወታ (ሎቢ) ሥራ ከመሥራት ጀምሮ የአሜሪካ ባለሥልጣናትንና የፖለቲካ መሪዎችን <a href="http://www.goolgule.com/somalia-car-bomb-and-tplf-who-works-to-thwart-hr-128/" style="text-decoration-line: none;">በ“አልሻባብ ምስራቅ አፍሪካን ይወራል” ድራማ ለማስፈራራት ተደጋጋሚ</a> በርካታ ሙከራዎችን ቢያደርግም አልተሳካለትም። ላለፉት በርካታ ወራትም (በቅርቡ ወደ አሜሪካ የመጡትን እነ <a href="http://www.goolgule.com/tplf-decides-workineh-to-be-the-next-pm/" style="text-decoration-line: none;">ወርቅነህን ጨምሮ) ሊያሳምኑ ይችላሉ</a> የሚላቸውን ሹሞቹን በመላክ ረቂቅ ሕጉ በተግባር እንዳይውል የአሜሪካ ባለሥልጣናትንን – ጊዜ ስጡን፣ ሁሉን እናስተካክላለን፣ … የመሳሰሉ ተማጽንዖዎችን ሲያቀርብ ቆይቷል። በግምባር ቀደምትነትም <a href="http://www.goolgule.com/inhofe-on-a-rescue-mission/" style="text-decoration-line: none;">የህወሓት ወዳጅ የሆኑት ሴናተር ኢንሆፍ ህወሓት/ኢህአዴግን ለመታደግ</a> ኢትዮጵያ ድረስ እስኪሄዱ ያደረሰ የውትወታ ሥራ ተካሄዷል።</div>
<a name='more'></a><br />
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ይህንን ረቂቅ ህግ ገና <a href="http://www.goolgule.com/hr-128-a-threat-to-tplf-and-their-cronies/" style="text-decoration-line: none;">ከጅምሩ የፈራው ህወሓት ለወትዋቾች (ሎቢይስቶች)</a> በጀት መድቦ መንቀሳቀስ <a href="http://almariam.com/wp-content/uploads/2017/04/Ethiopia-SGR-Lobby-Agreement-Jan-2017.pdf" style="text-decoration-line: none;">ከጀመረ አንድ ዓመት አልፎታል</a>። በዋሽንግቶን ዲሲ የኢህአዴግ ጽ/ቤት ተጠሪ የነበረው ግርማ ብሩ SGR Government Relations ከተባለ የወትዋቾች ድርጅት ጋር በተፈራረመው ሰነድ ላይ በግልጽ እንደተመለከተው ለዚህ የውትወታ ሥራ ድርጅቱ (SGR) በወር <a href="http://almariam.com/wp-content/uploads/2017/04/Ethiopia-SGR-Lobby-Agreement-Jan-2017.pdf" style="text-decoration-line: none;">150ሺህ ዶላር፤ በጥቅሉ 1.8 ሚሊዮን ዶላር ተከፍሎት ረቂቅ ሕጉን የማክሸፍ ዘመቻ እንዲሠራ ስምምነት ተደርጓ</a>ል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ይህንን ሁሉ አድርጎ <a href="http://www.goolgule.com/the-sun-is-setting-on-hr-128sr-168/" style="text-decoration-line: none;">ረቂቅ ሕጉ ፀሐይ እንድትጠልቅበት በሥፋት ሲንቀሳቀስ</a> የነበረው ህወሓት ድርጎ ሰፋሪዎቹን ያሁኑን ማሩኝ ሁሉን አስተካክላለሁ፤ እስረኞችን እፈታለሁ፤ … በማለት ተማጽንዖ በማቅረቡ እስከ ፌብሩዋሪ 28 ድረስ ገደብ ተሰጥቶታል። በማንም በምንም አንደፈርም እያለ ምስኪኖች ላይ ሲደነፋ የነበረው ህወሓት ይህ ረቂቅ ሕግ ለምንድነው ይህንን ያህል ያስፈራው? ለሚለው ጥያቄ ብዙ ምላሾች ቢኖሩም ዋንኛው ግን በረቂቅ ሕጉ ውስጥ የተጨመረው የማግኒትስኪ ሕግ ነው።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
የHR 128 <a href="https://www.congress.gov/bill/115th-congress/house-resolution/128/text?format=txt" style="text-decoration-line: none;">ረቂቅ ሕግ ተራ ቁጥር 8 እንዲህ ይላል</a>፤ “(ዜጎችን) ያለ ፍርድ በመግደል፣ በማሰቃየት (ቶርቸር በማድረግ)፣ ወይም ሌሎች በዓለምአቀፍ ደረጃ ዕውቅና የተሰጣቸውን የከፉ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች በማንኛውም ዜጋ ላይ በኢትዮጵያ ውስጥ የፈጸሙ “በዓለምአቀፉ የማግኒትስኪ የሰብዓዊ መብቶች ተጠያቂነት ሕግ” መሠረት ማዕቀብ እንዲጣልባቸው የውጭ ጉዳይ ሚ/ር (ስቴት ዲፓርትመንት) ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር እንዲተገብር (የአሜሪካ) እንደራሴዎች ምክርቤት ጥሪ ያደርጋል”።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ለመሆኑ ይህ ዓለምአቀፉ የአሜሪካ የማግኒትስኪ የሰብዓዊ መብቶች ተጠያቂነት ሕግ ምንድነው? ህወሓትስ የፈራው ለምንድነው? ከHR 128 ጋር ተዳብሎ በረቂቅ ሕጉ ውስጥ መካተቱ ለምን አስፈለገ? የሚያስከትለውስ ተጽዕኖ ምንድነው? ይህንን እና የመሳሰሉ ጥያቄዎችን <a href="https://www.hrw.org/news/2017/09/13/us-global-magnitsky-act" style="text-decoration-line: none;">ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ ጥበቃ ድርጅት (Human Rights Watch) በድረገጹ ላይ በጥያቄና መልስ ያቀረበውን</a> ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ በዚህ መልኩ ተርጉመን አቅርበነዋል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<strong>አጭር መግቢያ</strong></div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ሕጉ የተሰየመው ሩሲያዊው የንግድ ሒሳብ ሠራተኛ በነበረው ሰርጊዬ ማግኒትሰኪ ነው። ሰርጊዬ በሩሲያ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት የተሳተፉበትን ግዙፍ የግብር ማጭበርበር ዕቅድ በማጋለጥ ውስጥ በተጫወተው ሚና ባለሥልጣናቱ እርሱን ዒላማ በማድረግ ካሳሰሩት በኋላ እኤአ በ2009 ዓም በሞስኮ በሚገኝ እስርቤት ስቅየት ደርሶበት (ቶርቸር ተደርጎ) እና የህክምና ዕርዳታ እንዳያገኝ ተከልክሎ እዚያው ሞቶ ተገኘ።</div>
<div class="wp-caption alignright" id="attachment_19911" style="background-color: whitesmoke; float: right; margin: 5px 0px 20px 20px; max-width: 310px; padding: 10px; text-align: center;">
<div class="wp-caption-text" style="line-height: 16px; margin-top: 4px; padding: 5px 0px;">
<img src="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/02/Sergei_Magnitsky-300x200.jpg" />ሰርጊዬ ማግኒትሰኪ</div>
</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
በሰርጊዬ ማግኒትስኪ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ላይ ተሳትፎ በነበራቸው የሩሲያ ባለሥልጣናት ላይ የአሜሪካ ኮንግረስ በ2012 ዓም በስሙ ሕግ አወጀ። ሕጉም እነዚህ ወንጀለኞች በአሜሪካ ያላቸው ማንኛውም ንብረታቸው እንዲታገድ እነርሱም ወደ ዩናይትድ ስቴትስ እንዳይገቡ በጥብቅ የሚያግድ ሆኖ የታወጀ ነው።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
በቀጣይ ጉዳዩን ዓለምአቀፋዊ ተጠያቂነት በሚያስከትል መልኩ ለመተግበር ኮንግረስ በሩሲያ ላይ ብቻ ትኩረት በማድረግ ያጸደቀውን ሕግ በ2016 ዓም ዓለምአቀፋዊ ይዘት እንዲኖረው በማሰብ አሳደገው። በዚህም መሠረት ሕጉ የሥራ አስፈጻሚውን ቅርንጫፍ በተለይ የሰብዓዊ መብቶችን ጥሰት የፈጸሙና በሙስና የተዘፈቁ የተወሰኑ ግለሰቦችን ቪዛ ለመከልከልና በዓለም ላይ በየትኛውም ቦታ ቢገኙ ማዕቀብ ለመጣል የሚያስችል ፈቃድ እንዲኖረው በሚያደርግ መልኩ የሰፋ ሆነ። ይህ በሁለቱም የአሜሪካ ፓርቲዎች ድጋፍ ያገኘ ሲሆን ረቂቅ ሕጉን ዓለምአቀፋዊ ይዘት በመጨመር አስተካክለው የሜሪላንዱ ጠቅላይ ግዛት ዴሞክራት ሴናተር ቤን ካርዲን አምስት ሪፓብሊካን እና አምስት ዴምክራት ሴናተሮችን በማስፈረም የረቂቁ ተባባሪ ስፖንሰሮች እንዲሆኑ በማድረግ በሕግ እንዲጸድቅ አደረጉ። በቀጣይም ፕሬዚዳንት ኦባማ ሥልጣናቸውን ከመልቀቃቸው አንድ ወር በፊት ፊርማቸውን በማኖር ሕግ ሆኖ እንዲፀድቅ አደረጉ።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<strong>ዓለምአቀፉ የማግኒትስኪ ሕግ የሚያደርገው ምንድነው?</strong></div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<span style="color: black;"><a href="https://www.congress.gov/bill/114th-congress/senate-bill/284/text" style="text-decoration-line: none;">ዓለምአቀፉ የማግኒትስኪ የሰብዓዊ መብቶች የተጠያቂነት ሕግ</a> (<a href="https://www.congress.gov/bill/114th-congress/senate-bill/284/text" style="text-decoration-line: none;">Global Magnitsky Human Rights Accountability Act</a>) የተወሰኑ “የውጭ ሰዎችን” (ግለሰብ ወይም ድርጅት ሊሆን ይችላል) ቪዛ እንዳያገኙ ለመከልከል፣ ለመሻር፣ ለመዘረዝ፣ ለመንጠቅ እንዲችል ወይም ንብረታቸው ላይ ማዕቀብ እንዲጣል ለፕሬዚዳንቱ ሙሉ ሥልጣን ይሰጣል። ሰዎች ማዕቀብ የሚጣልባቸው፤</span></div>
<ol style="margin: 0px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<li style="list-style-type: decimal; margin: 0px 0px 0px 35px; padding: 0px;">“ፍትህ ሳይበየን ግድያ፣ ስቅየት (ቶርቸር ማድረግ) ወይም በዓለምአቀፍ ደረጃ ዕውቅና የተሰጣቸውን አስከፊ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶችን” በሌሎች ሰዎች ላይ ከፈጸሙ፤ ወይም</li>
<li style="list-style-type: decimal; margin: 0px 0px 0px 35px; padding: 0px;">የመንግሥት ባለሥልጣናት ወይም የመንግሥት ባለሥልጣናት ከፍተኛ ተባባሪዎች በመሆን “መጠነ ሰፊ የሙስና ተግባር” ከፈጸሙ ነው</li>
</ol>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<strong>ዓለምአቀፉ የማግኒትስኪ ሕግ ለምንድነው ጠቃሚ መሳሪያ የሆነው?</strong></div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ሕጉ የሰብዓዊ መብቶች በሁሉም የመንግሥት የሥልጣን ዕርከኖች እንዲከበሩ የሚያበረታታ ሲሆን የሰብዓዊ መብቶችን በጣሱ ከከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ጀምሮ እስከ ዝቅተኛ ግለሰቦች ድረስ ይህም መንግሥታዊ ያልሆኑ ተባባሪዎቻቸውን ጨምሮ በእነርሱ ላይ ያነጣጠረ ማዕቀብ የአሜሪካ የሥራአስፈጻሚው አካል እንዲጥል የሚያስችል ነው። ይህ ማዕቀብ በአሜሪካ ውስጥ የሚገኝ ማንኛውንም ንብረት ሆነ ገንዘብ ከማገድ ጀምሮ ግለሰቦቹ ወደ አሜሪካ እንዳገቡ ቪዛ እስከመከልከለ የዘለቀ ነው። … ይህንን ሕግ በማስከበር አገራት ከአሜሪካ ጋር በሚያብሩበት ጊዜ በአገራቸው ለሚገኙ የሰብዓዊ መብቶችን ለሚጥሱ ግፈኞች ትዕግስት እንደሌላቸው ያሳያሉ።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<strong>ዓለምአቀፉ የማግኒትስኪ ሕግ የሚጥለው ማዕቀብ ምን ያህል ውጤታማ ነው?</strong></div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
የሚጣለው ማዕቀብ ግለሰቦችን ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ ማገድ፣ በዚህ አገር ውስጥ ያላቸውን ንብረት መቆጣጠር እና ከበርካታ ባንኮች እና ኩባንዎች ጋር ምንም ዓይነት የንግድ ልውውጥ እንዳያደርጉ መከልከልን ያካተተ ነው። ከእነዚህ ማዕቀብ ከተጣለባቸው ግለሰቦች ጋር ምንም ዓይነት የንግድ ልውውጥ የሚያደርጉ የአሜሪካ ድርጅቶች እና/ወይም አሜሪካ ቅርንጫፍ ያላቸው ዓለምአቀፍ ድርጅቶች ይህንን ሕግ እንደጣሱ ተቆጥሮ በሕግ ይጠየቃሉ።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<strong>ፕሬዚዳንት ትራምፕ በዚህ ሕግ ላይ ያላቸው አቋም ምንድነው?</strong></div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ባፈው ዓመት ሚያዚያ ወር (ኤፕሪል 20፣2017) ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለኮንግሬስ አባላት <a href="https://www.whitehouse.gov/the-press-office/2017/04/20/letter-president-certain-congressional-committee-chairs" style="text-decoration-line: none;">በላኩት ደብዳቤ የእርሳቸው</a> አስተዳደር ይህንን “አስፈላጊ ሕግ እንደሚደግፍ” እና “ለተግባራዊነቱ ያለንን ቁርጠኝነት” እንገልጻለን ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪም ፕሬዚዳንቱ በደብዳቤያቸው እንደገለጹት አስተዳደራቸው ሕጉ ተግባራዊ ሊደረግባቸው የሚገቡ ግለሰቦችንና ድርጅቶችን በመለየት ሂደት መሆኑን በመጠቆም “በተግባር ለመፈጸም አስፈላጊውን ማስረጃ እየተሰበሰበ” እንደሆነ ገልጸዋል። እስካሁን በሥልጣን በቆዩባቸው ወራት የሰብዓዊ መብቶች ጥበቃን በተመለከተ ይህ ነው የሚባል ተግባር ባይፈጽሙም፤ ፕሬዚዳንቱ ዓለምአቀፉ የማግኒትስኪ ሕግ ተግባራዊ በማድረግ በሰብዓዊ መብቶች ላይ ጥበቃ ማድረግ አሁንም የአሜሪካ የውጭ ፖሊሲ መሠረታዊ ዓላማ መሆኑን የማሳየት ዕድሉ አላቸው።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<strong>ግለሰቦች ማዕቀብ እንዲጣልባቸው ለፕሬዚዳንቱ ሐሳብ የሚያቀርበው ማነው?</strong></div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ሕጉ እንደሚለው ከሆነ በውጭ ጉዳይ ሚ/ር (ስቴት ዲፓርትመንት) የዴሞክራሲ፣ የሰብዓዊ መብቶች እና የሠራተኞች ረዳት ሚኒስትር (ጸሃፊ) ከሌሎች የውጭ ጉዳይ መ/ቤት ባለሥልጣናት ጋር በመመካከር ለሚኒስትሩ ማዕቀብ ሊጣልባቸው የሚገቡ ሰዎች ስም ዝርዝር ያቀርባል። በሕግ መወሰኛው ም/ቤት (ሴኔት) የባንክ፣ የቤቶች እና ከተማ ጉዳዮች ኮሚቴ እና የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ እንዲሁም በእንደራሴዎች ም/ቤት የፋይናንስ አገልግሎቶች ኮሚቴ እና የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ለፕሬዚዳንቱ ስም ዝርዝር ሊያቀርቡ ይችላሉ። ማዕቀቡን መጣል ተገቢ መሆኑን ለመወሰን ፕሬዚዳንቱ ሌሎች አገራትና የሰብዓዊ መብቶችን ጥሰቶች በሚከታተሉ መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ያወጧቸውን ተዓማኒነት ያላቸውን መረጃዎች በድጋሚ ሊመለከቱ ይችላሉ። ይህም ሆኖ የተግባር አሠራሩ በአብዛኛው የሚከናወነውና ማዕቀቡ የሚጣለው የውጭ ጉዳይ እና የገንዘብ ሚ/ር መ/ቤቶች በጥምረት በሚያደርጉት ውሳኔ ነው።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<strong>በአሁኑ ጊዜ ዓለምአቀፉ የማግኒትስኪ ሕግ በተመለከተ ምን እየተደረገ ነው?</strong></div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
በሕግ መወሰኛው ም/ቤት የውጭ ግንኙነቶች ኮሚቴ ካሉት አባላት የላቀ ደረጃ ያላቸው ሴናተር ካርዲን እና የውትድርና አገልግሎቶች ኮሚቴ ሊቀመንበር የሆኑት ሴናተር ጆን ማኬይን ባለፈው ነሐሴ ወር <a href="https://www.cardin.senate.gov/newsroom/press/release/cardin-mccain-prod-trump-administration-to-use-global-magnitsky-tools-to-punish-human-rights-violators-and-corrupt-officials-from-around-the-world" style="text-decoration-line: none;">ለፕሬዚዳንት ትራምፕ በጻፉት ደብዳቤ</a> በዓለምአቀፉ የማግኒትስኪ ሕግ መሠረት ማዕቀብ ሊጣልባቸው የሚገቡ የ20 ግለሰቦችን ስም ዝርዝር ሰጥተዋል። ፕሬዚዳንቱም ደብዳቤውን ከተቀበሉ በኋላ መስከረም ወር መጀመሪያ አካባቢ በሕጉ መሠረት የገንዘብ ሚኒስትሩ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ <a href="https://www.whitehouse.gov/the-press-office/2017/09/08/presidential-memorandum-secretary-state-and-secretary-treasury" style="text-decoration-line: none;">ማዕቀብ እንዲጥሉ በይፋ ሥልጣን</a> ሰጥተዋቸዋል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<strong>ዓለምአቀፉ የማግኒትስኪ ሕግን የሚመስል ሕግ ሌሎች አገራት አሏቸው?</strong></div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
በርካታ የአውሮጳ አገራት፣ ካናዳ እና የአውሮጳ ፓርላማ ከሰርጊዬ ማግኒትስኪ ሞት ጋር ግንኙነት ባላቸው የሩሲያ ባለሥልጣናት ላይ ሕግ አውጥተዋል። በቅርቡ በርካታ አገራት የሚጥሉትን ማዕቀብ ሰፋ በማድረግ የሰብዓዊ መብቶችን የጣሰ የየትኛውም አገር አገዛዝ ማዕቀብ እንዲጣልበት ወስነዋል። በያዝነው የካቲት ወር (ፌብሩዋሪ 21) ታላቋ ብሪታኒያ የአሜሪካው ዓለምአቀፍ የማግኒትስኪ ሕግን የሚመስል የራሷን ሕግ አጽድቃለች። ኢስቶኒያ እኤአ በ2016 ተመሳሳይ ሕግ አውጥታለች። የካናዳ ፓርላማ እና የአውሮጳ ፓርላማ ዓለምአቀፍ የሰብዓዊ መብቶች የጣሱ ሁሉ ላይ ያነጣጠሩ ረቂቅ ህጎችን እያወጡ ነው።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<span style="color: black;"><a href="http://www.goolgule.com/tplfs-threat-hr-128-and-the-global-magnitsky-act/" rel="noopener" style="text-decoration-line: none;" target="_blank">ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ</a> ከዚህ ሕግ ጋር በተያያዘ እስካሁን ተግባራዊ የሆነባቸው ግለሰቦችም ሆነ ድርጅቶች እንዳሉ ባደረገው ፍለጋ ይህንን አግኝቷል፤</span></div>
<div class="wp-caption alignright" id="attachment_19908" style="background-color: whitesmoke; float: right; margin: 5px 0px 20px 20px; max-width: 160px; padding: 10px; text-align: center;">
<div class="wp-caption-text" style="line-height: 16px; margin-top: 4px; padding: 5px 0px;">
<img src="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/02/chayka_artem-150x150.jpg" />አርቴም ቻይካ</div>
</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<span style="color: black;"><a href="https://www.humanrightsfirst.org/press-release/human-rights-first-welcomes-initial-global-magnitsky-sanctions-designations-and-calls" style="text-decoration-line: none;">የሰብዓዊ መብት ድርጅት ባለፈው ታህሳስ ወር ባወጣው አጭር መግለጫ</a> ላይ እንዳመለከተው ፕሬዚዳንት ትራምፕ በ15 የውጭ አገር ዜጎችና 37 ድርጅቶች ላይ ዓለምአቀፉ የማግኒትስኪ ሕግን ተግባራዊ በማድረግ ማዕቀብ ጥለውባቸዋል። ማዕቀቡ የተጣለባቸው ከ12 በላይ በሚሆኑ አገራት የሚገኙ ኃያላን ፖለቲከኞች የንግዱ ማኅበረሰብ አባላት፤ በፖሊስና መሰል የሕግ አስፈጻሚ አካላት ውስጥ የሚገኙ፣ የመከላከያ አመራሮች፣ ሌሎችም ይገኙበታል። በውሳኔው መሠረት ግለሰቦቹ የንብረት እና የቪዛ ዕገዳ ተጥሎባቸዋል። ከእነዚህም መካከል የአባቱን ሥልጣን ሽፋን በማድረግ ጠቀም ያለ ትርፍ የሚያስገኙ የመንግሥት ጨረታዎችንና ኮንትራቶችን ተፎካካሪ ነጋዴዎች ላይ ጫና በማድረግ ሲያሸነፍ የነበረው የሩሲያው ጠቅላይ ዓቃቤሕግ ዩሪ ቻይካ ልጅ አርቴም ቻይካ፤ በበርካታ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ተጠያቂ የሆነውየቼችኒያ መሪ ራምዛን ካዲሮቭ፣ በበርማ የሮሂንጋ ሕዝብ ላይ የሰብዓዊ መብቶች በመጣስ በኃላፊነት የሚጠየቀው ወታደራዊ ኮማንደር ማውንግ ማውንግ ሶዪ፣ እንዲሁም በቻይና የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች የሆነውን ካዎ ሹንሊ ለእስር፣ ለስቅየትና ለሞት የዳረገው የቻይና ከፍተኛ የፖሊስ ሹም ጋዖ ያን ይገኙበታል።</span></div>
<div class="wp-caption alignright" id="attachment_19915" style="background-color: whitesmoke; float: right; margin: 5px 0px 20px 20px; max-width: 160px; padding: 10px; text-align: center;">
<div class="wp-caption-text" style="line-height: 16px; margin-top: 4px; padding: 5px 0px;">
<img src="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/02/kadyrov-150x150.jpg" />ራምዛን ካዲሮቭ</div>
</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ህወሓት HR 128ን ለምንድነው የፈራው የሚለውን ጥያቄ <a href="https://freedomhouse.org/blog/us-congress-should-call-ethiopia-s-bluff" style="text-decoration-line: none;">በፍሪደም ሃውስ የአፍሪካ ከፍተኛ የፕሮግራም ኦፊሰር የሆኑት ዮሴፍ ባድዋዛ</a> በቅርቡ ባወጡት መጣጥፍ ላይ እንዲህ በማለት መልሰውታል፤ “ኢትዮጵያ የምትከተለው የልማት ስትራቴጂ ዋንኛ ትኩረቱን ያደረገው የተሳካ የልማት ተግባር አከናውኛለሁ፤ የሰላም ሻምፒዮን ነኝ፤ ውጥረት በነገሠበት የአፍሪካ ቀንድ የመረጋጋት ተምሳሌት ነኝ በማለት ነው። ይህ የስኬት ትርከት መጠነ ሰፊ ኢንቨስትመንት የሚጠይቅ ሲሆን ደጓሚዎቹም አሜሪካ ብቻዋን ሳትሆን ሌሎች በዓለም የሚገኙ ለጋሽ መንግሥታትና ዓለምአቀፋዊ ድርጅቶች ናቸው።</div>
<div class="wp-caption alignleft" id="attachment_19907" style="background-color: whitesmoke; float: left; margin: 0px 0px 10px; max-width: 160px; padding: 10px; text-align: center;">
<div class="wp-caption-text" style="line-height: 16px; margin-top: 4px; padding: 5px 0px;">
<img src="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/02/Maung-Maung-Soe-150x150.jpg" />ማውንግ ማውንግ ሶዪ</div>
</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
አንድ ምሳሌ ለመጥቀስ፣ በቅርቡ የዓለም ባንክ እስከ 5ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ የአምስት ዓመት የጋራ ወዳጅነት ስምምነት ተፈራርመዋል። ከዚህ አንጻር ይህ ረቂቅ ሕግ ከፀደቀ ይህ ሁሉ የስኬት ትርከት ገደል ይገባል፤ ይህም ከፍተኛ የሆነ የኢኮኖሚ ቀውስ በአገሪቱ ሊያስከትል ይችላል።”</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
የዚህ ረቂቅ ሕግ ዋንኛ አዘጋጅና አቅራቢ የሆኑት ሪፓብሊካኑ ክሪስ ስሚዝ ይህ ሕግ እንዲፀድቅ አሜሪካ ለምን አቋም መውሰድ እንዳለባት ሲገልጹ “ሕጉ የኢትዮጵያ መንግሥት (ህወሓት/ኢህአዴግ) የሰራውን ሥራ ቁልጭ አድርጎ እንደሚያሳይ መስታወት ነው። የኢትዮጵያ መንግሥት ሥራውን በመስታወት ማየቱ ብዙም የሚያስፈራው አይደለም፤ ሆኖም ዋናኛ ፍርሃቻው ለረጅም ጊዜ ቸልታን የመረጠችው አሜሪካ (በኢትዮጵያ) ስለሚካሄደው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ድምጽዋን ለማሰማት ፈቃደኝነት ማሳየቷን (በመጥቀስ) ለለጋስ ድርጅቶችና መንግሥታት በማሳየቱ ላይ ነው” ብለው ነበር። የአሜሪካ ድምፅ የዓለም ድምፅ የመሆን ስፋት ስላለው HR 128 በአሜሪካ የመጽደቁን ሁኔታ ተከትለው ሌሎችም አገራት ተመሳሳይ እርምጃ በህወሓት ላይ መውሰዳቸው አይቀሬ ይሆናል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<span style="color: black;"><a href="http://www.goolgule.com/tplfs-threat-hr-128-and-the-global-magnitsky-act/" rel="noopener" style="text-decoration-line: none;" target="_blank">ህወሓት ይህንን ሕግ ለማኮላሸት በርካታ ስልቶች ብትጠቀምም፣ እስረኞችን ብትፈታም፣ የውስጥ ማንነቷ ግን ለውጥን እንድትቀበል የሚያደርጋት አይደለም።</a> በመሆኑም ይህ ረቂቅ ሕግ ከማግኒትስኪ ሕግ ጋር የተቆራኘ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን በርትተው በመሥራት ለውሳኔ እንዲቀርብ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል። በHR 128 ላይ በስፋት እየተንቀሳቀሰ ካለው <a href="http://hr128.org/" style="text-decoration-line: none;">የኢትዮጵያ አሜሪካውያን የሲቪክ ምክርቤት – Ethiopian Americans Civic Council in Colorado (EACC)</a> ጋር ሊተባበሩ ይገባቸዋል። ምክርቤቱን ለማግኘት የሚከተሉትን አድራሻ በመጠቀም ምን ማድረግ እንዳለባቸው በቂ መረጃ ለማግኘትና በግፍ ለተገደሉትና ለተሰቃዩት ወገኖች ሲሉ የበኩላቸውን ለመፈጸም ይችላሉ። Email: <a href="mailto:Info@hr128.org" style="text-decoration-line: none;">Info@hr128.org</a>, Facebook: <a href="https://www.facebook.com/pg/EthiopianAmericanCivicCouncil/posts/" style="text-decoration-line: none;">H.Res. 128 Respect Human rights in Ethiopia</a>, Twitter: @Ethio-American Civic Council, phone: 720 477 5711. HR 128 በሕግ መጽደቅ ይገባዋል።</span></div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<span style="color: black;"><a href="http://www.goolgule.com/tplfs-threat-hr-128-and-the-global-magnitsky-act/" target="_blank">http://www.goolgule.com/tplfs-threat-hr-128-and-the-global-magnitsky-act/</a></span></div>
</div>
</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-90917164100779472652018-02-27T09:15:00.001-08:002018-02-27T09:15:15.784-08:00“ታሪክ ራሱን ቧልት በሆነ መንገድ ሲደግም!”<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
<em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ኤርሚያስ ለገሰ</em></div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
<a href="https://ecadforum.com/Amharic/archives/17174/ermias-legesse2-2/" rel="attachment wp-att-17175" style="color: #0f06ba; list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px; text-decoration-line: none; transition: all 0.2s ease-in-out;"><img alt="Ermias Legesse, author and ESAT TV and Radio contributor" class="aligncenter size-full wp-image-17175 jetpack-lazy-image--handled" data-lazy-loaded="1" height="330" sizes="(max-width: 620px) 100vw, 620px" src="https://i2.wp.com/ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2016/10/Ermias-Legesse2.jpg?resize=620%2C330" srcset="https://i2.wp.com/ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2016/10/Ermias-Legesse2.jpg?w=620&ssl=1 620w, https://i2.wp.com/ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2016/10/Ermias-Legesse2.jpg?resize=300%2C160&ssl=1 300w" style="border: 1px solid rgb(203, 205, 204); clear: both; display: block; height: auto; list-style: none; margin: 2px auto; max-width: 100%; outline: 0px; padding: 4px;" width="620" /></a></div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
አንድ safegurding Tegaru lives በሚል ስያሜ የሚጠራ ካድሬ ” ደኢህዴን ከኃይለማርያም ወደ ሽፈራው ሽጉጤ ያደረገው ለውጥ የጥልቅ ተሃድሶ እድገት ነው፣ ወይንስ ከድጡ ወደ ማጡ ነው?” በሚል ያነሳሁት ጥያቄ ላይ አስተያየት ሊሰጥ ወደ ገፄ መጥቶ ነበር። ከላይ ከተጠቀሰው ኮካ በተጨማሪ በለውጥ ሀይል ዙሪያ ያሉ ወገኖች ” ሲራጅ ፈርጌሳ የደኢህዴን ሊቀመንበር ሆነ ብለህ ነበር!” የሚል ጥያቄ ስላነሳችሁልኝ ሁኔታውን ትንሽ ልበልበት። በትግራይ ነፃ አውጪ ደጃፍ ታሪክ እራሱን ስለሚደጋግሞ መለስ እያሉ ማስታወሱ ሳይበጅ አይቀርም። ከላይ የተጠቀሰው አይነት ሾርት ሜሞሪ ያላቸውን ኮተታም ካድሬዎች አፍ ማዘጋት የሚቻለው በዚህ መልኩ ነው። በሚያገኙት መረጃ ወደ ሰው ይመለሳሉ ብሎ ተስፋ ማድረግ ታማኝ እንዳለው ” እባብ ለመደ ተብሎ በኪስ አይያዝም!” ቢሆንም እባብነታቸውን እንዳይረሱ ያደርጋቸዋል። እናም እንደሰሞኑ በጅምላ ግድያ በርሜላቸውን እስኪሞሉ አድብተው እንዲቀመጡ ያደርጋቸዋል።</div>
<a name='more'></a><br />
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ወደ ገደለው ስመለስ ጠዋት ከእንቅልፌ ነቅቼ መረጃዎች ሳነፈንፍ የኃይለማርያም ድርጅት (ደኢህዴን) ፌስቡክ ድረገፅ ፊትለፊቴ መጣ። የድረ ገፁን ትክክለኛነቱን ለማረጋገጥ ከታች እስከ ላይ ወረድኩበት። ያለምንም ጥርጥር የድርጅቱ መሆኑን አረጋገጥኩ። በፓርቲው ማህበራዊ ድረገፅ ዘገባ መሰረት ሲራጅ ፈጌሳ ሊቀመንበር ሆኖ መመረጡን ያበስራል። አስቀድሞ የተወራ ስለነበር ብዙም አልገረመኝም። ከአራት ቀን በፊት በደቡብ ክልላዊ መንግስት ሬዲዬ የሚሰራ ጋዜጠኛ ” ወዲ ሽጉጤን ተገላገልነው!” በሚል በፌስቡኩ የፃፈውን ተመልክቼ ነበር። ዋሽንግተን ዲሲ ከሚኖሩ የኃይለማርያም እጅግ የቅርብ ዘመዶች በተዘዋዋሪ በደረሰኝ መረጃ መሰረት ሽፈራው ሽጉጤ የሙስና ችግር በሰፊው እንደተነሳበት ጠቁመዋል። ወደ ኃላ ተኪዶ በቡና እርሻ መሬት አሰጣጥ ላይ ከፓስተር ባደግ በቀለ ጋር በሼር የጀመረው ኢንቨስትመንት በአውጫጪኝ እንደቀረበበት መረጃው ደርሶናል። እቤት ውስጥ ተቀምጠው የነበሩ የ70 አመት ሽማግሌ አባቱ ፓስተር ባደግ በወር 50ሺህ ብር እየከፈለ ለቡና እርሻው ስራ አስኪያጅ ማድረጉም በሂስ መቅረቡን ሰምተናል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ለማስታወስ ያህል ፓስተር ባደግ ለሁሉም ባለስልጣናት እና ጄኔራሎች የማስተርስ ዲግሪ በ30ሺህ ዶላር የሸጠላቸው ሰው ነው። ለምሳሌ አቶ በረከት ስምኦን ከ11ኛ ክፍል በቀጥታ ማስተርሱን እንዲወስድ አድርጐታል። በፓርላማ መለስ ሲያሾመው እየሳቀ ” አቶ በረከት ስምኦን የትምህርት ዝግጅት ማስትሬት ዲግሪ በተቋማዊ አመራር” በማለት አስጨብጭቦለታል። ራሱም አንጨብጭቧል። አንዳንድ የዋሆች ( የዋህነቱ በመርፌ ቀዳዳ የመሹለክ ያህል ከሆነ እኔንም ይጨምራል) እንደዚህ አይነቱን ” ተወዳጅ ፓርላማ!” የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ይሽረዋል ብለን ተስፋ እናደርጋለን።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ወደ ተነሳሁበት ልመለስ እና የኃይለማሪያም ፓርቲ ድረገፅ ላይ የወጣው የሲራጅ ፈጌሳ ሊቀመንበር መመረጥ በአንድ ጊዜ ተሰራጨ። የለማ መገርሳ ድርጅት የሆነው ኦህዴድ በድረገፁ ተቀብሎ አስተጋባው። ከዚህ በላይ መተማመኛ ለማግኘት መሄድ አስፈላጊ አልነበረም። ከበቂ በላይ ነው። በሌላ በኩል እስከ ቀትር ድረስ ደኢህዴን ማስተባበያ ባለመስጠቱ የኢሳት ኢዲቶሪያልም የፓርቲውን ድረገፅ ዋቢ በማድረግ ዜናውን አሰራጨ። ደኢህዴንን የበላው ጅብ አልጮህ አለ። ሁኔታዎች ወደ አልተፈለገ መሄዳቸውን የተገነዘበው የስለላው ቢሮ ( የሽማግሌው ስብሃት ነጋ ቡድን በተለይም ቀጣዩ ስውር ጠቅላይ ሚኒስትር የምትሆነው ፈትለወርቅ ሞንጆሪኖ) ማስተባበያውን በተከፋይ የህውሓት ፌስቡክ የኮካ አለቆች አማካኝነት ማሰራጨት ቻሉ ። የፌስቡክ የኮካ አለቆቹ ከማስተባበያው ባልተናነሰ የለማ ቡድንን መረጃ ተቀብሎ በፍጥነት ማሰራጨቱን ደቂቃና ሰከንድ እየመተሩ ለመሳለቅ ሙከራ አደረጉ። እነዚህ አለቆች አዙረው መመልከት ቢችሉ ኖሮ መጠየቅ የሚኖርባቸው <em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">” </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የደኢህዴንን </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የውስጥ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ግምገማ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">እንዴት </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">እኛ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የትግራይ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ነፃ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">አውጪ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ሰራዊቶች </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ቀድመን </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">እናወጣለን? </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ነውር </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">አይደለም </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ወይ? </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ደኢህዴን </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ተላላኪ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ነው </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የሚለውን </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ምስክርነት </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">እየሰጠን </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">አይደለም </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ወይ?”</em> ይሉ ነበር።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
እናም በሰፊው የተሰራጨውን የሲራጅ ፈጌሳ ወደ ደኢህዴግ ሊቀመንበርነት መምጣት ተመርኩዤ የህውሓት ጨዋታ ( <strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">Game theory)</strong> ምን ሊሆን እንደሚችል የቢሆን መላምቶች መስራት ጀመርኩ። የጨዋታውን መመዘኛዎች ከሶስቱ እጩዎች( ዶክተር አቢይ፣ ደመቀ መኮንን እና ሲራጅ ፈጌሳ) ጋር በማጐዳኘት ነጥብ መስጠት ጀመርኩ። ሲናሪዬዎቹ በማቲማቲክስ እና ማይክሮ ኢኮኖሚክስ ኮርስ ስወስድ ከተማርኩት እና መልሼ መላልሼ ካነበብኩት የእስረኞች ወለፈንዲ ( <strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">prisoner dilemma)</strong> ከሚባለው ጨዋታ ጋር ተመሳሰለብኝ። (የዘርፋ ሙያተኞች በሁለት ኮርስ ያገኘሁትን ሚጢጢ እውቀት ወደ ተግባር ለመቀየር ላሳየሁት ተገቢ ድፍረት ይቅርታዬ ከወዲሁ ይድረሳችሁ።) ለማንኛውም በጨዋታው ህግ መሰረት ህውሓት ብአዴንና ደኢህዴንን ባህርዳር እና ሐዋሳ ጨለማ ቤት እንዳይገናኙ አድርጐ አስሮ የለማ ቡድንን ሊጫወትበት ሲሞክር በልበ ህሊናዬ ወከክ ብሎ ታየኝ። ጨዋታውን በእያንዳንዱ መመዘኛ (የስልጣን መወጣጫ መስፈርት) አብጠርጥሬ ተመለከትኩ።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ህውሓት ሌሎችን ከስልጣን ለማግለል የሚጠቀምባቸው <strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ስትራቴጂና </strong><strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ታክቲኮች</strong> አሁንም አልተቀየሩም። በመሰረቱ በሁለት ከፍለን ልናያቸው እንችላለን። ከእነዚህ ስትራቴጂዎች <strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">አንዱ</strong> ኢህአዴግን መሰረቱ የተባሉት አራቱ ድርጅቶች በስራ አስፈፃሚም (እያንዳንዱ ዘጠኝ) ሆነ በኢህአዴግ ምክርቤት (እያንዳንዱ 45) እኩል ውክልናና ድምፅ እንዲኖራቸው መደረጉ ነው። ይሄ መሆኑ ህውሓትን ቢጠቅመውም በሶስቱ ድርጅት ካድሬዎች እና አባላት ዘንድ የቆየ ቅሬታ እና ቁጭት የፈጠረ ነው። በዘውጌ ድርጅቶቹ ጉባኤ ላይ ዘወትር የሚነሳና ቢያንስ በፓርላማ ወንበር ቀመር መሰረት የፓርቲዎቹ ቀመር ይስተካከል በሚል የሚገለፅ ነው። ዛሬ ሁኔታዎች ወደ ህዝብ ወርደው ቢያንስ በኦሮሞና አማራ ህዝብ) የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ እና ምክርቤት ቁጥር በሕዝብ ብዛት ይሰራ መባል ተጀምሯል። የለማ ቡድን ደግሞ በህልምም በውንም ሊታሰብ የማይችል ከሶስቱ ድርጅቶች ሊለያየው የሚችል አዲስ የአይዲኦሎጂ ለውጥ ማድረጉ ” ኢህአዴግ ውስጥ ምን ያደርጋል?” የሚል ጥያቄ በሕዝቡ ዘንድ እየተጠየቀ ነው። እርግጥም ” ጨቋኝ ተጨቋኝ” ተረት ተረት እና ” አብዬታዊ ዲሞክራሲ” የሚባል እንቶፈንቶ እንጮቆረር የወረወረው የለማ ቡድን የኢህአዴግ የውሸት ዣንጥላ ውስጥ መቆየቱ ከፍተኛ ኪሳራ ላይ ሊጥለው ይችላል። ህጉ በሚፈቅድለት መሰረት በፍጥነት ፍቺውን ካልፈፀመ የሞት መንገዱን ያፋጥናል። ህውሓት ጊዜ ባገኘ ቁጥር መርዙን አጠራቅሞ በመርጨት ወደ ፍፃሜ ይወስደዋል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ሕውሓት ባህርዳር እና ሐዋሳ ጨለማ ቤት አስሮ የለማ ቡድንን ከጨዋታ ውጭ የሚያወጣው ” የፓርቲው የስልጣን አተያይ እና መያዣ መንገዶች” የሚለውን ድርጅታዊ መመሪያ ፊት ለፊት በመደንቀር ይሆናል። የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ( ከእያንዳንዳቸው 9 አባላት) ወደ ምክርቤት ከመሄዱ በፊት የድርጅት ሊቀመንበርና ጠቅላይ/ ተጠቅላይ ሚኒስትር በሚኮንበት መስፈርቶች ላይ በመወያየት አስቀድሞ አቋም ይወስዳል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
እነዚህ መስፈርቶች አብዬታዊነት፣ ብቃት፣ ስነ ምግባር ዋናዎቹ ናቸው። ከ40 በመቶ በላይ የሚይዘው <strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">አብዬታዊነት</strong> ( አብዬታዊ ዲሞክራሲን ማመን እና መጠመቅ፣ የጨቋኝ ተጨቋኝ ትርክትንና አንቀፅ 39 በፅናት ማመን፣ ማእከላዊነትን ሳያንገራግሩ መቀበል፣ ድርጅቱ የመደበውን ቦታ መቀበል፣ ከግለሰብ ክብር ይልቅ ለድርጅቱ ክብር መጨነቅ) በመስፈርትነት ያስቀምጣል። የኢህአዴግ ባለስልጣናት ” ድርጅቴ ሊስትሮ ሁን ካለኝ እሆናለሁ” ሲሉ የሚደመጡት በዚህ ምክንያት ነው። በነገራችን ላይ በዚህ መመዘኛ 40/40 የሚያገኙት ከጫካ ድረስ የመጡት የህውሓት ካድሬዎች ብቻ ናቸው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የብቃት </strong><strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">መለኪያ</strong> ተደርጐ የሚወሰደውም የአብዬታዊ ዲሞክራሲ አስተሳሰቦችን በሙሉ ተረድቶ በፓሊሲው መሰረት የማስፈፀም አቅም ነው። ” ገበሬም ቢሆን የድርጅቱን ፓሊሲ ማስፈፀም እስከቻለ ድረስ ከበቂ በላይ ነው” ተብሎ በተደጋጋሚ ሲነገር የምንሰማው በዚህ ምክንያት ነው። ትልቅ አገር፣ የታሪክ አቅጣጫ፣ብሔራዊ አላማና ሕልም የሚባል ነገር የለም። ከዚህ ይልቅ ሁሉንም ነገር አጥቦና በጐሳ መነፅር ማየት መቻል የተሻለ ተመራጭነትና ትልቅ ነጥብ የሚያስቆጥር ነው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የትምህርት </strong><strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ዝግጅትን</strong> በተመለከተ በኢህአዴግ <strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">” </strong><strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የአመራር </strong><strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ምደባ </strong><strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ፓሊሲ”</strong> ውስጥ የተቀመጠው እጅግ በጣም የሚያስደነግጥ ነው። ብዙ ሰዎች ህውሓት/ ኢህዴግ የመሐይማን ጥርቅም መሆኑ በጣም እየገረማቸው ሲናገሩ ይሰማል። ይሄ ግን ሆን ተብሎ በታቀደ መልኩ የሚፈፀም ነው። በህውሓት ውስጥ ትምህርት እና ከፍተኛ ስልጣን ተቃራኒ ተዛምዶ (Inversely related) ናቸው። ጥቂት አብዬታዉያን ብቻ ናቸው የአካዳሚያዊ ትምህርት የመጨረሻው እርከን ( ዶክተር ልበለው) እንዲደርሱ የሚፈቀድላቸው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ይሄን በማስመልከት ” የመለስ ትሩፋት: ባለቤት አልባ ከተማ” በሚለው መፅሐፍ ላይ በገፅ 309 ላይ፣</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em 30px;">
<em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">“</em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የኢህአዴግ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የውስጠ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ድርጅት </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">መመሪያ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ከፍተኛ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ምሁራንን </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">በሁለት </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ጐኑ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የተሳሉ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ቢላዋ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">በማለት </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">በንዑስ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ከበርቴነት </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ጐራ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ይመድባቸዋል። </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">በጀማሪ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ካፒታሊዝም </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ውስጥ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የምሁራን </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ማህበራዊና </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ኢኮኖሚያዊ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">መሰረት </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ለጥገኛ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ዝቅጠት </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የተመቸ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">እንደሆነና </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ከፍተኛ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">መደላድል </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">እንደሚፈጥር </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ያሳስባል። </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">በመሆኑም </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የምሁራን </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">አሰላለፍ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">በንዑስ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ከበርቴ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ደረጃ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">በመሆኑ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">በህዝቡ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ውስጥ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የሚካሄድ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ትግል </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ሲፋፋም </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">በመጀመሪያው </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የንቅናቄው </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">መስመር </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">በመሰለፍ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ግንባራቸውን </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ለጥይት </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">እንደሚሰጡ፣ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ትግሉ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ሲቀዛቀዝ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ደግሞ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ከሌላው </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የበለጠ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ተስፋ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የሚቆርጡና </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የሚያስቆርጡ፣ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ይባስ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ብሎም </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ለግል </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ጥቅማቸው </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የሚሯሯጡ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ሆዳሞች </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ይሆናሉ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ይላሉ። </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">በመሆኑም </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ድርጅቱን </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የሚቀላቀሉ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ምሁራን </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">አብዬቱን </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የመምራት </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ሃላፊነት </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ስለሚሸከሙ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">በመርፌ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ቀዳዳ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ማለፍ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የሚችሉ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ሆነው </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ከአጠቃላይ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ተመልማዬች </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ከ1 </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">በመቶ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">መብለጥ </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የለባቸውም </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">በማለት </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ይገልፃል” </em><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ይላል።</em></div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
እንግዲህ ህውሓት ስልጣንን እንደ ርስት ለመያዝ የሚጠቀምባቸውን መስፈርቶች በመመልከት የለማ ቡድን ወደ ድርድር መምጣት ካልቻለ <strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;"><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">( </em></strong><strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;"><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ቢያንስ </em></strong><strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;"><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">አስቸኳይ </em></strong><strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;"><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ጊዜ </em></strong><strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;"><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">አዋጁን </em></strong><strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;"><em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">መቀበል)</em></strong> ሲራጅ ፈጌሳ ሊቀመንበር እና ተጠቅላይ ሚኒስትር ሊሆን እንደሚችል የትንበያ ለውጥ አደረኩ። ከእኩለ ቀን በኃላ የደኢህዴን እና የለማ ቡድን ደረገፆች ባይቀየሩም የህውሓት ኮተታም ካድሬ አለቆች ከሚከፍላቸው ስለላው መስሪያቤት ( የስብሃት ነጋ ገዥ መደብ በበላይነት ሞንጆሪኖ) ከሲራጅ ፈጌሳ ወደ ” ወዲ ሽጉጤ!” መቀየሩን ይፋ አደረጉ። መጀመሪያ ስሰማ በጣም ተገርሜ ነበር። የጥልቅ ተሐድሶው ለውጥ ከድጡ ወደ ማጡ መሆኑን በቀጥታ ማረጋገጣቸው እጅጉን አስደነቀኝ። በውስጤ ኃይሌንና ሽጉጤን ሚዛን ላይ እያስቀመጥኩ ኃይለማርያም በምን ጣዕሙ አልኩኝ። የጀርመኗ የአገልግል ዶሮ ወጥ በአይኔ ላይ ሄደች። ለመወሰን መረጃ የለኝም የሚለው ንግግሩ ትውስ አለኝ። ዲሊቨሮሎጂ በእጄ ላይ ተንከባለለ። ጄኔራል ሳሞራ በህዝቡ በጥፊ ስለተመታው ወታደር የተረከለትን አስታወስኩ። የግመል ቁመት የማያውቀው የቻይና መሐንዲስ ቤጂንግ ድረስ በትውስታ ወሰደኝ። ለኃይሌ እናንተ ኢትዬጲያውያን መኪና ትበላላችሁ እንዴ? በማለት የጠየቀው ፈረንጅ የየት አገር ዜጋ ሊሆን እንደሚችል ግምቴን አስቀመጥኩ። የመብራት ፓል እየገጨ አዲሳአባን በጨለማ የሚያውላት ሰካራም ስሙ ማን ሊሆን እንደሚችል ጠረጠርኩ። ኸረ ወዲያ! ኸረ ወዲያ! አሁን እውነት ከህውሓቶች ውጭ ከኃይለማርያም የሚብስ ሰው ይመጣል ብሎ የሚጠብቅ አለ?</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
የሆነው ሆኖ ከሲራጅ ፈጌሳ ወደ ” ወዲ ሽጉጤ!” ከመቅፅበት የተቀየረው ድራማ አንዲት ነገር አስታወሰኝ። ታሪክ ራሱን በቧልት መልኩ ይደግማል ያልኩት በዚህ ምክንያት ነው። ታሪኩ ፎርቹን በሚባለው ጋዜጣ ላይ ወጥቶ ስለነበር እንዲሁም ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና በተደጋጋሚ የሚያነሳው በመሆኑ በብዙዎች ጭንቅላት ውስጥ እንደሚኖር እገምታለሁ። የመጀመሪያው ታሪክ ባለቤት ሟቹ መለስ ዜናዊ ሲሆን ተጨዋቾቹ አባዱላ ገመዳና ሟቹ አለማየሁ አቶምሳ ናቸው። የዛሬዎቹ ቧልተኛች ጄኔራል ሳሞራ ( ሲራጅ) እና ጌታቸው አሰፋ ( ሽፈራው ሽጉጤ) ናቸው። ታሪኮቹ ተመሳሳይ ስለሆኑ የሟቹ መለስ ዜናዊን ላጫውታችሁ እና መጣጥፌን ልቋጭ።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
እንዲህ ነበር የሆነው፣</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
የኦህዴድ ማእከላዊ ኮሚቴ በአዳማ ይሰበሰባል። አጀንዳው የድርጅት ሊቀመንበር ምርጫ በመሆኑ አባዱላ ኔትወርኩን ተጠቅሞ በሙሉ ድምፅ ራሱን ሊቀመንበር ያስመርጣል። አባዱላ ራሱን ማስመረጡ ያበሳጨው መለስ ዜናዊ አባዱላ ስብሰባውን አቋርጦ ወደ አዲሳባ እንዲመጣ ያደርገዋል።በማስፈራራት አለማየሁ አቶምሳን በአስቸኳይ እንዲተካ ይነግረዋል። ውሃ የገባ ፀጉራም ውሻ የሆነው አባዱላ በውስጡ ቂም ቋጥሮወደ አዳማ በመመለስ ” ራሴን አግልያለሁ አለማየሁ አቶምሳ ሊቀመንበር እንዲሆን አቅርቤያለሁ!” ይላል።ለጥቂት ሰአታት የማእከላዊ ኮሚቴው የብርጭቆ ማዕበል አስነስተው ድምፅ እንስጥ ይባባላሉ። ከአንድ ሰው በስተቀር አባዱላ ተሽሮ አለማየሁ አቶምሳ ይተካ በሚለው ላይ ይስማማሉ። በነገራችን ላይ አባዱላ በውጭ ተፅእኖ መቀየር የለበትም ብሎ ድምፅ የሰጠው የዛሬው የኦሮሚያ ሊቀመንበር ለማ መገርሳ ነበር። የዛሬው የቲም ለማ ቡድን መሪ።እነሆ! አለማየሁ አቶምሳ ብዙም ሳይቆይ የተመረዘ ውሃ እንዲጠጣ በማድረግ የቂም ቋጠሮው ፍቺ አገኘ። ፀረ ሌባው አለማየሁ አቶምሳ ለዘላለም አሸለበ።ለማ መገርሳ የአለማየሁ እጣ እንዳይደርሰው የእግዜር መላእክት ክንፋቸውን ይዘርጉለት።</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-70749143375901746482018-02-22T08:08:00.001-08:002018-02-22T08:08:41.141-08:00ወርቅነህ ገበየሁ ቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆን ህወሃት ወስኗል<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
<em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ክንፉ አሰፋ</em></div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
<a href="https://ecadforum.com/Amharic/archives/18653/workneh-gebeyehu/" rel="attachment wp-att-18654" style="color: #0f06ba; list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px; text-decoration-line: none; transition: all 0.2s ease-in-out;"><img alt="Workneh Geeyehu, Ethiopia's Minister of Foreign Affairs." class="aligncenter size-full wp-image-18654 jetpack-lazy-image--handled" data-lazy-loaded="1" height="330" sizes="(max-width: 620px) 100vw, 620px" src="https://i1.wp.com/ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2018/02/Workneh-Gebeyehu.jpg?resize=620%2C330" srcset="https://i1.wp.com/ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2018/02/Workneh-Gebeyehu.jpg?w=620&ssl=1 620w, https://i1.wp.com/ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2018/02/Workneh-Gebeyehu.jpg?resize=300%2C160&ssl=1 300w" style="border: 1px solid rgb(203, 205, 204); clear: both; display: block; height: auto; list-style: none; margin: 2px auto; max-width: 100%; outline: 0px; padding: 4px;" width="620" /></a></div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ወርቅነህ ገበየሁ ቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆን በህወሃት ተሹሟል። ይህ ከታማኝ ምንጭ የደረሰን መረጃ ነው። መረጃው እንደሚጠቁመው፤ እነ ዶ/ር ደብረጽዮን ሹመቱን ያጸደቁለት፤ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ገና በስልጣን ላይ እንዳሉ ነበር። የህወሃት ሰዎች “የኦሮሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን ሃገሪቱ አሁን የገባችበትን አስከፊ ችግር ይፈታል” የሚል ቅኝት ይዘው ወደ ምዕራቡ አለም እንዲሰማሩም ተደርጓል። </div>
<a name='more'></a> ከሀገሬው ሕዝብ ይልቅ የአሜሪካ እና የአውሮፓን ልብ መግዛት ከቻሉ ለተለመደው የበጀት ድጎማ ዋስትና ያገኛሉ። ሁሉም ወገኖች ሳይስማሙበት በሸፍጥ የተፈጸመው ይህን ሹመት ከአሜሪካ ባለስልጣናት ይሁንታ አግኝቷል ተብሏል። የአሜሪካ መንግስት ይህንን ሹመት ለመቀበል ሁለት ምክንያቶች አሉት። አንደኛው ምክንያት አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኦሮሞ ስለሆነ የተቀሰቀሰውን የቄሮ አመጽ ሊያስቆም ይችላል በሚል የተሳሳተ መረጃ ሲሆን ሁለተኛው እና ዋነኛው ምክንያት ደግሞ አገዛዙ የኢትዮጵያን ሳይሆን ይልቁንም የአሜሪካን ብሄራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ፍቃደኛ በመሆኑ ነው።<br />
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
የወያኔ ባለስልጣናት “እኛ ከሌለን ሃገሪቱ ትበታተናለች!” የሚል የማስፈራርያ መፈክር ይዘው ምእራባውያንን ለሶስት አስርተ-ዓመታት ሲደልሉ ቆይተዋል። አሁን ደግሞ ራሳቸው እያጠናከሩ ያሉትን አልሻባብ ማንሰራራት እንደ አጀንዳ ይዘው ብቅ ብለዋል። በያዝነው ሳምንት በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የሚመራ አንድ ቡድን በአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት በመገኘት፤ አገዛዙ ከተወገደ አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ ላይ የሚኖራት ብሄራዊ ጥቅም አደጋ ውስጥ እንደሆነ ገለጻ አድርጓዋል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
የአሜሪካ መንግስት የአስቸኳይ ግዜ አዋጁን መቃወሟ ይታወሳል። ይህ ተቃውሞ ለሁለተኛ ግዜ መሆኑ ነው። የአስቸኳይ ግዜ አዋጆችን ብቻ ሳይሆን አገዛዙ የሚያወጣቸውን አፋኝ ህጎች እና አዋጆጅ ሳይቃወሙ ያለፉበት ግዜ የለም። የመለስ መስተዳደር አልሻባብን ለመምታት ሶማልያን በወረረ ግዜም አሜሪካ በአደባባይ ተቃውሞዋን አሰምታለች። ይሁን እንጂ የወረራ ትእዛዙ ከአሜሪካ በስውር እንደመጣ ወደ ኢትዮጵያ ይገባ የነበረው ወታደራዊ ቁሳቁስ ምስክር ነው። አሜሪካኖች ሕገ-ወጥ ድርጊት ሲፈጸም ለማስመሰል ይቃወማሉ እንጂ በተግባር አንድም እርምጃ ሲወስዱ አይታይም።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የችግሩ ቁልፍ መሆናቸውን በጋዜጣዊ መግለጫ ተናግረው እንዲወርዱ መደረጉ በድንገት የመጣ ዱብ-እዳ እንደ ነበር አሁን ይፋ እየሆነ ነው። ሃገሪቱ ለገባችበት ውስብሰብ ችግር፣ መፍትሄው የእሳቸው ከስልጣን መውረድ መሆኑን በብሄራዊ ቴሌቭዢን ተናግረው እንዲወርዱ ማድረጋቸው አሳማኝ ባይሆንም ፤ አቶ ሃይለማርያም ይህን ከማለት ውጭ ሌላ አማራጭ እንዳልነበራቸው ተገልጿል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ተተኪው ጠቅላይ ሚኒስትር ወርቅነህ እንዲሆን ህወሃት ወስኗል። ሙሉ ስሙ ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን ሲሆን፣ ለምርጫ ቦርድ ያስመዘገበው ግን ወርቅነህ ገበየሁ ነገዎ ነው። የአያቱን ስም አንዳንዴም “ነገዬ” ይለዋል። “ነገዎ”ም ሆነ “ነገዬ” – ሁለቱም በማጭበርበር ኦሮሞ ለመሆን የወጡ ስሞች ናቸውና ለውጥ አያመጣም። ይህ ሰው ከየት ተነስቶ አሁን ያለበት ስፍራ እንዴት እንደደረሰ ከዚህ ቀደም በስፋት ስለሄድኩበት አሁን አልደግመውም።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
በሙስና ታስሮ ከነበረበት የሻሸመኔ እስር ቤት በድንገት ተጠርቶ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነርነት ማዕረግ ሲሰጠው፤ ጥቂት እንኳ አልተግደረደረም። ዘሩን እና ሸሚዙን ቀይሮ ወንበሩ ላይ ቁጭ አለ። ከዚያ በስሩ ከነበረው ከሃሰን ሽፋ የሚሰጠውን ትዕዛዝ ማስፈጸም ሙሉ ስራው አደረገ። አፈናው፣ ቶርቸሩ፣ ግድያው ሁሉ በኦህዴድ ስም፣ በኦሮሞ ስም ይፈጸም ነበር። ኮሚሽነር ሆኖ ከፈጸመው እጅግ የከፋ ወንጀል መካከል በምርጫ 97 ወቅት በሕዝብ ላይ የደረሰው ስቃይ እና ግድያ ይጠቀሳል። በዚህ ዙርያ ተሰይሞ የነበረው አጣሪ ኮሚሽን ያሰባሰበው ዘግናኝ ዘገባ ለታሪክ ተቀምጧል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በሕዝብ ላይ እርምጃ ለመውሰድ ማንገራገራቸው ለስልጣናቸው መልቀቅ ምክንያት እንደሆነ ይነገራል። በዚህም ምክንያት “ለዘብተኛ” የሚል ስም ወጥቶላቸዋል። ህወሃቶች ወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆን የፈለጉበት ምክንያት በአመራር ብቃቱ እንዳልሆነም ግልጽ ነው። “የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም” እንዲሉ በእጁ ላይ ቀድሞ የሰራው የሙስና ወንጀል እና ደም ስላለ፣ የሚሰጠውን ትዕዛዝ ከመፈጸም ወደ ኋላ አይልም በሚል እሳቤ እንደሆነ ይነገራል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ሃገሪቱ አሁን የገባችበትን ችግር ልትላቀቅ የምትችለው ሕዝብ ላይ በደል የፈጸመን ሰው መሪ ማድረግ አይደለም። እንዲህ አይነቱ አካሄድ ሕዝብን የባሰ ያስቆጣዋል እንጂ እነሱ እንዳሰቡት ፍርሃት እንዲያድርበት አያደርግም። ይህንን አድርጎ ስለ ሰላም ማሰብ ፣ ይህንን እያደረጉ በስልጣን መቆየት፣ ፈጽሞ የማይታሰብ እንደሆነ ሕዝብ በተግባር እያሳየ ይገኛል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ሃገሪቱ ብሄራዊ ችግር ውስጥ ነች። ወያኔ ይህንን ብሄራዊ ቀውስ እንደ እድል ተጠቅሞ ለእውነተኛ ብሄራዊ መግባባት ቢጠቀምበት ለራሱም ይበጀው ነበር። እንደ ለማ መገርሳ ያሉ አስታራቂ ሚና እየተጫወቱ ያሉ፣ ሕዝብ የሚፈልጋቸውን መሪዎች ወደ መድረክ የማምጣቱ እድል አሁንም አለ። ኳሱ በነሱ እጅ ላይ ነው። ሰዓቱ ሳይረፍድ ይህንን እውን ማድረግ ይችላሉ። ይህ ዕድል ካመለጣቸው ግን አወዳደቃቸው የሚያምር አይሆንም።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ምዕራቡ አለምም ቢሆን የሃይል ሚዛን እያየ ነው የሚቀየሰው። ከግብጹ ሆስኒ ሙባረክ እና ከቱኒዥያው ቤን አሊ የበለጠ የአሜሪካ ወዳጅ አልነበረም። በነዚህ አንባገነኖች ላይ ሕዝብ ሲነሳባቸው፣ አሜሪካም ተነሳች!</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-59506082363814106652018-02-19T07:28:00.002-08:002018-02-19T07:28:20.316-08:00የጠቅላይ ተጠቅላይ ጨዋታ<div style="background-color: white; color: #1d2129; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; font-size: 14px; margin-bottom: 6px;">
<em style="color: black; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ኤርሚያስ ለገሰ</em></div>
<div style="background-color: white; color: #1d2129; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; font-size: 14px; margin-bottom: 6px;">
<img alt="Image result for ermias legesse" height="364" src="https://netsanetlegna.files.wordpress.com/2017/06/fb_img_1498685905024.jpg?w=350&h=200&crop=1" width="640" /></div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ቀጥሎ የኢትዬጲያን የፓለቲካ አየር የሞላው የሚቀጥለው " ጠቅላይ/ ተጠቅላይ" ማን ይሆናል የሚለው ነው። ይህንን ጉዳይ ሰዎች በተለያዩ አቅጣጫዎች ይመለከቱታል። በተለይም በማህበራዊ ድረገጾች ካሉት ፍትጊያዎች አንዱ በዚህ ዙሪያ ያለው እሰጣ ገባ ሆኗል። በአንድ በኩል ስርነቀል የስርአት ለውጥ ለማምጣት እየታገልን ባለንበት ሰአት በዚህ አነስተኛ አጀንዳ ዙሪያ ለምን ጊዜያችንን እናጠፋለን የሚሉ ብዙዎች ናቸው። በሌላ በኩል ከራሳቸው እምነት፣ ጥቅም እና ፍላጐት በመነሳት " እከሌ ጠቅላይ መሆን አለበት!" የሚለውን የሚገፋም አልታጡም።</div>
<a name='more'></a><br />
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
የትግራይ ነፃ አውጪ የፌስቡክ ካድሬዎች በሁኔታዎች ተደናግጠው ቢጠፉም ከእናት ፓርቲያቸው ጋር እያሴሩ መሆኑ የሚደበቅ አልሆነም። ትኩረት ለሰጣቸው በሕዝብ ፊት የሚደሰኩሩትና ከመጋረጃ ጀርባ የሚሰሩት የአልሞት ባይ ተጋዳይነት ለየቅል መሆኑን ማየት ይቻላል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
ነገርን ነገር ያነሳዋል እና አንድ ወዳጄ ሰሞኑን ተወዳጅ ሆና ከአብዛኛው አንደበት በተነገረችው አዝናኝ ቃል ተጠቅሞ " ኮካዎች ሸሹ ወይስ አፈገፈጉ?" ብሎ ጠይቆኝ ነበር። እኔም " ኮተታም ካድሬዎችን በዝንብ ከፍ ካለም በጆፌ አሞራ ልትመስላቸው ትችላለህ። ደም እንደ ጐርፍ ሲወርድና የሰው ህይወት በአጋዚ ሲቀጠፍ ጐርፍ ሆነው ይመጣሉ" አልኩት። እውነት ለመናገር ኮካዎች በደም ካልሰከሩ እስትንፋስ ያላቸው አይመስለኝም።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
ያም ሆነ ይህ የትግራይ ነፃ አውጪ " የጠቅላይ/ተጠቅላይ" ጨዋታን የሚመለከተው ከራሱ ህልውና አንፃር ብቻ ነው። የዘረጉት ሕግና የአፈና ስርአት የፓለቲካና የኢኮኖሚ የበላይነታቸውን እስካረጋገጠላቸው ድረስ ለተፈፃሚነቱ በትጋት ይንቀሳቀሳሉ። ሕገ መንግስቱን ለማስከበር በሚል ሽፋን የፓርቲያቸውን የበላይነት ለማረጋገጥ የቻሉትን በሙሉ ያደርጋሉ። የተፈጠረባቸውን ቀውስ ለመደበቅ በሚያደርጉት መፍጨርጨር መዳመጥ ያለባቸውን ለመዳመጥ ህገ መንግስት በመጠበቅ ስም አስፈሪ ተኩላ ይሆናሉ። ለዚህ እንዲያግዛቸው የራሳቸው የጫካ ፕሮግራም ግልባጭ የሆነውን ሕገ መንግስት እንደ ጋሻ ይጠቀማሉ። በተጨማሪም በዣንጥላነት እያገለገላቸው ያለውን የኢህአዴግ ህገ-ደንብ ያለምንም ለውጥ እንዲተገበር ያደርጋሉ።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
በመሆኑም የጠቅላይ /ተጠቅላይ ጨዋታን በዋናነት ማየት የሚገባን የትግራይ ነፃ አውጪ ፍላጐት ምንድነው ከሚለው አንፃር ይሆናል። ህውሓት ፓለቲካዊ ሞቱን ለመሞት እያጣጣረ ቢሆንም የፀጥታና የስለላ መዋቅሩ ገና አልተነካም። አሁንም ማሰር፣ መግደል፣ መሰወር ይችላል። አሁንም ህገ መንግስቱን ከአደጋ ለመጠበቅ በሚል ሰበብ እየሞተ ያለውን የፓለቲካ መዋቅር አዛዥና አናዛዡ የፀጥታና ስለላ መዋቅሩ ነው። እያንዳንዱ የፓርላማ አባላት ጋር እየደወለና በአካል እየሔደ " አስቸኳይ ግዜ አዋጁን ባታፀድቅ በሞቀው ህይወትህ ፍረድ። እንደውም ተቃውሞ እያስተባበርክ ያለኸው አንተ መሆንህን ደርሰንበታል" እያለ ያስፈራራል። ለምሳሌ የስለላው መዋቅር አባል የሆነው አስመላሽ ወልደስላሴ ከስብሰባው በፊት በቀጭኑ ሽቦ " አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የፓሊሲ ጉዳይ ነው" ማለት በቂው ሊሆን ይችላል። በኢህአዴግ መንግስታዊ መመሪያም ሆነ የድርጅት ህገ ደንብ አንፃር " የፓሊሲ ጉዳይ ነው!" ከተባለ በተፃራሪው መቆም ፈፅሞ አይቻልም። እናም የፀጥታና ስለላ መዋቅሩ የፓለቲካ አመራሩን እንደ ህዝብ ግንኙነት ተጠቅሞ የፈለገውን በሀይል ሊፈፅም ይችላል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
ወደ ጠቅላይ ተጠቅላይ ጨዋታ ስንመለስ ቀደም ብሎ እንደተጠቀሰው የትግራይ ነፃ አውጪ ሁለት ሰነዶችን መዞ ያወጣል። እነዚህም የኢህአዴግ ሕገ መንግስትንና ህገ ደንቡ ናቸው። እስቲ እያንዳንዱን በተናጠል እና በተዛምዶ እንመልከት።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
# የኢህአዴግ ሕገ መንግስት</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
አስቀድሞ እንደተገለጠው የትግራይ ነፃ አውጪ ሁሉንም መቆጣጠር የሚፈልገው " ሕገ መንግስታዊ ስርአቱን" ለማስጠበቅ በሚል እንደሆነ ይታወቃል። በተለይም የህገ መንግስቱ አንቀፅ ዘጠኝ እየተጠቀሰ የሕግ የበላይነት ለማስከበር ሀላፊነት አለብን የሚባለው በዚህ ምክንያት ነው። አንቀፅ ዘጠኝ የኢህአዴግ ህገ መንግስት የአገሪቱ የበላይ ህግ መሆኑ፣ ማንኛውም ሕግ፣ ልማዳዊ አሰራር እንዲሁም የመንግስት አካል ወይም ባለስልጣን ውሳኔ ከህገ መንግስቱ ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈፃሚነት እንደማይኖረው ይደነግጋል። በሕገ መንግስቱ ከተደነገገው ውጭ በማንኛውም አኳኃን የመንግስት ስልጣን መያዝ እንደተከለከለ ይገልጣል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
ምንም እንኳን የትግራይ ነፃ አውጪ ቅጥፈት ሞራላዊ እሴት ብቻ ሳይሆን የአገዛዙ ዋልታና ማገር መሆኑ ቢታወቅም እስከጠቀማቸው ደረስ " ሕገ መንግስቱ ይከበር" ማለታቸው አይቀርም። ስለዚህም በደብረፂዬን መሪነት በፀጥታና ስለላ የበላይነት የያዘው ፓርቲ " የጠቅላይ ሚኒስትሩ አሰያየም!" የሚለውን የሕገ መንግስት አንቀፅ 73 ላይ ሙጭጭ ማለቱ አይቀርም። በአዋቂነት ውስጥ ሆነው በኩራት ይገልጡታል። በነገራችን ላይ አንቀፅ 73 ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሕዝብ ተወካዬች ምክርቤት አባላት መካከል ይመረጣል ይላል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
በእኔ እምነት የደብረፂዬን ፓርቲ ይሄን የህገ መንግስት አንቀፅ የሚቀየረው በመቃብሬ ላይ ነው ማለቱ አይቀርም። በተደጋጋሚም " ህገ መንግስቱ ይከበር!" የሚል ከበሮ መደለቅ ይጀምራል። እናም ይሄ ከሆነ ዘንዳ ከውሳኔው የማያሻማ ቁምነገሮችን ማውጣት ይቻላል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
የመጀመሪያው ቁምነገር " ጠቅላይ/ ተጠቅላይ" የሚሆነው ግለሰብ የግዴታ የፓርላማ አባል መሆን ይገባዋል። ይሄ መመዘኛ ለማ መገርሳ፣ ዶክተር አቢይ አህመድ እና ወርቅነህ ገበየሁን በመጀመሪያው ዙር ከጨዋታ ውጭ ያወጣል። ስለዚህ የለማም ሆነ የዶክተር አቢይ ጠቅላይ መሆን እንደማይችሉ የተረጋገጠ ነው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
በሌላ በኩል ደመቀ መኮንን፣ አባዱላ ገመዳ፣ ደብረፂዬንና አዲሱን የደኢህዴን ሊቀመንበር( ምንአልባት ሽፈራው ሽጉጤ) ወደ ቀጣዩ ዙር የሚያልፋ ይሆናል። በመሆኑም የትግራይ ነፃ አውጪ ክንፍ የሆነው የፀጥታና ስለላ መዋቅር ሕገ መንግስቱ ሳይሸራረፍ ይተግበር ካለ ጠቅላዩ ደብረፂዬን ሊሆን ይችላል። ተጠቅላዬቹ ደመቀ፣ አባዱላ እና ሽፈራው ሽጉጤ ሊሆኑ ይችላሉ።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
የራሴን ግምት አስቀምጬ ለመሄድ ያህል የስለላ እና የፀጥታ መዋቅሩ ለደመቀ መኮንን 60 በመቶ፣ ለአባዱላ 40 በመቶ በመስጠት የደሜክስን ተጠቅላይነት የሚያፀና ይመስለኛል። እናም ከሐይለማርያም ተስተካካይ ሰው በዙፋኑ ላይ እናገኛለን።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
እዚህ ላይ የትግራይ ነፃ አውጪ ክንፍ የሆነው የፀጥታና ስለላ መዋቅር በሚፈልገው የህገ መንግስት ማእቀፍ የሚዘልቅ ከሆነ ስለ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርም ጥቂት ማውራት ያስፈልጋል። በህገ መንግስቱ መሰረት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ለመሆን የፓርላማ አባል መሆን አይጠይቅም። በሌላ አነጋገር ም/ ጠ/ ሚኒስትሩ የፓርላማ አባል መሆን አይጠበቅበትም። እናም ለም/ጠ/ ሚኒስትርነት ህውሓት ወይዘሪት ፈትለወርቅ ( ሞንጆሪኖ)፣ ኦህዴድ ዶክተር አቢይ ሊያቀርቡ ይችላሉ። በእኔ ግምት ወቅቱ ከምንግዜውም በላይ ለትግራይ ነፃ አውጪ ወሳኝ በመሆኑ ወይዘሪት ፈትለወርቅ የመመደብ እድሏ ሰፊ ነው። በሌላ በኩል ዶክተር አቢይን ከስሩ ነቅለው በውሃ ላይ የሚንሳፈፍ ደረቅ ኩበት ማድረጉ የበለጠ የሚጠቅማቸው ከሆነ ምክትል ተጠቅላይ ሚኒስትር በማድረግ ይመድቡታል። በመሆኑም የምክትልነት ጨዋታው ( game theory) የሚሆነው ደመቀ መኮንንን በምትጠቀልለው ሞንጆሪኖ እና ተጠቅላዪ ዶክተር አቢይ መካከል ይሆናል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
# የሕውሓት/ ኢህአዴግ ድርጅታዊ ህገ ደንብ</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
በህውሓት/ ኢህአዴግ ህገ ደንብ መሰረት 180 አባላት ያሉት ( ከእያንዳንዱ 45) የኢህአዴግ ምክርቤት የድርጅቱን ሊቀመንበር በሚስጥር በሚሰጥ ድምፅ ይመርጣል። በድምፅ አሰጣጡ ላይ 180 የምክር ቤት አባላት እኩል ድምፅ አላቸው። ምንም እንኳን ከ3ሚሊዬን አባል እና ከ40 ሚሊዬን በላይ ህዝብ ወክያለሁ የሚለው ኦህዴድ ከግማሽ ሚሊዬን በታች እና ከ5 ሚሊዬን በታች ወክያለሁ የሚለው ህውሃት እኩል ድምፅ መያዛቸው ሊያነጋግር ቢችልም።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
በህገ ደንቡ መሰረት አራቱም የዘውጌ ድርጅቶች የኢህአዴግ ሊቀመንበር እና ምክትል አጩ የማቅረብ መብት አላቸው። ለሊቀመንበርነት የሚወዳደሩት የብሔር ድርጅቶቹ ሊቀ መናብርት ይሆናሉ። እዚህ ላይ በህገ ደንቡ ሊቀመንበሩ የድርጅቱ የበላይ አስፈፃሚ መሆኑን ቢገልፅም በመንግስት ስልጣን ውስጥ ጠቅላይ ሚኒስትር ይሆናል የሚል በግልፅ የተቀመጠ ነገር የለም። ለነገሩ ፓርቲው እንደ አቶ መለስ የመንግስት ዘላለማዊነትን ካልተላበሰ በስተቀር ሊያስቀምጥ አይችልም። ነገር ግን ድርጅት መንግስትን የሚመራ እንደመሆኑ መጠን ፓርቲው በውድም ይሁን በግድ ስልጣኑን የተቆናጠጠ በመሆኑ የፓርቲው ሊቀመንበር የመንግስት የበላይ ሆኖ መቀመጡ ተመራጭ ይሆናል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
እናም በዚህ ስሌት መሰረት ከወዲሁ ግምቴን ለማስቀመጥ ህውሓት "ለሊቀመንበርነት እንዲወዳደር የማቀርበው እጩ የለኝም" ይላል። ደብረጲዬንን ከትግራይ አምጥቶ ማወዳደር ከባድ ስለሚሆንበት። ፌዴራሉን በስውር ለመምራት ደብሪፅን ማምጣት አደጋ ይኖረዋል። ብአዴን በሊቀመንበርነት ደመቀ መኮንን እጩ እንዲሆን ያቀርባል። ኦህዴድ ለድርጅት ሊቀመንበርነት በእጩነት የሚያቀርበው የሚኖር አይመስለኝም። ለማ መገርሳ የኢህአዴግ ሊቀመንበር ሆኖ ቢመረጥ እንኳን ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን ስለማይችል የፓርቲው ቁንጮ መሆን የሚፈይድለት ነገር የለም። የደቡብ ድርጅቱ ደኢህዴግ አዲሱ ሊቀመንበሩን ለኢህአዴግ ሊቀመንበርነት እጩ አድርጐ ሊያቀርብ ይችላል። የደኢህዴኑ ሊቀመንበር የፓርላማ አባል ከሆነ ከደመቀ መኮንን ጋር የሚገጥመው ለድርጅት ሊቀመንበርነት ብቻ ሳይሆን ለተጠቅላይነትም ጭምር ይሆናል። እናም የትግራይ ነፃ አውጪ ሙሉ ድጋፍ ያለው ደመቀ መኮንን በተጠቅላይነት አራት ኪሎ ይሰጠዋል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
# እና ምን ይጠበስ?</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
አንዳንድ ሰዎች የቅርብ ወዳጆቼን ጨምሮ በዚህ ጉዳይ ላይ ጊዜ ማጥፋት እንደማያስፈልግ ሲገልጡ እሰማለሁ። የትግራይ ነፃ አውጪ በሰጠን አጀንዳ ላይ የተጠመድን አድርገው ይወስዱታል። በመሰረቱ በዚህ አስተያየት አልስማማም።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
በመጀመሪያ ደረጃ የትግራይ ነፃ አውጪ የገባበት ሁኔታ ቀውስ እንጂ ስኬት አይደለም። የቀውሱ መሰረታዊ ምንጭም የኢትዬጲያ ህዝብ እምቢተኝነት የወለደው እንጂ አገዛዙ የመለወጥ ፍላጐት ስላለው አይደለም። በሕዝብ አመፅ ምክንያት የትግራይ ነፃ አውጪ እየተፍረከረከ፣ የአመራር ሽኩቻው በግልፅ እየታየ ትኩረት አንስጠው ማለት አያስኬድም።አይደለም የአገሬው ሰው ምእራባውያን፣ አለም አቀፍ ተቋማት እና ሚዲያው በትግራይ ነፃ አውጪ ውስጥ የተፈጠረውን የስልጣን ፍጥጫ በአንክሮት እየተከታተሉ ስጋታቸውን በሚገልፁበት ሁኔታ የስርአት ለውጥ ፈላጊዎች ትኩረት ካልሰጠነው የለውጥ ግንዛቤያችንን መፈተሽ ይኖርብናል። ይሄን ማስታወሻ እየፃፍኩ በኢትዬጲያ የአሜሪካን ኤምባሲና አምባሳደር የአቶ ኃይለማርያም ከስልጣን መውረድ ጋር ተያይዞ ይፋ ያደረጉት ማስጠንቀቂያና በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ላይ ያወጡት መግለጫ በትዝታዬ መጥቶ ነበር። የስርአት ለውጥ ፈላጊውም ሆነ የሚዲያ ተቋማት እንዴት ተሯሩጠው እንደተቀባበሉት ጭው አለብኝ። በብዙ ሰዎች ትንተና ውስጥም ይህ በተደጋጋሚ የሚጠቀስና በእያንዳንዳችን አእምሮ ውስጥ የሚንገዋለል ነው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
በሁለተኛ ደረጃ ደጋግሜ እንደገለፅኩት ትናንሽ ለውጦች ትላልቅ ለውጦችን ይጋብዛሉ። ለነገሩ በትግራይ ነፃ አውጪ ውስጥ የሚኖርን የስልጣን ሽኩቻ እንደ ትንሽ ለውጥ ሊወሰድ ይገባል ወይ የሚለውም መጠየቅ ይኖርበታል። የትግራይ ነፃ አውጪ ድርጅት የፋሺስት እና አፓርታይድ ድቃይ በመሆኑ በጣም አደገኛ ነው። ይሄ አደገኛ ስርአት በተነሳበት የሕዝብ ጥያቄ ውስጣዊ ህይወቱ ውስጥ ያጋጠመው የአመራር መፍረክረክ በቀላሉ የሚታይ አይደለም። እነሱ ሲወድቁ እኛንም ይዘው እንዳይወድቁ ፣ ሽብርና የእርስ በርስ እልቂት እንዳይፈጠር በቅርበት መከታተል ያስፈልጋል። ለማንም ግልጥ እንደሆነው ይሄ ፋሽስታዊ አገዛዝ እስከአሁን ለግፍና ለጭፍጨፋ አዲስ ባይሆንም ከኢትዬጲያ ህዝብ ጋር ለመጨረሻ ጊዜ የተቆራረጠበት እና እርስ በራስ መበላላት የጀመረበት ነው። ይሄ በአግባቡ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል። ይሄን ማድረግ ዋናውን ትግል ያግዘዋል እንጂ የሚያዘናጋው አይሆንም። ይልቁንስ በትግራይ ነፃ አውጪ እና ተላላኪዎቹ ውስጥ የተፈጠረው ክፍፍል ለመሰረታዊ ለውጡ በአቀጣጣይነት ሊታይ የሚችል ነው። " የጉልቻ ለውጥ" ብቻ ተደርጐ መወሰድ የለበትም። እንደዚህ ማሰብ ተራራ የሚያክል ስህተት ለመስራት እንደመዘጋጀት ተደርጐ ሊወሰድ የሚችል ነው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
በሶስተኛ ደረጃ በስርአት ለውጥ ፈላጊው ዘንድ የሚታዩ የተሳሳቱ ዝንባሌዎችን ነቅሶ በማውጣት ለመታገል ያግዛል። ይሄ ወቅት ዘረኝነት እና ፋሺዝም አብረው የቆሙበት የሞትና የሽረት ዘመን ነው። የዘረኝነት ፓለቲካ በአገዛዙ ውስጥ ብቻ አይደለም። ተቃዋሚ ሀይሉም ጋር የDNA ፓለቲካ ስር እየሰደደ ሄዷል። እንደዚህ ባለ አደገኛና ደካማ አቋም ምክንያት አመዳዩን አለላ ለማስመሰል ጥረት እየተደረገ ነው። እከሌ በሕዝብ ተወዳጅ ስለሆነ በጠቅላይ/ ተጠቅላይነት ካላየሁት ሞቼ እገኛለሁ የሚሉ አደገኛ አስተያየቶች እየተደመጡ ነው። ሌሎች ድብቅ ፍላጐት ያላቸው ደግሞ የሕዝቡን ልቦና በማዳመጥ እነሱ ወደሚፈልጉት ለማሽከርከር ያለ የሌለ ጉልበታቸውን በመጠቀም ላይ ናቸው። ለዚህ ጥሩ ምሳሌ የሚሆነው ለማ መገርሳ እና ዶክተር አቢይን ወደ ፌዴራል ተጠቅላይነት እንዲሄዱ የሚደረገው ግፊት ነው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
በእኔ እምነት በለማ እና አቢይ ላይ እየተካሄደ ያለው ዘመቻ ከስራቸው በመንቀል አስብቶ የማረድ ነው። እርግጥም ከአፈራቸው ላይ ስራቸውን መንቀል እንዳያብቡ ያደርጋል።ለማና አቢይ ለመካከለኛ ጊዜ የኦሮሚያን የፓለቲካና የድርጅት ስራ በበላይነት መምራት ይኖርባቸዋል። እስከ ሶስት ሚሊዬን ይጠጋል የተባለውን የኦህዴድ አባልና ቄሮን በአዲሱ አስተሳሰባቸው ኢንዶክትሬት ማድረግ ይኖርባቸዋል። በመንግስት የስራ አመራርና የካድሬ ስልጠና ማእከላት " ኢትዬጲያዊነት ሱስ መሆኑን፣ የብሔር ጭቆና የሚባል ተረት ተረት መሆኑን፣ የኦሮሞ ጀግኖች ኢትዬጲያ አገራቸውን ለማቆየት ያደረጉትን ተጋድሎ፣ ኢትዬጲያዊነት እንደ ጉልት ማንም ሲፈልገው የሚያቋቁመው እና የሚበትነው እንዳልሆነ፣ መታወቂያ ላይ ብሔር መፃፍ ያስቆሙበትን ምክንያት፣ የኦሮሞ ህዝብ ወርቃማ እሴቶችን…ወዘተ" የሚያስተምሩበት ካሪኩለም በመቅረፅ ማስተማር ይኖርባቸዋል። ሚሊዬን ለማዎችና አቢዬች መፈጠር ይኖርባቸዋል። የትምህርት ቤት ካሪኩለሞችን በእነሱ አዲስ ተራማጅ አስተሳሰብ መቃኘት የቅድሚያ ስራቸው ሊሆን ይገባል።</div>
<div style="background-color: white; display: inline; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-top: 6px;">
የለማ ቡድን አባላት ከላይ የተጠቀሰውን እያደረጉ የአገሪቱን ሕገ መንግስት ወደ ፕሬዝዳንታዊ ስርአት ( የአንድ ሰው አንድ ድምፅ) የሚቀየርበት ሁኔታ ማመቻቸት ይኖርባቸዋል። በዚህ ዙሪያ የፕሮፌሰር መረራ ፓርቲ እና የሌሎች ድርጅቶች ድጋፍ ስለሚያገኙ ትግሉ አስቸጋሪ ላይሆን ይችላል።የለማ ቡድን ይሄን ማድረግ ከቻለ በኢትዬጲያ ታሪክ ውስጥ ዘወትር የሚታወስ ደማቅ ታሪክ ይሰራል። የኢትዬጲያ አምላክ ይርዳቸው።</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-11349127597143640802018-02-18T07:30:00.000-08:002018-02-18T07:30:51.957-08:00 የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ህወሀት ክፉኛ ቆስሏል። ከእንግዲህ በመንግስትነት የመቆም እድል የለውም። ኳሷ በኢትዮጵያውያን እግር ስር ገብታለች።<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px;">
<a href="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2017/12/Mesay-Mekonnen-Articles.jpg?x81575" imageanchor="1" style="clear: right; float: right; margin-bottom: 1em; margin-left: 1em;"><img alt="Mesay Mekonnen, ESAT journalist" border="0" height="170" src="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2017/12/Mesay-Mekonnen-Articles.jpg?x81575" width="320" /></a></div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px;">
<em style="font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">መሳይ መኮንን</em></div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px;">
ያለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ትልልቅ ክስተቶች የተሰተናገዱበት ነው። ተስፋና ስጋት፡ ብርሃንና ጽልመት፡ አንድነትና መነጣጠል፡ ከፊታችን ተደቅነው ጉዟቸንን እንድናሳምር፡ መንገዳችንን እንድንመርጥ፡ አካሄዳችንን እንድናስተካክል፡ እድል እጣፈንታችንን እንድንወስን ከሚያስችለን ዋናው ምዕራፍ የተጠጋን ይመስላል። የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ህወሀት ክፉኛ ቆስሏል። ከእንግዲህ በመንግስትነት የመቆም እድል የለውም። ኳሷ በኢትዮጵያውያን እግር ስር ገብታለች። የጊዜ ጉዳይ ነው። በጣም ጥንቃቄ የሚያስፈግበት ወቅት ላይ ነን። ጥሞና ያስፈልገናል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
አዎን! እስረኞች ተፈተዋል- የሚቀሩ ቢኖሩም። አቶ ሃይለማርያም ስልጣን ለቋል- ስልጣን ባይኖረውም። አስቸኳይ አዋጅ ተደንግጓል- ለውጥ ባያመጣም። ህዝባዊ ትግሉ ተጠናክሯል- በፈረቃ መሆኑ ባይቀርም። ይህ ሁሉ የሆነው በዚህ ሳምንት ውስጥ ነው። በኢትዮጵያ የ27 አመታት የትግራይ ነጻ አውጪ የአገዛዝ ዘመን እንደዚህ ሳምንት ክስተቶች በፍጥነት ተደራርበው የመጡበት ጊዜ ያለ አይመስለኝም። እነኚህ ክስተቶች ወዴት ይመሩናል? በእርግጥ ቁልፍ ጥያቄ ነው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
የእስረኞች መፈታት</div>
<a name='more'></a><br />
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
ጀግኖቻችን ነጻ ሆነዋል። ዶ/ር መረራ ተፈተዋል። እነበቀለ ገርባ ከቤተሰቦቻቸውና ከህዝባቸው ጋር ተቀላቅለዋል። እክንድር ነጋ፡ አንዱዓለም አራጌ፡ እማዋይሽ ዓለሙ፡ አህመዲን ጀበል፡ ሌሎችም ከትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር የግዞት ማዕከላት ወጥተዋል። ብ/ጄ ተፈራ ማሞ፡ ብ/ጄ አሳምነው ጽጌ ኮ/ል ደመቀ ዘውዴ፡ ወጣት ንግስት ይርጋና ሌሎች እንዲፈቱ ተወስኗል። እሰየው ነው። የሚቀሩ ጀግኖቻችን አሉና እንጠብቃለን።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
የዋልድባ አባቶች ከአረመኔዎቹ እጅ አልወጡም።ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ከድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ናቸው። ዮናታን ተስፋዬ አሁንም በዚያ አስቀያሚ እስር ቤት ውስጥ እንደተቆለፈበት ነው። ፍቅረማረማርያም አስማማው ከወጣትነት እድሜው ተቀንሶ ከገባበት የማጎሪያ እስር ቤት አልወጣም። አንዳርጋቸው ጽጌ ምን ላይ እንዳለ አናውቅም። በሺዎች የሚቆጠሩ፡ በስም የማናውቃቸው፡ ጀግንነታቸው በወርቃማ መዝገብ ላይ የሚቀመጥላቸው ወንድምና እህቶቻችን አሁንም በትግራይ ደህንነቶች ስቃይና መከራውን እየተጋቱ ነው። ሁሉም ነጻ መሆን አለባቸው። የታሰሩበት ምክንያት አንድ ነው። የሚፈቱበት ምክንያት መለያየት የለበትም።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
የትግራዩ ነጻ አውጪ ግንባር እጁ ተጠምዝዞ መፍታቱ እርግጥ ነው። የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት፡ ብሄራዊ መግባባትን ለመፍጠር በሚል እንዲፈቱ ተወስኗል የሚለው ጨዋታ ካድሬዎቹን ካረጋጋለት፡ ካጠገበለት ይበቃል። ለእኛ አይመጥንም። የተፈቱት በሙሉ በአንድ ቃል የሚመሰክሩት ''ያስፈታን ህዝባችን ነው። የህዝብ ጉልበት ነጻ አውጥቶናል'' በሚል ነው። የኢትዮጵያውያን ወጣቶች ክርን አለኝታ መከታችን ነው። ወጣት የነብር ጣት። የእነ ደብረጺዮንን እብሪት ያስተነፈሰለን፡ የጌታቸው አሰፋን ድንፋታ ያስታገሰልን፡ የሳሞራ የኑስን ጥጋብ ያበረደልን፡ የአባይ ጸሀዬን እብጠት ኩምሽሽ ያደረገልን የኢትዮጵያ ወጣቶች ተጋድሎ ክብር ምስጋና ይግባው። በደማቅ ቀለም በታሪክ መዘገብ ላይ የሚሰፍር ታላቅ ተጋድሎ። ኢትዮጵያ እስክትፈታ የማይቆም የነጻነት ጉዞ።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
የተፈቱት ጀግኖቻችን በእስር ዘመናቸው ከመረጃ ጋር ተቆራርጠዋል። የውጭ ሚዲያ አያገኙም ነበር። ኢትዮጵያ ውስጥ የሚሆነውን ሲሰሙ የነበረው ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ብቻ ነው። አያነቡም። አይጽፉም። ፍጹም ጨለማ ውስጥ እንደነበሩ ከማንም የተሰወረ አይደለም። እናም ከወጡ በኋላ በሚናገሩት አንዳንዶች ሲከፋቸው አስተውዬአለሁ። የመረጃ ክፍተት ያለባቸው በመሆኑ ልንፈርድባቸው አይገባም። የነበሩበትን፡ የከረሙበትን የሚያውቁት እነሱ ብቻ ናቸው። የኢትዮጵያ ህዝብ እነሱ እስር ቤት በነበሩ ጊዜ የደረሰበትን ውሳኔ አያውቁትም ይሆናል። ህዝባችን የመረረ ትግል ውስጥ መግባቱን እንዲረዱ ትንሽ ጊዜ ያስፈልጋቸዋል። አሁን ማለት ያለባቸውን እያሉ ነው። ሲረዱትና ሲገባቸው የሚሉት ሌላ ሊሆን ይችላል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
ዓንዱአለም አራጌ ከእስር ከተፈታ በኋላ እንዲህ ብሏል "ስለወደፊቱ ለመናገር ገና ነኝ። ታስሬ የነበረው ምንም መረጃ በሌለበት ቦታ ነው። መጀመሪያ ጆሮና ዓይኔን ከፍቼ አካባቢውን መረዳት አለብኝ። እኔ ባልነበርኩበት ጊዜ የተፈጠረው የፖለቲካ እንቅስቃሴ ምን ይመስል እንደነበርና የአገሪቱን ሁኔታ በጥሞና ለመረዳት ጥረት አደርጋለሁ"</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<br />የሃይለማርያም ከስልጣን መልቀቅ</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
በ17 ቀናቱ የኢህአዴግ ጉባዔ ወቅት አቶ ሃይለማርያም ከስልጣን እንደሚለቅ ፍቃዱ እንደሆነ መግለጹ ሾልኮ ወጥቶ ነበር። በወቅቱም ''ወንድ ልጅ ቆረጠ'' ከሚል ስላቅ ጋር ''የትኛውን ስልጣን ነው የሚለቀው?'' የሚል ጥያቄ በብዙዎች ዘንድ ተነስቶም ነበር። እርግጥ ነው ሃይለማርያም ስልጣን አልነበረውም። መከላከያውንና ደህንነቱን የማያዝ፡ የማይቆጣጠር ጠቅላይ ሚኒስትር እንደምን ስልጣን ነበረው ይባላል? ከአቶ መለስ ዜናዊ ሞት በኋላ ለውጭ መንግስታት ግራ እስኪገባቸው በሀገሪቱ አባወራውን መለየት አቅቷቸው ነበር የሰነበቱት። ለማንኛውም የአቶ ሃይለማርያም ወደ ስልጣን ወደ ቤተመንግስት መግባት ወንበሩን ኦሮሞና አማራው እንዳይዘው በትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር በኩል ጠንከር ያለ አቋም ስለነበር መሆኑ ሁላችንንም የሚያስማማ ነው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
አቶ ሃይለማርያም እንዲሁ እንደባከነ ሳያምርበት ወንበሩ ላይ ቆየ። እያሳቀቀንና እያሳቀን ለ5ዓመታት ተጎልቶ ከኢትዮጵያውያንም፡ ከአምላኩም ተጣልቶ፡ ጥቁር ሌጋሲ ትቶ ተሰናበተ። ሃይለማርያም ፈጣሪን በመለስ ለውጧል። ዘላለማዊ ክብርናሞገስ ለታላቁ መሪያችን ካለበት ጊዜ አንስቶ መንፈሳዊ ካባው ተገፎ፡ በመለስ አስተምህሮት ተተክቷል። መጽሀፍ ቅዱስን ትቶ፡ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ተጠምቋል፡፡ በመጨረሻም ከሁለቱም ሳይሆን ቀርቷል። ፈጣሪ ምህረት አይነፍግምና<br />ከአምላኩ ሊታረቅ ይችላል። ሊስትሮ ቢሆን ጠርጌ አገለግለዋለሁ ያለው የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ግን እንደሸንኮራ አገዳ መጦ ተፍቶታል።ምስኪን ሃይለማርያም!</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
ሃይለማርያም ሄዷል። የትግራይ ነጻአውጪ ግንባር ደህነቱንና መከላከያውን የሙጥኝ እንደያዘ ስልጣን አልባው ወንበር ላይ አሻንጉሊት ጠቅላይ ሚኒስትር ለማስቀመጥ ፈልጓል። በእርግጥ ነገሮች እንደትላንቱ አይደሉም። እንዳሻው መፈንጨት የሚችልበት ዘመን አልፏል። ኦህዴድ ቀና ብሏል። ብአዴን እየተንደፋደፈም ተግደርዳሪ ሃይል ሆኖ መጥቷል። እናም ጠቅላይ ሚኒስትርነቱ ላይ የሚቀመጠው ሰው ከእነዚህ ከሁለቱ ድርጅቶች ውጭ ሊወጣ አይችልም። የእኛ ጭንቀት ባይሆንም ሰሞኑን በአንዳንድ የኦሮሞ አክቲቪስቶች ዘንድ እየተራገበ ያለ ጉዳይን በዝምታ ማለፍ ተገቢ ሆኖ አልታየኝም።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
ኢህዴግን መምራት የጠቅላይ ሚኒስትርነቱን ቦታ የመያዝ ተራው የእኛ ነው የሚል በዘመቻ የተከፈተ አጀንዳ በማህበራዊ መድረክና በዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ሳይቀር እየተቀነቀነ ነው። ኦህዴድ ውስጥ ያሉ የድርጅቱን ገጽታ በማህበራዊ መድረኮች ላይ ወጥተው የሚያስተጋቡና በባህር ማዶ የሚገኙ አንዳንድ የኦሮሞ አክቲቪስቶች አቶ ለማ መገርሳ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን አለባቸው ብለው አንድ ላይ ተሰልፈዋል። አልጀዚራ ላይ የማከብረው የኦፕራይድ ሚዲያ አዘጋጅ መሀመድ አዴሞ ስልጣኑ ለኦሮሞ መሰጠት አለበት ሲል ሰማሁት። ሀሳቡ እንዲሁ እንደወረደ ችግር የለበትም። የአቶ ለማ መገርሳ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን የሚያስከፋ አይደለም። ሲያንሳቸው ነው። ጉዳዩ ግን ያ አይደለም። ደህንነቱና መከላከያው በትግራዩ ነጻ አውጪ መዳፍ ውስጥ በተቀረቀረበት ሁኔታ ስልጣን በሌለው ወንበር ላይ መቀመጡ ነው ችግር የሚሆነው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
የቄሮዎች ትግል መስዋዕትነት የስርዓት ለውጥ እንጂ ሌላ ሃይለማርያም ከኦህዴድ ለማስቀመጥ አይደለም። ደግሞም የኢትዮጵያውያን የዘመናት ጥያቄ በብሄር ኮታ ስልጣን እንዲከፋፈል አይደለም። ህዝብ በነጻነትና ፍትሀዊ በሆነ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ የፈለገውን መንግስት የመሰየምና ሲያሻው የማንሳት መብቱ እንዲረጋገጥ ነው። በዕወቀት፡ በብስለት፡ በጥበብና በእኩልነት የሀገሪቱን ልጆች የሚመራ መንግስት እንጂ የተራብነው ዘርና አጥንቱ ተቆጥሮ አራት ኪሎ ቤተመንግስት የሚገባ ሰው ለመሰየም አይደለም።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
እነለማ ለዕወቀቱና ጥበቡ የሚያንሱ አይደሉም። ስለሀገራቸው ኢትዮጵያ ያላቸው ስሜት፡ ስለኢትዮጵያውያን ውስጣቸው የሚንቀለቀለው ፍቅር ሀገር እንዲመሩ ከበቂም በላይ ተመራጭ ያደርጋቸዋል። በዘር ማንነታቸው ለክተው ቦታው ይገባቸዋል ለሚሉት ግን የኢትዮጵያ ህዝብ እየተዋደቀ ያለው ህወሀትን በኦህዴድ ለመተካት አለመሆኑን በሚገባቸው ቋንቋ ሊነገራቸው ይገባል። አቶ ለማን በህወሀቷ ኢትዮጵያ ውስጥ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆኑ አጀንዳ ከፍተው የሚያራግቡ ወገኖች ሰውዬው በኢትዮጵያውያን ዘንድ ያገኙትን ተወዳጅነት ለማጥፋትና በአቋራጭ የኦሮሞ መሪ ሆኖ ብቅ ለማለት እንደሆነ መገመት ይቻላል። የአቶ ለማ መምጣት ስምና ዝናቸውን ያደበዘዘባቸው አንዳንዶች የሚያጮሁት አጀንዳ መሆኑ አይጠፋንም። አቶ ለማ ኢትዮጵያውያን የመረጡት፡ ፈቅደውና ይሁንታ ሰጥተው የሰየሙት መንግስት መሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሆኑ ድምጼን የማልነፍጋቸው ሰው ናቸው። ከመጀመሪያዎቹ ምርጫዎቼ ፊት የሚቀመጡ ምርጥ ኢትዮጵያዊ መሪ ናቸው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
የአስቸኳይ አዋጁ ነገር</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
የቃላት ጨዋታ እንጂ ኢትዮጵያ ውስጥ በይፋ መፈንቅለ መንግስት ተካሂዷል። ደም ያልፈሰሰበት መፈንቅለ መንግስት። አሜሪካ አውግዛዋለች። በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ ''ያሳስበኛል'' ከሚል አዙሪት ወጥታ ጠንከር፡ ከረር ባለ አቋም አስቸኳይ አዋጁን ማውገዟ ብዙ ነገሮችን ያሳየናል። አሜሪካ በትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ላይ ተስፋ መቁረጧን ምልክት ካሳየች ቆይታለች። ማን ይተካ የሚለው ጨንቋት እንጂ የትግራዩ ቡድን በቶሎ ቢሰናበት ትመርጣለች። ለዚህም ነው ተከታታይ ጫናዎችን እየፈጠረች ያለችው። በHR 128 የሰነዘረችው ዱላ ቀላል አይደለም። አምባሳደሩ በቅርቡ ያስተላለፉትም መልዕክት 'አለ ነገር' የሚያሰኝ ነው። አስቸኳይ አዋጁን በተመለከተም የአሜሪካ አቋም ለትግራዩ ቡድን ዱብእዳ ነው። ወዳጅ ሲንሸራተት አይጣል ነው። እርጥባን የሚያቀርብ ጌታ ሲከዳ ሰማይ ምድሩ ይዞራል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
የትግራዩን ቡድን ለአራት ኪሎ ቤተመንግስት ያበቁት አንጋፋው ዲፕሎማት ኸርማን ኮሀን በቲውተር ላይ እንደጻፉት አስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ወታደራዊ ፍንቀላ ነው። ሁሉንም አካላት ያሳተፈ የእርቅ ጉባዔ ስንጠብቅ ወታደራዊ አገዛዝ ተተከለ ሲሉ ነው አስቸኳይ አዋጁን የወረፉት። ለመንግስታቸውም ጥሪ አድርገዋል- ''የአሜሪካን መንግስት ሆይ! ይህ በፍጹም እንዳይሆን አድርግ''</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
አስቸኳይ አዋጁ የተደነገገው እየፈራረሰ ያለውን የትግራዩን ነጻ አጪ ግንባር ለማረጋጋት እንደሆነ ብዙዎች ይገልጻሉ። የመንግስት ኮሚኒኬሽ ጉዳዮች ሚኒስትሩ ዶ/ር ነገሬ ሌንጮ ሀሙስ ዕለት እዚህ አሜሪካ ሆነው ሲናገሩ ''አስቸኳይ አዋጅ ሊያስወጣ የሚያስችል ምንም ሁኔታ የለም'' ብለው ነበር። በማግስቱ የሚኒስትሮች ምክር ቤት አዋጁን ደነገገ። በሚቀጥለው ቀን ሲራጅ ፈርጌሳ በቴሌቪዥን መስኮት ብቅ ብሎ ሀገሪቱ በወታደራዊ ዕዝ ስር ለስድስት ወር እንደምትቆይ ገለጹ። ጥያቄው የዶ/ር ነገሬ ሌንጮ አቋም የማን ነው የሚል ነው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
በተደጋጋሚ በሚሰጧቸው የተዛቡና፡ በውሸት የተለበጡ መግለጫዎች ትዝብት ላይ የወደቁት ዶ/ር ነገሬ የአትላንቲክን ውቅያኖስ ተሻግረው ሲመጡ ሰዎቹ መረጃ ደበቀዋቸው ሊሆን ይችላል የሚል ግምት ተሰጥቶ ነበር። ነገር ግን የሳቸው ምላሽ የፌደራሉ መንግስት(የትግራዩ ቡድን) ሳይሆን የኦህዴድን አቋም ያንጸባረቁበት ሊሆን ይችላል ብሎ ማሰቡ ሊያስኬድ ይችላል። ምክንያቱም አስቸኳይ አዋጁ ላይ በኢህ አዴግ አባል ድርጅቶች መሀል ጫፍና ጫፍ የቆመ ልዩነት መፈጠሩ በስፋት እየተነገረ መሆነ ነው። ኦህዴድ በአስቸኳይ አዋጁ ላይ አቋም መያዙን መረጃዎች ያመለክታሉ። ብ አዴንም እየተንገዳገደም ቢሆን የተለየ አቋም እንዳለው ጭምጭምታዎች ያሳያሉ። በአዋጁ ላይ ከትግራይ ነጻ አውጪ ቡድን ጋር የተሰለፈው የደቡቡ የህወሀት ክንፍ ደኢህዴን ብቻ ነው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
በዚህኛው የአስቸኳይ አዋጅ የኮማንድ ፖስት ከፍተኛ አመራሮች ዝርዝር የሚያሳየን የጭምጭምታውን እውነትነት ነው። ከስድስቱ የኮማንድ ፖስቱ ከፍተኛ አመራሮች ውስጥ ኦህዴድ የለበትም። ብአዴንም ቢሆን በወላዋይ አቋሙ በሚታወቀው፡ በአደርባይነቱና አገልጋይነቱ በማያፍረው ደመቀ መኮንን ነው የተወከለው። በተረፈ 3ቱ አመራሮች ከደቡብ፡ ሁለቱ ከትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ናቸው። አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ፡ አቶ ሲራጅ ፈረጌሳና አቶ አሰፋ አቢዬ ከደኢህዴን፡ አቶ ጌታቸው አሰፋና ጄነራል ሳሞራ የኑስ ከትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር አባል የሆኑበት ኮማንድ ፖስት ነው የተቋቋመው። ይህም ኦህዴድ በአስቸኳይ አዋጁ አልተስማማም የሚለውን መረጃ ያጠናክረዋል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
አዋጁ ከ15 ቀናት በኋላ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ መጽደቅ አለበት። እስከዚያው በአሰራር ተግባራዊ ሆኖ ይቆያል። እንግዲህ ጦርነቱ የሚጠበቀው በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው። የኦህዴድ አቋም የሚታወቀውም ያን ጊዜ ነው። እንደሚባለው ኦህዴድና ብአዴን አዋጁን ውድቅ ሊያደርጉት ይችላል። ያ ከሆነ የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ይበልጥ ቀውስ ይገጥመዋል። ኢህአዴግ የሚባል የኩሸት ስብስብም የመፍረስ አደጋ ይደቀንበታል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<br />ህዝባዊ ተቃውሞ የት ደርሷል?</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<br />አንዱዓለም ''ፍርሃትን የሰበረ ህዝብ ማየት ምኞቴ ነበር። ከ6ዓመታት የእስር ቆይታ በኋላ ከቃሊቲ እግሬ ሲወጣ ያየሁት ህዝብ ያ የምመኘው ህዝብ ነው። ፍርሃትን የሰበረ ህዝብ።'' ብሎ ነበር ከእስር ቤት እንደወጣ። እውነት ነው። ፍርሃት ተሰብሯል። ዳመናው ተገፏል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
በ1997ቱ ምርጫ ወቅት ለቅስቀሳ ወደ ቦንጋ ያመሩት የኢህአዴግ እጩዎች ከሀገር ሽማግሌዎች የገጠማቸው ምላሽን አስታወስኩት። ''ቡሉኮ(ጋቢ) ከስድስት ወራት በላይ ከቆየ ተባይ ያፈራል። መቀየር አለበት። ኢህዲግም ይበቃዋል። መቀየር አለበት''። የቦንጋ የሀገር ሽማግሌዎች ያን ከተናገሩ 13 ዓመታት አለፈ። የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር አሁንም እዚያው ነው። ከተባይም በላይ ደም መጣች አውሬ ወጥቶታል። ለመጪውም ልቀጥል ብሎ ወታደራዊ አገዛዝ አውጇል። ሰሞኑን ጉራጌዎች ተነስተዋል። ወልቂጤን በአመጽ ቀጥ አድርገዋታል። ወደ ሌሎችም ወረዳዎች ተዛምቷል። ጉራጌዎች ''መንግስት አርጅቷል። ደክሞታል። ይረፍ'' የሚል መልዕክት አሰምተዋል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
ይህን ማስታወሻ በማዘጋጅበት ሰዓት ከተለያዩ የአማራ ክልል አከባቢዎች መልዕክት እየተቀበልኩ ነበር። ለነገ ለተጠራው ተቃውሞ ሰዉ መዘጋጀቱን የሚገልጹ መልዕክቶች ናቸው። አስቸኳይ አዋጁ በታወጀ ማግስት የሚደርግ ከሆነ ለአገዛዙ አደገኛ ነው። የትኛውም የሃይል እርምጃ የቆረጠን ህዝብ ሊመልሰው እንደማይችል ግልጽ መልዕክት የሚያስተላልፍ ነው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
የህዝብ ጉልበት የማያንበረክከው ሃይል የለም። አሜሪካም ቅኝቷን እንድትቀይር የተገደደችው የህዝብ ጉልበት እያየለ መምጣቱን ስትረዳ ነው ማለት ይቻላል። ሁሌም ከጉልበተኛ ጋር መሰለፍ የምትመርጠው አሜሪካ ከወዲሁ ምልክት አሳይታለች። የሙባረክ ወዳጅ ሆና ለ30 ዓመታት የዘለቀችው አሜሪካ የሙባረክ ጠላት ለመሆን ብዙ ጊዜ አልፈጀባትም። የጃስሚን አብዮት ግብጽን በጥፍሯ ሲያቆማት አሜሪካም ለሙባረክ ጀርባ ሰጠች። አሁንም ይሄ እየሆነ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ስርዓት ሳይለወጥ የሚቆም ትግል እንዳልጀመረ አሜሪካ ተረድታለች። የህዝብ ጉልበት ለHR 128ም ዋስትና ሆኗል። ረቂቁ ወደ ህግነት እንዲቀየር የህዝብ ጉልበት ይበልጥ መጠናከርን ይፈልጋል። ቀሪዎቹ በየማጎሪያ እስር ቤት የሚገኙ ጀግኖቻችን እንዲፈቱ ህዝባዊ ተቃውሞ አድማሱን አስፍቶ መቀጠል ግድ ይለዋል። የሁሉም ነገሮች ዋስትና የህዝብ ንቅናቄ ነው። አሜሪካ አይደለችም። HR 128ም አይደለም። ለማና ገዱም አይደሉም። ወይም ውጭ ያሉ ሃይሎችም አይደሉም። እነዚህ ሁሉ ዋስትናቸው የህዝብ ሃይል ነው። የተጀመረው ተቃውሞ ነው። ኦሮሚያ ክልልን ያዳረሰው፡ የአማራን ክልል ያጥለቀለቀው፡ ደቡብ ኢትዮጵያ ላይ የጀመረው፡ በሌሎችም የሚጠበቀው የህዝብ እምቢተኝነት ነው።</div>
<div style="background-color: white; display: inline; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-top: 6px;">
27 ዓመት ኪሳራ ነው:: የደርግ ሲጨመርበት ግማሽ ክፍለዘመን ከእድሜአችን ተቀንሷል:: ሀገሪቱም በዚያው መጠን ደቃለች። ይበቃታል። ከዚህ በኋላ አምባገንነና ዘረኛ ስርዓትን የምትሸከምበት ጫንቃ አይኖራትም።</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-23922091557629595792018-02-18T07:20:00.003-08:002018-02-18T07:20:44.670-08:00የትግላችን መጨረሻ ነፃነታችን ብቻ ነው! (የዲሲ የጋራ ግብረ ሃይል)<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
<em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">የዲሲ የጋራ ግብረ ሃይል</em></div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
<a href="https://ecadforum.com/Amharic/archives/6983/washington-dc-demo-2013/" rel="attachment wp-att-6984" style="color: #0f06ba; list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px; text-decoration-line: none; transition: all 0.2s ease-in-out;"><img alt="Ethiopians demonstration against the Amhara eviction" class="aligncenter size-full wp-image-6984" height="387" sizes="(max-width: 624px) 100vw, 624px" src="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2013/04/washington-dc-demo-2013.jpg?x81575" srcset="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2013/04/washington-dc-demo-2013.jpg 624w, https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2013/04/washington-dc-demo-2013-300x186.jpg 300w" style="border: 1px solid rgb(203, 205, 204); clear: both; display: block; height: auto; list-style: none; margin: 2px auto; max-width: 100%; outline: 0px; padding: 4px;" width="624" /></a></div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
የዋሽንግተን ዲሲ የጋራ ግብረ ሃይል ከፈጣሪ በታች የምንመካበት የኢትዮጵያ ህዝብ ክንዱን አስተባብሮ ስለነፃነቱ በጋራ በመቆም ለነፃነቱ ገፋፊዎች ባሳየው ማንነቱ አንገታችንን እንድናቀና ስላደረገን ምስጋናችን ከልብ የመነጨ ነው።</div>
<a name='more'></a><br />
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ድል የመስዋዕትነት ውጤት ነውና ባለፉት ሃይ ሰባት አመታት ውድ ህይወታቸውን ሰለነፃነት ለገበሩ በእስርና እንግልት ከፍተኛ ዋጋ ለከፈሉ እንቁ ወገኖቻችን ከበሬታችን ወደር የለውም፤ በተለይ ከደቡብ እስከ ሰሜኑ ጫፍ ከምስራቅ እስከ ምእራብ እየተናነቁ ያሉ ወጣቶችን እንዲሁም በተለያየ የትግል ስልት ተሰልፈው የአቅማቸውን ላደረጉና እያደረጉ ላሉ ሁሉ ግብረ ሃይሉ አድናቆቱን ይገልፃል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
እኛ በግብረ ሃይሉ የተሰባሰብን ኢትዮጵያዊያን መነሻና መድረሻችንን ኢትዮጵያን አድርገን የድርጅትና የሃይማኖት አጥርን ሰብረን በአንድነት እየተጓዝን ያለን አባላት የህዝባችንን የአንድነት ውጤት እያጣጣምን ነገር ግን ወያኔ ካለው ባህሪ በመነሳት ሳንዘናጋ ትግላችንን ለመቀጠል መነሳታችንን ደማቸው እየፈሰሰ ባሉት ወገኖቻችን ስም እየገለፅን አገራችንን ቀስፎ ከያዛት ዘረኛ አገዛዝ ነፃ እስክትወጣ ድረስ አቅማችን የፈቀደውን ሁሉ ለማድረግ ቃል እየገባንና ሁሉን አቀፍ የሆነ ስብስብ ለመፍጠር የሚደረጉ ጥረቶችን እያደነቅን ለተግባራዊነቱ ራሳችንን ማዘጋጀታችንን እንገልፃለን።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
በድጋሚ በወገኖቻችን ደም ለተገኘው ድል ባለፉት አመታት ድምፅ ለሌለው ወገናችን ድምፅ ለሆናችሁ ሁሉ እንኳን ደስ አለን እያልን በተጨማሪም ከወያኔ የግፍ እስራት ለተፈቱትና ለቤተሰቦቻቸው የተሰማንን ደስታ እየገለፅን ያልተፈቱትም ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ በኢትዮጵያውያን ህዝብ ትግል እንደሚፈቱ እምነታችን የፀና ነው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
በመጨረሻም በአሁኑ ወቅት የተገኙት ውጤቶች ሁሉ የትግላችን የመጨረሻ ምእራፍ መጀመሪያ እንጂ በራሱ ግባችን ስላልሆኑ አሁንም እንደ በፊቱ የተገኙት ድሎች ሳያዘናጉን የመጨረሻ ግባችን ለሆነው ውድ አገራችንንና ህዝባችንን ከዘረኛውና ግፈኛው የወያኔ ስርአት ለአንዴና ለመጨረሻ ግዜ የምንገላገልበትንና ፍትህ፣ ዲሞክራሲና እኩልነት የሰፈነባት ነፃ አገር ለመመስረት የምንችልበትን ሁኔታ እንፈጥር ዘንድ በአገር ቤት ይሁን በውጭ የምንገኝ ነፃነት አፍቃሪዎች አሁንም ዘር ሃይማኖት ሳይለያየን ለማይቀረው ድል የተጋረጠብንን ሁሉ በጋራ እንድናስውግድና በተገኙትም ጥቃቅን ድሎች እንዳንዘናጋ አበክረን እየገለፅን የተፋፋመውን ትግል ከዳር እንድናደርስ በመከራ ውስጥ ባሉት ወገኖቻችን ስም እንጠይቃለን።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ሞት ለዘረኛው ወያኔ!</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
አንድነት ሃይል ነው!</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
የዲሲ የጋራ ግብረ ሃይል dcjointtaskforce@gmail.com</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-51215564159415482312018-02-14T08:52:00.000-08:002018-02-14T08:52:25.491-08:00“ሁሉንም ባለድርሻዎች ያካተተ የሽግግር መንግስት ሂደት” አቶ ንአምን ዘለቀ<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ሁሉንም ባለድርሻዎች ያካተተ – ማለትም የፓለቲካ ሃይሎች፡ የሲቪክ ማህበረሰቡን፡ ታዋቂ ምሁራንን፣ የሀገር ሽማግሌዎች የሚገኙበት ማንንም ያላገለለ የብሔራዊ ዉይይትና ከዚህም የሚወጣ ሁሉን አቀፍ የሽግግር መንግስት ሂደት</strong></div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
<iframe allowfullscreen="allowfullscreen" frameborder="0" height="360" src="https://www.youtube.com/embed/xZ5-ELntOCM" style="list-style: none; margin: 0px; max-width: 100%; outline: 0px; padding: 0px;" width="640"></iframe></div>
<ul style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 18px; list-style: none; margin: 0px 0px 25px 10px; outline: 0px; padding: 0px;">
<li class="m_1216617468665165885aolmail_MsoNormal" style="list-style: disc outside none; margin: 0px 0px 5px 10px; outline: 0px; padding: 0px;">ሁሉንም ባለድርሻዎች ያካተተ – ማለትም የፓለቲካ ሃይሎች ፡ የሲቪክ ማህበረሰቡን፡ ታዋቂ ምሁራን ፣ የሀገር ሽማግሌዎች የሚገኙበት ማንንም ያላገለለ የብሔራዊ ዉይይትና ከዚህም የሚወጣ ሁሉን አቀፍ የሽግግር መንግስት ሂደት ብቻ ነው ተቀባይነት የሚኖረው፡፡<a name='more'></a> ሰፊው የኢትዮጵያው ህዝብ ይህ ነው የማይባል የህይወት መስዋእትነት በመክፈል ከፋሽታዊው የህወአት ስርአት ጋር እየታገለ፣ እየተጋተረ የሚገኘው ወደ ሀቀኛ ዴሞክራሲያዊ ስርአት የሚያደርስ ፡ ሙሉ መብቶችና ነጻነቶችን የሚጎናጸፍበትን ስርአታዊ ለውጥ ለማምጣት እንጂ የወያኔን የበላይነት የሚያስቀጥል ወይንም ስርአቱን ጠጋግኖ ለማቆየት ለሚደረግ የተለያዩ መከራዎች እንዲጠለፍ አይደለም።</li>
<li class="m_1216617468665165885aolmail_MsoNormal" style="list-style: disc outside none; margin: 0px 0px 5px 10px; outline: 0px; padding: 0px;">የሕወአትን የበላይነት የነገሰበትን ስርአት ጠጋግኖ ለማስቀጠል የሚደረጉ ጥረቶች አገዛዙ የገባበትን ጥልቅ የፓለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች ሊፈቱ የሚችሉ አለመሆናቸው ብቻ ሳይሆን የስርአት ለውጥ እየጠየቀና ከፍርሃት ወጥቶ ሞትን በማሸነፍ ከወያኔ ፋሽስታዊ ነፍሰ ገዳዮች ጋር በመጋፈጥ ላይ የሚገኘው የኦሮሞ፣ የአማራ፣ የአፋር፣ የደቡብና ሌሎችም ማህበረሰቦች በጥቅሉም የኢትዮጵያ ህዝብ የሚቀበሉት ዘላቂና እሰተማማኝ መፍትሄ አይሆንም፣ – ኦሄድድ በቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚወስዳቸው እርምጃዎች የሚበረታቱና የህዝቡን ጥያቄዎች ውስን በሆነም መልኩ እየመለሱና የሕወአትን የበላይነት እየተፈታተኑ በመሆናቸው ለሚፈልገው ለውጥ ጥሩ ጅምር ነው ብለን እናምናለን።</li>
<li class="m_1216617468665165885aolmail_MsoNormal" style="list-style: disc outside none; margin: 0px 0px 5px 10px; outline: 0px; padding: 0px;">የአግ 7 በብዙ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በሚደረጉ የህዝብ ትግሎች ውስጥ አለ፣ ክፍለጦሮች ፣ ብርጌዶች፡ መድፍና ታንኮች ይዞ ግን አይደለም፣ እግ7 የህዝቡን ትግል የሚያግዙ በርካታ ልዩ ልዩ የትግል ስልቶችን በበርካታ የሀገሪቱ አካባቢዎች ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል፣ ትግሉ ግን በቀዳሚነት የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል ነው። – ከደሚት ጋር በ አግ7 ያወጣው የጋራ መግለጫ በጣም አስፈላጊም ፣ ወቅታዊም ነው፣ የትግራይ ህዝብ፣ የትግራይ ምሁራን፡ ልዩ ልዩ ሃይሎች ከዘራፊው ፋሽስታዊ የህወአት ጨካኝ ቡድን መነጠል ብሎም የትግሉ አካል እንዲሆኑ ተደጋጋሚ ጥሪ ማድረግ የውያኔን አጥፍቶ መጥፋት አገር እፍራሽ እካሄድ ለማምከን ለሀገሪቱ ሰላም፣ እንድነትና፣ የወደፊት እጣ ፈንታ ወቅታዊና በጣም እስፈላጊ ነው።</li>
</ul>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-50368935193332647612018-02-13T08:47:00.000-08:002018-02-13T08:47:21.809-08:00የኦጋዴን ነፃ አውጪ ግንባርና የወያኔ ድርድር በኢትዮጵያ አንድነት ላይ የተቃጣ ሴራ!<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
<em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">ከዶ/ር ዲማ ነገዎ፣ ፕ/ር ጌታቸው በጋሻው እና ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ</em></div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
<a href="https://ecadforum.com/Amharic/archives/18424/ogaden-map/" rel="attachment wp-att-18425" style="color: #0f06ba; list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px; text-decoration-line: none; transition: all 0.2s ease-in-out;"><img alt="Ogaden is the unofficial name of the Somali Region of Ethiopia" class="aligncenter size-full wp-image-18425" height="330" sizes="(max-width: 620px) 100vw, 620px" src="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2017/12/Ogaden-Map.jpg?x79395" srcset="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2017/12/Ogaden-Map.jpg 620w, https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2017/12/Ogaden-Map-300x160.jpg 300w" style="border: 1px solid rgb(203, 205, 204); clear: both; display: block; height: auto; list-style: none; margin: 2px auto; max-width: 100%; outline: 0px; padding: 4px;" width="620" /></a></div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ከታማኝ ምንጮች እንደተረዳነው በወያኔና በኦብነግ መካከል ሲካሄድ የቆየው ውይይት በመጠናቀቅ ላይ ነው:: በናይሮቢ ተጀምሮ በዱበይ ከተማ ሲካሔድ ቆይቶ አሁን እንደገና ወደ ናይሮቢ ተመልሶ ፍፃሜ ላይ መድረሱን ምንጮቻችን ገልፀዋል:: ይህ ሤራ ወያኔ ኢትዮጵያን ረግጦ ገዝቶ ለመኖር ካልቻለ ኢትዮጵያን ሽብር ውስጥ ከቶ ትግራይን ለመገንጠልና የትግራይን ሪፑብሊክን ለማቋቋም ያለውን ግልፅ አቋም በተግባር እየተረጎመ መሆኑን ያሳያል::</div>
<a name='more'></a><br />
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
የኦብነግ አላማ ከስር መሰረቱና እስካሁን ድረስ ኦጋዴንን ለመገንጠል መሆኑን በብዙ ጥናቶች ተጠቁሟል:: በቅርቡም በሻለቃ ዳዊት ተፅፎ በድህረ ገፆች ላይ የተለጠፈውን ጥናት ይህንኑ ጠቋሚ ነው::</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
የኦብነግ አላማ ከወያኔ አላማ ጋር ተመሳሳይነት አለው:: ኦብነግ ኢትዮጵያን አዳክሞ : ኦጋዴንን ከኦሮሞ ከአማራ እና ከሌሎችም ብሔረሰቦች ነፃ አድርጎ በተዳከመችና ሽብር ላይ በምትኖር ኢትዮጵያ ላይ ነፃነቱን ለማወጅ ነው :: ይህ ሊሆን የሚችለው ወይ ከወያኔ ጋር በመተባበር ፤ አለያም ደግሞ በኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል የወያኔ የጦር ሀይል ተዝረክርኮና ተዳክሞ የኦጋዴንን ተገንጣይ ሀይል ለመቋቋም አቅም የማይኖረው ደረጃ ላይ ሲደርስ ነው:: ኦብነግ በዚህ ከሕዝብ ጀርባ ከሕወሓት የጦር አዛዦች ጋር የሚደረግ ድርድር ላይ መገኘቱ ፤ ከወያኔ ጋር መተባበር ቀላሉና ፍላጎቱን ለማሳካት አቋራጭ እድል አድርጎት ይሆናል::</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ዛሬ የአማራና የኦሮሞ መተባበር ወያኔን ከባድ ሥጋት ላይ ጥሎታል:: ወያኔ የኦሮሞንና የአማራን መተባበር ሲከላከልና በመሀላቸው ነዋሪና ዘላቂ ልዮነቶችና ግጭቶች እንዲኖር ያላደረገው ነገር አለመኖሩን የኢትዮጵያ ሕዝብ ያውቃል:: የሁለቱ ሕዝቦች መተባበር የኢትዮጵያን አንድነትና ሉአላዊነት እንዲሁም የወያኔን የበላይነት የሚደመስስ መሆኑን ስለተረዱት ብዙ ሤራዎች ሸርበው: ብዙ ግድያዎች ፈፅመው : ለብዙ ሕዝብ መፈናቀልና መሰደድ ምክንያት ከሆኑ በሗላ ዛሬ ማጠፊያው አጥሯቸው እራሳቸው ባዘጋጁት ማነቆ ውስጥ ገብተዋል::</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ኦሮሞና አማራው ብቻ ሳይሆን መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የኢትዮጵያን አንድነት የሚፈታተኑ ሀይሎችን ሁሉ ለመዋጋትና ለመታገል ዝግጁ መሆኑን አገር አቀፍ በሆነ ንቅናቄው እያሳየ ይገኛል:: የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድነቱ ላይ ያለውን የማይናወጽ አቋም ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ እያስተጋባ ነው ::</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ይህ ሕዝባዊ ንቅናቄ ወደኃላ የሚመልሰው ምንም ሀይል አለመኖሩን ወያኔ ስለተረዳ የሕዝቡን ድምፅ እድምጦና ተረድቶ የሽግግር መንግስት አቋቁሞ ሁኔታዎችን ከማረጋጋት ይልቅ ወደ ተፀነሰበት ትግራይን የመገንጠል አላማ እየተጓዘ መሆኑ በመሬት ላይ የሚታዩ እርምጃዎቹ ይጠቁማሉ::</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
የወያኔ አላማ የኦብነግን ሰራዊት በመጠቀም በኦሮሞ: በአማራውና በደቡብ ህዝቦች ላይ በመዝመት በዚህ ትርምስ ውስጥ የኦጋዴንና የትግራይን መገንጠል ዕውን ለማድረግ ነው:: ( ታላቁ ሴራ በሚል ርዕስ ወያኔ ኢትዮጵያ ሊገባ ሲል የተፃፈውን ማንበብ ይጠቅማል)</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ይህ የወያኔና የኦብነግ ሰራዊት አንድነት መፍጠር ኢትዮጵያን ወዳልታሰበ ፍፁም አደገኛ ወደሆነ ሌላ ትርምስ ውስጥ ሊከታት እንደሆነ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሊረዳው ይገባል::</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ኦህዴድ እና ብአዴን እንደ ድርጅት እስከዛሬ የወሰዳችሁትና እየወሰዳችሁት ያለው አወንታዊ እርምጃዎች እንደተጠበቁ ሆነው: በሰከነ ልቦና ይህንን ሴራ መርምራችሁ በየድርጅቶቻችሁ ሕልውናና በምትወክሉት ህዝብ ላይ የተቃጣውን ዘመቻ በትብብርና በአንድነት ለመቋቋም በአጣዳፊ መዘጋጀት ሁኔታው ግድ ይላል::</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ለኢትዮጵያ አንድነት የቆማችሁ ሁሉ ዛሬ ዘር ፤ ሐይማኖት ፤ የፓለቲካና የቋንቋ ልዩነት ፤ ሳይለያያችሁ ይህንን አደገኛ ሃገር የማፍረስ ሴራ ለማክሸፍ የተጀመረውን ትግል ማጠናከር አለባችሁ::</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ይህ ለጥቂቶች የማይተው እውነተኛ አገር አድን ዘመቻ ነው::</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
በኢትዮጵያ አንድነት ላይ የምታምኑ ፤ የኢትዮጵያ የፖለቲካና የሲቪክ ድርጅቶች ፤ የሀይማኖት ኣባቶች ፤ በተሰማራችሁበት ዘርፍ ተቃውሞአችሁን አሰሙ ::</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ለኢትዮጲያ አንድነት የቆማችሁ የሶሻል ሚዲያ የሬዲዮ : የጋዜጣ : የቴሌቭዥንና የድህረ ገፅ ሚዲያዎች ሁሉ ያላችሁን መድረክ ወገን ሳትለዩ ለዚህ አንገብጋቢ ጉዳይ ውይይት አውሉት::</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ይንንም ኢሳትን ኦኤምኤን: ገበታ ሚድያ ሕብር ሬድዮ የአማርኛና የኦሮሚኛ የቴሌቭዥንና ሬድዮ ፤ ጣቢያዎችን ያጠቃልላል::</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
በዚህ አጋጣሚ የሃገራችንና የሕዝባችን ሕልውና የከፋ አደጋ ላይ ከመውደቁ በፊት ፤ ሁሉም በየመስኩ ሁኔታውን እየተከታተለ በአንድ የኢትዮጵያዊነት ድምጽ ትግሉን ያስተባብር :: የምንዘላለፍበት ፤ የምንሰዳደብበት እና የምንወቃቀስበት ጊዜ አይደለም:: በታሪክ እንደታየው ታላቅ ፈተና ሲመጣ በአንድነት የምንቆምበት ጊዜ ነው::</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ዶ/ር ዲማ ነገዎ</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ፕ/ር ጌታቸው በጋሻው</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com1tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-21659271090237459382018-02-11T06:10:00.001-08:002018-02-11T06:10:51.384-08:00የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ህወሀት ከኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጪ ግንባር ጋር በኬኒያ ሸምጋይነት ድርድር ጀምረዋል። <em style="font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">በመሳይ መኮንን</em><br />
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
<a href="https://ecadforum.com/Amharic/archives/18619/onlf-fighters/" rel="attachment wp-att-18620" style="color: #0f06ba; list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px; text-decoration-line: none; transition: all 0.2s ease-in-out;"><img alt="Ogaden National Liberation Front" class="aligncenter size-full wp-image-18620" height="330" sizes="(max-width: 620px) 100vw, 620px" src="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2018/02/ONLF-fighters.jpg?x87351" srcset="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2018/02/ONLF-fighters.jpg 620w, https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2018/02/ONLF-fighters-300x160.jpg 300w" style="border: 1px solid rgb(203, 205, 204); clear: both; display: block; height: auto; list-style: none; margin: 2px auto; max-width: 100%; outline: 0px; padding: 4px;" width="620" /></a></div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ህወሀት ከኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጪ ግንባር ጋር በኬኒያ ሸምጋይነት ድርድር ጀምረዋል። የሶማሌ ክልል ፕሬዛዳንት አብዲ ኢሌና በሶማሊያ የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ተወካይ ጄነራል ገብሬ የህወሀትን መንግስት ወክለው በድርድሩ እየተሳተፉ መሆናቸው ተገልጿል። የሚጠበቅ ነው። በዚህን ወቅት፡ የህዝብ ንቅናቄ ሲጠነክር፡ ፖለቲካዊ ትኩሳት ሲጨምር የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ከሚወስዳቸው የተለመዱ እርምጃዎች አንዱ የኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባርን ደጅ መጥናት ነው። ድርድር።</div>
<a name='more'></a><br />
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ህወሀት በማዕከላዊ መንግስቱ የበላይነቱን አስጠብቆ በስልጣን ላይ መቆየት የማይችል ከሆነ ለአደጋ ጊዜው ካስቀመጣቸው ካርዶች መሀል የኦጋዴኑ በዋናነት የሚጠቀስ ነው። ይህን ካርድ በሁለት ምክንያቶች ሊጠቀም ይፈልጋል። አንደኛው እስከአሁንም በተደጋጋሚ እንዳደረገው የፖለቲካ ውጥረት ሲገጥመው በድርድር ወሬ ማደንዘዝ፡ ለኢትዮጵያውያን እኔ ከሌለሁ ሀገሪቱ እንደሶቪየት ህበረት ትበታተናለች የሚል መልዕክት መስደድ በዚህም ውጥረቱን ማርገብና በስልጣን የመቆየት ዕድሜን ማራዘም ነው። ሌላው የህዝብ ተቃውሞ ጠንክሮ ከገፋና ቤተመንግስቱን የሚነጠቅ ከሆነ ደግሞ ኢትዮጵያን ለማተራመስ እንዲረዳው የኦጋዴንን የመገንጠል ጥያቄ ተቀብሎ በእንግሊዝ መንግስት ከዘመናት በፊት የተቀመመውን ቦንብ ማፈንዳት ነው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ይህን ቢያደርግ የሚደንቅ አይሆንም። የኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባርን የሚመሩ ሰዎች ከስህተታቸው አለመማራቸው ግን አስገራሚ ነው። በተደጋጋሚ እንዲህ ዓይነት ድርድር ተደርጎ በትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ሸፍጥና ሴራ ሲከሽፍ እንደነበረ ራሳቸው በአገኙት አጋጣሚ ይገልጻሉ። በየግዜው ይሄን ግንባር ለማፍረስ በህወሀት በኩል ከፍተኛ ገንዘብ ተመድቦ አመራሮቹን የማስከዳት እርምጃ ተወስዷል። ህወሀት በገንዘብ ሃይል ካስከዳቸው የግንባሩ አመራሮች ጋር ዋንጫ አንስቶ ”ኦብነግ በእጄ ገብቷል” የሚሉ ዜናዎችን ነግሮናል። እነዚያ የከዱት ሰዎች ገንዘባቸውን በኪሳቸው አድርገው የህወሀትን ጊዜያዊ የፕሮፖጋንዳ ጥም ካረኩ በኋላ የት እንደሚገቡ አይታወቅም። አሁንም ኦብነግ አለ። አሁንም ድርድር አለ።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
የኦብነግ ሃላፊዎች ከዚህ ቀደም ለድርድር ወደናይሮቢ የላኳቸው ሁለት አመራሮቻቸው በትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ደህንነቶች ታፍነው መወሰዳቸውን ሲገልጹ እኚህ ሰዎች ዳግም ከህወሀት መንግስት ጋር ለድርድር አንድ ጠረጴዛ ላይ ይቀመጣሉ ብሎ የጠበቀ አልነበረም። ባለፈው ዓመትም አንድ የኦብነግ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዥ በሶማሊያ መንግስት አማካኝነት ለትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ተላልፈው መሰጠታቸውና በማዕከላዊ ሰቆቃ እየተፈጸመባቸው መሆኑን ላስታወሰ በዚህ አጭር ጊዜ ኦብነህግ የህወሀትን የድርድር ጥያቄ ይቀበላል ብሎ ለመገመት ይቸገራል። የኦብነግ አመራሮች ሁሌም ለትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር የለበጣና ትኩሳት ማብረጃ ለታለመ ድርድር ፍቃደኛ የሚሆኑበት ምክንያት ግራ ያጋባል። አሁንም ሄደዋል። ኬኒያ ናቸው። ህወሀት ለመጣበት አደጋ መሻገሪያ የሚሆንለት ድርድር አድርጎ ስለሚያምን ቢያደርገው አይገርምም። ኦብነግ ግን ከእንዲህ ዓይነቱ ድርድር ምን ሊያተርፍ ይሆን? ህወሀት በዚህኛው ዙር ድርድር አብዲ ኢሌን የላከውስ ለምንድን ነው?</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
በ2006 እኤአ ኦብነግ በቻይና የነዳጅ አውጪ ኩባንያ ላይ እርምጃ ወስዶ ከ70 በላይ ሰራተኞችን ከገደለ በኋላ የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር እሾህን በእሾህ የሚል ስልትን ነው የመረጠው። ከዚያው ከሶማሊያ ክልል በስራ ማጣትና በሱስ የተተበተቡ ወጣቶችን ሰብስቦ የስራ እድል ሰጣቸው። የሶማሌ ክልል ልዩ ሃይል በሚል አደራጃቸው። ከእንግሊዝ መንግስት በሚገኝ ከፍተኛ ድጋፍ ለዚህ ልዩ ሃይል ዘመናዊ መሳሪያ አስታጠቀው። ተወርዋሪ፡ ተወንጫፊ፡ ልዩ ጦር አድርጎ ካዋቀረው በኋላ የኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባርን እንዲደመስስ አሰማራው። በዚህና በዚያ ወገን የተሰለፉ የአንድ እናት ልጆች በኦጋዴን ምድር ፍልሚያ ገጠሙ። እናም ህወሀት በመጠኑ ተሳካለት። የኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባር ጂጂጋ ድረስ እየዘለቀ የሚሰነዝረው ጥቃት እየቀነሰ መጣ። ይህ ልዩ ሃይል ሌላም ተልዕኮ ነበረው። የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባርን ዙፋን ለማስጠበቅ ከሚሰለፉ ሃይሎች ግንባር ቀደም እንዲሆን ተደርጓል። በቅርቡ በኦሮሞ ወገናችን ላይ እንዲዘምት የተደረገውም የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባርን ስልጣን ለመከላከል እንደሆነ ከምንም የተሰወረ አይደለም።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
እንግዲህ የኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባር ከዚህ ፍጹም አረመኔ፡ ጸረ ሰላም ሃይል ከሆነ የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ህወሀት ጋር በየጊዜው ድርድር የሚቀመጥበት ምክንያት ግልጽ አይደለም። የኦጋዴን ነጻ መንግስት በህወሀት ፍቃድ አገኛለሁ ብሎ የሚጠብቅ ከሆነ ታሪካዊ ስህተት እየሰራ ነው። ደግሞም ግንባሩ በኢትዮጵያ ጥላ ስር ሆኖ ለዲሞክራሲና ነጻነት እንደሚታገል በቅርቡ ገልጿል። በይፋም ባይሆን በተዘዋዋሪ የመገንጠል አጀንዳውን እንደተወው አስታውቋል። ከመገንጠል አጀንዳ ባለፈ ከህወሀት ጋር ድርድር የሚያስቀምጠው ጉዳይ የስልጣን መጋራት ከሆነ በዚህ በኩል መንገዱ ዝግ እንደሆነ ከግንባሩ አመራሮች የተሰወረ አይመስለኝም። አብዲ ኢሌ የተባለ ነውረኛ፡ ከዕውቀት ነጻ የሆነ ሰው እያለ ስልጣን መጋራት የሚታሰብ አይደለም። የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር በተዳከመበትና ወንበሩ በተነቃነቀበት በዚህን ጊዜ ስልጣን ለመጋራት ድርድር መቀመጥ ያልተጠና፡ ወቅቱን ያላገናዘበ ደካማ የፖለቲካ እርምጃ ነው። የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር እንኳን ለሌላው የሚያጋራው ስልጣን ይቅርና ማዕከላዊ መንግስቱ ላይ ያለውን የበላይነት አስጠብቆ ለማቆየት የሚያስችል አቅም የሌለው፡ መቃብሩን በቅርብ ርቀት እየተመለከተ፡ ውድቀቱን እያሸተተ ያለ ሃይል መሆኑን የኦብነግ አመራሮች ካልተረዱት የፖለቲካ ግንዛቤአችውን እንድንጠራጠር የሚያስገድደን ነው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
የሆነስ ሆኖ ድርድሩ ለኢትዮጵያ ህዝብ የሚፈይደው ነገር የለም። የኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባር የሚያገኘው አንዳችም ትርፍ የለም። የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር የተዘፈቀበትን የፍርሃታና የስጋት ዳመና ለመግፈፍ ከታለመ የሸፍጥ ድርድር የሚጠቀም አካል አይኖርም። ከምንም በላይ የኢትዮጵያ ህዝብ የደረሰበት ውሳኔ የትኛውንም የሴራ ድርድር የሚሳካ አያደርገውም። ህዝብ ተነስቷል። የኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባር አመራሮች ከትግራዩ የህወሀት ቡድን ጋር የሚያድርጉት አሰልቺ የድርድር ድራማ ከሁለት አንድ የሚያሳጣቸው መሆኑን ሊያውቁት ይገባል። ወራጅ ወንዝ እንዲወስዳቸው መፍቀድ የለባቸው። እየሞተ ካለ ስርዓት ጋር ለድርድር መቀመጥ ምንም ትርፍ የለውም። ይልቅስ የኢትዮጵያ ህዝብ እያደረገ ያለውን የሞት ሽረት ተጋድሎ ማገዝ ከኦብነግ የሚጠበቅ የወቅቱ እርምጃ ነው።</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-7079186397029147622018-02-08T13:20:00.000-08:002018-02-08T13:20:11.064-08:00ፋሽስታዊው የሕወአት አገዛዝ የቆመበትን ኢኮኖሚያዊ ምሰሶዎች ለማሽመድመድ አለም አቀፍ የሃዋላ ተአቅቦ ዘመቻ አካል እንሁን!!<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
<em style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;">በነአምን ዘለቀ</em></div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
<a href="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2018/02/Remittance-Embargo1.jpg?x28047" style="color: #0f06ba; list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px; text-decoration-line: none; transition: all 0.2s ease-in-out;"><img alt="Ethiopians Remittance Embargo." class="aligncenter size-full wp-image-18608" height="330" sizes="(max-width: 620px) 100vw, 620px" src="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2018/02/Remittance-Embargo1.jpg?x28047" srcset="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2018/02/Remittance-Embargo1.jpg 620w, https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2018/02/Remittance-Embargo1-300x160.jpg 300w" style="border: 1px solid rgb(203, 205, 204); clear: both; display: block; height: auto; list-style: none; margin: 2px auto; max-width: 100%; outline: 0px; padding: 4px;" width="620" /></a></div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ከፋሽስቱ የወያኔ አገዛዝ ጋር በሚደርገው ሁለገብ ትግል ስልቶች መካከል <a href="https://ecadforum.com/2017/12/28/ethiopia-a-call-for-worldwide-remittance-embargo/" style="color: #0f06ba; list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px; text-decoration-line: none; transition: all 0.2s ease-in-out;">የኢኮኖሚያዊ ጦርነት (Economic Warfare)</a> አንዱ ነው። ስርአቱ የቆመበትን ምሰሶ የማዳከም የኢኮኖሚያዊ ጦርነት ስልቶች እንዱ የሃዋላ ተአቅቦ ነው። የሃዋላ ተአቅቦ ለአጠቃላይ ትግሉ ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግና ስርአቱን ለማዳከም ያለው ሚና ከፍተኛ ነው።</div>
<a name='more'></a><br />
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
በፋሽስቱ የሕዝባዊ ወያኔ አርነት ትግራይ የበላይነት ስር የሚገኘው አምባገነናዊ አገዛዝ በከባድ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ እንደሚገኝ ከሶስት ወራት በፊት በስርአቱ ሾልኮ የወጣ የራሱ የብሄራዊ ጸጥታ ም/ቤት የውይይት ሰነድ ያረጋግጣል። ከዚህም በላይ በልዩ ልዩ መገናኛ ብዙሃን መዘገቡ ፣ እንዲሁም የተለያዩ መረጃዎች በየጊዜው እንደወጡ ይታወቃል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ፋሽታዊው የወያኔ አገዛዝ የገባበትን ሁለንተናዊ የፓለቲካና የኢኮኖሚያዊ ቀውሶች ትተን በውጭ ምንዛሪ በኩል አገዛዙ የደረሰበት የቀውስ ደረጃ በሚመለከት በቅርቡ በኢሳት ፥ ኦሜን፣ ዋዜማ፣ ኣንዲሁም በልዩ ልዩ የሚዲያ አውታሮች የወጡ መረጃዎችን ስንመለከት የቀውሱን ጥልቀት ለመረዳት ይቻላል። ከእነዚህም መረጃዎች ውስጥ የሚከተሉትን ለናሙና እንይ፦</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
1. የቴሌ ፣ የንግድ መርከብ ድርጅት፣ የመብራት ሃይል፡ ለልዩ ልዩ ፕሮጄክቶች ከውጭ ባንኮች የተበደሩትን ገንዘብ ለመክፈል (Debt servicing) በውጭ ምንዛሪ እጥረት ሳቢያ መክፈል እንዳልቻሉ፣<br style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;" />2. የአገዛዙ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በውጭ ለሚገኙ ኢምባሲዎችና ቆንስላዎችን በጀት በገባበት የውጭ ምንዛሪ እጥረት ሳቢያ መሸፈን አለመቻሉ፣<br style="list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px;" />3. በአዲስ አበባ የአርማታ ብረት ዋጋ ሰማይ እየነካ መሆኑ፣ የዶላር ግዢ በጥቁር ገበያ 35 ብር መድረሱ፣ ብረት በ9 ወራት ውስጥ በእጥፍ መጨመሩ፣ በአዲስ አበባ ብቻ 26ሺህ የሕንጻ ግንባታዎች ሊስተጓጎሉ እንደሚችሉ ከላይ በተጠቀሱት የሚዲያ አውታሮችና ሌሎችም ተዘግቦአል።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ስርአቱን እየናጡ ከሚገኙት የኢትዮጵያ ሕዝብ የእምቢተኝነትና የአመጽ ትግሎች ሳቢያ የህወአት ፋሽታዊ አገዛዝ ከባድ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ እንደሚገኝ ሌሎችም መገለጫዎችና መረጃዎች ማቅረብ ይቻላል። ለዚህም ነው የውጭ ምንዛሪ ተአቅቦ ዘመቻው ከተጀመረ በኋላ አገዛዙ ከፍጠኛ ድንጋጤ ውስጥ የገባው። በቅርቡም ወደ ሀገር ውስጥ ግለሰቦች ይዘው የሚገቡትንና ይዘውም የሚወጡትን የውጭ ምንዛሪ ለመቆጣጠርና ለመገደብ አዲስ ህግም እስከማውጣት ድረስ የተገደደው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
ከላይ የቀረቡት መረጃዎች አለም አቀፍ የሀዋላ እቀባ ዘመቻው በስርአቱ ላይ ከፍተኛ ጫና እያመጣ መሆኑን ያረጋግጣሉ። የፋሽስቱ የህዝባዊ ወያኔ ስርአት አገዛዝ አንዱና ትልቁ ጭንቀት የገባበት የኢኮኖሚያዊ ቀውስና ከዚህ ጋር የተያያዘው የውጭ ምንዛሪ እጥረት ቀውስ መሆናቸውን ሁሉም ኢትዮጵያዊ መገንዘብ ያለበት ጉዳይ ነው።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
የወያኔ አገዛዝ ከውጭ በሃዋላ የሚያገኘው 4.5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ የአፈና ስርአቱን ለማንሰራርት፡ ገዳዮቹን ፣ አፋኞቹን ለመክፈል ፡ ህዝብን የሚጨፈጭፍበት መሳሪያዎች ለመግዛት ጭምር የሚጠቀምበት በመሆኑ፡ የአገዛዙን የውጭ ምንዛሪ ምንጮች ማድረቅ የትግሉ ትልቅና ወሳኝ አካል መሆኑን መገንዘብ በጣም አስፈላጊና ወቅታዊ ነው ።</div>
<div style="background-color: white; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: 0px; padding: 0px 0px 1em;">
በኢትዮጵያዊያን አለም አቀፍ ግብረ ሃይል የተጀመረውን <a href="https://ecadforum.com/2017/12/28/ethiopia-a-call-for-worldwide-remittance-embargo/" style="color: #0f06ba; list-style: none; margin: 0px; outline: 0px; padding: 0px; text-decoration-line: none; transition: all 0.2s ease-in-out;">የሃዋላ ተአቅቦ ዘመቻ</a> እንደግፍ፣ ለዘመድ አዝማድ ፣ ለጓደኞች፣ በማህበራዊ ግንኙነቶችና በሁልም መንገዶች የዘመቻውን አላማና ግብ በማሰራጨት ይህን ዘመቻ ለማጠናከር፣ ግቡንም እንዲመታ ሁላችንም መረባረብ ይገባናል።</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-79638831353851829822018-02-08T05:27:00.001-08:002018-02-08T05:27:12.188-08:00ህወሓትና ኢትዮጵያን የማፈራረስ ዓላማው!<h1 class="entry-title" style="background-color: white; color: #333333; font-family: Georgia, Times, "Times New Roman", serif; font-size: 24px; line-height: 30px; margin: 0px 0px 10px; padding: 0px;">
<img src="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2017/09/tplf-top-officials-e1505460595967-620x310.jpg" /></h1>
<div class="entry-content" style="background-color: white; font-family: Verdana, Geneva, sans-serif; overflow: hidden;">
<div class="pf-content">
<div class="entry-title" style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<em><strong>የአዘጋጆቹ ማስታወሻ፤</strong> ባለፉት ዓመታት ከህወሓት እየኮበለሉ የወጡ የቀድሞ አባላት በርካታ ናቸው። እንዳንዳቸው የሚወጡበት ምክንያት ቢኖራቸውም ህወሃትን በማጋለጥና ማንነቱን ለኢትዮጵያ ሕዝብ በማሳወቅ የአቶ ገብረመድኅን አርአያን ያህል ታላቅ ሥራ የሠራና መስዋዕትነት የከፈለ አለ ለማለት ያስቸግራል። አብዛኛዎቹ የቀድሞው አባላቱ የህወሓትን ምሥጢራዊ አሠራር እና እጅግ አረመኔያዊ ግፍ፤ ኤፈርት በኢትዮጵያ ሐብት ላይ የፈጸመውንና እስካሁንም እየፈጸመ ያለውን የኢኮኖሚ ግፍ፣ ዝርፊያ፣ ሌብነት፣ … የመሳሰሉ ጉዳዮች በአደባባይ ከመናገር ሲቆጠቡ ተስተውለዋል። አንዳንዶቹም በህወሓት ከፍተኛ አመራር ላይ የነበሩ የቀድሞ አባላት ቢሆኑም፤ ኤፈርትም ሲያስተዳድሩ የቆዩ ቢሆኑም ስለጉዳዩ ሲጠየቁ የሚሰጡት ምላሽ አባይ ጸሐዬ ወይም ስብሃት ነጋ ከሚሰጡት ምላሽ ያልተለየ ሆኖ ተገኝቷል።</em></div>
<a name='more'></a><em> አቶ ገብረመድኅን አርአያ <a href="http://www.goolgule.com/tplf-the-destructive-force-of-ethiopia/" style="text-decoration-line: none;">“ዝሆን ላይ የሚጮህ እብድ ውሻ ብቻ ነው</a>” በሚል ርዕስ ያቀናበሩትን ዳጎስ ያለ ሠነድ በድረገጻችን ላይ እንድናትመው በላኩልን መሠረት ከጥቂት ወራት <a href="http://www.goolgule.com/tplf-the-destructive-force-of-ethiopia/" style="text-decoration-line: none;">በፊት ክፍል አንድን</a> አቅርበን ነበር። (ይህንን ዕትም ለመረዳት <a href="http://www.goolgule.com/tplf-the-destructive-force-of-ethiopia/" style="text-decoration-line: none;">ክፍል አንድን ማንበብ አስፈላጊ በመሆኑ እዚህ ላይ በመጫን እንዲያነቡ እናሳስባለን</a>)። ስማቸው የግድ መገለጽ ስላለበት ስማቸው የወጣ ለዚህ ጽሁፍ ምላሽ መስጠት ለሚፈልጉ በራችን ክፍት ነው። የዝግጅት ክፍላችን ለአቶ ገብረመድኅን ምስጋናውን እያቀረበ ሌሎችም የህወሓት የቀድሞ አባላት ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱና በዚህ መልኩ ከሕዝብ ጋር እንዲታረቁ ሃሳብ እንሰጣለን። ያለ እውነት ዕርቅ የለም፤ ያለ ዕርቅ አብሮ መኖር የለም።</em><br />
<hr align="center" size="2" width="100%" />
<h4 style="font-family: Oswald, arial, serif; font-weight: normal; line-height: 18px; margin: 0px 0px 10px; padding: 0px; text-align: justify;">
<strong>ዝሆን ላይ የሚጮህ እብድ ውሻ ብቻ ነው!</strong></h4>
<div class="entry-title" style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ወያኔዎች በትግራይ ህዝብ የጥቃት ዘመቻ የከፈቱበት ምክንያት የትግራይ ህዝብ በኢትዮጵያዊነቱ እምነቱ ከፋፋይና ዘረኛው ወያኔ ፤ በእውቅና አለመቀበሉ ቀጥሎ ያለውን ዋና ምክንያቶች እንመልከት።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
1. አማራ ደመኛ ጠላትህ ሲሉት አይደለም ወንድሜ ወገኔ ኢትዮጵያዊ ነው በማለቱ፣</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
2. ተሓህት የትግራይን ሕዝብ አይወክልም አናውቃችሁም በማለቱ፣</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
3. ተሓህት የነጠቀውን የሰሜን ጎንደርና የሰሜን ወሎ ለም መሬቶች አንቀበልም፣ የሰሜን ጎንደሩ የጎንደር ጠ/ግዛት ነው፣ የሰሜን ወሎ የወሎ ጠ/ግዛት ነው፣ ከትግራይ ግንኙነት የላቸውም፤ በጎንደር በኩል የሚያዋስነን ተከዜ ወንዝ ነው። በወሎ በኩል ማይጨው ችንኮማጂ ነው፤ ሲሆን በምን መልኩ ነው የትግራይ የሚሆነው በማለቱ፣ ከወንድሞቻችን ጥላቻና ቅራኔ አትፍጠሩብን ብሎ ጮሆ በመናገሩ፤ ሸዋዊ የትግራይ አማራ ተብሎ የግድያ ኖህ የወረደበት።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
4. የተሓህትን ፕሮግራም አንቀበልም 1ኛ ትግራይ የኢትዮጵያ የታሪክ አስኳል የትግራይ ህዝብ በኢትዮጵያዊነቱ የሚኮራ የሚመካ ነው፤ ትግራይ የኢትዮጵያ አካል ግዛት እንጂ ቅኝ ተገዢ አይደለችም፤ አማራው ኢትዮጵያዊ፤ ትግራይም ኢትዮጵያዊ ፤ ምንም ልዩነት የለንም በማለት ጮሆ በመናገሩ።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
5. በጣሊያን ጊዜ የተዋጉና በኢትዮጵያዊነታቸው የሚኮሩ የትግራይ ልጆችን የህ.ወ.ሓ.ት.ን መርህ የሚያጨናግፉ ናቸው ብሎ በማሰብ ህ.ወ.ሓ.ት አጥፍትዋቸዋል። በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የታሪክ አዋቂዎች አዛውንት ሊቃውንት የአምስት ዓመት ከወራሪው ጣልያን የተዋጉ አርበኞች በመብራት እየፈለገ የወያኔው መሪዎች የገደልዋችው ያጠፍዋችው፤ ተገድለውም ሃብት ንብረታቸው ህ.ወ.ሓ.ት ወርሶታል። እነዚህ የሃገርና የህዝብ አለኝታዋች ሙሉ በሙሉ በትግሉ ጊዜ አጠፉዋቸው፤ ገደልዋቸው። ዛሬ ስለ ትግራይም ሆነ አጠቃላይ ስለ ነበረው ጥንታዊ ታሪክ በትግራይ ውስጥ የሚያውቅ ተፈልጎ አንድም አይገኝም።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ትግራይ በ17ቱ የህ.ወ.ሓ.ት. የትግሉ ዘመን ወድማለች። የታሪክ አዋቂ በኢትዮጵያዊነቱ የሚቆረቆር በትግሉ ዘመን ተመልሶ እንዳያንሰራራ ተመልሶ እንዳይፈጠር አድርገው በመምታት አጥፍተዉታል። በጣም የሚያስገርም ሁኔታም የተፈፀመው በወልቃይት፤ ጠለምት፤ ጠገዴ ብቻ በሰሜን ጎንደር አማራው በተመሳሳይ ሁኔታ አዛውንቶች እየተፈለጉ በስውር እየታፈኑ፣ የት እንደገቡ የማይታወቁ ማን ተያዘ ማን ተገደለ የሚለው በግልጽ ለማወቅ አስቸጋሪ ቢሆንም ብዙ የሰሜን ጎንደር አዋቂ ሽማግሌዎች የውሃ ሽታ ሆነው የቀሩ አሉ፤ ይህን ለማወቅ የሚችሉት የየአካባቢው ነዋሪዎች ናቸው። የታሪክ አዋቂ ሲጠፋም ተተኪው ትውልድ ይቸገራል። የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች ይህ እንደፖሊያሳቸው የሚጠቀሙበትም የቆየው ታሪክ ለማጥፋትና ለማክሰም ነው።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
በእነዚህ ንጹሃን የትግራይ እና የሰሜን ጎንደር ኢትዮጵያውያን የፈሰሰሰው ደም ተጠያቂው ማነው? ማነውስ ሃላፊነቱ የሚቀበለው? ምንስ አጥፍተው ነው? ወደ ትግራይ ስንመለስ፤ የተናገሩት እውነት ነው፤ ትግራይ የአማራው ቅኝ ተገዢ አይደለችም፤ ሰሜን ጎንደር፤ ወልቃይት፤ ጠገዴ ጠለምት፤ ቃፍታ (ሰቲት) ሁመራ የሰሜን ወሎን መሬቶች የትግራይ አይደሉም፤ አልነበሩም፤ ይህም ታሪክ የሚያውቀው ሃቅ ነው። የትግራይ ህዝብ ምን አጠፋ ህ.ወ.ሓ.ት የገደለው የረሸነው ያጠፋው። ማንኛውም ህዝብ አስተዋይና አርቆም ሃሳቢ እንደሆነ ሁሉ የትግራይ ህዝብም ከዚሁ ተነስቶ ነበር እውነቱን የተናገረው። ይህ ህ.ወ.ሓ.ት. የጀመረው በትግራይ ህብረተሰብ ማጥቃትና መግደል የንጹሃን ዜጎችን ደም በከንቱ የፈሰሰው ይህ ደም አሁንም በእግዚአብሔር ፊት እየጮኸ ይኖራል። መሬትና ሰማይ የፈጠረ ጌታም ፍርዱን ይሰጣል፤ የማይቀር ነው። የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች የአማራው ጎንደሬው ለምና ሰፊ መሬት በሕገ ወጥ በጉልበት ለመንጠቅ፤ የአማራው ደም የንጹሁን ኢትዮጵያውያን ዜጎች ደማቸው በትውልድ መንደራቸው እንደጎርፍ ካለምንም ጥፋትና ሃጥያት ፈሰዋል፤ ዘራቸው አጥፍተዋል፤ ህፃን፣ አራስ፣ እርጉዝ፣ ሽማግሌ፣ ወጣት፣ ተገድለዋል፣ በስዉር ጠፍተዋል። የእነዚህ ንጹሃን ኢትዮጵያዊ ዜጎችም ፈጣሪ አምላክ ፊት ደማቸው እየጮኸ ነው። ቀሪዎቹ በሂወት ያመለጡም በስደት እየተንከራተቱ ይኖራሉ።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ይህን አሳዛኝ ታሪክ ያነሳሁት የትግራይ ሕዝብ ነፃአውጪ ህ.ወ.ሓ.ት.፤ ማ.ገ.ብ.ት ተብሎ ሲፈጠር ቀጥሎም ደደቢት በርሃ ወርዶ ተ.ሓ.ህ.ት. (ተጋድሎ ሓርነት ህዝቢ ትግራይ) ከዛም ስሙን ለውጦ ህ.ወ.ሓ.ት. (ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ) ቢልም እውቅና ያልሰጠው በአንጻሩ ግን የትግራይ ሕብረተስብ ፀረ ወያኔ አምርሮ የታገለው ህዝብ ነበር። ፀረ ወያኔ ሆኖ መታገሉ ከባድ መስዋእትነት በሂወቱ በንብረቱ በሃብቱ ከፍሎ ነው ያለፈው። ሁሉ ኢትዮጵያዊም ይህን በእምነት ሁሉ ኢትዮጵያዊ ያምንበታል። ለዚሁም ተጠያቂዎቹ አረጋዊ በርሄ፣ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሃየ፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ ስዩም መስፍን፤ መለስ ዜናዊ ሲሆኑ፣ እነዚህ በዋና የንፁሃን ደም በሰሜን ጎንደር በትግራይ በኢትዮጵያውያን ንፁህ ደም በፈጸሙት ወንጀል ግንባር ቀደም ተጠያቂ ናቸው። ቀጥሎ ደግሞ፣ ስየ አብርሃ፣ አውአሎም ወልዱ አርከበ ዕቁባይ ገብሩ አስራት በዋናነት ግንባር ቀደም ይጠቀሳሉ።የኢትዮጵያ ህዝብ ክስ ሲመሰርትም መነሻው ከዚሁ ነው። የህ.ወ.ሓ.ት. ፋሺስት ድርጅት ለብዙ ዓመታት የመሩትም እነዚህ፤ ተከታትለው ወደ ሥልጣን የመጡ እንደሆነ እንመለክታለን።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ይህ የትግራይ ሕዝብ በማጥፋት የተሰማራው የህወሓት አመራር ሕዝብ በመግደሉ በተሰማራበት ወቅት በተሓህት ውስጥ የነበርው ታጋይ በዝምታ አልተመለከተውም ነበር። ከዲሞክራሲያዊ ጥያቄዎችእና በህዝቡ እየተፈጽሙት ያሉትን ግፍን ሰቆቃ ድርጅቱ ከምን ተነስቶ በምን ምክንያት ሰላማዊ ህዝብ እያሰረና እያሰቃየ ሽማግሌዎች ወጣቱን ወንድ ሴት ይፈጃል የሚሉና ተዛማች ብዙ ጥያቄዎች ተነሱ። አመራሩ በታጋዩ የተነሱ የዲሞክራሲ ጥያቄዎች ተቀብሎ በሰላም ከመፍታት ይልቅ ታጋዩን በመወንጀል፤ ይህ ፀረ ተ.ሓ.ህ.ት እንቅስቃሴ ነው በማለት ራሱ አመራሩ ለተነሱ የዲሞክራሲ ጥያቄ በመወንጀል ሕንፍሽፍሽ የሚል ስም በመስጠት፣ በበዙ ታጋዮችና ሰላማዊ ዜጋውም በሕንፍሽፍሽ ተመርዘዋል ተብሎ ሰላማዊ ዜጋው ከየቤቱ እየተለቀመ፤ ታጋዩ ከትግል ሜዳው እየተለቀመ፣ እየታፈነ፣ በቶርቸርና በእሳት እየተቃጠለ፣ በእሳት የጋለ ፍም ሳንጃ ሆድ እቃው እየገባ ተገደል፣ ጠፋ፣ የተገደሉት ሰላማዊ ዜጎችም ሙሉ ንብትና ሃብታቸው በህወሓት ተወረሰ። የብዙዎች ቤት ፈረሰ።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
የትግራይ ሕብረተሰብ ለዚሁ ሁሉ መጥፎ ጥቃት የተዳረገበት ዋና ምክንያት ከላይ የተጠቀሱ ሲሆኑ ሌላው ደግሞ ጣልያን ኢትዮጵያ በ1928 በወረረበት ጊዜ በአርበኝነት የተዋጉ ሁሉ የተሓህት-ህወሓት አመራርን በመኮነናቸው ነበር። ይህ ሲሆን አረጋዊ በርሄ፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ አባይ ፀሃየ፣ ስብሃት ነጋ፣ ስዩም መስፍን፣ መለስ ዜናዊ ያሳለፉት መመሪያ እነዚህ የትግራይ ሸዋ አማራ በአጭሩ አነጋገር ሸዋዊ ትግራዋይ በሙሉ በየትም ትግራይ መሬት የሚኖሩ በሕዝብ ግንኙነት እየተለቀሙ ታስረው ሃለዋ ወያኔ (06) በሚስጢር እንዲገቡ በማለት በሰጡት የትእዛዝ መመሪያ ሁሉም ከያሉበት ተለቅመው ሃለዋ ወያኔ እየገቡ ተገድለዋል፣ ንብረታቸውን ተወርሰዋል። ዛሬ በትግራይ እንኳንስ ከጣልያን የተዋጋ በወቅቱ ሕጻናት የነበሩትም አንድም ሰው አይገኝም፣ ተገድለዋል። ዋና የተገደሉበት ምክንያት፤</div>
<ol style="margin: 0px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<li style="list-style-type: decimal; margin: 0px 0px 0px 35px; padding: 0px;">የህ.ወ.ሓ.ት የፖለቲካ አቋም ወይም ፕሮግራም አንቀበልም ብለው በማውገዛቸው</li>
<li style="list-style-type: decimal; margin: 0px 0px 0px 35px; padding: 0px;">አማራ የትግራይ ህዝብ ደመኛ ጠላት ስለሆነ አብረን እንምታው እናጥቃው ሲባሉ፤ አማራ የትግራይ ህዝብ ጠላት አይደለም፤ ሁላችን አንድ ኢትዮጵያ ወንድማሞች ነን፤ አማራ የፈጸመብን በደል ጥቃት የለም፤ አማራው የኛ፤ እኛም የሱ ነን በማለታቸው፤</li>
<li style="list-style-type: decimal; margin: 0px 0px 0px 35px; padding: 0px;">የሰሜን ጎንደር፣ የሰሜን ወሎ መሬት የትግራይ ነው የምትሉን የትግራይ አይደለም፤ በታሪክም አልነበረም፤ የወንድሞቻችን በጉልበት የምትወሩት ያላችሁ ርስተ መሬት አንቀበልም በማለቱ</li>
<li style="list-style-type: decimal; margin: 0px 0px 0px 35px; padding: 0px;">ጣልያን ጣልያን የምትሉት በየቦታ ከጣልያን የተዋጋነው ሃገራችን ኢትዮጵያ ለመውረር በቅኝ አገዛዝ ስርአቱ ሊገዛን የመጣው፤ ወራሪ ቅኝ ገዢ ጠላት ነው፤ የሃገራችን ኢትዮጵያ አንድነትና ሏላዊነት አሳልፈን አንሰጥም በማለት ጣልያን መታነው አሸነፍነው፤ ኢትዮጵያን ነፃ አወጣን፤ በማለት ፀረ ወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት አቅዋም በመያዛቸው ነበር።</li>
</ol>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ሆኖም ይህንን መቀበል ያቃታቸውና ጸረ ኢትዮጵያ የሆኑት ከላይ በተጠቀሱ የወያኔ መሪዎች ከባድ ጥቃት በመሰንዘር ህዝቡን ጨረሱት፤ ህጻናትም ሳይቀሩ አብረው ተጨፈጨፉ። ዛሬ ታሪክ ነጋሪ በትግራይ ፈጽሞ አይገኝም። የታሪክ ፈላስፋዎች የታሪክ አዋቂዎች የሆኑት የወያኔው መስራቶችና አሁንም በሥልጣን ያሉት ደንቆሮች የወያኔ መሪዎች በሥልጣን ኮረቻ የተንጠለጠሉ ቅኝ ገዢዎች የህ.ወ.ሓ.ት. ባንዳዎች ናቸው።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ይህ በዚሁ እንዳለ፣ የትሓህት-ህወሓት መሪዎች በትግራይ ሕብረተሰብ የጀመሩትን ጥቃት እንደቀጠለ ሁኖ የወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ጠለምት፤ ሰቲት ሁመራን፤ በጉልበትና በማንአለብኝነት በካርታቸው የተካተተው በፕሮግራማቸው ውስጥ የትግራይ መሬት ነው በማለት ሰፊዉን የጎንደር ክፍለ ሃገር መሬት የሰሜን ወሎ መሬት በማካተት (ፀሃፊና አዘጋጅ አረጋዊ በርሄ ነው) ሕገ ወጥ የለም ሰፊ መሬት ወረራ ፈጽመዋል። ይህን ወረራ ለማስፈጸም የተካሄድ ቅድመ ዝግጅት በሰሜን ቤገምድር (ሰሜን ጎንደር)፤ <strong>መ</strong><strong>ኮ</strong><strong>ንን ዘለለው</strong> የተባለው ነገር ግን አካባቢውን የማያውቀው በስመ ተወላጅ በአባቱ በኩል ተወላጅ የሆነውን ታጋይና በህዝብ ግኑኝነት ክፍል የተመደበ በሱ የሚመራ ቡድን በወልቃይት፤ በጠገዴ፤ በጠለምት ጥናት እንዲያካሂድ በ1969 ዓ.ም ውስጥ ተላከ። ይህ ከሃዲ ግለሰብ ከግለሰው እስከ ቡድን ከቡድን በየበአላቱ እሁድ ወ.ዘ.ተ. በየቤተክርስትያኑ እየተንቀሳቀሰ ወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ጠለምት፤ ቃፍታ ሁመራ የትግራይ መሬት መሆኑ የሰሜን ጎንደር ህዝብም ሁሉ ትግራዋይ መሆኑ የታሪክ ሃቅነት በጎደለው ለማሳመን ባካሄደው መፍጨርጨር ሳይሳካለት በሙሉ የሰሜን ጎንደር ህዝብ በልበ ሙሉነት ወድቅ አደረገው። በግልጽም እናንተ ወራሪ የጣልያን አሽከሮች ውላጅ ናችሁ በማለት አሸማቀቃችው። ይህ የጎንደር ግዛት በማንም ያልተደፈረ በእናንተ ከሃዲዎች እይፈፈርም ብሎ ህዝቡ በግልጽ የተናገረበት ጊዜም ነው። ከዚያም ተዋርዶ ተደብዶቦ፤ ህዝቡም ወደ ማንም ቤት ዝር እንዳይሉ በማስጠንቀቅ በርሃብ ጠውልገው ወደመጡበት እንዲመለሱ አደረጋቸው። ነገር ግን መኮንን ዘለለውና ቡድኑ ሲያደርጉት የነበረው ሤራ ህዝቡ ሁሉ ቢቃወምም ትልልቅ ሰዎች የታሪክ አዋቂዎች የበሰሉ ጠንካራ ሰዎች በብዛት በሚስጢር እየመዘገቡ፤ እነዚህ ሰዎች በሂወት ካሉ ነገሩ አይሳካም በማለት በድብቅ ስማቸው ወደ ወያኔ መሪዎች በየእለቱ በማስተላለፍ ለክፉ ሞት ዳረጉዋቸው።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
የህ.ወ.ሓ.ት . መሪዎች አሁን የገጠማቸው ክሽፈትና ወርደት አጸፋውን ለመመለስ ዝግጅታቸውአሰቀመጡ። ቀደም በማለት በትግራይ ሕብረተሰብ የአፈና ዘዴ በመጠቀም አነስተኛ ሀይል አፋኝ ጉጅሌ በማደራጀት ክፉና አረመኔው ጨካኞች አፋኝ ቡድን ሶስት አቅጥጫ ተሰማራ። ይህ ጊዜም በ1969 ዓ.ም. ወደ መጨረሻው አካባቢ በሶስት አቅጣጫ በማሰማራት</div>
<ol style="margin: 0px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<li style="list-style-type: decimal; margin: 0px 0px 0px 35px; padding: 0px;">ወልቃይት፣</li>
<li style="list-style-type: decimal; margin: 0px 0px 0px 35px; padding: 0px;">ጠለምት፣</li>
<li style="list-style-type: decimal; margin: 0px 0px 0px 35px; padding: 0px;">ጠገዴ</li>
</ol>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ውስጥ ሲገቡ ጉጅሌያቸውን ይዘው በሶስቱ ቦታዎች ተሰማርተው ቀደም ሲል ከመኮነን ዘለለው የነበሩ የህዝብ ግኑኝነት መሪነት በድብቅ በዘዴ የተቃወሙት የሰሜን ጎንደር አማሮች አንድ በአንድ በተናጠል እያፈኑ ሰውን በመልቀም ያፈኑዋቸውን ሓለዋ ወያኔ በማስገባት ወንድ፣ ሴት ሳይሉ ገደሉዋቸው። ሃብት ንብረታቸውም እየተወረሰ ዝርፍያው ቀጠለ ቀስ በቀስም የጀመሩት ጥቃት እየተስፋፋ ሄደ።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ተ.ሓ.ህ.ት. ለ1ኛው ጉባኤ ይዘጋጅም ስለነበረ 1ኛ ጉባኤው የካቲት 5 ቀን 1971 ዓ.ም. ዓዲ ዳዕሮ አካባቢ ማይ አባይ በተባለው ቦታ ተካሂዶ የአመራር ቦታ ለውጥም ተደረገ። በዚሁ መሰረት እንደሚከተለው ተደላደሉ።በዚሁ ጉባኤ የተመረጡ አመራሮች አምስቱ የቆዩ ፖሊት ቢሮ (ሥራ አስፈጻሚ) እንዳሉ ተመልሰው ሥልጣናቸው ሲይዙ ቀሪዎቹም ዝርዝር የሚከተለው ነው፤</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
1ኛ. አረጋዊ በርሄ፤ ወታደራዊ አዛዥ፤ ፖሊት ቢሮ</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
2ኛ. ስብሃት ነጋ፤ የህ.ወ.ሓት ሊቀ መንበር፤ ፖሊት ቢሮ</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
3ኛ. ግደይ ዘራፅዮን፤ የህ.ወ.ሓ.ት ም/ሊቀመንበር፤ ፖሊት ቢሮ</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
4ኛ. አባይ ፀሃየ፤ የፕሮፓጋንዳ ክፍል ዋና ሃላፊ፤ ፖሊት ቢሮ</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
5ኛ. ስዩም መስፍን፤ የውጭ ጉዳይ ዋና ሃላፊ፤ ፖሊት ቢሮ</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
6ኛ. ገብሩ አስራት፤ ማዕከላዊ ኮሚቴ</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<a href="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2017/09/tplf-top-officials-e1505460595967.jpg" imageanchor="1" style="clear: right; float: right; margin-bottom: 1em; margin-left: 1em;"><img border="0" height="197" src="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2017/09/tplf-top-officials-e1505460595967.jpg" width="400" /></a>7ኛ. መለስ ዜናዊ፤ የፕሮፓጋንዳ ጽ/ቤት ም/ሃላፊ፤ ማዕከላዊ ኮሚቴ</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
8ኛ. አስፍሃ ሓጎስ፤፤ ማዕከላዊ ኮሚቴ</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
9ኛ. አርከበ (ዮሓንስ) እቁባይ፤ ማዕከላዊ ኮሚቴ</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
10ኛ. ፃድቃን ገብረተንሳይ፤ ማዕከላዊ ኮሚቴ</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
11ኛ. ስየ አብርሃ፤ ማዕከላዊ ኮሚቴ</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
12ኛ. አታክልት ቀፀላ፤ ማዕከላዊ ኮሚቴ፤ ግንቦት ወር 1971 ዓ.ም በስብሃት ነጋና በአባይ ፀሃየ እንዲሁም በመለስ ዜናዊ የተገደለ። ገዳይ ሳሞራ (መሓመድ) የኑስ በሲሞኖቭ ባልር መነጽር ጠመንጃ።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
13ኛ. ዘርአይ አስገዶም፤ ማዕከላዊ ኮሚቴ</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
14ኛ. አውዓሎም ወልዱ፤ ማዕከላዊ ኮሚቴ</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
15ኛ. ተወልደ ወ/ማርያም፤ ማዕከላዊ ኮሚቴ ብዙም ሳይቆይ በህመም ምክንያት ሱዳን ሂዶ 1975 ዓ.ም የተመለሰ ነው።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
የነዚህን ስም ዝርዝር ያስቀመጥኩበት ካለ ምክንያት አይደለም፤ በተለይ በአማራው ላይ የዘር ማፅዳት ከባድ ወንጀል በመፈጸማቸው ነው። አማራው ያፈራው ሃብት ንብረት ወ.ዘ.ተ. መርፌም ሳትቀር ለህ.ወ.ሓ.ት. ውርስ እንዲሆን ብለው የህዝብ ሃብት ንብረት የዘረፉ፤ የአማራው ህዝብ የገደሉ፤ የግድያውም ቀንደኛ ተባባሪዎችና ፈፃሚዎች የነበሩ ናቸው። እነዚህ ተሰባስበው ነው በንጹሃን ዜጎች ላይ እልቂትና ሰቆቃ እያደረሱ የመጡ፤ ከአምስቱ ፖሊት ቢሮ ስድስተኛው መለስ ዜናዊ አብረው ሊጠየቁና ሊከሰሱ የሚገባቸውናቸው። የሰሜን ጎንደር ህዝብ በአረጋዊ በርሄ የሚመራው የህ.ወ.ሓ.ት ሰራዊት ቀሪው አራቱ ፖሊት ቢሮ በየቦታው ተሰማርተው ትዕዛዝና አመራር በመስጠት ማእከላዊ ኮሚቴውም ይበልጥ በዘር ማጥፋቱ ተሰማርተው የነበሩ፤</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<a href="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2017/09/tplf-criminals.jpg" imageanchor="1" style="clear: right; float: right; margin-bottom: 1em; margin-left: 1em;"><img border="0" height="240" src="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2017/09/tplf-criminals.jpg" width="320" /></a>1. አዋአሎም ወልዱ፤ 2. ስየ አብርሃ፤ 3. መለስ ዜናዊ ከስየ አብርሃ ተደራቢ በመሆን፤ 4. ዘራይ አስገዶም፤ 5. ፃድቃን ገብረ ተንሳይ፤ 6. ገብሩ አስራት፤ 7. አርከብ እቁባይ፤ 8. አስፍሃ ሓጎስ ናቸው።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ከዚህ ቀጥሎ ያሉት ደግሞ በየተዋጊው ሰራዊት ተመድበው ትእዛዝ በመስጠት በአማራው ላይ ጥቃት በመክፈት የአማራ ዘር ማጥፋት ከባድ እርምጃ በመውሰድ፤ አማራው ሊቋቋመው በማይችል ሁኔታ ሰላማዊው ኢትዮጵያዊ ዜጋ ዘሩን ለማጥፋት ያለው የሌው ሃይላቸው አጠናክረው ግፍ የፈጸሙ የህ.ወ.ሓ.ት. መሪዎች፤ 1. አረጋዊ በርሄ፤ 2. ግደይ ዘራጽዮን፤ 3. ስብሃት ነጋ፤ 4. አባይ ጸሃየ፤ 5. ሥዩም መስፍን፤ 6. መለስ ዜናዊ፤ በሰሜን ጎንደር አማራ በትንሹ ከ1969ዓ.ም. የጀመረው ጥቃት በክፉ መልኩ ተጠናክሮ ከታህሣስ ወር 1972 ዓ. ም. የተጀመረው የአማራ ዘር ማጥፋት ዘመቻ እስከ 1977 ዓ .ም. በቀጠለበት ጊዜ በዋናነት የዘር ማጥፋት ወንጀሉን በአማራው ላይ የፈጸሙ ዋናዎቹ እነዚህ ናቸው። በዚሁ የወያኔ ጥቃት ከ2 ሚልዮን በላይ ነብሰ ጡር አራስ ህፃናት ሽማግሌዎች ወጣቶች ወንድ ሴት ልዩነት በሌለው በወያኔ እጅ ተገድለዋል። አገዳደሉም በተለያየ ስልትና ዘዴ ተፈጽሞባቸውል። ቀሪው ለስደት ተዳርጓል፤ የመጣ ይምጣ ከቤቴ ወጥቸ አልንገላታም ያለም አለ።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ከማ.ገ.ብ.ት ምስረታ እስከ የካቲት ወር 1967 ዓ.ም. የማገብት ሊቀ መንበር፤ ቀጥሎም በትግሉ ሜዳ ከየካቲት ወር 11ቀን 1967 ዓ.ም እስከ የካቲት ወር 1971 ዓ፣ም ሊቀ መንበርና ወታደራዊ አዛዥ የነበረው አረጋዊ በርሄ ነው። በምን ምክንያት ሊቀ መንበርነቱን ለቀቀ ለሚል ጥያቄ አጭር መልስ።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
አረጋዊ በርሄ፤ ስብሃት ነጋ፤ መለስ ዜናዊ ስብሰባዎች በሚካሄዱባቸው ጊዜያት ገና ወደ ጉባኤው ሳይገባ ሶስቱ እየተደበቁ የሚያደርጉት ስምምነት ነበራቸው። ድርጅቱን በሞኖፖል ለመቆጣጠር የሚያስችላቸው ሶስቱን የተስማሙበት አረጋዊ ሊቀመንበርነቱን ለስብሃት ነጋ ሊሰጠው አረጋዊ በወታደራዊ አዛዥነቱ እንዲወሰን መለስ ዜናዊ የማርክሲስት ሌኒንስት፤ በሌኒናዊ መርሀግብር የካድሬዎች አሰልጣኝና አደራጅ ኮሚሽን እንዲሆን በተስማሙት መሰረት ነበር። 1ኛው ጉባኤው ተካሂዶ 15 አመራር ተመርጠው የሥራ አስፈፃሚው ምርጫ በሚመረጥበት ጊዜ በሁሉም ተሰብሳቢ በሙሉ ድምጽ የተመረጠው አረጋዊ በርሄ የህ.ወ.ሓ.ት. ሊቀመንበር ቢመረጥም ብሞትም አልቀበልም ስብሃት ነጋ ነው ብቁ ለሱ ይስጠው ብሎ አንገቴን ለካራ አለ። የተመረጡ አመራር ስብሃት ለዚሁ ብቃት የለውም እባክህ ተቀበለን ቢሉቱም በፍፁም አልቀበልም በማለቱ ለስብሃት ነጋ ሰጡት። መለስ የተሰጠውን ቦታ አደላድሎ ያዘ፤ አረጋዊም ድሮም የራሱ የነበረው ወታደራዊ አዛዥነቱን ያዘ፤ቀሪው በየቦታው ተደላደለ። በአጭሩ ነው የገለፅኩት እንጂ ብዙ ታሪክ አለው፤ ለወደፊቱ ራሱን በቻለ ርዕስ ለህዝብ አሳውቃለሁ፤ ለአሁኑ ይህ ይበቃል። አረጋዊ በርሄ ደግሞ በታጋዩ እንዲጠላ እንዲናቅ ያደረገው ዋናው ይህ ነው። ስብሃት ነጋ ማለት አእምሮው የዞሮበት ደፍድፍ ደንቆሮ ገዳይ ጨካኝ አውሬ ነው።</div>
<div class="wp-caption alignright" id="attachment_19792" style="background-color: whitesmoke; float: right; margin: 5px 0px 20px 20px; max-width: 396px; padding: 10px; text-align: center;">
<div class="wp-caption-text" style="line-height: 16px; margin-top: 4px; padding: 5px 0px;">
<img height="180" src="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2018/02/aregawi-b-1024x576.jpg" width="320" />አረጋዊ በርሄ</div>
</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ህወሓት ከኢህአፓ ጦርነት ስለአጋጠመው ደፍሮ ሰሜን ጎንደር ሕዝብ ለማጥቃት ሁኔታውና ጊዜው አልፈቀደለትም ነበር። ከኢህአፓ ጋር በተካሄደው ጦርነት ኢህአፓ ጥቃት ደርሶበት ሰሜን ጎንደርን ለቆ በመውጣቱ ምክንያት በአረጋዊ በርሄ ወታደራዊ አዛዥ የሚመራው የወያኔ ሰራዊት ጠቅላላ ወልቃይት ጠገዴ፣ ጠለምት(‘ሰሜን ጎንደር’) በመውረር ከፍተኛ የዘር ማጥፋት ወንጀል ፈጸመ። <strong>ስብሃት ነጋ፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ አባይ ፀህየ፣ ስየ አብርሃ፣ ስዩም መስፍን</strong><strong>ና</strong> <strong>መለስ ዜናዊ</strong> የወያኔውን ሰራዊት ተከፋፍለው በመያዝ ሰሜን ጎንደር የንጹሃን ዜጎች አማራ የሬሳ ክምር መሬት አደረጉት። እነዚህ ሁሉ አመራር በቀጥታ ትእዛዝ የሚቀበሉት፣ የሚንቀሳቀሱት፣ ጥቃት የሚፈጽሙበት ቦታዎች ከአረጋዊ በርሄ በሚሰጣቸው መመሪያ ነበር። በዚሁ ጊዜም ተጨማሪ (06) ሃለዋ ወያነ በስፋት እንዲዘጋጁ አመራሩ ስላመነበት በምክትል ሊቀመንበሩ ግደይ ዘርአጽዮን ቁጥጥር ተጨማሪ ሃለዋ ወያን እንዲዘጋጅ በታዘዘው መሠረት በርሱ ኃላፊነት ተጨማሪ ከመሬት በታች 12 ሜትር ጥልቀት ትንሽ ጠባብ መስኮት 150 እስከ 200 እስረኞች የሚይዙ ሆነው እንዲሰሩ ወስኖ የነበሩትም እንዲሰፉ አድርጎ አሰራው። የሚሰሩበትም ቦታዎቹም፣ ግህነብ (ቃሌማ)፣ ፍየል ውሃ፣ ባኽላ ሳምረ፣ ሱር እስር ቤት ሲሆን፣ እንዲሰፋ የተደረጉባቸው ቦታዎች ደግሞ አዲ በቅሎ፣ ወርዒን ፃኢ ጨምሮ በስፋትና በብዛት ከመሬት በታች ሃለዋ ወያኔ ተሰሩ። በዚሁ ጊዜ አማራዎች፣ ሽማግሌ፣ ወጣት፣ ህፃን፣ ሴት፣ ወንድ ሳይለዩ ወደነዚህ ሃለዋ ወያኔ እየታፈሱ ታጋዙ። እዛው እንደገቡም በተለያዩ የጭካኔ ግፍ ተገደሉ። በጢስ እየታፈኑ የሞቱት አማራዎች ብዙ ናቸው። በጅምላ ጉድጓድ በጥይት እየተደበደበ ያለቀው አማራ ብዙ ነው። ወህኒ ቤት ውስጥ በገባው ተላላፊ በሽታ ምክንያት ኮሌራን ሌላ በሽታዎች በመተላለፍ ሕዝብ አለቀ። በቶርቸር፣ በመርዝ፣ በእሳት፣ የጋለ ብረት ወደ ሆዱ በመክተት አሰቃይተው ንጹህ ኢትዮጵያዊ ዜጋ አጠፉት። የህ.ወ.ሓ.ት መሪዎች በአማራው ያልፈጸሙት ግፍ የለም ። እነዚህ አረመኔ ግፈኞች በአንድ ህዝብ ላይ አማራ ጠላታች ብለው የዘር ማጥፋት ዘመቻ አካሂደዋል። የሞተም በሂወት ያሉትና የሞቱትም እንደነ መለስ ዜናዊ በከባድ ወንጀል</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
1. ዘር በማጥፋት፤</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
2. ሃገር ለባእዳን መሸጥ (ለሱዳን)፤</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
3. የመሬት ወረራ መፈጸም (ሰሜን ጎንደር፤ ሰሜን ወሎ) የታላቅዋን ዲሞክራቲክ ሪፓብሊክ የትግራይ መንግሥት ማስፋት የሌላው ክፍለ ሃገር ለምና ሰፊ መሬት በመንጠቅ የህዝቡ ማንነት፣ ባህሉን፣ ወጉን፣ ፀረ ዲሞክራሲ፣ ፀረ ህልውና፣ በመሆነ መልኩ የፈጸሙት ከባድ የወንጀል ተግባር ነው። አሁንም ህ.ወ.ሓ.ት በዚሁ እየቀጠለበት ሲሆን እንዲያውም በከፋ መልኩ በግማሹ ወደ ትግራይ በማካለል ግማሹ ለሱዳን መንግሥት በመሸጥ በአማራው ላይ የሚፈጸመው ግፍ አባብሶታል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
በአማራው እየተፈጸመ ያለው ግፍ አማራን ብቻ የሚመለክት አይደለም፤ የሁሉ ኢትዮጵያዊ ጥቃት ነው፤ አማራው ዘሩ ሲጠፋ አማራው ብቻ አይደለም ዘሩ የሚጠፋው ያለ ሁሉ ኢትዮጵያው ነው ዘሩ የሚጠፋ ያለው፤ የጎንደር ለምና ሰፊ መሬት ለሱዳን እየተሸጠ ያለው የጎንደር ብቻ አይደለም የሁሉ ኢትዮጵያዊ ነው፤ የኢትዮጵያ የታሪክ ቦታዎች፤ ቴዎድሮስ በመቅደላ፤ ዮሃንስ በመተማ እምቢ ለጠላት ብለው የተሰዉበት መሬት ወያኔ ለኢትዮጵያ ህዝብ ጠላት ለሆነው የሱዳን መንግሥት አሳልፎ መሸጥ ታሪካችንም አሳልፎ እየሸጠው ይገኛል።ስለሆነም የጎንደር ህዝባዊ ትግል የሁሉ ኢትዮጵያዊ ትግልም ነው። የምንታገልበትም ጊዜው አሁን ነው። ጎንደርና ትግራይ፤ ጎንደርና ሲዳሞ፤ ጎንደርና ሓረር፤ ጎንደርና አፋር፤ ጎንደርና ኦጋዴን፤ ጎንደርና ጋምቤላ፤ ወ.ዘ.ተ ምንም ልዩነት የለንም! ሁላችን የኢትዮጵያ ልጆች ነን፤ ኢትዮጵያ የሁላችን ሃገር መመክያ ናት፤ ሁላችን ሃገራችን ከወያኔው ፋሽሽት ስርአት ከሃዲ ባንዳ ተባብረን ኢትዮጵያን እናድን።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
የወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ጠለምት፤ ሌላውም አማራ በህ.ወ.ሓ.ት.፤ የወረደበት ከባድ የጥቃት ዘመቻ በዝምታ ወይም እየተገደለ አልቀረም። ተወልዶ ያደገበት የትውልድ ቦታው ስለሆነ መግቢያው መውጫው ስለሚያውቀው፤መሳሪያ ያለው ታጥቆ፤ የሌለው በቤቱ ያገኘው ጎራዴ፤ ፋስ፤ ገጀራ፤ ወ.ዘ.ተ. እናቶች ወጣት ሴቶች ወንድም ሳይቀር በርበሬ በመያዝ ወያኔን በሚገባ በሁሉ አቅማቸው ገድለዉታል፤ አጥቅተዋል። በአንዳንድ ቦታዎችም ሙሉ በሙሉ ለማለት የሚቻለው የወያኔ ሠራዊት ደምሠዉታል። የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ በታሪክ የተመሰከረለት አርበኛ ተዋጊ፤ ሙሉ ወኔ ያለው ህዝብ ከመሆኑ የተነሳ ከ1972 ዓ.ም. ጀምሮ ወያኔ ህ.ወ.ሓ.ት. እንደፈለገው ኢትዮጵያን እንዲያፈርስ ህዝብ ሊበታትን በደም ሊያቃባ እድል አልሰጠዉም። የወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ጠለምት ህዝብ ቆለኛም ደገኛም ህዝብ ነው። የመሬቱ ነፋስ የተስማማ ከመሆኑ የተነሳ ወያኔ ይህ ህዝብ በቀላሉ ሊያጠቃው ጠራርጎ ሊያባርረው አልቻለም። ሌላው አማራ ቶሎ ብሎ በመቻኮል ወደ በቀል አርምጃ አይሸጋገርም፤ ከተነሳ ግን ወደ ኋላ አይታጠፍም፤ በአማራ ጥርስ የገባ ጠላት የመጨረሻ እጣ ፈንታው ውድቀት ምርኮ ናት። አማራ ለኢትዮጵያ አንድነት ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ዋልታና ማገር፤ የሃገሩ ድንበር በመጠበቅ፤የእስልምና፤ የክርስትና ሃይማናት ባለቤት በመሆኑም እነዚህ ሁሉ ተዳምረው በኢትዮጵያዊነቱ የሚኮራ ህዝብ፤በባንዴራው አረንጓዴ፤ ብጫ፤ ቀይ የሚኮራ ህዝብ ነው። ይህ አማራ የሚባለው ህዝብ ዘሩን ካልጠፋ ኢትዮጵያ የምትባል ሃገር በአፄ ምኒሊክ የተፈጠረች ናት፤ ከተፈጠረችም ከ100 ዓመት ያነሰ ዕድሜ ያላት ታሪክ-አልባ ሃገር ናት፤ ከዓለም ካርታ ለመፋቅ ይቻላል፤ ብሎ የተነሳው የባእዳን ቅጥረኛ ባንዳ ወያኔ፤ የአማራው ወኔ ጥንካሬ ጀግንነት አይቶታል፤ አሁን እያየው ነው።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ህ.ወ.ሓ.ት አማራውን ሲያጠቃ አብሮም የተጠቃው የኢትዮጵያ ተዋህዶ ክርስትናም ነው። ቀደም ሲል በ1971 ዓም በአክሱም አውራጃ እንዳባ ጴንጦሌን (ብዙ አክሱማዊም እንዳባ ፍሬሚናጦስ) እያለ የሚጠራው ከአክሱም ከተማ የ5 ኪሎሜትር ርቀት ያለው አካባቢው የሚጠራበት ስም ደግሞ እንዳየሱስ በተባለው ቦታ ጥንታዊው ገዳም እንዳ አባ ጴንጦለን ብዙ ጥንታዊ ቅርሶች፤ ብዙ ጥንታዊ የታሪክ መጻህፍት፤ ጥንታዊ የብራና ጽሁፎች የሚገኝበት ገዳም ለመዝረፍ ህ.ወ.ሓ.ት በሰነዘረው ጥቃት ሳይሳካለት ቀርቷል። ቀጥሎም በአድዋ ውስጥ የሚገኘው እንዳሥላሴ ገዳም ላይ ቢሞክርም አልተሳካለትም። ይህ ኦፐረሽን የተመራው በአረጋዊ በርሄ ነበር፤ቀጥሎ ወያኔ የዘመተው ወደ ዋልድባ ገዳም፤ በዚሁ ገዳም ተልእኮው ሙሉ ለሙሉ ተሳካለት፤ በህ.ወ..ሓ.ቱ ሊቀ መንበር ስብሃት ነጋና በህ.ወ.ሓ.ቱ ም/ሊቀመንበር ግደይ ዘራጽዮን መሪነት ዋልድባ ገዳም ሙሉ በሙሉ ተዘርፈዋል። ብዙ ብጹዓን ባህታውያን፤ ቀሳውስት፤ አባዎች ተገድለዋል፤ ታሪካዊ ቅርሶች መጻህፍት ብራናዎች ሃብቱ ንብረቱ ወ.ዘ.ተ. ተዘርፈዋል። አሁንም ዋልድባ ገዳም እየተጠቃ ይገኛል፤ ባለታሪክ ጥንታዊ ገዳም እየወደመ ለህልፈቱም ገደል አፋፍ ነው ያለው፤ ይህ ገዳም አማራን ብቻ አይመለከትም የሁሉ ኢትዮጵያዊነው፤ <strong><a href="http://www.goolgule.com/tplf-and-the-waldiba-monastery/" style="text-decoration-line: none;">ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይና ዋልድባ ገዳም</a></strong> በሚል ርእስ ለሁሉ ኢትዮጵያዊ ስለ አሰራጨሁት የዚሁ ቅዱስ ዋልድባ ገዳም በህ.ወ.ሓ.ት. የደረሰበትና እየደረሰበት ያለው ጥቃት በዝርዝር ስለፃፍኩት ጽሁፉ በየዌብ ሳይቱ ስለሚገኝ እዛው ፈልገን እንመልከት።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
<a href="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2014/05/arkebe.jpg" imageanchor="1" style="clear: right; float: right; margin-bottom: 1em; margin-left: 1em;"><img border="0" height="240" src="http://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2014/05/arkebe.jpg" width="320" /></a>በአማራው የተፈጸመው አሰቃቂ ጥቃት ደግሞ ከሁሉ የከፋ በአርከበ እቁባይ፣ ዘርአይ አስገዶም፣ ሳሞራ የኑስ፣ ታደሰ ወረደ፣ ሃየሎም አርአያ ወዘተ የሚመሩ የገዳይ ቡድን ሕዝቡን እየሰበሰቡ በሳር ቤት ውስጥ በማስገብት ቤቱን በእሳት በማቃጠል ያለቅው ሰው ቁጥር ብዙ ነው። <strong>እኔ ራሴ ያየሁት አርከብ እቁባይ 12 ቤተሰቦችን ሰብስቦ በገዛ ቤታቸው፣ አባት፣ እናት፣ ልጆች፣ የተዳሩ ሴቶች ልጆቻቸውን ጨምሮ ከነህፃናቱ ሰብስቦ ሳር ቤት አዳራሽ አስገብቶና ቤቱን ዘግቶ እሳት ለቀቀባቸው። ሁሉም ቤተሰብ በእሳቱ አለቁ።</strong> በዚሁ በሰሜን ጎንደር የተካሄደው የዘር ማጥፋት ወንጀል በተጨማሪ ሁሉም ንብረታቸው ሃብታቸው፣ በሬ፣ ላም፣ ፍየል፣ በግ፣ አጋሰስ ጠቅላላ የቤት እንሣት ሁሉ በህወሓት ተዘርፈው ተወርሰው ተወሰደዋል።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ከ1972 ዓ.ም. ታህሳስ ወር ይህ ሁሉ ጥቃት የተጀመረው አጠቃላይ የጠገዴ፣ ጠለምት፣ ወልቃይት አማራ ዘሩ ሲጠፋ ቀሪው ደግሞ ወደ ሱዳን ተሰደደ፤ ጫካ ውስጥ ገብቶ ፀረ ወያኔ በሽምቅ ውጊያም የተሰማራ ጥቂት አልነበረም። ህዝብም ባገኘው መንገድ ሁሉ ወያኔን ከማጥቃት አላቆመም፤ የወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ጠለምት፤ ሴቶች በርበሬ በትንሽ ከረጢት ቋጥረው ከወገባቸው አትለይም በቤታቸው ውስጥም የተዘጋጀ አለ የወያኔ ታጋይ በመንገድ ሲገኙት አቁመው ለማነጋገር በመሰለ መልኩ ከያዝዋት በርበሬ ዘግነው በማውጣት አይኑ ላይ በመርጨት እዛው ሲደናበር መሣሪያ ማርከው ብዙ የወያኔ ታጋይ ገድለዋል። ወደ ቤታቸው የሚመጣ ታጋይም በርበሬ በውሃ በጥብጠው የሚበላ የሚጠጣ አቅርበው ደህና ነው ብሎ ሆዱን ሲሞላ፤ የበጠበጡት በርበሬ አይኑ ላይ በመድፋት የታጠቀው መሳሪያ ማርከው ታጋዩም በድምፅ አልባ መሳሪያ ይገድሉታ፤ በዚሁም ተገድሎ የጠፋ የወያኔ ታጋይ ብዙ ነው።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
በ1973 ዓ.ም . በተለያየ መንገድ የተገደሉ ከማስታውሳቸው ውስጥ፤ በህዝብ ግንኙነት የነበሩት፤ አለማየሁ፤ብርሃነ፤ ፍስሃ፤ ገብረተንሳይ፤ ነጋሽ፤ አማረ፤ ደስታ የተባሉና ሌሎችም ብዙ ተገድለዋል። እነዚህን የጠቀስኩት ከማውቃቸው ነው። በወያኔ ታጋይ ሰራዊትም በተለያዩ መንገዶች በህዝቡ የተገደሉም ብዙ ናቸው ከማስታውሳቸው ለመጥቀስ ገብረ ሥላሴ፤ በላይ፤ ፍጹም፤ ካህሳይ፤ ነጋሽ፤ ገረግዚሄር፤ አባይ፤ አበበ፤ ጸጋይ፤ የሚባሉ ህዝቡን ለመግደል በቡድን በቡድን ተከፋፍለው ሲንቀሳቀሱ የወልቃይት ጠገዴ ህዝብም በየጫካው ተደብቆ በማድፈጥ የገደላቸው እነዚህን አስታውሳለሁ። የወልቃይት፤ ጠገዴ፤ ጠለምት ህዝብ የሚቻለውን ሁሉ አቅሙ በፈቀደለት መጠን ህ.ወ.ሓ.ት. ወያኔን ከማጥቃት ባለው መሣሪያ እየተጠቀመ ወደ ኋላ ሳይል ጀግንነቱን ያስመሰከረና ያሳየ ህዝብ ነው። እኔ ባለኝ እምነት ይህ ኩሩ ጀግና ህዝብ ከወያኔ ፋሽሽት ቅኝ ገዢ አረመኔ ስርአት እየታገለ የመጣና ባለኝ እምነት መሠረት እውነትም የኢትዮጵያ መድህን ጠባቂም ነው። ተስፋ ሳይቆርጥ ከ1972 ዓ ም. አንስቶ እስከ ዛሬዋ ዕለት የማንነት ጥያቄው አድማሱን በማስፋት ወያኔ በማጥቃት ተሰማርቶ ይገኛል። በመሬቴ ላይ እሞታለሁ እንጂ ትወልድ ቦታየ አለቀም ያለው በ1969 ግንቦት ወር የተጀመረው ጥቃት እስከ ዛሬ ድረስ ቀጥሏል። ይህ የሰሜን ጎንደር ህዝብ በወያኔ እየሞተ እየተገደለ ማንነቴን አሳልፌ አልሰጥም ብሎ 42 ዓመት ሙሉ ከተሓህት-ህወሓት ዘራችንም ብታጠፉ አንድ ሰወ እስኪቀር ማንነታችን አሳልፈን አንሰጥም እኛ አማራ ጎንደሬዎች እንጂ ትግሬዎች አይደለንም፤ ብሎ እስከ አሁን ድረስ በማንነቱ የማይደራደር ማንነቱን አሳልፎ የማይሰጥ ኩሩ ኢትዮጵያዊ አማራ ነው።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
በምሬት እየታገለ የሚገኝ የጎንደሩ ህዝብ ከቀን ወደ ቀን ጥንካሬው በግልጽ እየታየ ነው። በየትም ቦታ የተገኘ አማራ እንዲገደል ህ.ወ.ሓ.ት. ያወጀው በ1969 ሲሆን፣ በትግራይ ውስጥ የሚኖሩ አማራዎችም ከየቦታው እየተለቀሙ እንዲገደሉ አምስቱ የተሓህት አመራሮች፣ አረጋዊ በርሄ፣ ሊቀመንበር፣ ግደይ ዘርአጽዮን፣ የድርጅቱ ም/ሊቀመንበር፣ አባይ ፀሃየ፣ ስዩም መስፍን፣ ስብሃት ነጋ አድርገዋል። ትግራይ የትግራዮች እንጂ የሌላው መጤ ቦታ አይደለችም፣ ስለሆነም ማንም የትግራይ ተወላጅ ያልሆነ ከትግራይ ይውጣ ተብሎ እንዲታወጅም ያደረጉት እነዚሁ ናቸው። በአዋጁ መሰረትም አማራው በነቂስ እየተፈለገ ተገደለ፣ እነዚህ ይህ ውሳኔ የተላለፈባቸው ከትግራይ ተጋብተው ልጆች ወልደው ያሳደጉም ናቸው፤ ያመለጠውም ሂወቱና ቤተሰቦቹን ይዞ የሸሸም ብዙ ነው። ይህ የተመለከተና ያየ የትግራይ ህዝብም ወያኔን አወገዘ፤ መሬታቸው ነው አይወጡም፤ ይህ የኢትዮጵያ ቦታ ነው፤ ማነው ወጪ ማነውስ አስወጪ፤ ከፈለጋቹህ ወያኔዎች ውጡ እያለ ከአማራው ወንድሙ ጋር ቆመ። በየቦታው ፀረ ወያኔ እንቅስቃሴ ተነሳ፤ ወያኔም በየቦታው ይህ እንቅስቃሴ የታዩባቸው ቦታዎችን በህዝብ ግንኙነት ክፍል በኩል በፀረ ወያኔ ፖሊሲ ተንቀሳቅሰዋል ያላቸውን የትግራይ ሰዎች አንድ በአንድ እየለቀመ ሓለዋ ወያነ በማስገባት ደብዛቸው አጠፋቸው፤ በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ተሓህት-ህወሓት ይህን ሁሉ በሰሜን ጎንደር አማራው ኅብረተሰብ ላይ ይህን ሁሉ ግፍ ሲፈጽም እጃቸውን ለወያኔ የሰጡ የኢህአፓ አባላት የነበሩ፤ ታምራት ላይኔ፣ አዲሱ ለገሰ፣ ተፈራ ዋልዋ፣ በረከት ስምኦን፣ ዮሴፍ ረታ፣ መለሰ ጥላሁን፣ ህላዊ ዮሴፍ፣ ታደሰ ካሳ፣ ሙሉአለም አበበ፣ ወዘተ ይገኙበታል። ከወያኔ ህወሓት ጋር በመተባባር የሰሜን ጎንደር፣ ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት ወዘተ የቀድሞዎቹ ኢ.ህ.ዴ.ን. በህ.ወ.ሓ.ት. አምሳልና ቡራኬ ተጠፍጥፈው የተሰሩ ተላላኪዎች የዛሬዎቹ ብአዴን አካባቢው ለብዙ ጊዜ የቆዩበትና የሚመሩበት ስለነበሩ ሕዝቡን በነቂስ ስለሚያውቁት አካባቢ እየመሩ ለወያኔ ጥቃትና የዘር ማጥፋት ወንጀልም ተባባሪ ሆነዋል። ወያኔን እየመሩ የሰሜን ጎንደሬውን አማራ አጥቅተውታል። ስለሆነም በማራው ላይ የደረሰው የዘር ማጥፋት ወንጀል በተለያዩ የጥቃት ዘዴዎች በህወሓት የተፈጸመው እነዚህ የብአዴን አመራር ከህወሓት አመራር ጋር አብረው ተጠያቂ ናቸው።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
በሕዝብ ላይ ለሚደርሰው ጥቃት፤ ሃብት ንብረት ዘረፋ፤ ለሚደርሰው ማንገላታት ሰላማዊ ዜጋው ተይዞ ለእስር የሚዳረገው በሕዝብ ግንኙነት በኩል ጥናትና ሪፖርት ነው። መኮንን ዘለለው ለመጀመሪያ ጊዜ በህ.ወ.ሓ.ት በኩል ወደ ወልቃይት ጠገዴ የተሰማራው እሱ ነበር፤ የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ግን አልተቀበለውም። ሪፖርቱ ሲያስተላልፍም ሁሉም ፀረ ተ.ሓ.ህ.ት./ህ.ወ.ሓ.ት ናቸው በማለት ከነስም ዝርዝራቸው ለወያኔ ፖሊት ቢሮ (ከ100 በላይ ሰዎች ሴቶችም አሉበት) ቀስ በቀስ አንድ በአንድ ብስራት አማረ በሚመራው አፋኝ ቡድን ተለቅመው በቡምበትና ሱር ሓለዋ ወያነ ገብተው ጠፍተዋል፤ ንብረታቸውም ሙሉ በሙሉ በወያኔ ተዘርፎ ባዶ ቤት ቀርቶዋል። የዚህ ሁሉ ተጠያቂው ስንመለከት፣ መኮንን ዘለለው ነው። በዚህም ላይ የሚጠየቁ መረሳ ረዳ፣ አጽብሃ ሃይለማሪያም፣ ፀጋይ በርሄ (ሃለቃ)፣ መኮንን የአዲረመጽ ሕዝብ ግንኙነት፣ አርአያ ወርቅነህ፣ ቅዱሳን ነጋ፣ ቀሺ ታደሰ፣ መሃሪ ግብርገርግስ፤ ሃለቃ ታደለ አለምሰገድ፤ መብራት በየነ፤ ወዘተ ናቸው። እነዚህም አንኳር ተጠያቂ ናቸው።</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
ገብረመድህን አርአያ፣ ፐርዝ፣ አውስትራሊያ</div>
<div style="line-height: 18px; margin-top: 4px; padding: 0px 0px 15px; text-align: justify;">
በሚቀጥለው ዕትም “የህወሓት ፕሮግራም” በሚል ርዕስ ሃተታ እናቀርባለን።<a href="http://www.goolgule.com/tplfs-objective-of-destroying-ethiopia/" target="_blank">http://www.goolgule.com/tplfs-objective-of-destroying-ethiopia/</a></div>
</div>
</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-65787076535961549372018-02-05T11:35:00.000-08:002018-02-05T11:35:28.872-08:00የንግድ ስርአቱና “የቲም ለማ” ግኝት!<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ኤርሚያስ ለገሰ</em></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">#1: </strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መግቢያ</strong></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
በአቶ ለማ መገርሳ ሊቀመንበርነት የሚመራው የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ በአዳማ የ10 ቀን ዝግ ስብሰባ ለማድረግ ተቀምጧል። በዚህ ስብሰባ ላይ የተለያዩ ድርጅታዊ፣ ክልላዊ፣ አገራዊ እና አለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን በመመርመር ታላላቅ ውሳኔዎችንና የቀጣይ አቅጣጫዎችን እንደሚያስቀምጥ በግምገማው ቃል አቀባይ ተነግሯል። የድርጅቱ ስራ አስፈፃሚ እና የግምገማው ቃል አቀባይ አቶ ሐብታሙ ሐ/ ሚካኤል ለየኦሮሞ ብዙሃን መገናኛ ( OBN) በሰጠው መረጃ መሰረት ግምገማው በአሁን ሰአት ወደ አቢይ አጀንዳዎች ተሸጋግሯል።</div>
<div class="wp-caption alignright" id="attachment_18281" style="background: rgb(241, 241, 241); border: 0px none; float: right; font-family: nyala; font-size: 18px; line-height: 18px; list-style: none; margin: 0px 0px 20px 20px; max-width: 310px; outline: none; padding: 4px; text-align: center;">
<a href="https://ecadforum.com/Amharic/archives/18280/lemma-megersa/" rel="attachment wp-att-18281" style="border: 0px none; color: #0f06ba; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px; text-decoration-line: none; transition: all 0.2s ease-in-out;"><img alt="Lemma Megersa, with his team, was in Bahir Dar." class="size-medium wp-image-18281" height="160" sizes="(max-width: 300px) 100vw, 300px" src="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2017/11/Lemma-Megersa-300x160.jpg?x46032" srcset="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2017/11/Lemma-Megersa-300x160.jpg 300w, https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2017/11/Lemma-Megersa.jpg 620w" style="border: 0px none; height: auto; list-style: none; margin: 0px; max-width: 100%; outline: none; padding: 0px;" width="300" /></a><div class="wp-caption-text" style="border: 0px none; color: #888888; font-size: 17px; list-style: none; margin: 5px; outline: none; padding: 0px;">
Lemma Megersa</div>
</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ከእነዚህ አቢይ አጀንዳዎች መካከል በአገሪቱ የንግድ ስርአት ላይ ውይይት እየተደረገ መሆኑ ቃል አቀባዩ ተናግሯል። የንግድ እንቅስቃሴው ስልጣንን ተገን በማድረግ በተወሰኑ አካላት ተይዞ የኦሮሚያን ኢኮኖሚ እያቀጨጨው መሆኑ በጥልቀት መታየቱን ገልጿል። ስልጣንን መሰረት በማድረግ በተወሰኑ አካላት የሚለውን በቀይ ብዕር አስምሩልኝና ወደ ቃል አቀባዩ መግለጫ እንመለስ። አቶ ሐብታሙ ለOBN በሰጠው መግለጫ ላይ፣</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">” </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የአገሪቱ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የንግድ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ስርአት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከአድሎነት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የፀዳ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ነወይ? </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የንግድ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ስርአቱ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በፍትሐዊነት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሁሉንም </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የህብረተሰብ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ክፍል </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እኩል </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ተጠቃሚ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እያደረገ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ነወይ? </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ወይንስ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የተወሰኑ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አካላት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ብቻ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከድንብር </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ድንበር </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እየተዘዋወሩ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እንደፈለጉት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ተጠቃሚ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የሚሆኑበት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ነው? </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በሚለው </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ጉዳይ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ላይ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በጥልቀት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ተወያይተናል። </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በአገሪቱ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የንግድ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ስርአቱ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ውስጥ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ትልልቅ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ችግሮች </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አሉ። </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ስልጣንን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ተገን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በማድረግ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በተወሰኑ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አካላት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ተይዞ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ያለ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የኮንትሮባንድ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እንቅስቃሴ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አራማጆች </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ላይ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ታግለን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መስመር </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እንዲይዙ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በማድረግ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ረገድ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ምን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እንደምንመስል </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ፈትሸናል” </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ብሏል።</em></div>
<a name='more'></a><br />
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">#2: </strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የፕሮፐጋንዳው</strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"> ( </strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ህዝብ</strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ግንኙነቱ</strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">) </strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አካሄድ</strong></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
በንግድ ስርአቱ ላይ የለማ ቡድን ያደረገውን አበረታች ምርመራ ግኝቶቹ ላይ ከማተኮሬ በፊት በስብሰባው አካሄድና መረጃው ለህዝብ እየቀረበበት ባለበት ሁኔታ ላይ ጥቂት ልበል። እዚህ ላይ የህዝብ ግንኙነቱን በቅድሚያ መመልከት የፈለግኩት በደባል አሳብነት ላቀርብ የምፈልገው ነጥብ ስላለኝ ነው።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
የመጀመሪያው ለማ መገርሳ የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ(ሰአኮ) ያደረገውን ግምገማ አስመልክቶ አራቱ ሊቀመናብርት በቤተመንግስት መግለጫ ሲሰጡ አንድ ነገር ተናግሮ ነበር። በግምገማው ላይ ያደረጉትን ተጋድሎ የኢትዬጲያ ህዝብ እንዲያውቀው በቀጥታ ስርጭት ቢተላለፍ ፍላጐቱ እንደነበር አሳውቋል። በወቅቱ የህውሓት ማእከላዊነት ጥሶ በድፍረት ፍላጐቱን በይፋ መናገሩን አድንቀንለት ነበር። ግን ደግሞ የትግራይ ነፃ አውጪ እና ሁለቱ ጠፍጥፎ የፈጠራቸው ድርጅቶች( ብአዴን እና ደኢህዴግ) ሳይስማሙ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚያስቸግር አስተያየት ተሰጥቷል። ሆኖም ግን ቲም ለማ በራሱ የስልጣን እርከን ውስጥ የሚካሄደውን የኦህዴድ ሰአኮ ግምገማ በቀጥታ እንዲሰራጭ ማድረግ እንደሚገባው ምክረ ሃሳብ ሰጥተን ነበር። ይሄን ማድረግ ግልፀኝነትን ከማሳየቱም በላይ በኦህዴድ ውስጥ ማን ከኢትዬጲያ ህዝብ ጐን እንደቆመ፣ ማን የትግራይ ነፃ አውጪን ተልእኮ ለማሳካት እንደሚንቀሳቀስ በቀጥታ መገንዘብ እንደሚያስችል ተገልጦ ነበር። ከዚህ አንፃር Team ለማ ከባድ ነጥብ ጥሏል። እናም ለምን የቀድሞ ፍላጒቱን በራሱ የስልጣን ማእቀፍ ውስጥ ማድረግ እንዳልቻለ በይፋ መናገር ይኖርበታል። አለበለዚያ አንቺው ታመጭው፣ አንቺው ታሮጭው ይመስልበታል። በባላንጣዎቹም መዘባበቻ ይሆናል።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
በሌላ በኩል የግምገማውን ሂደትና የተደረሰበትን ድምዳሜ እየተገለፀበት ያለው አግባብ ከላይ የተነሳውን ጥፋት ባይጋርደውም ከፍተኛ ለውጥ የታየበት ነው። የተመረጠው የህዝብ ግንኙነት ስልት የለማ ቡድን ሀላፊነት እና ሚናውን በተሻለ ሁኔታ አሳይቶበታል። አንደኛ: መግለጫው እየተሰጠ ያለው በፓሊት ቢሮ ደረጃ ባለ ከፍተኛ ካድሬ ነው። ስጠረጥር ወጣት ሐብታሙ ሐ/ሚካኤል የቲም ለማ አካል ይመስላል። ርግጥ ወጣቱ የስብሰባውን ውጤቶች በሚፈለገው መልኩ ገለጥለጥ አድርጐ ማሳየት ባይችልም ለፍተሻ በቂ ተደርጐ ሊወሰድ የሚችል ነው። ሁለተኛ: መረጃዎቹ ለህዝብ እየተሰራጩ ያሉት በኦሮሞ ብዙሃን መገናኛ ( OBN) አማካኝነት ነው። ይሄ አካሄድ ከዚህ በፊት በሞኖፓሊ ያለ ከልካይ መረጃ ሲቀበሉና ሲያሰራጩ የነበሩትን የትግራይ ነፃ አውጪ የሚዲያ ተቋማትንና የፌስቡክ ስኳዶች ( የኮካ አለቆች) ያስደነገጠ ነው።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
የትግራይ ነፃ አውጪ የፌስቡክ አለቆች ድንጋጤያቸው እንዳይታወቅና አጀንዳ ለማስቀየር አርበኞች ግንቦት ሰባት እና ኢሳት ላይ ባለ በሌለ ሐይላቸው ርብርብ አደረጉ። አርበኞች ግንቦት ሰባትና ኢሳት ካልተዳከሙ በስተቀር የሚፈልጉት የዘር ( DNA) አደረጃጀት እና “የጐሳ ሚዲያ” መመስረት የማይችሉ የሚመስላቸው ( ጭንቅላት፣ ልብ፣ አንጀት፣ምላስ፣ እጅና እግራቸውን ያሰርናቸው ይመስል!) ከትግራይ ነፃ አውጪ የፌስ ቡክ ሰራዊት አለቆች ጋር ተጃምለው ገቡ።ለኮካ አለቆች በጊዜያዊነት አጀንዳ ለማስቀየስ ጥሩ አጋጣሚ ፈጠረላቸው። ጊዜያዊ የሆነበት ምክንያት ቲም ለማ በአዳማ የደገሰላቸው ድግስ አይደለም እነሱን እናት ድርጅታቸውን የሚያስደነግጥ ስለሆነ ነው።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
እየተሰማ እንዳለው ከሆነ አዳማ የከተመው የለማ ቡድን ጠንካራ ውሳኔዎችን እየወሰነ ነው። የትግራይ ነፃ አውጪ ተላላኪ ከሆኑት ውስጥ እንደ አስቴር ማሞ፣ ሶፊያን አህመድ አይነቶቹን አባረዋል። ሶፊያን ከተዘፈቀበት ሌብነት እና ዝርፊያ አንፃር እግረ ሙቅ እንዲጠልቅለት አስተያየት እንደቀረበም ተሰምቷል። በሌላ በኩል የበረከት ስምኦን እና የትግራይ ነፃ አውጪ ጠላት የሆነው ሱሊማን ደደፎ ወደ ስራ አስፈፃሚ መጥቷል።( ሱሊማን የኢትዬጲያን መርከቦች አስመልክቶ ለውጭ ጉዳይ የፃፈው እና ሾልኮ የወጣው ደብዳቤ የትግራይ ነፃ አውጭን የአለም አቀፍ ፍርድ ቤት የሚያስከስሰው እንደሆነ ልብ ይሏል።) የለማ ቡድን OBN በተመለከተም ከማንም ጣልቃ ገብነት ነፃ ሆኖ እንዲሰራ ከሚዲያው ጐን እንደሚቆም ቃል ገብቷል። ይሄ ዘርአይ አስግዶምን ለመሰሉ የትነግ የሚዲያ ጠርናፊዎች፣ የትነግ የሚዲያ ተቋማትና የፌስቡክ የኮካ አለቆች ሌላ ራስ ምታት ነው።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
እርግጥም የለማ ቡድን የገባውን ቃል ኪዳን የሚጠብቅ ከሆነ የኦሮሞ ህዝብ የኢትዬጲያን አንድነት ለማስጠበቅ የከፈለውን ጀግንነት ሳይበረዝ በሚዲያው እንሰማለን። የኦሮሞ ህዝብ በአገር ፍቅር ስሜት የውጭ ጠላቶቹን ለመመከት ያደረገውን ተጋድሎ በዘጋቢ ፊልም ቀርቦልን እንማርበታለን። OBN ነፃነቱን ከተጐናፀፈ የጐብልስን “ኩሸት ሲደጋገም እውነት ይሆናል” ስራ የያዙትን የትነግ የሚዲያ ተቋማትና የፌስቡክ የኮካ አለቆች እርቃናቸውን ያስቀራል። በምትኩም እውነትን በመግለጥ ብሔራዊ ስሜትን ለመቅረፅና ኢትዬጲያዊ ወኔን ለማነሳሳት እድል ያገኛል።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">#3:</strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የንግድ</strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ስርአቱና</strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"> “</strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የ</strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">Team </strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ለማ</strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">” </strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ግኝት</strong></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
የለማ ቡድን ስብሰባውን ሲጨርስ በሚያወጣው መግለጫ አብነቶች እያስቀመጠ የትግራይ ነፃ አውጪ ለ26 አመት የተገበረውን ወንጀለኛ የንግድ ስርአት እንደሚነግረን ይጠበቃል። ለጊዜው በቃል አቀባዩ ሐብታሙ ሐ/ሚካኤል አማካኝነት የአገሪቱ የንግድ ስርአት አድሎአዊ እንደሆነ አስረግጦ ነግሮናል። ሐብታሙ የንግድ ስርአቱ ፍትሐዊ እንዳልሆነ አረጋግጧል።በተለይም ስልጣንን ተገን በማድረግ የንግድ ተቋማት በተወሰኑ አካላት ቁጥጥር ስር እንደዋሉ ማረጋገጫ ሰጥቷል። እነዚህ ለጊዜው ስማቸው ያልተጠቀሰ የተወሰኑ አካላት ስልጣናቸውን ተጠቅመው ከድንበር ድንበር እየተዘዋወሩ እንደሚፈልጉ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ሁኔታ እንደፈጠሩ ግኝቱን አቅርቧል።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
እውነቱን ለመናገር አዳማ የመሸገው የለማ ቡድን የአገሪቱን የንግድ ስርአት አስመልክቶ አስተውሎት ያነገበ ድምዳሜ አስቀምጧል። ይህ ነገ ከነገ ወዲያ በዳኝነት መንበር ላይ የሚመዘን አስተውሎት የተፈፀሙ ወንጀሎችን ለማመን ያለውን ፍላጐት የሚፈነጥቅ ነው። ከቃል አቀባዩ አንደበት እንደተረዳሁት የለማ ቡድን የግምገማ ውጤት የንግዱ ስርአት ብሎም የኢኮኖሚ ግንባታው “ወዴት እየሔደ ነው?” ከሚለው ባሻገር ” ወዴት መሄድ አለበት?” ወደሚለው በቁጭት የመምራት ፍላጐት የታየበት ነው። በአጠቃላይ መልኩ የአገሪቱን የንግድ ስርአት አስመልክቶ የተገለጠው የትግራይ ነፃ አውጪ የገነባው የንግድ ስርአት ምን ያህል አደገኛና ለራሱ የንግድ ድርጅቶች ብቻ ጠቀሜታ የሚሰጥ መሆኑን ነው።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">#4:</strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የለማ</strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ቡድን</strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ቀጣይ</strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሐላፊነት</strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እና</strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሚና</strong></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
አዳማ የተቀመጠው የለማ ቡድን የሕዝብ ቁጣና የመደፈር እልህ ያቃጠለው ሁሉ በአንድነት መነሳቱን አይቶ ጠንካራ ውሳኔ አሳርፏል። በዚህም የተነሳ የትግራይ ነፃ አውጪ ከመጀመሪያው የአገዛዝ ቀን አንስቶ በሌላው ህዝብ ኪሳራ ና ማቆርቆዝ ላይ ተመስርቶ የሃብት ማማ ላይ መውጣቱን በእንድምታ (Deductive logic) ነግረውናል። መቼም ባለፋት 26 አመታት ስልጣኑን ተጠቅሞ ከጫፍ እስከ ጫፍ ንግዱን ያጧጧፈው ማን እንደሆነ መናገሩ ለቀባሪው ማርዳት ይሆናል።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ተደጋግሞ እንደታየው የኢትዬጲያ ህዝብ ወደ አደባባይ በመውጣት በጥይት የተጨፈጨፈው ኢፍትሐዊነት የፈጠረበትን የሕሊና ህመም መቋቋም ባለመቻሉ ነው። ለለማ ቡድንም ቢሆን ቅፅበታዊ አቀጣጣይ ሆኖ ለሕዝቡ ተቆርቋሪ እንዲሆንና በሕዝቡ ህሊና ውስጥ ስሙ እንዲገዝፍ የሆነው ህዝባዊ ማዕበሉ የማይቆም በመሆኑ ነው። እርግጡን እንነጋገር ከተባለ ይህ የለማ ቡድን ውሳኔ በቀላሉ የሚታይ አይደለም። በተቃራኒው የግል ሀብትንና ስልጣንን የማደላደል ቢሆን ኖሮ ወደ ፍፅም አፓርታይድነት እየተቀየረ ላለው ዘረኛ አገዛዝ መስሎ መደር ይቻል ነበር። በኢትዬጲያውያን ሕይወትና ንብረት ላይ የሚደርሰውን ብዝበዛ አይቶ እንዳላየ አሊያም የድርሻን መዝረፍ ይቻል ነበር። በመሆኑም Team ለማ የትግራይ ነፃ አውጪ የበላይነት፣ የትግራይ ዋነኛ ተጠቃሚነት፣ አግአዚነት ላይ የጋረጠውን አደጋ ወደ ተግባር እንዲመነዝረው መጐትጐት ( “መደገፍ”) ያስፈልጋል።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ለለማ ቡድን ከሚሰጠው ድጋፍ ውስጥ የቅድሚ ቅድሚያ የሚሆነው እና ለድርድር የማይቀርበው ጉዳይ ሕዝባዊ እምቢተኝነትን አጠናክሮ መቀጠል ይሆናል። የቡድኑ አባላት አፍ አውጥተው አይናገሩት እንጂ ህዝባዊ እምቢተኝነት ነዳጃቸው ነው። ነዳጅ የሌለው መኪና ሹፌሩ ምንም ያህል ጐበዝ ቢሆን መሄድ እንደማይችለው ሁሉ ህዝባዊ እምቢተኝነት ከሌለ የለማ ቡድን ይሸነፋል። ከጨዋታ ውጭ ይሆናል።በምትኩም በኦህዴድ ውስጥ የተገዥነት ስነ ልቦና ያላቸው ሰዎች በትግራይ ነፃ አውጪ ጉልበት ወደ ፊት ይመጣሉ። በሂደትም የስርአት ለውጥ ፈላጊዎቹ በሚደርስባቸው አካላዊና መንፈሳዊ ዛቻ ሰማይ እንደ አክንባሎ የተደፋባቸው ሊመስላቸው ይችላል። እናም በአጭር ጊዜ ውስጥ ባልተጠበቀ ሁኔታ የትግራይ ነፃ አውጪን ይቅርታ ጠይቀው ከኢትዬጲያ ሕዝብ ጋር ለመጨረሻ ጊዜ ሊቆራረጡ ይችላሉ። በመሆኑም ቲም ለማ ወዳልተፈለገ አቅጣጫ እንዳይሄድ ዋስትናው አንድ እና አንድ ብቻ ነው። ያልተቋረጠ ህዝባዊ እምቢተኝነት! ያልተቋረጠ ህዝባዊ ማእበል!</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ለለማ ቡድን ከሚሰጠው ድጋፍ ውስጥ ቀጣይ የሚሆነው ውሳኔያቸውን ሊያጠናክር የሚችል ሀሳቦችን መስጠት ይሆናል። ለምሳሌ ያህል ከኢፍትሐዊ የንግድ ስርአቱ ጋር በተያያዘ ቡድኑ በአጭር ቀናት ውስጥ መስራት ያለበት ነገር አለ። ከእነዚህ መካከል፣</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em 30px;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">*</strong> የትግራይ ነፃ አውጪ ንብረት የሆነው ጉና ትሬዲንግ በኦሮሚያ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ ሙሉ ለሙሉ ማገድ። ሁሉም እንደሚያውቀው የኤፈርት ንብረት የሆነው ጉና የኢትዬጲያን የቡና ኤክስፓርት 33 በመቶ ይዟል። ይሄንን ቡና የሚወስደው ከኦሮሚያ እና ደቡብ ነው። ከዚህ በተጨማሪ ጉና በኦሮሚያ ከተሞች በራሱ እና በአብዛኛው በግለሰብ ስም የያዛቸው የጅምላ እና የችርቻሮ ሱቆች አሉት። እነዚህን በአጭር ጊዜ አጣርቶ መዝጋት።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em 30px;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">*</strong> በኦሮሚያ ቅርንጫፍ የከፈቱትን የኤፈርት ንብረት የሆኑትን የፋይናንስ እና የኢንሹራንስ ተቋማት በአስቸኳይ መዝጋት። ከእነዚህ ውስጥ ወጋገን ባንክ፣ አንበሳ ባንክ፣ አፍሪካ ኢንሹራንስ…ወዘተ ቅድሚያ ሊሰጣቸው ይገባል።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em 30px;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">* </strong>በኦሮሚያ የተገነቡና ንብረትነታቸው የኤፈርት የሆኑትን ፋብሪካዎች የግንባታ፣ የማሽን ግዢና ተመሳሳይ ክፍያዎችን በመክፈል በጊዜያዊነት መውረስ። በሂደት በግልፅ ጨረታ ወደ ግል ማዞር።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em 30px;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">*</strong>በኦሮሚያ ዋና ዋና ከተሞች የሚገኙ የትግራይ ልማት ማህበር ፅህፈት ቤቶች እና ንብረቶችን መውረስ። የማህበሩ ንብረት የሆነው ሰላም ባስ በኦሮሚያ እንዳይንቀሳቀስ ማገድ።የትግራይ ልማት ማህበር አባላትን ስም ዝርዝር በመያዝ የትግራይ ነፃ አውጪ አባል መሆን እና አለመሆናቸውን ማጣራት። የነፃ አውጪ አባልነታቸውን በፍቃደኝነት መሰረዝ ፍቃደኛ ካልሆኑ ነፃ ወዳወጡበት አካባቢ እንዲሄዱ በሰላም መሸኘት።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em 30px;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">*</strong> የህውሓት አባላት ሆነው በኦሮሚያ ንግድና ኢንቨስትመንት ያላቸውን ግለሰቦች ቢዝነስ እና ኢንቨስትመንታቸውን እንዲያቋርጡ ማድረግ። የትግራይ ተወላጅ ሳይሆኑ ከህውሓት/ ኢህአዴግ የንግድ ተቋማት እና ባለስልጣኖች ጋር በመሻረክ ቢዝነስ የከፈቱትን በሙሉ ማገድ።</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-1909530664531651792018-02-02T06:44:00.001-08:002018-02-02T06:44:14.814-08:00“የህውሓት የአዲስ አበባ ልዩ ዞን!” እና የ HD አዲሱ ዲስኩር <div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በኤርሚያስ ለገሰ</em></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መንደርደሪያ</em></strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አንድ</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">:- 1998 </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ዓ</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">•</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ም</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">•</em></strong></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<a href="https://ecadforum.com/Amharic/archives/17174/ermias-legesse2-2/" rel="attachment wp-att-17175" style="border: 0px none; color: #0f06ba; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px; text-decoration-line: none; transition: all 0.2s ease-in-out;"><img alt="Ermias Legesse, author and ESAT TV and Radio contributor" class="aligncenter size-full wp-image-17175" height="330" sizes="(max-width: 620px) 100vw, 620px" src="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2016/10/Ermias-Legesse2.jpg?x99262" srcset="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2016/10/Ermias-Legesse2.jpg 620w, https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2016/10/Ermias-Legesse2-300x160.jpg 300w" style="border: 1px solid rgb(203, 205, 204); clear: both; display: block; height: auto; list-style: none; margin: 2px auto; max-width: 100%; outline: none; padding: 4px;" width="620" /></a></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
የመለስ ትሩፋት ባለቤት አልባ ከተማ መፅሐፍ ” የአዲስአባ ፓለቲካ ምህዳር” በሚል ርእስ ስር በገፅ 252 ላይ የሚከተለውን ትለናለች፣</div>
<a name='more'></a><br />
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em 30px;">
<em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">“</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የ</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">1998 </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ዓ</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">•</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ም</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">• </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የአዲሳአባ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የፓለቲካ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ስራ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አቅጣጫ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ለማስቀመጥ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከአቶ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መለስ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ጋር</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በነበረን</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ስብሰባ</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"> ” </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከእንግዲህ</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በአዲስአባ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ምድር</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የብሔር</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አደረጃጀት</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መከተል</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ራስን</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ለተደጋጋሚ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሽንፈት</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ማዘጋጀት</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ነው።</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የመዲናይቱ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ነዋሪ</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በተለይም</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ወጣቱ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በብሔር</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አደረጃጀት</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መታቀፍ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አይፈልግም</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">” </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በማለት</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አቶ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መለስ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ተናግሮ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ነበር።</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ይህን</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የአቶ</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መለስ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ውሳኔ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ተከትሎ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከህውሓት</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ውጭ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ያሉት</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የብሔር</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ድርጅቶች</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እጃቸውን</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከአዲስአባ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ላይ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አነሱ።</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ህውሓቶች</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አስቀድመው</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ራሳቸውን</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከኢህአዴግ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ቢሮ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ስላገለሉ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ውሳኔውን</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አልቀበልም</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በማለት</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በመዲናይቱ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የትግራይ</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አደረጃጀት</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እስከማቋቋም</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የሚደርስ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የትእቢት</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እርምጃ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ወሰዱ።</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ለድርድር</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ቢጠሩም</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ፍቃደኛ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሳይሆኑ</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ቀሩ።ሌሎቹንም</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የእነሱን</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እርምጃ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እንዲከተሉ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከጀርባ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አደራጁ።</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እሰጣ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ገባው</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሳይጠናቀቅ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የኢህአዴግ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ጉባኤ</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በአዋሳ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ተጠራ።</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">“</em></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መንደርደሪያ</em></strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሁለት</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">:- 2010 </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ዓ</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">•</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ም</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">•</em></strong></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
“የኢህአዴግ ሊቀመንበሩ!” አቶ ሐይለማርያም ደሳለኝ(HD) በትላንትናው እለት ( ከ12 አመት በኃላ) የአዲስ አበባ ኢህአዴግ ሊግ ኮንፍረንስ ላይ ተገኘ። “ተወዳጁ ኢቲቪ” ( EBC) በዜና ዝግጅቱ ከሐይለማርያም ንግግር ውስጥ የሚከተለውን ቀንጭቦ አሰማን፣</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em 30px;">
<em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">“</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የአዲስ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አበባ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ኢህአዴግ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሊግ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አደረጃጀት</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ኢህአዴግ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከግንባር</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ወደ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አንድ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ፓርቲ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ለሚያደርገው</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሽግግር</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ምሳሌ</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ይሆናል።</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሕብረ</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">–</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ብሔራዊ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሆናችሁ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መደራጀታችሁ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ለተለያየ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ጥገኛ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አስተሳሰቦች</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"> ( </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ትምክህት፣</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ጠባብነት</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">) </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ያለው</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ቦታ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ምን</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እንደሚመስል</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ኢህአዴግ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከእናንተ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ትምህርት</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ይወስዳል።</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">“</em></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መንደርደሪያ</em></strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሶስት</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">:- 2010 </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ዓ</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">•</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ም</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">•</em></strong></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
በዛሬው እለት “ተወዳጁ ኢቲቪ”(EBC) እና የኤፈርት ንብረት የሆነው ፋና ብሮድካስቲንግ ለተመሳሳይ ኩነት የተለያየ መሪ ርዕስ ያለው ዜና ይዘው ወጡ። ኢቲቪ <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">” </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የህውሓት</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የአዲስ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አበባ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ልዩ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ዞን</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከፍተኛ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አመራሮች</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የዘጠኝ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ቀናት</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ኮንፍረንስ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በማካሄድ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ባለ</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"> 7 </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ነጥብ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የአቋም</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መግለጫ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በማውጣት</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ስብሰባው</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ተጠናቀቀ</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">“</em> በማለት ዘገበ። የህውሓት ንብረት የሆነው ሬዲዬ ፋና ዜና ደግሞ <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">” </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከትግራይ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ክልል</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ውጭ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የሚገኙ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የህውሓት</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከፍተኛ</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አመራሮች</em> <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ኮንፍረንስ</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ተጠናቀቀ</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">“</em> የሚል ነበር።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መንደርደሪያ</strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አራት</strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">:- </strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መሪ</strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ጥያቄዎች</strong></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><u style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ጥያቄ</u></em></strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><u style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አንድ</u></em></strong> : – በሶስቱ መንደርደሪያዎች መካከል ያለው ተዛምዶ እና ልዩነት ምንድነው?</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><u style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ጥያቄ</u></em></strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><u style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሁለት</u></em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><u style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">:</u></em></strong> – ህውሓት ከ12 አመታት በኃላ በ HD ውስጥ አድሮ ለምን ስለ ኢህአዴግ ወደ አንድ ፓርቲ መምጣት ዶሰኮረ? ኢህአዴግ አንድ ወጥ ፓርቲ መሆን ይችላል ወይ? ወደ አንድ ፓርቲ ለመምጣት ምን የተቀየረ መዋቅራዊ ለውጥ አለ? የብሔር አደረጃጀት እንዲጠፋ ህውሓት ይፈልጋል ወይ? ህውሓት ድርጅታዊ ፕሮግራሙ ( ህገ መንግስቱ) እንዲቀየር ይፈልጋል ወይ?</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><u style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ጥያቄ</u></em></strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><u style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሶስት</u></em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><u style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">:</u></em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">–</em></strong> በኢቲቪ እና ሬዲዬ ፋና የዜና ዘገባ ላይ ምን ልዩነት አለ? ህውሓት እንዴት የአዲስ አበባ ልዩ ዞን አደረጃጀት ኖረው? መቼ የተፈጠረ አደረጃጀት ነው? ህውሓት ትግራይን የምመራ ድርጅት ነኝ ብሎ ሲያበቃ እንዴት ከትግራይ ክልል ውጭ አደረጃጀት ሊኖረው ቻለ? የህውሓት የአዲስ አበባ ልዩ ዞን አመራሮች እና አባላት ያነገቡት አላማ እና ተልእኮ ምንድነው?</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em; text-align: center;">
***</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መንደርደሪያ</strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አምስት</strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">:- </strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ታሪካዊ</strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ዳራ</strong></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እስከ</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"> 1995 </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አ</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">•</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ም</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">• </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ድረስ</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">:-</em></strong></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
እስከ 1995 አም ድረስ አዲስ አበባ ስትተዳደር የነበረው ካዛንችስ በሚገኘው የኢህአዴግ ጥምር ኮሚቴ ነበር። ስያሜው የኢህአዴግ ጥምር ኮሚቴ ይባል እንጂ የበላይ አመራሮቹ በሙሉ የህውሓት ታጋዬች ነበሩ።ሊቀመንበር ተስፋማርያም ፣ የፕሮፐጋንዳ ጠርናፊ ፍስሀ ዘሪሁን መአሲ ( አሁንም የህውሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ) ፣ የድርጅት ጉዳይ ጠርናፊ ፈትለወርቅ ሞንጆሪኖ(አሁንም የህውሓት ሰአኮ) ነበሩ። በዚህን ሰአት ኢህአዴግ የነበረው አባል ከ500 የማይበልጥ ሲሆን 350 ያህሉ የትግራይ ተወላጆች( ህውሓት) ነበሩ። በወቅቱ ህውሓት የአዲሳአባን ህዝብ በጥላቻና ጥርጣሬ የሚመለከተው በመሆኑ የነዋሪ መዋቅር ለመመልመል አልቻለም። በህዝቡ ውስጥም ” የኢህዴግ አባል ነኝ” ብሎ መናገር የሚያሳፍር ከመሆኑም በላይ ” የትግሬ ቂጥ ላሽ!” የሚል ስያሜ በማህበረሰቡ ስለሚሰጥ በጣም ያሸማቅቅ ነበር።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
በሌላ በኩል የፌዴራል መስሪያቤቶች የኢህአዴግ ጥምር ኮሚቴ አደረጃጀት በሚል ሁሉንም የኢህዴግ አባላት( ህውሓት፣ ኦህዴድ፣ ብአዴን፣ ደኢህዴን) የሚጠረንፍ መዋቅር ነበር። የዚህ አደረጃጀት የበላይ አመራሮቹ በሙሉ የህውሓት ታጋዬች ነበሩ። የደህንነት ሀላፊዎቹ ኢሳያስ እና ወልደስላሴ፣ የዋልታው ነጋሽ እና ዘርአይ አስግዶም የፌዴራሉ ፕሮፐጋንደሰ እና ድረረጅት ጠርናፊዎች ነበሩ።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
የተለያዩ አደረጃጀቶች ቢሆኑም የአዲስ አበባው ጥምር ኮሚቴ (ተስፋማርያም፣ ሞንጆሪኖ ፣መአሲ) እና የፌዴራሉ ጥምር ኮሚቴ ( ወልደስላሴ፣ ኢሳያስ፣ ነጋሽ፣ ዘርአይ) በወር አንድ ጊዜ ካዛንችስ በመገናኘት አፈፃፀማቸውን እና የቀጣይ ወራት ተግባሮችን ይገመግማሉ። ከተግባሮቻቸው ቁልፍ ስራ ተደርጐ የሚወሰደው የስለላ መዋቅር መዘርጋትና መገምገም ነበር። ከዚህ በተጨማሪ የፓለቲካ መሪዎችና የመንግስት ባለስልጣን መሾምና ማባረር ትልቁ ስራቸው ነበር።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከ</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">1995 </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ዓ</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">•</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ም</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">• </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እስከ</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"> 1998 </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ዓ</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">•</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ም</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">• </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ድረስ</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">:-</em></strong></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
እነዚህ ሶስት አመታት አርከበ እቁባይ ከድርጅቱም በላይ ገዝፎ የታየበት ነበር። በዚህ ምክንያት አባላቱን በሙሉ እንዲባረሩ አድርጐ የመንግስት፣ የድርጅት እና የፕሮፐጋንዳውን ሰራ ብቻውን ተያይዞት ነበር። በከተማው የኦህዴድ እና ብአዴን አባላት በመባረራቸው ባይ ዲፎልት ድርጅቶቹ አልነበሩም። ኦህዴድ እና ደኢህዴንን አቶ መለስ ” የዝንብ ጥርቅሞች!” በማለት በድርጅቱ ሪፓርት ላይ ማካተቱ ለአርከበ እቁባይ ጠራርጐ ለመጣል ምቹ ሁኔታ ፈጥሮለት ነበር። ስለዚህም የቀሩት የህውሓት አባላት ብቻ ነበሩ። በዚህ ምክንያት ” የህውሓት የአዲስ አበባ ዞን” የሚል አደረጃጀት ተፈጠረ። የዚህ አደረጃጀት ዋነኛ አላማ በአዲስ አበባ የትግራይ (ህውሓት) የበላይነትን በፅኑ መሰረት ላይ መገንባት ነበር። ( ዝርዝሩን ለመመልከት የመለስ ትሩፋት: ባለቤት አልባ ከተማ መፅሐፍን ይገርቡ!)</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
የፌዴራል ጥምር ኮሚቴው በነበረበት የቀጠለ ሲሆን ግንኙነቱ ” ከህውሓት የአዲስ አበባ ዞን” ጋር ብቻ ነበር። አመራሮቹም ከዋልታው ነጋሽ ውጭ ሁሉም በቦታቸው ነበሩ። በተለይ ግን የደህንነት ሐላፊዎቹ ኢሳያስ እና ወልደስላሴ የጐላ ሚና ነበራቸው።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከ</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">1998 </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ዓ</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">•</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ም</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">• </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በኃላ</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">:-</em></strong></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
የምርጫ 97 ውጤት ሁሉንም ነገር ቀያየረው። በአዲሳአባ ውስጥ የትግራይ ተወላጅ እጅግ በጣም የተጠላበት ሰአት ስለነበር ፊትለፊት የሚወጣ ማግኘት ከባድ ሆነ። አቶ መለስ የአዲሳአባ ህውሓት መዋቅር አመራሮቹን በሙሉ ሰብስቦ ” የአዲሳአባ ህዝብ ጠልቷችኃል” በማለት ወደ ትግራይ እና ህውሓት በሀይል የተቆጣጠራቸው ቦታዎች ሰደዳቸው። ለምሳሌ የዛሬው የአዲሳባ ስራ አስኪያጅ( የድሪባ ኩማ አለቃ) የሁመራ ዋና አስተዳዳሪ ሆኖ ተላከ። ቦሌን ወደ መቀሌ የቀየረው የቦሌ ከንቲባ የነበረው ሀይለስላሴ የአንዱ የትግራይ ዞን አስተዳዳሪ ሆነ።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ከወራቶች በኃላ 30ሺህ የሚጠጉ የአዲሳአባ ወጣትና ሴት ሊግ አባላት በሞሉት መጠይቅ ላይ የብሔር አደረጃጀት አንፈልግም የሚል ከ90 በመቶ በላይ ምላሽ ሰጡ። አቶ መለስም የብሔር አደረጃጀትን ይዞ ሙጭጭ ማለት እንደማያዋጣ ተረድቶ ይሁን አሊያም ለጊዜያዊ ስልት ” የብሔር ፓለቲካ በአዲስ አበባ አያዋጣም” የሚል ውሳኔ ወሰነ። የከተማዋን ህዝብ በነዋሪ፣ ወጣት እና ሴት ፎረምና ሊግ እንዲደራጁ መመሪያ አስተላለፈ። የአዲስ አበባ ኢህአዴግ ፅህፈት ቤት አመራሮችም ትልቁ ስራ እነዚህን ማህበራዊ አደረጃጀቶች ማጠናከር እንደሆነ ጥብቅ ትእዛዝ ተሰጠን። ኦህዴድ፣ ብአዴን እና ደኢህዴግ ከአዲሳአባ ላይ እጃቸውን አነሱ። የቀረው ህውሓት ነበር።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ህውሓት የአዲሳአባ ዞን አደረጃጀቱን እንዲያፈርስ በተደጋጋሚ ቢጠየቅም አሻፈረኝ አለ። በረከት፣ ታደሰ ጥንቅሹን ጨምሮ የአዲሳአባ የኢህአዴግ ኮሚቴ የህውሓትን እንቢተኝነት ለአቶ መለስ ነገርነው። እየሳቀ ” ለቴዎድሮስ እና ጐበዛይ በረከት ንገራቸው” ብሎ አጀንዳውን ዘጋው። በወቅቱ ቴዎድሮስ እና ጐበዛይ የህውሓት የፕሮፐጋንዳና ድርጅት ሀላፊዎች ነበሩ። በረከት በተሰጠው ትእዛዝ መሰረት ቢጠራቸውም ” አንተ ስለ ህውሓት አደረጃጀት ምን አገባህ?” በማለት አፍንጫህን ላስ አሉት።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያለ ህውሓት ባደረገው የአደረጃጀት ለውጥ በሰባት ዞኖች መደራጀቱን ይፋ አደረገ። ስድስቱ በትግራይ የሚገኙ መሆናቸውን ተናገረ። የተቀረው <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">” </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የህውሓት</em></strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የአዲስ</em></strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አበባ</em></strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ልዩ</em></strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ዞን</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">“</em></strong> የሚል ስያሜ እንደተሰጠው ተበሰረ።የዚህ የአዲሳባ ህውሃት ልዩ ዞን አባላት… የአዲሳአባ መዋቅር፣ የፌዴራል መስሪያቤት የትግራይ ተወላጆች፣ የልማት ድርጅት የትግራይ ተወላጆች፣በሚዲያ ተቋማት የሚሰሩ የትግራይ ተወላጆች፣ በኢምግሬሽን፣ ደህንነት፣ ፌዴራል ፓሊስ የሚሰሩ የትግራይ ተወላጆች፣ በኤፈርት የሚሰሩ የትግራይ ተወላጆች፣ ከትግራይ ውጭ የሚኖሩ የትግራይ ባለሀብቶች፣ ከትግራይ ውጭ ባሉ ክልሎች የሚሰሩ የትግራይ ተወላጆች፣ በኤንባሲ እና ቆንስላ የሚሰሩ የትግራይ ተወላጆችን የሚያቅፍ መዋቅር እንደሆነ ተገለፀ። “ልዩ” የምትለው ቅፅል የተጨመረችው በዚህ ምክንያት መሆኑ ተነገረ።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em; text-align: center;">
***</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">“</strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የህውሓት</strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የአዲስ</strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አበባ</strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ልዩ</strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ዞን</strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">” </strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ተልእኮ</strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ምንድነው</strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">?</strong></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አንደኛ</strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">:-</strong> ለህውሓት ከፍተኛ ገንዘብ ማሰባሰብ። እንደሚታወቀው ህውሓት ባለስልጠናት፣ አመራሮችና ካድሬዎች ከወር ገቢያቸው ውስጥ 10 በመቶ ድርጅታዊ መዋጮ የመክፈል ግዴታ አለባቸው። ስለዚህም ከላይ የተጠቀሱት የህውሓት አባላት በልዩ ዞኑ አማካኝነት በሚሊዬን የሚቆጠር ገንዘብ ለህውሃት ገቢ ያደርጋሉ። ለምሳሌ በአንድ ወቅት የደህንነት ምክትል ሀላፊ የነበረው ኢሳያስ ወ/ ጊዬርጊስ ለህውሓት በወር 3ሺህ ብር ይከፍል ነበር። ኢሳያስ ከደህንነት ሹመቱ በተጨማሪ በአቶ መለስ ምደባ የተባበሩት መንግስታት ፀጥታው ም/ቤት ኢትዬጲያን ይወክል ነበር።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሁለተኛ</strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">:</strong>– የህውሓት የአዲሳአባ ልዩ ዞን ከትግራይ ክልል ውጭ በሌሎች ክልሎች፣ አዲስ አበባ፣ ድሬደዋ፣ ፌዴራል ተቋማት፣ ኤምባሲ እና ቆንስላ ፅህፈት ቤቶች ውስጥ የስውር መንግስትነት ሚና አለው። በጀት ይደለድላሉ። ባለስልጣናት ሊሆኑ የሚችሉ ይመለምላሉ። ለህውሓት አይመችም የሚሉትን ካድሬ እና ባለስልጣን ያባርራሉ። በሚኖሩበት አካባቢ ለትግራይ ልማት ማህበር ገቢ ይሰበስባሉ።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሶስተኛ</strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">:-</strong> የስለላ መዋቅርም በሁሉም ቦታዎች ይዘረጋሉ። በሁሉም የኢትዬጲያ አካባቢ ለስርአቱ ተገዥ ያልሆኑትን በመሰለል ለፀጥታው መስሪያቤት ያቀብላሉ። የተለያዩ ባለሀብቶችን፣ የሐይማኖት ተቋማት አባቶችን፣ አገር አቀፍ እና አለም አቀፍ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ይሰልላሉ። ሀብትና ፍቃዳቸውን እስከማስነጠቅ የሚያደርስ መረጃ ያቀብላሉ።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አራተኛ</strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">:</strong>– ከትግራይ ክልል ውጪ ኤፈርት እና የትግራይ ተወላጆች ሊሰማሩባቸው የሚገቡ አዋጭ የኢኮኖሚ ሴክተሮችን ይለያሉ። ኤፈርትና ህውሓት ለሚሰሩት ህገወጥ ተግባራት ከለላ ይሰጣሉ። ሚስጥር ይደብቃሉ። ኤፈርትን የሚግደረደሩ ባለሀብቶች ኢኮኖሚክ ኢንስትሩመንት ( ታክስ በመጫን፣ ጉምሩክ በማጉላላት፣ መሬት በመከልከል) ከጨዋታ ውጭ እንዲሆኑ ያደርጋሉ።</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-33632237308010055282018-01-28T08:52:00.004-08:002018-01-28T08:52:51.382-08:00ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ ጆሮና አይኔ ወሎ ላይ ተተክሎ ሰንብቷል<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መሳይ መኮንን</em></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ከወልዲያው ጭፍጨፋ፡ ከቆቦዎች አይበገሬነት እስከመርሳዎች ጀግንነት፡ ክስተቶችን እዚያው አጠገባቸው እንዳለ ሆኜ ነበር ስከታተል የቆየሁት። ስሜቴ ከወዲህ ውዲያ ሲላጋ፡ ቅጭም ሲል፡ በሀዘን ሲመታ፡ ደግሞም በጀግንነታቸው ልቤ ሲሞቅ፡ ወዲያኑም በሚደርስባቸው የግፍ በትር ውስጤ ሲደማ፡ በሞታቸው ኩምትር ስልበወርቃማ መስዋዕትነታቸው ስጽናና፡ እንዲሁ ላይ ታች ስል ሰነበትኩ። አሁንም ከዚያው ነኝ። ከወልዲያ ምድር፡ ከቆቦዎች መንደር፡ ከሮቢት ሰፈር፡ ከሀራ ገበያ፡ ከጎቢዬዎች ሀገር፡ ከመርሳዎች መንደር፡፡ የማያውቁት ሀገር አይናፍቅም የሚለው አባባል አይገባኝም። ወሎን ባላውቀውም ይናፍቀኛል።</div>
<div class="wp-caption alignright" id="attachment_18388" style="background: rgb(241, 241, 241); border: 0px none; float: right; font-family: nyala; font-size: 18px; line-height: 18px; list-style: none; margin: 0px 0px 20px 20px; max-width: 160px; outline: none; padding: 4px; text-align: center;">
<a href="https://ecadforum.com/Amharic/archives/18387/mesay-mekonnen-articles/" rel="attachment wp-att-18388" style="border: 0px none; color: #0f06ba; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px; text-decoration-line: none; transition: all 0.2s ease-in-out;"><img alt="Mesay Mekonnen, ESAT journalist" class="size-thumbnail wp-image-18388" height="267" src="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2017/12/Mesay-Mekonnen-Articles-150x100.jpg?x35320" style="border: 0px none; height: auto; list-style: none; margin: 0px; max-width: 100%; outline: none; padding: 0px;" width="400" /></a><div class="wp-caption-text" style="border: 0px none; color: #888888; font-size: 17px; list-style: none; margin: 5px; outline: none; padding: 0px;">
መሳይ መኮንን (የኢሳት ጋዜጠኛ)</div>
</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ፖለቲካው ግሏል። ሙቀቱ ጨምሯል። ህወሀቶች መቀሌ ላይ የቀመሙትን መርዝ በእጅ አዙር ሊረጩት ተሰማርተዋል። የዘርዓይ አስገዶም ያልተጠና ዲስኩር የህወሀቶችን ቀጣይ አካሄድ እርቃኑን ያጋለጠው ሆኗል። አንጻራዊ የህዝብ ድምጽ በማሰማት ቀና ማለት የጀመሩትን የኦሮሞ ብሮድካስት ኔትወርክና የአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅትን ወደ ቀድሞ አገልጋይነታቸውና በቀቀንነታቸው ለመመለስ በህወሀት አማካኝነት የተዘጋጀውና እነዘርዓይ የተላኩበት ዘመቻ ድባቅ ሲመታ ለመታዘብ ችለናል። አፋቸው ተሎጉሞ የከረሙት ወይም ከህወሀት አገልጋይነት መላቀቅ አቅቷቸው ህዝባቸውን ሲያሳዝኑ የምናውቃቸው እነንጉሱ ጥላሁን እንኳን አፍ አውጥተው፡ ወኔ አግኝተው፡ ድፍረት ተላብሰው ”በዘረኝነት ትዕቢት የተወጠረውን” ዘርዓይን እሳት እንዳየ ላስቲክ ኩምሽሽ ሲያደርጉት አይተናል።</div>
<a name='more'></a><br />
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ህወሀት በደም ነፍስ የቀረ አገዛዝ ሆኗል። በደህንነቱና መከላከያው ብቻ እየተነፈሰ ነው።የእነዚህ ሁለት ተቋማትም ነገር የጊዜ ጉዳይ እንጂ የህወሀት ማጥፊያ መድሃኒት መሆናቸው አይቀርም። ህወሀት የበተናቸውን መሰብሰብ አቅቶታል። ያሰለጠናቸውን ማዘዝ ተስኖታል። ባሪዎቹ እየፈነገሉት ነው። ቀኝ እጄ የሚላቸው እየካዱት ነው። ህዝቡ አልታዘዝ ብሏል። ለሚያወጣቸው ህጎች ጀርባውን እየሰጠ። ማስፈራራያውን ከቁብም የሚቆጥር የለም። ግድያ የማያስበረግገው፡ ጭፍጨፋ የማያስፈራው፡ የአጋዚ ጭካኔ፡ የቅልብ ፌደራል ዱላ፡ የመከላከያ አፈሙዝ የማያስደነግጠው፡ ልበ ሙሉ፡ ሞትን የማይፈራ፡ ደረቱን ለጥይት የሚሰጥ ደፋር ትውልድ እዚህም እዚያም ተፈጥሯል።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
በቅርቡ የብሄራዊ ደህንነት ምክር ቤት ”በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ሰልፍ የተከለከለ ነው” ብሎ ካስጠነቀቀ ወዲህ ሁሉን ነገር የተቆጣጠረ መስሎት ነበር። አዋጁን ያነበበው ሲራጅ ፈርጌሳ ቃለመጠይቁ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተላልፎ ሳያልቅ በማግስቱ የህዝብ እምቢተኝነት በየቦታው ተቀስቅሷል። ወልቂጤም ተቀላቀለች። አርባምንጭ ተነሳች። ወሎ አቀጣጠለች። ከእንግዲህ የሚመልሰው አይኖርም። ነጻነት የሸሸተውን ህዝብ ማን ሊያቆመው?</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ትላንት ማታ እዚህ አሜሪካ የህወሀቱ አምባሳደር ካሳ ተክለብርሃን ለ400 የህወሀት ደጋፊዎች በተዘጋጀ የቴሌ ኮንፈረንስ ላይ ተገኝቶ ያደረገው የመግቢያ ንግግር ላይ እንዲህ አለ ”ይህቺን ሀገር ያቆምናት በመርህ ነው። ምንም ማዕበል ቢመጣ፡ ወጀቡ ቢያሰፈራ ለጊዜው እንጂ ያቆምነውን መሰረት የሚንድ አይሆንም። ” ቴሌ ኮንፈረሱ በሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የተቃውሞ ሱናሚ ተቋርጦ፡ ካሳ ተክለብርሃንም ስልኩን ዘግቶ ጠፋ። ኢትዮጵያውያኑ ” ብሶት የወለደው ጀግናው የኢትዮጵያ ልጅ ለዘመናት ወያኔ ሲጠቀምበት የነበረውን ቴሌኮንፍረንስ ተቆጣጥሮታል። ጉንበት…..” እያሉ በመድረኩ ቆዩበት።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ካሳ ተክለብርሃን ይህቺን ሀገር ያቆምናት በመርህ ነው አለና አረፈው። መቼም ይሉኝታ ሲከዳ፡ ሞራል ሲላሽቅ የማትደፍረው ነገር የለም። የፈጣሪን ዕይን መጠንቆልም አይቀርም። ድንቁርና ከእውቀት ጋር ቦታ በተቀያየሩበት የህወሀት ሰፈር ”መርህ” የሚለው ቃል አፋቸው ላይ ሲመላለስ መስማት ያሳፍራል። በደንቆሮዎች ስብስብ፡ በመሃይማን ጉባዔ፡ እውቀት በነጠፈችባቸው፡ ማስተዋል በራቃቸው፡ ፍጹም ደካማ በሆኑ ሰዎች እጅ ላይ የወደቀችውን ሀገር ”በመርህ ያቆምናት” ሲል አጠገቡ ብኖር መቼም በአንደበት የሚገለጽ መልስ አይኖረኝም። ጆሮ ግንዱን በጥፊ ከማላጋት ውጪ። ሰውዬው ሲበዛ ደፋር ነው። የመሃይም ደፋር። መርሳ ላይ 13 ኢትዮጵያውያን በተገደሉበት ዕለት፡ ትኩስ ሀዘን ውስጣችንን እየበላው፡ በመሳሪያ ጉልበት አፍኖ የሚመራትን ሀገር ”በመርህ” እያለ ሲያላዝን እንደመስማት የሚያም ምንም ነገር የለም። ለማንኛውም ምሱን ቀምሶ ተባሯል።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ወደ ተነሳሁበት ነጥቤ ልግባ። ህወሀት በብአዴን ውስጥ ከተከላቸዎች ሙጃና አረሞች አንዱ ካሳ ተክለብርሃን ነው። እሱና መሰሎቹ ብአዴን ውስጥ ተሰግስገው የአማራው ህዝብ በህወሀት የባርነት ቀንበር ውስጥ እንዲቆይ እስከመቃብራቸው ድረስ ቃል ገብተው እየሰሩ ነው። እነዚህ አገአልጋዮችና በጎ ፈቃደኛ ባሪያዎች ዋናው ተልዕኳቸው የህወሀትን ህልውና ማስጠበቅ ነው። ሌላው ተግባራቸው ትርፍ ነው። በአለቆቻቸው የሚመዘኑት፡ ሹመትና ስልጣን የሚደረብላቸው የህወሀትን ጥቅም ለማስጠበቅ የሄዱበት ርቀት ተለክቶና ተሰልቶ ነው። እነዚህ ሰዎች በሆድና ህሊና መሀል ልዩነቱን አያውቁም። ሲበዛ ፈሪዎች ናቸው። አደርባይነት ውስጣቸው ቤት ሰርቷል። ህወሀት ከሳቀች የሚስቁ፡ ካዘነች ብሶባቸው ለቅሶ የሚቀመጡ፡ የራሳችን የሚሉት የሌላቸው፡ እንደሰው ተፈጥረው፡ ባሪያ ሆነው አድገው፡ በአሽከርነት ጎልምሰው፡ በሎሌነት አርጅተው ሰው መሆን አቅቶአቸው ወደ መቃብራቸው የሚያመሩ፡ የትውልድ ማፈሪያ፡ የሀገር ሸክም ናቸው። ከእነዚህ አንዱ የሆነው ካሳ ነው እንግዲህ የአትላንቲክን ውቅያኖስ ተሻግሮ መጥቶ ”በመርህ ያቆምናት ሀገር” የሚለን።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ህወሀት አሽከሮቿን አዝምታለች። ስብሰባ አቋርጠው እሳት እንዲያጠፉላት በየቦታው አሰማርታለች። የወሎው ነገር አላማራትም። የእንጀራ ገመዷ ሊበጠስ ነው። ከመሃል ሀገር ጋር ያለው ግንኙነት በሰማይ ካልሆነ በየብስ የሚቻል ከማይሆንበት ደረጃ ላይ መድረሱ አይቀርም። የወሎው መስመር ለትግራይ የህይወትና ሞት ጉዳይ ነው። ቀለብ የሚጓጓዝበት፡ ሸቀጥ የሚመላለስበት፡ ትግራይን ቀጥ አድርጎ የያዘው መስመር ነው። የህይወት መስመር። ከየትኛውም አከባቢ በላይ የወሎው ተቃውሞ ለህወሀት አደገኛ እንደሆነ ይታወቃል። በአንድ ሳምንት ተቃውሞ በተፈጠረ የመንገድ መዘጋት ትግራይ ውስጥ የተፈጠረውን ጭንቀት ሰምተናል። የዋጋ መጨመር፡ የምርቶች ከገበያ መጥፋት ተከስቶ ተጋሩዎች በስጋትና ፍርሃት ተውጠው እንደከረሙ የሚያሳዩ መረጃዎች ወጥተዋል። ህወሀቶች የአፋርን መስመር በአማራጭነት ለመጠቀም እያሰቡ ነው።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
በግፍ ገንዘብ የተቋቋመው የሰላም ባስ ድርጅት የውሎውን መስመር ዘግቶ በአፋር በኩል ከ300 ኪሎ ሜትር በላይ ተጨማሪ መንገድ መጓዝ ግድ ሆኖበታል። ተሳፋሪዎች ከ500 ብር በላይ ተጨማሪ እንዲከፍሉ ተገደዋል። አፋሮች እጃቸውን እያሟሹ ነው። እኛ ጋ ያለው ስቃይና በደል ቢብስ እንጂ የሚያንስ አይደለም ያሉት የሱልጣን ዓሊሚራህ ልጆች እርምጃ ሊወስዱ እንደሚችሉ ከወዲሁ እያስጠነቀቁ ናቸው። ነገሮች እየከፉ መምጣታቸው አይቀርም። ወሎ ከተነሳ አይመለስም የሚለው ብሂል መሬት ረግጧል። ወልዲያ ጀምሮ፡ ቆቦን አዳርሶ፡ ከመርሳ የገባው እምቢተኝነት ደሴን ኮምቦልቻን ሀይቅን ዳር ዳር እያለ ነው። ህወሀቶች ብርክ ይዟቸዋል። ወሎ አምርሮባቸዋል። የየብሱ ነገር እያከተመ። የሰማዩን ይሞክሩ ይሆን?</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ለህወሀት መጪው ጊዜ አስፈሪ ነው። ወሎ የተነሳው ተቃውሞ የመቃብር ጉዞውን እንደሚያፋጥነው ተረድቶታል። ሞቱን በጣም ቅርብ አድርጎበታል። እናም አሽከሮቹን አሰበ። ባሪዎቹን ጠራ። ብአዴኖችን። እሳቱን እንዲያጠፉለት ሲል የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባቸው እንዲያቋርጡ አድርጓቸዋል። ከዚህ በላይ የሚያሳስበው ምንም ነገር የለም። ለጉባዔው ሌላ ጊዜ ይደረስበታል። ውሎን ዝም ማሰኘት፡ የወቅቱ አንገብጋቢ ጉዳይ ነው። ከዚህ የሚበልጥ አጀንዳ ለጊዜው የለም። ብአዴኖች ጉዛቸውን ጠቅልለው ወደየዞኑ ተሰማርተዋል። የህወሀትን ነፍስ ሊያድኑ። የአማራውን ህዝብ ስቃይ ሊያራዝሙ።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
እንግዲህ ይለይለታል። ከዚህ በኋላ የብአዴን ሰዎችን ልመናም ይሁን ሽንገላ የሚሰማ ጆሮ የለም። እነዚህ ሰዎች ስለአማራ ብለው ስብሰባቸውን አላቋረጡም። ስለአማራው ብለው አልተሯሯጡም። አማራው ከቤንሻንጉል፡ ጉራፈርዳ፡ ከየቦታው ሲፈቀልና ሲገደል እንኳን ስብሰባቸውን ሊያቋርጡ፡ ለሀዘኔታ የምትሆን አንዲትም ቃል አልወጣቻቸውም። ባለፉት 27 ዓመታት የአማራው ህዝብ የአማራው ህዝብ በህወሀቶች የበትቻኝነት ስሜት በፈጠረው ቂም በቀል ሲቀጠቀጥ ዱላ ሲያቀብሉ የነበሩት እነዚህ የብአዴን አመራሮች ናቸው። የአማራው ህዝብ ክፉ ጠላት እንጂ ወዳጅ አይደሉም። አማራው እነዚህ የትውልድ ኩሶችን ሊገላገላቸው ይገባል። ጀርባው ላይ እንደአልቅት ተጣብቀው፡ ለህወሀት የባርነት አገዛዝ መንገድ የሚጠርጉትን የብ አዴን ጉዶች ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ሊፋታቸው ጊዜው አሁን ነው።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
አዎን! የህወሀትን የእሳት አደጋ ብርጌድ ማሳፈር ይገባል። የተሰማራውን የነፍስ አድን ቡድን አንገት አስደፍቶ መመለስ ግድ ይላል። ስብሰባቸውን መታደም፡ በግፍ በተገደሉት ላይ መሳለቅ ነው። ከብአዴኖች ጋር በአንድ አዳራሽ በአንድ ጉባዔ መቀመጥ፡ የእነዚያን መስዋዕትነት ማራከስ ነው። የአማራው ህዝብ አሳፍሮ ሊመልሳቸው ይገባል። የህወሀት አለቆቹን ለማስደስት የአማራውን ህዝብ በአደባባይ የዘለፈው አቶ አለምነው መኮንን ከቆቦ እጅና እግሩን ይዞ እንዳይወጣ ማድረግ ከሞራል አንጻር የሚያስጠይቅ አይደለም። ሌሎችንም እንደዚያው።</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-51516692267270483152018-01-24T02:28:00.001-08:002018-01-24T02:28:15.054-08:00አዲስ ድራኮኒያን ህግ! ( በቅርብ ቀን ይጠብቁ!)<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በኤርሚያስ ለገሰ</em></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<a href="https://ecadforum.com/Amharic/archives/17174/ermias-legesse2-2/" rel="attachment wp-att-17175" style="border: 0px none; color: #0f06ba; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px; text-decoration-line: none; transition: all 0.2s ease-in-out;"><img alt="Ermias Legesse, author and ESAT TV and Radio contributor" class="aligncenter size-full wp-image-17175" height="330" sizes="(max-width: 620px) 100vw, 620px" src="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2016/10/Ermias-Legesse2.jpg?x82458" srcset="https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2016/10/Ermias-Legesse2.jpg 620w, https://ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2016/10/Ermias-Legesse2-300x160.jpg 300w" style="border: 1px solid rgb(203, 205, 204); clear: both; display: block; height: auto; list-style: none; margin: 2px auto; max-width: 100%; outline: none; padding: 4px;" width="620" /></a></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
በቅርቡ የፀረ ሽብርተኝነት ህግ ተስተካካይ የሆነና ከሌሎች ጨቋኝ ህጐች (የፕሬስ ህግ፣ የፀረ ሽብርተኝነት ህግ) ጋር እርስ በራስ የሚመጋገብ አዋጅ ሊወጣ ያቆበቆበ ይመስላል። የአዋጁም ስያሜ <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">” </strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የማህበራዊ </strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሚዲያ </strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ህግ”</strong> ሊባል ይችላል። ይሄ ህግ ህውሓት የአርማጌዶ ፍልሚያ ጀምሬያለሁ በማለት በድርጅታዊ መግለጫው የገለፀውን ወደ ተግባር ለመቀየር የታሰበ ነው። እንደታዘብኩት ከሆነ ለዚህ አደገኛ ህግ ለመውጣት የሚያስችል ቅድመ ሁኔታዎች እየተሰሩ ነው። አንዳንድ ማሳያዎችን አንስተን ጉዳዩን እንመልከተው።</div>
<a name='more'></a><br />
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የመጀመሪያው</em></strong> የኢህአዴግ ቢሮ <em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">” </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሶሻል </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሚዲያ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የደቀነው </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ፈተና </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እና </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ልንከተለው </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የሚገባ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የትግል </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ስልት”</em> በሚል ወደ 20 ገፅ የሚደርስ ፅሁፍ አውጥቶ ውይይት ማድረጉን እንመለከታለን። በሰነዱ ላይ ካድሬውን እና አባላቱ እንዲሁም የህውሃት የፌስቡክ ሰራዊት ( ኮካ) እንዲሰለጥኑበት ተደርጓል። ሰነዱ እንደመሰከረው ሶሻል ሚዲያው የህውሃት አገዛዝን ፈተና ላይ ጥሎታል።በዚህ ምክንያት ” ሶሻል ሚዲያ ያስፈልጋል ወይ?” የሚል ጥያቄ የሰነዱ መሰረታዊ ነጥብ ሆኗል። በገፅ ሁለት ላይ ” ሶሻል ሚዲያ ያስፈልጋል ወይ?” በሚል ርዕስ የሚከተለው ሰፍሮ እናገኛለን፣</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em 30px;">
<em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">“</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሶሻል </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሚዲያውን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በመጠቀም </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሀገር </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እና </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ህገ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መንግስታዊ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ስርአት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ለማፍረስ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የድርጅታችን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እና </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የስርአታችን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ጠላቶች </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ያልፈነቀሉት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ድንጋይ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የለም። </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በህዝቦች </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መካከል </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እርስ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በራስ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መቃቃር </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እንዲፈጠር </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">፣ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ህዝቡ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በመንግስት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ላይ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ያለው </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አመኔታ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እንዲቀንስ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ለማድረግ፣ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በድርጅቱ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ውስጥ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የርስ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በርስ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መቃቃር </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እንዲፈጠር </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እና </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሐይል </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እንዲዳከም </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">፣ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መደበኛ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የመንግስት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ስራ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እንዲስተጓጐል </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">፣ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ማህበራዊ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ግንኙነት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እንዲቆም </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ወዘተ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሞክረዋል። </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በዚህ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ምክንያት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በድርጅቱ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ውስጥ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ይህን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሁላ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ችግር </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ያመጣው </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሶሻል </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሚዲያ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በመሆኑ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መንግስት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ለምን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አይዘጋውም </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በሚል </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የሚቀርቡ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሀሳቦችም </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እንዳሉ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ይታወቃል” </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ይላል።</em></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
የህውሃት/ ኢህአዴግ አባላት እየተወያዩበት ያለው ይህ ሰነድ ” ሶሻል ሚዲያው ለጥፋት አላማ የሚውል ከሆነ መንግስትን ከስልጣን መውረድ ብቻ ሳይሆን ሀገር የማፍረስ አቅም እንዳለው ሊታወቅ ይገባል” በማለት ያስጠነቅቃል። በአረብ አገራት በተለይም በቱኒዚያ፣ ግብፅ፣ ሊቢያ የተካሄዱ ብጥብጦች በኃላም መንግስት እንዲለወጥ የተደረገው አብዬት የፌስቡክ ሪቮሊውሽን እስከ መባል መድረሱን ሰነዱ ያስታውሳል። ከዚህ በተጨማሪም እነዚህ የሶሻል ሚዲያ ተጠቃሚዎች የጋራ ጠላታቸው የትግራይ ነፃ አውጭ ( ህውሓት) እንደሆነ በገፅ 8 ላይ እንዲህ በማለት ይገልፃል፣</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em 30px;">
<em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">“</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሶሻል </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሚዲያ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በመጠቀም </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በድርጅታችን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ወይም </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መንግስታችን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ላይ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ተቃውሞ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የሚያሰሙ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ግለሰቦች </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የጋራ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ጠላታችን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ብለው </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የሚያስቡት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አካል </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ህዝባዊ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ወያኔ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሀርነት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ትግራይ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እንደሆነ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ያነሳሉ። </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ኢህአዴግ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አራት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በእኩልነት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መርህ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ላይ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በመመስረት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የመሰረቱት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ድርጅት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሲሆን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሕውሓት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከሌሎች </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ድርጅት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የሚበልጥበት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ወይም </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የሚያንስበት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አሰራር </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሊኖር </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">እንደማይችል </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የድርጅቱን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ታሪክ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከወገንተኝነት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ነፃ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በሆነ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መልኩ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የሚያዩ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አካላት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ያረጋገጡት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ነው” </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ይላል።</em></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ይህ የህውሓት ዶክመንት በመደምደሚያው ላይ ቀጣይ መወሰድ ያለባቸውን እርምጃዎች ይጠቁማል። ከእነዚህ እርምጃዎች ውስጥ ሰነዱ ሀሳባቸውን በነፃነት የሚገልፁ ሀይሎችን ( ሰነዱ ” አፍራሽ ሀይሎች” ይላቸዋል) ተጠያቂ እንዲሆኑ መስራት እንደሚያስፈልግ ያስጠነቅቃል። ከድርጊታቸው ጋር የሚመጣጠን እርምጃ መወሰድ እንዳለበት ያስገነዝባል።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em; text-align: center;">
***</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ለማህበራዊ ሚዲያው ሕግ መውጣት ዝግጅት እንዳለ የሚጠቁመው <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሁለተኛው </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ምልክት</em></strong> የፓርቲው ልሳኖች እና ሚዲያዎች የሚያወጡት ዘገባ ነው። ልሳኖቹ የህጉን መውጣት አስፈላጊነት ለማሳየት የሚከተሉት ስልትም ወዴት እየተሄደ እንደሆነ የሚጠቁም ነው። ለምሳሌ ENN የተባለው የህውሃት ንብረት የሆነው ቴሌቪዥን የህጉ መኖር አስፈላጊነት ላይ አስተያየት እንዲሰጡ የጋበዛቸው ሰዎች በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት ይኖራቸዋል፣ የራሳቸው ማህበራዊ መሰረት አላቸው ተብለው የሚታሰቡ ግለሰቦችን ነው። እነዚህ ግለሰቦች በማህበራዊ ሚዲያ ሰፊ ተሳትፎ ለማድረግ የራሳቸው መጦመሪያ አውድ ያላቸው ናቸው። በሃይማኖታዊ እና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎችም ላይ ከፍተኛ ተሳትፎ በማድረግ የኢትዬጲያ ህዝብ ያውቃቸዋል።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
እነዚህ ሰዎች የህውሃትን የጀርባ ሴራ አያውቁትም ተብሎ የሚታሰብ ባይሆንም አገዛዙ ያዘጋጀውን ሸምቀቆ እና ጥልቅ ጉድጓድ ቁፋሮ መሳሪያ ሆነው እያገለገሉ መሆኑን ላያስቡት ይችላል። ስገምት በቅን ልቦና እየተናገሩ ይሆናል። እንደውም አሁን ላይ ቆመህ በሚወጣው አዋጅ የመጀመሪያ ገመድ የሚጠልቅላቸው እነማን ይሆናሉ ተብዬ ብጠየቅ ከእነዚህ ግለሰቦች ውስጥ የቅድሚያ የምሰጣቸው ይኖራሉ። ለአገዛዙ ከሚያቀርቡት ጠንካራ ጥያቄ እና ሙግት በመነሳት።በተጨማሪም የህውሃት የፌስቡክ አስተኳሾች ” እንቶኔ እንዲህ አይነት ፅሁፍ አስፍሮ ለምን ዝም ይባላል?” በማለት ሲዝቱባቸው አይቻለው። አሁንም ቢሆን የትግራይ ነፃ አውጪ ያዘመታቸው የፌስቡክ ደፈጣ ተዋጊዎች በየጊዜው በሚያወጧቸው መጣጥፎች ላይ ቋጥኝ የሚወረውሩት በእነሱ ላይ በመሆኑ ለህጉ የቅድሚያ ሰለባነት እያዘጋጇቸው ይመስለኛል።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
በነገራችን ላይ እንደዚህ አይነት ጨቋኝ አዋጆችን ህውሃት ሲያወጣ የተከተለው አንዱ ስልት ይሄ ነበር። የበጐ አድራጐት አዋጅ፣ የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ፣ የፕሬስ ህጉ በዚህ መልኩ የፕሮፐጋንዳ ስራዎች ተሰርቶባቸዋል። በኢትዬጲያ ህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያላቸው ታዋቂ ግለሰቦች የህጐቹን ምንነት እና ከጀርባ ያዘለውን ፍላጐት ሳይመለከቱ አስተያየት ሲሰጡ ነበር። አዋጆቹ ከወጡም በኃላ የፕሮፐጋንዳ ማሽኖቹ በሰሯቸው ዶክመንተሪዎች ውስጥ በግብአትነት ውለዋል። ለኢህአዴግ የምርጫ ቅስቀሳ ሳይቀር በጥቅም ላይ ውለዋል። መቼም አገዛዙ የነፃ ፕሬስ ጋዜጠኝነት ወንጀል አድርጐ ሲያሳድድ፣ ሲያስርና ምድረበዳ አድርጐ ለተመለከተ የዛን ወቅት በየዋህነት አስተያየት የሰጡ ሰዎች የእግር እሳት ሳይሆንባቸው አይቀርም። በተመሳሳይ ሁኔታ የሽብርተኝነት ህግ እንዲወጣ አስተያየት የሰጡ ሰዎች ዛሬ በዚህ ህግ ውስጥ የሰፈሩ ጨቋኝ እና ጨካኝ ድንጋጌዎች ያደረሱትን ጉዳት ሲመለከቱ መቆጨታቸው የሚቀር አይደለም።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em; text-align: center;">
***</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ለሶሻል ሚዲያው ህግ መውጣት <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሶስተኛ </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ምልክት</em></strong> ተደርጐ ሊወሰድ የሚችለው በትላንትናው እለት የህውሓት የሚዲያ መቆጣጠሪያ አውድማ ( “የብሮድካስት ባለስልጣን” የሚል መንግስታዊ ካባ እንዲለብስ የተደረገው ተቋም) መሪነት የተደረገው ኮንፍረንስ ነው። ” የማህበራዊ ሚዲያው የህግ ማዕቀፍ” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ስብሰባ የማህበራዊ ትስስር ሚዲያው መተዳደሪያ የህግ ማዕቀፍ ሊወጣለት ይገባል የሚል ድምዳሜ ላይ ደርሷል። በኮንፍረንሱ ከኢትዬጲያ ህዝብ ውስጥ 53 ሚሊዬን የግል የሞባይል ስልክ ( ዳታ ያለው) እንደሆነ ተበስሯል። እንዲሁም 16 ሚሊዬኑ የሶሻል ሚዲያው ተጠቃሚ እንደሆነ ተገልጿል። ህውሓት መቼም የቁጥር ነገር አይሆንለትም። በቁጥር መቀቀያ ቶፋው እንደ ጉም ይዘግነዋል።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
የኮንፍረንሱን ዋና ማእከላዊ መልእክት ስንመለከት ባለፋት ሁለት አመታት በኢትዬጲያ ለነበሩት ግጭቶች ሶሻል ሚዲው ዋነኛ ተዋናይ እንደሆነ የተገለጠበት ነበር። ከዛም ባሻገር ሶሻል ሚዲያው ኢትዬጲያዊ እሴቶችን በመሸርሸር ሰዎች እንደሰው እንዳይታዩ ክፋትን የሚያለማምድ ነው ተብሏል። ሶሻል ሚዲያው ግጭትን የሚቀሰቅስና የሚያስፋፋ፣ የሀይማኖት ንትርክን የሚጋብዝ እንደሆነ ተወስቷል። ማህበራዊ ሚዲያዎች ሰብአዊነት የሌለው አፍራሽ የግለኝነት ባህሪ ያዳብራሉ ተብሏል። እናም እንደዚህ አሉታዊ ነገሮች ላይ ለምን ማተኮር አስፈለገ ብሎ የሚጠይቅ ሰው ለወደፊት የሚወጣው ህግ ምን አይነት ይዘት ይኖረዋል የሚለውን በቀላሉ መገመት ይችላል። እንሰሳይቱ ” ሳታማኸኝ ብላኝ!” እንዳለችው ማለት ነው።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em; text-align: center;">
***</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ለጨቋኝ</em></strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ህጉ</em></strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መውጣት</em></strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ገፊ</em></strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ምክንያት</em></strong> <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ምንድነው</em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">?</em></strong></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
የመጀመሪያውና ቀዳሚው ምክንያት ህውሃት በመቀሌ ያደረገው የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ እና ድርጅታዊ ኮንፍረንስ የደረሰበት ድምዳሜ ነው። የኮንፍረንሱ መግለጫ በግልፅ እንዳመላከተው ህውሓት ለማድረግ የተዘጋጀው ጦርነት የመጨረሻውን ነው። ስያሜውንም የአርማጌዶን ጦርነት ብሎታል። እርግጥ ህውሃት አርማጌዶንን ሲያውጅ ይህ የመጀመሪያው አይደለም። የዛሬ 17 አመት አቶ መለስ ነብስ ውጭ፣ ነብስ ግቢ ውስጥ ሰጥሞ ሲያገኘው አርማጌዶንን አውጆ ነበር። ይሄንን አዋጅ የአቶ መለስ ገድል የተገለፀበት የአቶ በረከት ” የሁለት ምርጫዎች ወግ” መፅሀፍ ላይ በገፅ 31 ላይ ፣</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em 30px;">
<em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">“</em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ኢህአዴጐች </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ጥገኛ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ዝቅጠት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በአገራችን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከተንሰራፋ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሊከተል </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ስለሚችለው </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አደጋ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የሚሰጡት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ምላሽ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አርማጌዶን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የሚል </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ነው። </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አርማጌዶን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በጥንታዊ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሃይማኖታዊ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መፅሀፍ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሰፍሮ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የሚገኝ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በመናፍቃንና </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በአማንያን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መካከል </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የመጨረሻው </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ወሳኝ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ፍልሚያ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የሚካሄድበት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ቦታ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ነው። </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ይህ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ተምሳሌታዊ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አገላለፅ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የተመረጠበት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ምክንያት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">በኢትዬጲያ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ጥገኛ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ዝቅጠት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከተንሰራፋ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ተወደደም </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ተጠላም </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አገራችን </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ከማትወጣው </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ቀውስ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ውስጥ </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ትዘፈቃለች </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ለማለት </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ነው” </em><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ይላል።</em></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ዛሬ ህውሓት በመግለጫው ላይ በድጋሚ የአርማጌዶን የመጨረሻ ወሳኝ ፍልሚያ ላይ እንደገባ ይፋ አድርጓል። በአብዬታዊ ዲሞክራሲ አዳኝነትን በተቀበሉ (አማኒያን) እና አብዬታዊ ዲሞክራሲ እንደ ህይወት መመሪያ ባልወሰዱ( መናፍቃን) መካከል የሞት የሽረት ትግል መቀጣጠሉን በአደባባይ ገልጠዋል። በሌላ አገላለፅ ከኢትዬጲያ ህዝብ ውስጥ አብዬታዊ ዲሞክራሲን አምኖ እና ተጠምቆ አዳኙ አድርጐ የወሰደ ( ከመቶሺህ የማይበልጠው) በቀረው 100 ሚሊዬን ህዝብ ላይ ጦርነት አውጇል። ይሄንንም ጦርነት በድል አድራጊነት ለመወጣት ጊዜ የለንም በሚል በፍጥነት መሮጥ እንዳለባቸው በደም አስምረውታል። የሶሻል ሚዲያው ህግም ህውሓት ከተደቀነበት የአርማጌዶን የህልውና አደጋና ከአደጋው ለማምለጥ የሚካሄድ የአቦ ሸማኔ ሩጫ ትጥቅ ሆኖ የሚያገለግል ነው። ለመቶ ሜትር ሩጫው ከሚያገለግሉ ትጥቆች ዋነኛው!!</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ዛሬ በብሮድካስት ባለስልጣን በተካሄደው <strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">” </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የማህበራዊ </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሚዲያ </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">የህግ </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ማዕቀፍ </em></strong><strong style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;"><em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">አስፈላጊነት”</em></strong> ኮንፍረንስ ላይ የህውሓት ቁልፍ ሰዎችን በፊት መስመር ተሰልፈው ሲፋለሙ ለማየት የቻልነው በዚህ ምክንያት ነው። 6 ቁጥር ለብሶ የሚያከፋፍለው ሽማግሌው ስብሃት ነጋ፣…5 ቁጥር የለበሰችው የወንድሙ ልጅ ፈትለወርቅ ገ/ እግዚአብሔር( ሞንጆሪኖ)፣…1 ቁጥር የለበሰው የፓርላማው ንጉስ እና የብሮድካስት ባለስልጣን የቦርድ ሰብሳቢ አስመላሽ ወ/ስላሴ፣… 7 እና 11 ቁጥር የለበሱት የብሮድካስት ዋና እና ምክትል ዴሬክተር ዘርአይ አስገዶም እና ልዑል ገብሩ ( ሁለቱም ህውሃቶች)፣ …8 ቁጥር የለበሰው የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ተቆጣጣሪ( ዛዲግ አብርሃ)፣… መጠባበቂያ ወንበር ላይ የተቀመጠው የሰብአዊ መብት ዴሬክተር ዶ/ር አዲሱ ገ/ እግዚአብሔር( ህውሓት)፣.. የፋና ስራ አስኪያጅ ወልዱ ይመስል( ህውሓት) ፣… የዋልታ ኢንፎርሜሽን ሀላፊ አልማዝ (ህውሓት) በቅድሚያ የደም መስመር ተሰልፈው እና ጐላ ብለው የታዩት እኩልነትንና የበጣም እኩልነትን ለማድመቅ አይደለም።</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-38126409952288293252018-01-23T06:26:00.001-08:002018-01-23T06:26:40.963-08:00የእኛ ስሜት እና የቴዲ አፍሮ ቁስል<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px;">
<a href="https://scontent-arn2-1.xx.fbcdn.net/v/t1.0-9/26903869_1942427129119610_6323561493646552422_n.jpg?oh=494f3809100c5254ef55bafe81f10358&oe=5AE12A0C" imageanchor="1" style="clear: right; float: right; margin-bottom: 1em; margin-left: 1em;"><img alt="Image may contain: 1 person, standing" border="0" height="400" src="https://scontent-arn2-1.xx.fbcdn.net/v/t1.0-9/26903869_1942427129119610_6323561493646552422_n.jpg?oh=494f3809100c5254ef55bafe81f10358&oe=5AE12A0C" width="224" /></a></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">~አንድ እርምጃ ወደኋላ ሁለት እርምጃ ወደፊት!</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">(ጌታቸው ሺፈራው)</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ቴዲ አፍሮ ባህርዳር ላይ "ጃ ያስተሰረያል!"ን ዝፈንልን ተብሎ ሳይዘፍን ከመድረክ ወረደ፣ ሕዝብም ቅር ተሰኘ አሉ። ይህን ስሰማ በሁለቱም ጫማ ውስጥ ገብቼ አየሁት። የኮንሰርት ተሳታፊ እና ዘፋኙን ሆኜ!</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ሕዝብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ቁስሉ እየጠዘጠዘው ነው። ቴዲ የብሶቱን እንዲዘፍንለት ይፈልጋል። ባህር ዳር ደም ያልደረቀባት ከተማ ነች፣ ቁስሉ ያልጠገገ፣ በየጊዜው እየደማ ያለ ሕዝብ ነው። ትናንት እንኳ ሕዝን የወልዲያን ሰቆቃ ሰምቶ ነው ወደ ኮንሰርቱ የገባው። ሕዝብ የፍቅር ሳይሆን የትግል ዜማ፣ የብሶት ዜማ ነበር መስማት የሚፈልገው።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">በሌላ በኩል ደግሞ ቴዲ አፍሮ "ይህን ከዘፈንክ አይቻልም" እየተባለ ፍዳውን አይቷል። ገንዘብ ከስሯል። ዋናው ገንዘቡ አይደለም። አድናቂዎቹን ማግኘት አልቻለም። ሌላው ቀርቶ ስለ መተባበር፣ ስለ ሕዝብ ፍቅር በአካል ተገኝቶ መስበክ አልቻለም! ከ "ጃ" አንፃር ካላየነው በስተቀር አብዛኛው የቴዲ ዘፈን ፖለቲካ ነው። ሀገር የመሰረቱትን እንደሰይጣን የሚጠሉ ገዥዎች ባሉበት ሀገር "ጥቁር ሰው"ን ያህል ፖለቲካ ያለ አይመስለኝም። ቴዲ በቅርቡ ያወጣው አልበም የተወደደው "ጃ ያስተሰራልን"ስላካተተበት አይደለም። ዝም ብሎ ዘፈን ስለሆነም አይደለም። ፖለቲካም ስለሆነ ነው። ተወዳጁ ቴዎድሮስ ካሳሁን ስለዘፈነውም ጭምር ነው!</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">በመከራ ያለ ሕዝብ ስሜት ለማንም ሊያስቸግር ይችላል። የባሰው ሕዝብ በስልት፣ ቀስ እያልክ ከምትነግረው አፍርጠህለት ግንባርክን ብትባል "ወንድ" ይልሃል። እውነቱን ተናግሮ ከመሸበት ማደር የሚለውም ይህንኑ ነው። ይህ የሕዝብ ስሜት ከበደል ብዛት የመጣ ነው። የብሶት ነው!</span></div>
<a name='more'></a><br />
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ግን በእየ ግላችን እንኳ የምንቀንሳት፣ እንሰንብት፣ ውጭ እንቆይ "ኧረ እነዚህ ሰዎችኮ" የምንልበት አጋጣሚ በርካታ ነው። ገብስ ገብሱን የምናወራበት ብዙ ነው። የምንወደውንም "አታክረው፣ ምን ነክቶህ ነው?፣ ተው እነዚህ ሰዎች!፣ ተው ሞኝ አትሁን፣ አንዳንዴ ብልጠት ያስገልጋል……" እያልን ይደርሳል ከሚባለው ችግር ማይል ርቀን የምንፈራ ብዙ ነን። አንድን ትልቅ ጉዳይ ለማስፈፀም ከዋናው ያነሱ ነገሮችን የምንቀንስበት ጊዜ ብዙ ነው።"ልጆቼን ላሳድግ ብየ እንጅ፣ ትምህርቴን ብጨርስ ኖሮ፣ ውጭ ሀገር ብሆን……" የምንል ሞልተናል። ይህ ሁሉ የሰው ባዶ ፍራት አይደለም። የገዥዎቹ አረመኔነት ነው። እንዲያውም አዲስ የሚሆነው አለመፍራት ነው!</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ሰለሞን ተካ ነገ የቴዲን "ጃ ያስተሰረያልን" ቢዘፍን "ይቅር" የሚለው ሰው ያለ አይመስለኝም። ቴዲ ሌላ ሙዚቀኛ ቢዘፍነው ላይሰማ የማይችል ዘፈን ሲዘፍን እንኳ የሚሰማው ሕዝብ "የእኔ ነው!" ስላለው ነው። የ"እኔ ነው" የምትለውን ደግሞ የፈለከውን ሁሉ ስላላደረገልህ አይንህን ለአፈር ልትለው አይገባም። እንዲያውም የሚወደው አካል የጠየቀውን ያልፈፀመው ምን የከበደ ነገር ገጥሞት ይሆን ብለን መጠየቅ የጥሩ ወዳጅ ባህሪ ነው።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ቴዲ ቋሚ ስራው ዘፈን ነው። ሁሌም ስለዘፈን፣ ስለ ደጋፊዎቹ ነው የሚያስበው። ትናንት ባህርዳር ስቴዲዬም የተገኘው ሕዝብ ደግሞ በአብዛኛው ዘፈንን በተወሰነ የመዝናኛ ጊዜ ብቻ የሚያስታውሰው ነው። ቴዲን ለስንት አንዴ ቢሰማው ነው። ከዘፋኞች ሁሉ ሊያስቀድመው ቢችልም ቴዲ አድማጮን የሚያስበውን ያህል ቴዲን አያስበውም። ቴዲ ለታዳሚው ከዘፋኞች መካከል አንዱ ነው። ዋነኛው ቢሆንም። ለቴዲ ግን ብቸኛው አድማጩ ሕዝብ ነው። ትናንት "ዝፈንልን" ብሎ ለምኖ ሳይሆን ሲቀር ቅር ካለው ሕዝብ በላይ፣ እየተለመነ መዝፈን ያልቻለው ቴዲ ቅሬታ የባሰ እንደሚሆን መገመት ይቻላል።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ቴዲን የሚወደደው የሕዝብ ስሜትን ስለተረዳ ነው። ግን ጃ ያስተሰረያልን ዘፍኖ ቁጭ ቢል አሁን ያገኘውን የሕዝብ ፍቅር ማግኘት ባልቻለ ነበር። በተደጋጋሚ የሕዝብን ስሜት የሚገልፁ ዜማዎች በማውጣቱ ብቻ ሳይሆን ለሕዝብ የከፈለው ዋጋም ይበልጥ ተወዳጅና ታማኝ አድርጎታል። በዚህ ሁሉ ጊዜ ቴዲ ብቻ የሚያውቃቸው ለሕዝብ ያልተገለፁ በደሎች ደርሰውበት ይሆናል። እሱ የበገነበትን፣ የተቆጨበትን፣ ምን አልባት ያለቀሰበትን ሁሉ አልተጋራነውም ይሆናል። እሱ ግን የሕዝብን ስሜት በአደባባይ ገልፆአል። ዛሬ አንድ ዘፈኑን ለመዝፈን ሲከበድ ጭንቀቱን ልንጋራው ይገባል። የምር ስንወደው ቢጨንቀው እንጅ በእኛ አይጨክንም ነበር ማለት ነበረብን። የምንወደው ሰው ለእኛ ስሜት ግዴታ እንዳለበት ሁሉ እኛው ለውሳኔው ቦታ ልንተውለት፣ ለእሱ ስሜትም ግዴታ ሊኖርብን ይገባል።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">እንደኔ ቴዲ አድናቂዎችን ማግኘት ይፈልጋል። ይህን ሲያደርግ የተደራደረው ነገር “ጃ ያስተሰረያልን” አለመዝፈን ነው። ይህ ለእሱ ልብ የሚሰብር ሊሆን ይችላል። ግን ደግሞ ያለው አንድ ዘፈን ብቻ አይደለም። በሌሎቹ ዜማዎች አድናቂዎቹን እያገኘ፣ አሳካለሁ የሚለውን ለመተግበር ያቀደ ይመስለኛል። ቀስ በቀስ……እንዲሉ። ከአማራ ቲቪ ጋር ከነበረው ቆይታ መረዳት እንዳሚቻለው ስለ ሕዝብ ፍቅር፣ ታሪክ……መስበክ ይፈልጋል። የተወሰነውን አጥቶ ካጣው የተሻለ ነገር ማድረግ ይፈልጋል። ፖለቲከኞቹ ሁለት እርምጃ ወደፊት አንድ እርምጃ ወደኋላ እንደሚሉት ማለት ነው። አንድ እርምጃ ያተርፋል ማለት ነው! ትርፍና ኪሳራ አስልቶ ማለት ነው። ጃ ያስተሰረያልን ብቻ ከስሮ የምኒልክን ታሪክ፣ የቴዎድሮስን ታሪክ፣ የሙስሊም ክርስትያኑን ታሪክ………መስበክ ፈልጓል።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">እኔ በበኩሌ ይህ መንገድ አዋጭ ይመስለኛል። እኛ የለመድነው ወደፊት ገፍተን ቁም ስንባል “ቁም ተብያለሁ፣ አይታችኋል” ብለን እማኝ ቆጥረን መቆም ነው። አሊያም ይህ ካልሆነ ፈቀቅ አልልም ብለን ባለበት መርገጥ ወይጭራሽ ቀኝ ኋላ ዙር ነው።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ከምንም በላይ ግን ቴዲ ዘፈነ፣ ንዋይ አዜመ፣ እኛ የራሳችን ጥቅምና ጉዳት ምን ሊሆን ይችላል፣ ምን ሊሆንስ ይገባል ብለን አንቆጥርም። ከፍ ለማድረግ አንጥርም። ያ በሆነበትም ግን ሕዝብ ስሜቱን ገልፆአል። ከፍ ለማድረግ ብንጥር ደግሞ ከዚህ የተሻለ ሊሆን በቻለ ነበር። ቴዲን ከመጠበቅ ከራሳችን የሚጠበቀውንም ማድረግ እንችል ነበር።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ከአንድ ጓደኛዬ ጋር ከኮንሰርቱ ባህርዳር ምን ልታገኝ እንደምትችል እያወራን ነበር። ብዙዎቻችን በረባ ባረባው ስብሰባ፣ ኮንፈረንስ፣… እየተባለ የት የት እንደሚደረግ እንኳ መረጃው ላይኖረን ይችላል። በምሽት ዜና ዘገባዎች የሚታዩ ስብሰባዎች የት ከተማ፣ የት ሆቴል እንደሚደረጉ እንኳ አስበነው አናውቅም። በቴዲ ኮንሰርት የባህርዳር ባጃጆች፣ ሆቴሎች፣ ታክሲዎች፣ ማተሚያ ቤቶች፣ ጌጣጌጥ የሚሸጡ ወጣቶች የሚያገኙትን መንግስት በአንድ ቀን ቀርቶ በወር በጀት አይመድብላቸውም።</span></div>
<div style="background-color: white; display: inline; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-top: 6px;">
ከቴዲና ከጃ ያስተሰረያልስ ማን ይበልጣል? የወደድነው በዚህ ዘፈን ብቻ ነው? ከወደድነው ሊዘፍን ያልቻለበት ምክንያትስ ለምን አላስጨነቀንም? ጃ ከእኛ እና ከቴዲ ከማን ይቀርባል? ከፈጣሪው ቴዲ እና ከአድማጮቹ የጃ ያስተሰረያል መከልከል ማንን ያመዋል?</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com1tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-54203018907684396522018-01-20T09:13:00.000-08:002018-01-20T09:13:24.795-08:00የህወሀት ጸሀይ እየጠለቀች ነው<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px;">
<a href="https://scontent-arn2-1.xx.fbcdn.net/v/t1.0-9/281910_785270401518604_8752733323959217514_n.jpg?oh=6ec517700dda3010eddcb21a4559f0c8&oe=5AEE713C" imageanchor="1" style="clear: right; float: right; margin-bottom: 1em; margin-left: 1em;"><img alt="Image may contain: 1 person" border="0" height="400" src="https://scontent-arn2-1.xx.fbcdn.net/v/t1.0-9/281910_785270401518604_8752733323959217514_n.jpg?oh=6ec517700dda3010eddcb21a4559f0c8&oe=5AEE713C" width="258" /></a></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<em style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">መሳይ መኮንን</em></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ብዙ ምልክቶች በመታየት ላይ ናቸው። ተመልሶ የሚያንሰራራበት እድል ያለ አይመስልም። እየተንፏቀቀ ጊዜ ሊወስድ ይችላል። እግሮቹ ተሰብሮ በደረቱ እየተሳበ ከቤተመንግስት የተወሰነ ጊዜ ሊቆይ ይችላል። ስጋው አልቆ በአጥንቱ ቆሞ ጥቂት ጊዜያት መቆየቱ የማይቀር ነው። በዘላቂነት ግን አልቆለታል ማለት ይቻላል። የህዝቡ ተቃውሞ ሳይቋረጥ ከቀጠለ፡ ከያቅጣጫው የበረታው ግፊት ጉልበቱን ጨምሮ ይበልጥ ከገፋ የሚንፏቀቀውን፡ እግሮቹ የተሰበረውን፡ በአጥንቱ የቀረውን ህወሀት ከታሰበው ጊዜ በጣም በቅርብ ዘላለማዊ ሞቱን የሚጨልጥ ስለመሆኑ አያጠራጥርም። እስቲ ምልክቶቹን አንድ በአንድ እንመልከታቸው፥-</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">የትግራይ ህዝብ</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ህወሀት ከ2010 ዓም ዋዜማ ጀምሮ መቀሌ ከቷል። ላለፉት አምስት ወራት በስብሰባ፡ በኮንፈረንስ፡ በግምገማ፡ በህንፍሽፍሽ፡ በጉባዔ ተጠምዶ ከርሟል። አሁንም እንደሚኖር ይጠበቃል። ትግራይ የህወሀት የመጨረሻ ምሽግ ናት። ስልጣን ላይ ከወጣበት ጊዜ አንስቶ የኢትዮጵያ ልብ ማግኘት ያቃተው ህወሀት አክ እንትፍ፡ ተብሎ መተፋቱን አረጋግጧል። የኢትዮጵያን ህዝብ በፍቅርም፡ በጉልበትም መምራት እንደማይችል ተረድቶታል። ከእንግዲህ ወርቅ እንኳን ቢያነጥፍ የሚቀበለው እንደሌለ አውቆታል። ስለዚህ ወደ መጨረሻ ምሽጉ ፊቱን አዙሯል። ይህ ምሽግ የተወሰነ ዕድሜ እንደሚያዘልቀው ተማምኗል። በኋላ ኪሱ የሸጎጣትን ''የትግራይ ሪፑብሊክ'' ምስረታ ከተሳካለትም ይሞክራል። በኢትዮጵያ ማዕከላዊ መንግስት በበላይነት መቆየት ካልቻልኩ ያሉኝ አማራጮች ብሎ ከያዛቸው እርምጃዎቹ አንዱ ወደ ትግራይ ጠቅልሎ ገብቶ ምሽጉን ማጠናከር ነው።ለዚህም የትግራይን ህዝብ ልብ ሙሉ ለሙሉ ለማግኘት ቃል በመግባት ተግቶ እየሰራ ነው።</span></div>
<a name='more'></a><br />
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ህወሀት ምሽጉን ለማጠናከር እርምጃዎችን በመውሰድ ላይ ነው። ከእነዚህም አንዱ የትግራይን ህዝብ ታች ወርዶ ይቅርታ መጠየቅ ነው። በልማት ማንበሽበሽ ነው። ቀድሞውኑ ያዘነበለውን ተጠቃሚነት ይበልጥ አጠናክሮ መቀጠል ነው። ሰሞኑን እንደተሰማውም የትግራይ ህዝብ ለከፈለው መስዋዕትነት የሚመጥን ልማት ሊዘረጋለት ተወስኗል ተብሏል።። ከወዲሁ በሌላው የኢትዮጵያ ክፍል እስከአሁን ተገንብቶ የማያውቅ በፌደራል መንግስቱ በጀት በ2ቢሊየን ብር የኮንክሪት አስፋልት ግንባታ ስምምነት ተደርጓል። ኢፈርት የዘመናዊና ትልልቅ ኢንዱስትሪዎች ግንባታ ስምምነቶችን እያጣደፈ ነው። ከአማራና ከኦሮሞ አርሶአደሮች ከመደበኛው የገበያ ዋጋ ከፍ ባለ መጠን የተለያዩ የእህል አይነቶች እየተገዙ ወደ ትግራይ እየተጫኑ ነው። በትግራይ በተለያዩ አከባቢዎች ግዙፍ ጎተራዎች ተተክለው እህሎች እየተከመረባቸው ነው። ምናልባት ነገሮች ከረው ወደትግራይ የሚወስዱ መስመሮች ቢቋረጡ በሚል ብዙ ምርቶች በገፍ ተገዝተው እየተጠራቀሙ መሆናቸውን መረጃዎች ያሳያሉ።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ህወሀት የትግራይን ህዝብ እየተለማመጠ፡ እየተማጸነ መሆኑ የሚያሳየን ነገር ቢኖር ዞሮ መግቢዬን፡ መቃብሬን አጣለሁ ከሚል ስጋት ሊሆን እንደሚችል መገመት ቀላል ነው። የመቀሌው ኮንፍረንስ የህወሀት የነፍስ አድን ጥሪ እንደሆነ ይነገራል። የመጨረሻ ምሽጉን አስተማማኝ ለማድረግ ነው። የህወሀት አመራሮች ''ልባችሁን ክፈቱልን። በጠላት እጅ ላይ ከምንወድቅ በእናንተ ክንድ ላይ የመጨረሻዋ እስትንፋሳችን ታልፍ ዘንድ ፍቃዳችሁ ይሁን'' ዓይነት ልመና ባደረጉበት የቅርብ ጊዜው ኮንፍረንስ ያሰቡትን ያህል ስለማግኘታቸው የሚታወቅ ነገር የለም። አይናቸውን በጨው አጥበው ግን ''ከማንም በላይ መስዋዕትነት ስለከፈላችሁ ትካሳላችሁ። ጊዜው ደግሞ አሁን ነው '' የሚል በሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ኪሳራ ለትግራይ ባላት ላይ ሊከምሩባት፡ ወስነዋል። የሚያስጨንቃቸው ስልጣናቸው ነው። አዲስ አበባ ላይ ተነቃንቋል። ቢያንስ መቀሌ ላይ ምሽጋቸውን አጠናክረው ትንሽ ጊዜ የሚያቆያቸውን ሃይል ማጠራቀም አለባቸው። ማምሻም እድሜ ነውና።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">የትግራይ ህዝብ ውሳኔ ምን ሊሆን እንደሚችል አይታወቅም። የህወሀት ካድሬዎችን፡ ደጋፊዎችንና አባላትን ጩሀት ለሰማ ተስፋ ሊቆርጥ ይችላል። ጨፍነው ግፋ እያሉት ነው። አበጀህ የእኛ ልጅ ከሚል ሞራል ጋር የህወሀትን የጥፋት ዕቅድ እየደገፉት ነው። ይህ ስሜት የትግራይ ህዝብ በሙሉ ነው ለማለት ይከብዳል። ድምጹ ስለማይሰማ፡ የሚጮሁት ጥቂቶች የሌላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ስሜት ቀይረው በጅምላ የትግራይን ህዝብ ከወገኑ እንዳይነጥሉት ስጋቱ አለ። የትግራይ ህዝብ ለህወሀት የመጨረሻ ምሽግ መሆን የለበትም። ህወሀት ያልፋል። በቅርቡ። ከማያልፈው ህዝብ ጋር ሰልፉን እንዲያስተካክል ይጠበቃል። ህወሀት እየገነባ ያለውን የመጨረሻ ምሽግ ቀድሞ ማፍረስ ያለበት የትግራይ ህዝብ ነው።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">የኢኮኖሚው ቀውስ</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">አይ ኤም ኤፍ ሰሞኑን እንዳስታወቀው የህወሀት መንግስት ያለው የውጭ ምንዛሪ ክምችት ከአንድ ወር ከ8ቀናት በላይ የሚያዘልቀው አይደለም። መረጃዎች የሚያሳዩት ግን ከዚህም በላይ አስደንጋጭ ነው። ከአንድ ቢለየን ዶላር በታች የደረሰው የውጭ ምንዛሪ ክምችት ህወሀትን እጅና እግሩን አሳስሮ አስቀምጦታል። አይ ኤም ኤፍ ለህወሀት የሚጨክን አንጀት ስለሌለው እውነተኛውን ቁጥር ስለመግለጹ ጥርጣሬ አለ። የሆኖ ሆኖ የአይ ኤም ኤፍ መረጃ በራሱ ብዙ ነገሮችን ይነግረናል። አንድ መንግስት በዚህ ደረጃ የውጭ ምንዛሪ አቅም ላይ ከደረሰ ምንም ነገር ማድረግ አይችልም። ኢኮኖሚው በከፍተኛ ፍጥነት ወደ እየወደቀ ነው። የአገዛዙ ጠበቃ የሆነው ሪፖርተር ጋዜጣ ''ለመንግስት ከባድ አደጋ መጥቶበታል'' ሲል በተቆርቋሪነት ስጋቱን ገልጿል።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">የውጭ ንግድ ተዳክሟል። ኢንቨስትመንት የኋሊት እየገሰገሰ ነው። የንግድ ስርዓቱ ተፋልሷል። ግብይቱ ተረባብሿል። የቱሪዝሙ ዘርፍ እያቃሰተ ነው። በእንቅርት ላይ እንዲሉ የብር የመግዛት አቅም በ15 በመቶ እንዲቀንስ መደረጉ ቀውሱን አባብሶታል። የዋጋ ግሽበት ከአንድ አሀዝ ወደ ሁለት አድጓል።በሀገሪቱ በተለያዩ አከባቢዎች እየተካሄዱ ባሉ ተቃውሞችና ህዝባዊ አመጾች ምክንያት የንግድ ቦታዎች ስራ ፈተዋል። በየጊዜው የሚመታው አድማ መደብሮችንና ሱቆችን ጾማቸውን እንዲከርሙ እያደረገ ነው። በአጠቃላይ ኢኮኖሚው ተቃውሷል። መፍትሄው ከህወሀት አቅም በላይ ሆኗል። ከውስጥ የሚወጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት የህወሀት አገዛዝ በድጋሚ የብርን የመግዛት አቅም ለመቀነስ እየተዘጋጀ ነው። ይህ ከሆነ በኑሮ ውድነት ጀርባው የጎበጠው የኢትዮጵያ ህዝብ የመኖር ህልውናው ያከትማል ሲሉ መጪውን ጊዜ በስጋት የሚገልጹ ወገኖች አሉ። የኢኮኖሚ ባለሙያዎች እንደሚሉት ተጠያቂነት ባለባቸው ሀገራት እንዲህ ዓይነት ቀውስ በሩብ ያህል ቢከሰት እንኳን መንግስትን የሚመራው አካል በራሱ ጊዜ ከስልጣን ይወርዳል። በህወሀት መዝገበ ቃላት ግን ስልጣን መልቀቅ በተአምር የሚታሰብ አይደለም።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ህወሀት የኢኮኖሚው ነገር ከአቅም በላይ ሆኖበታል። መሰረታዊ አገልግሎቶችን ማቅረብ ተስኖታል። ውሃ መብራትና ሌሎች አገልግሎቶች የሚቆራረጥባቸው፡ ጭራሽኑ የማያገኙ ከተሞች እየጨመሩ መጥተዋል። የነዳጅ እጥረቱ ተባብሷል። ለነዳጅ መግዣ የሚሆነው የውጭ ምንዛሪ እየተሟጠጠ በመሆኑ በቀጣይ ቀውሱ ሊከፋ እንደሚችል ይጠበቃል። ለመድሃኒት መግዥ የምትሆነዋ የቀረችው የውጭ ምንዛሪም ተመናምናለች። ህገወጥ የመድሃኒት ዝውውር ይህን ተከትሎ የሚዛመት በመሆኑ ከፍተኛ የጤና ቀውስ ይከሰታል ተብሎ ይሰጋል። በአንዳንድ አከባቢዎች የመንግስት ሰራተኞች ደመውዝ ሳይከፈላቸው ወራት እንደሚቆጠሩ ተሰምቷል።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የከፈቱት የውጭ ምንዛሪ ተአቅቦም ለህወሀት መንግስት ራስምታት መፍጠሩ እየተነገረ ነው። የውጭ እርዳታ በነጠፈበት፡ ብድር ሰጪዎች እጃቸው ባጥረበት በዚህን ወቅት የህወሀትን ኢኮኖሚ ደጋግፎ የያዘው ሪሚተንስ(ከውጭ ወደ ሀገር ቤት የሚላክ ገንዘብ) እንዲቀንስ የተጀመረው ዘመቻ ውጤት እያሳየ ነው። ህወሀት ብርክ ይዞታል። መረጃዎች እንደሚጠቁሙት የህወሀትን አገዛዝ ነፍስ ቀጥ አድርጎ የያዘው የሪሚተንስ ገንዘብ ነው። እሱ በአንዳች ሁኔታ ከቀነሰ ለማፈኛ ተቋማቱ የሚከፍለው ገንዘብ አይኖረውም። ይህም የማፈን አቅሙን ያዳክማል።ያ አቅሙ ከተዳከመ ደግሞ ይገነደሳል። አዲዮስ ህወሀት!</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">የፖለቲካ ምሁራን እንደሚስማሙት በኢትዮጵያ እስከአሁን ከተደረጉት ህዝባዊ ተቃውሞዎች በላይ ሀገር አቀፍ የሆኑ አመጾችና እምቢተኝነቶች መቀጣጠላቸው አይቀርም። የኢኮኖሚው ሁኔታ በዚሁ ከቀጠለ ከተሞች፡ መንደሮች፡ አውራጎዳናዎች በተቃውሞ ይጠለቀለቁ ዘንድ የሚጠበቅ ነው። የአገዛዙ ደጋፊ የሆኑ ሚዲያዎችም ይህን ሀቅ እየጎመዘዛቸውም ቢሆን እየተናገሩት ነው። ሪፖርተር እንዳለው መንግስት በአስቸኳይ መፍትሄ ካልሰጠ የኢኮኖሚው ቀውስ የበለጠ የህዝብ ተቃውሞዎችን ያመጣል። በየቀኑ የአመጽ ሰልፎችን የምናይበት ጊዜ ሩቅ አይደለም።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ውስጣዊ ቀውስ</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ህወሀት በራሱ ውስጥና እንደኢህአዴግ ከአባል ድርጅቶች ጋር የገባበት ቀውስ የሚሰክን አልሆነለትም። ከመቀሌው የነፍስ አድን ኮንፍረንስ ጎን ለጎን እየተለቀቁ ያሉት ሚስጢሮች ህወሀት ይበልጥ በውስጣዊ ቀውስ እየተሰቃየ ለመሆኑ ምልክት የሚሰጥ ነው ማለት ይቻላል። በተሸነፈው ቡድን የሚዘከዘኩት ጉዶችና ቅሌቶች በህወሀት መንደር ያለው አንድነት መናጋቱን የሚያመላክት ነው። በተለይ የህወሀት ሊቀመንበርና የትግራይ ክልልን በም/ፕሬዝዳንትነት እንዲመራ የተሰየመው የወሲቡ ሻምፒዮን ደብረጺዮን ገብረሚካዔል ላይ የተከፈተው የማጋለጥ ዘመቻ ለህወሀት ትልቅ አደጋ እንደሚሆን ይገመታል። የተመታው ቡድን እጁን አጣጥፎ እንዳልተቀመጠ እያስመሰከረ ነው። ያለድርጅታዊ መተዳደሪያ ደንብ ወደ መቀሌ ዳግም እንዲከትና በኮንፍረንስ እንዲጠመድ ያደረገው የውስጣዊ ሽኩቻው እየበረታ በመምጣቱ እንደሆነም ይነገራል። በትግራይ ሽማግሌዎች እግዚዮታና ልመና ለጊዜው ጋብ ቢልም ህወሀት እንደ ድርጅት ለመቀጠል የሚያስችል ውስጣዊ አንድነቱ እንደሰባበረ የሚደብቁት አልሆነም።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ከኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ የ17 ቀናቱ ዝግ ስብሰባ በኋላ ''ልዩነታችንን ፈተናል። አንድ ሆነናል'' የሚለው መግለጫ በወረቀት ላይ እንጂ መሬት ላይ እንደሌለ ከዚያን ወዲህ የተፈጠሩ ነገሮችን በመጥቀስ መግለጽ ይቻላል። ለጊዜው ውጥረትን ማስተንፈስ የቻሉ ቢመስልም አንድነታቸው ላይመልስ መናጋቱ ከማይደበቅበት ደረጃ ላይ ተደርሷል። የኦህዴድና የብአዴን አመራሮች አሁንም በአቋማቸው እንደጸኑ ናቸው። የአቶ ለማ መገርሳ ቡድን ከዝጉ ስብሰባ በኋላም የሚያደርጋቸው፡ የሚናገራቸው ለህወሀት ምቾት የሚሰጡ አልሆኑም። በ17ቱ ቀናት ዝግ ስብሰባ ያደረግነውን ተጋድሎ ህዝቡ ቢያውቀው ጥሩ ነበር ያሉት አቶ ለማ ስምምነት እንደሌለ በጎን እየነገሩን እንደነበረ አልተረዳናቸውም። በእስረኞች መፈታት ላይ በተለይ የኦህዴድ አመራር የያዘው አቋም አሁንም ኢህአዴግ ቤት ቀውስ እንዳለ ግልጽ መልዕክት ነው። የፌደራል መንግስቱን የፍቺ መስፍርት አልቀበልም ያለው የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ህወሀቶች የሚተናነቃቸውን ''የፖለቲካ እስረኞች'' ን በሙሉ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንደሚፈታ አስታውቋል።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">አቶ ለማ የኢትዮጵያን ህዝብ ቀልብ የገዙበትን የፍቅርና የአንድነት መልዕክታቸውን ከዝጉ ስብሰባ በኋላም ቀጥለውበታል። ህወሀት ያወገዘውን ''የመርህ አልባ ግንኙነት'' የቀጠሉት አቶ ለማ መገርሳ ''ነፍስ ዘር የላትም'' በሚል አዲስ ቀልብ ሳቢ መልዕክታቸው ብቅ ብለዋል። ከዚያም ተሻግረው በለገጣፎ የኦሮቶዶክስ ቤተክርስቲያን የገጠማትን የጥገኛ ባልስልጣናት አደጋ አስወግደው ቤተክርስቲያኒቱ ይዞታውን አግኝታ አገልግሎቷን ያለምንም ችግር እንድትቀጥል ማድረጋቸው በእርግጥም ሰውዬው የህወሀትን የልዩነት ግንብ ሳይደረምሱ እንቅልፍ እንደማይወስዳቸው ያረጋገጡበት ውሳኔያቸው ነው። የድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን የባህርዳሩ ኮንሰርትም ከህወሀት ፍላጎት ውጪ ስለመፈቀዱ ምንም ጥርጥር የለውም። ኮንሰርቱ በመካሄዱ ህወሀት የሚያተርፈው አንዳችም ነገር ፈልጌ ላገኝ አልቻልኩም። ይልቅስ የገዱ ቡድን በብአዴን ውስጥ ያለውን የህወሀት ተላላኪ አመራርና የመቀሌውንም ገዢ ቡድን ተጋፍጦ የፈቀደው ኮንሰርት መሆኑን መግለጽ ይቻላል።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">እናም ኢህአዴግ ውስጥ የገባው ንፋስ ህወሀትን እያናጋው ቀጥሏል። ወደ መቀሌ አማትሮ የመጨረሻ ምሽጉን እንዲያጠናክር ያደረገውም በኢህ አዴግ ውስጥ የነገሰው ክፍፍል በቀላሉ የሚጠገን ባለመሆኑ እንደውም ህልውናን የሚያጠፋው እንደሆነ በመረዳቱ ነው።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">የአፍሪካው ቀንድና የምዕራባውያን አቋም</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">የምዕራባውያን ፍላጎት የህወሀት አገዛዝ እንደምንም ብሎ በስልጣን ላይ ቢቆይላቸው ነው። አሁን ግን ያ የሚሆን አልመሰላቸውም። ህወሀት የተለከፈበት በሽታ ለእነሱም መዘዝ እንደሚያመጣ የተረዱት ይመስላል። ከወዲሁ አንዳንዶቹ እጃቸውን መሰብሰብ ጀምረዋል። ለህወሀት ፊት መነሳታቸውን የሚያረጋግጡ ምልክቶችን በአደባባይ እያሳዩ ነው። በጀርባ አዝለው ከአራት ኪሎ ቤተመንግስት ያስገቡት የአሜሪካው ዲፕሎማት የሰሞኑ የቲውተር መልዕክት አንድ ፍንጭ የሚሰጥ ነው። ከ27ዓመት በኋላ የህወሀት ጭራቅነት የተገለጠላቸው ዲፕሎማቱ ሀርማን ኮን የኢትዮጵያ ህዝብ የደረሰበት አቋም አስደንግጦአቸዋል። ''ከህወሀት ደርግ የተሻለ ነበር''</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">በእርግጥም አሜሪካ እየተንሸራተተች ነው። ከህወሀት አገዛዝ ጋር ለዘመናት የተጣበቀችበትን የውጭ ፖሊሲዋን ልትቀይረው መውሰኗን ታውቋል። የአሜሪካው የመከላከያ ሚኒስትር ሰሞኑን እንደተናገሩት ''አሜሪካ የጸረ ሽብር አጋርነት ላይ የተመሰረተው የውጭ ፖሊሲዋ አብቅቷል'' ይህ ውሳኔ ለህወሀት አገዛዝ ታላቁ መርዶ ሊባል የሚችል ነው። ድሮውኑም ከፖለቲካ ድጋፍ በቀር ከህወሀት ጋር የኢኮኖሚ ወዳጅነት ያልፈጠረችው አሜሪካ ብቸኛውን የግንኙነት መስመር ለመበጠስ መወሰኗ ለነጻነትና ዲሞክራሲ ናፋቂ ኢትዮጵያውያን ትልቅ የምስራች ሲሆን ለህውሀትና ደጋፊዎቹ አስደንጋጭ ዜና ነው። ይህ ውሳኔ ህወሀትን የሚያሳጡት በርካታ ነገሮች አሉ። በዓለም ዓቀፍ ዲፕሎማሲ ላይ የአሜሪካንን ጭራ እየተከተለ ድጋፍ ሲያሰባስብ የከረመው ህወሀት በተላላኪነት ያገኘውን ተሰሚነት የሚያጣበት ይሆናል። በጸረ ሽብር አጋርነት የሚያገኛቸውንና ኢትዮጵያውያንን የሚገድልባቸውን አሜሪካ ሰራሽ የጦር መሳሪያዎችን ከእንግዲህ ይነጥፍበታል። በዚሁ የጸረ ሽብር አጋርነት የሚሰጠውም ዶላር ይቆማል። ይህ በፖለቲካ ድጋፍ የሚያገኘው ዶላር ለህወሀት የመኖር ዋስትናው ሆኖ ቆይቷል። የእንጀራ ገመዱ ነበር።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">የአፍሪካው ቀንድ ፖለቲካዊ ትኩሳት ላይ ነው። የግብጽና የሱዳን ፍጥጫ በርትቷል፡፡ የአረብ ሀገራት በረጅም እጃቸው የሚያምሱት ቀጠና ሆኗል። ወደለየለት አጠቃላይ ቀውስ ባይገባም ከወዲሁ የሚታዩት ፍንጮች ለህወሀት አገዛዝ ህልውና ወሳኝ መሆኑ አይቀርም። የህዝብ አመጽ ገፍቶ ከቀጠለ ከአፍሪካው ቀንድ ቀውስ በፊት ህወሀት ሊሰናበት ይችላል። ካልሆነም ቀውሱ የህወሀትን ዘላለማዊ ሞት እንደሚያስከትል የፖለቲካ ምሁራን ይገልጻሉ። ለዚህም በርካታ ምክንያቶችን ቢደረድሩም የኢትዮጵያ ህዝብ ህወሀትን የመሰለ ጨካኝ አገዛዝ ቤተመንግስት አስቀምጦ የትኛውንም የውጭ ወራሪ ሃይል ለመዋጋት የሚሰለፍ አለመሆኑ ዋናው ምክንያት እንደሆነ ይስማማሉ። ሻዕቢያ መጣብህ እያለ ህዝባዊ ድጋፍ ማሰባሰብ ከእንግዲህ የሚቻል አይደለም። እንኳን ሻዕቢያ ግብጽም ከመጣች ጦርነቱ የህወሀትና የግብጽ እንጂ የኢትዮጵያ ህዝብ አይሆንም የሚለው አቋም ከወዲሁ በኢትዮጵያውያን ዘንድ እየተመላለሰ ይሰማል። ህወሀትን ይዞ ጦርነት አያዋጣም። እንደውም ህወሀትን ለመሰናበት ጥሩ አጋጣሚ ሊፈጥር ይችላል።</span></div>
<div style="font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-bottom: 6px; margin-top: 6px;">
<span style="background-color: white;">ማጠቃለያ</span></div>
<div style="background-color: white; display: inline; font-family: Helvetica, Arial, sans-serif; margin-top: 6px;">
አስቸኳይ አዋጅ ያላስቆመው፡ የደህንነት ምክርቤት ማጠንቀቂያ ያላበረደው፡ የኢህአዴግ መግለጫ ያልገታው፡ የእስረኞች ፍቺ ያላዘናጋው ህዝባዊ ተቃውሞ ቀጥሏል። የጥምቀት ዋዜማ የከተራ በዓል በጸረ ህወሀት መልዕክቶች ደምቆ ነው የተከበረው። በአምቦ፡ ጎንደር፡ ነቀምት ፡ ወልዲያ አንድ መልዕክት ይሰማል ''ቻው ቻው ወያኔ፡'' ዛሬ በወልዲያ አራት ሰዎች የተገደሉበት ተቃውሞ ፡ በባህርዳርና ጎንደርም በተመሳሳይ እየታየ ያለው የህዝብ የእምቢተኝነት እንቅስቃሴም የሚያመላክተው የኢትዮጵያ ህዝብ የትኛውንም መስዋዕትነት ከፍሎ ህወሀት የሚባል ኋላቀር፡ አውሬ አገዛዝን ለመገላገል መቁረጡን ነው። አዎን! የህወሀት ጸሀይ እየጠለቀች ነው።</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-78536782770365267882018-01-19T08:12:00.000-08:002018-01-19T08:12:20.473-08:00ልክ ያጣው የእነ ገብረ እግዚያብሔር እብሪት <div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<em style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ጌታቸው ሽፈራው</em></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
<a href="https://ecadforum.com/Amharic/archives/18523/aschalew-desse/" rel="attachment wp-att-18524" style="border: 0px none; color: #0f06ba; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px; text-decoration-line: none; transition: all 0.2s ease-in-out;"><img alt="Ethiopian political prisoner Aschalew Desse." class="aligncenter size-full wp-image-18524" height="330" sizes="(max-width: 620px) 100vw, 620px" src="https://i1.wp.com/ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2018/01/aschalew-desse.jpg?resize=620%2C330" srcset="https://i1.wp.com/ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2018/01/aschalew-desse.jpg?w=620&ssl=1 620w, https://i1.wp.com/ecadforum.com/Amharic/wp-content/uploads/2018/01/aschalew-desse.jpg?resize=300%2C160&ssl=1 300w" style="border: 1px solid rgb(203, 205, 204); clear: both; display: block; height: auto; list-style: none; margin: 2px auto; max-width: 100%; outline: none; padding: 4px;" width="620" /></a></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
አስቻለው ደሴ የፌደራል ፖሊስ አባል ነበር። አማራ በሰበብ በሚታሰርበትና በሚከሰስበት ግንቦት 7 አባል ነህ ተብሎ ታሰረ። የተለመደውና የሌለው የ”ሽብር” ክስ ተመስርቶበታል። የታሰረው ደግሞ የአማራ ወጣቶች ዘራቸውን እንዳይተኩ ከሚኮላሹበት ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ነው። እንደሌሎቹ ወንድሞቹ አስቻለው ደሴንም ብልቱ ላይ ሁለት ሊትር ሀይላንድ ውሃ አንጠልጥለው ዘሩን እንዳይተካ አድርገውታል። ጆሮውንም ጎድተውታል። ለዚህ ሁሉ ቁስሉ ምንም አይነት የህክምና እርዳታ አላገኘም። በክሱና በማንነቱ ምክንያት ህክምና ተከልክሏል። ጥጋበኞች ላቆሰሉት፣ ለጎዱት አካልና መንፈሱ ምንም አይነት ህክምና አላገኘም።</div>
<a name='more'></a><br />
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ቀርቦ ማዕከላዊ የደረሰበትን አሰቃቂ በደል በቃል <span class="text_exposed_show" style="border: 0px none; list-style: none; margin: 0px; outline: none; padding: 0px;">ሊገልፅ ሲል “በፅሑፍ አቅርብ” ተባለ። አስቻለው ደሴ ግን የተፈፀመበትን ቢያንስ በችሎቱ የታደሙት ወገኖቹ ያዩለት ዘንድ ሱሪውን አውልቆ “የኢትዮጵያ ህዝብ ይፍረደኝ” አለ። ችሎቱን የታደሙት አነቡ፣ ከአስቻለው በምሬት እየተናገረ በችሎት የነበሩት በተለይም የሴቶች ሲቃም አጀበው። በፅሑፍ አቅርብ ያሉት ዳኞች፣ ያጀቡት ፖሊሶች በአስቻለው የሰቆቃ ድምፅ ፀጥ አሉ። ይሰማ የነበረው የእሱ የሰቆቃ ጩኸትና የታዳሚዎች ሲቃ ብቻ ነበር።</span></div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
አስቻለው ደሴ ይህን ሰቆቃ ተናግሮ ወደ ቂሊንጦ ሲመለስ፣ ሌላ ቅጣት ነበር የጠበቀው። ከቃጠሎው በኋላ በግዳጅ በእስረኛ ጉልበት ወደተሰራው ዞን 5 ተቀየረ። ዞን 5 ጥብቅ ቁጥጥርና አፈና ያለበት እስር ቤት ነው። የቂሊንጦ እስር ቤት ኃላፊዎች ምንም በማያገባቸው አስቻለውን ጨምሮ በርካቶችን ፍርድ ቤት በሚናገሩት ይደበድቧቸዋል። ወደ ጨለማ ቤት ይልኳቸዋል። የአሳሪዎቹ እብሪት ግን በዚህ ግን አላበቃም።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
የአስቻለው ቤተሰብ የሆኑ ቄስ ይህን መከረኛ ወጣት ለመጠየቅ ከአማራ ክልል ወደ ቂሊንጦ ይሄዳሉ። እስር ቤቱ በር ላይ ግን ያልጠበቁት ይገጥማቸዋል። ጥምጣማቸውን ካላወለቁ ወደ እስር ቤቱ እንደማይገቡ ይነገራቸዋል። ቄሱ ቢለምኑ የሰማቸው አላገኙም። አሳሪዎቹ የቄስ ማንነትንም ወደ ኋላ ያያሉ፣ በመጡበት አካባቢ ይመዝኗቸዋል፣ ያዋርዷቸዋል፣የእስረኛውን ማንነት ጋርም ያያይዙታል።</div>
<div style="background-color: white; border: 0px none; font-family: nyala; font-size: 17px; list-style: none; outline: none; padding: 0px 0px 1em;">
ቄሱ ሰቆቃ የደረሰበትን አስቻለውን ለመጠየቅ ሲሉ ቆባቸውን አውልቀው ገቡ። የተፈፀመባቸውን አስፀያፊ ተግባርም ለአስቻለው አጫወቱት። አስቻለው ለምን እንዲህ ይበድሉናል ብሎ በምሬት ሲናገር ከጎኑ የቆመው ጥበቃ ፖሊስ እየሰማ ነበር። ይህም ወንጀል ሆኖ ለእነ ገብረ እግዚያብሔር ተነገራቸው። ገብረ እግዚያብሔር የተባለ ፖሊስ እግዚያብሔርን የማይፈራ ከቂሊንጦ “ኃላፊዎች” መካከል አንዱ ነው። ቄሱ ቆባቸውን አውልቀው እንዲገቡ መገደዳቸው ሳይበቃ፣ ይህ መደረግ አልነበረበትም አለ ተብሎ አስቻለውን አስደብድቦ ጨለማ ቤት እንዲገባ አድርጓል። ያ ሁሉ በደል የተፈፀመበት አስቻለው በቤተሰቦቹ እንዳይጠየቅ ተከልክሏል። ማዕከላዊ በተፈፀመበት ድብደባ ቁስሉ ሳይጠግግና ህክምና ሳያገኝ አሁንም እየተደበደበ ነው። የእነ ገብረ እግዚያብሔር እብሪት ልክ አጥቷል!</div>
Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0tag:blogger.com,1999:blog-2956752375511358769.post-85065751182735472732018-01-19T07:19:00.001-08:002018-01-19T07:19:25.770-08:00የመንግስቱ ሃይለማርያም ልጅ ዶ/ር ትዕግስት መንግስቱ አወዛጋቢ ቪዲዮ ለቀቀች – “እንዴት ተደፈርን?”<div style="border: 0px; font-family: Arial, Helvetica, sans-serif; margin-bottom: 10px; padding: 0px; vertical-align: baseline;">
<span style="background-color: white;">(ዘ-ሐበሻ) የቀድሞው የኢትዮጵያ መሪ ኮ/ል መንግስቱ ሃይለማርያም ልጅ የሆነችው ዶ/ር ትዕግስት መንግስቱ በግብጽ እና በአባይ ፖለቲካ ዙሪያ አንድ ቪዲዮ ለቀቀች:: ቪዲዮውን የለቀቅችው በፌስቡክ ሲሆን የራሷን አስተያየት “እንዴት ተደፈርን?” ስትል ትጀምራለች:: ይመልከቱትና በአባይ ዙሪያ ያላትን አወዛጋቢ አቋም አስተያየት ይስጡበት::</span><br /><iframe allow="autoplay; encrypted-media" allowfullscreen="" frameborder="0" height="360" src="https://www.youtube.com/embed/pWmU0eVFRso" style="border-style: initial; border-width: 0px; font-family: inherit; font-style: inherit; font-weight: inherit; margin: 0px; padding: 0px; vertical-align: baseline;" width="640"></iframe></div>
<aside class="mashsb-container mashsb-main " style="background-color: white; border: 0px; color: #333333; font-family: Arial, Helvetica, sans-serif; font-size: 13px; margin: 0px; padding: 10px 0px; vertical-align: baseline;"><div class="mashsb-box" style="border: 0px; font-family: inherit; font-style: inherit; font-weight: inherit; line-height: 1; margin: 0px; padding: 0px; vertical-align: baseline;">
<div class="mashsb-buttons" style="border: 0px; font-family: inherit; font-style: inherit; font-weight: inherit; margin: 0px; padding: 0px; vertical-align: baseline;">
<div class="mashpv mashsb-count mash-large mashtip" data-mashpv-postid="87078" data-mashtip="This number shows the total pageviews since publishing of the article" style="border: 0px solid rgb(255, 255, 255); color: #5ea808; cursor: help; float: left; font-family: "Helvetica Neue", Helvetica, Arial, sans-serif; font-size: 43px; font-style: inherit; font-weight: 700; line-height: 13px; margin: 10px 10px 0px 0px; padding: 0px; position: relative; text-align: center; vertical-align: baseline;">
</div>
</div>
</div>
</aside>Anonymoushttp://www.blogger.com/profile/16008717806084891105noreply@blogger.com0