Translate

Sunday, July 31, 2016

የጻድቃን “መፍትሔ ሃሳቦች” – ልመና? ጥገና? ወይስ ህወሃት ቁጥር 2?

(ርዕሰ አንቀጽ)

which one

የራሳቸውን ጥቅም ለማስጠበቅና አለአግባብ ለመበልጸግ ያሰቡ አውሮጳውያን በአሜሪካ አካባቢ ያሉትን አገሮች በጥጥና በሸንኮራ አገዳ እያለሙ መጠነሰፊ ሃብት ለማጋበስ በሰላም የሚኖሩ አፍሪካውያንን በግፍ እያጋዙ ዓለማችን እስካሁን ዓይታ የማታውቀውን ዓይነት የባርነት ሥርዓት ለበርካታ ዓመታት አካሂደዋል፡፡ ከአፍሪካ ወደ አሜሪካ በግፍ የተጋዙት ወገኖች በመንገዳቸው ያሳለፉት መከራና ከዚያም ለማሽን እንኳን የሚሰጠው ዕረፍትና ጥገና እነርሱ ተነፍገው ለመቶዎች ዓመታት ከምንም ጋር የማይወዳደርና የማይነጻጸር ሰቆቃ አሳልፈዋል፡፡ የዚህ መራራ ግፍ ውጤት አሁንም አብዛኛውን የዓለማችንን ክፍል እየናጠው ነው፡፡

ከአዲስ አበባ ሀረርና ጅጅጋ የሚወስደው መንገድ ተዘጋ | አጋዚ በአወዳይ ሰላማዊ ሰልፈኞችን በጥይት አቆሰለ

oromia
(ዘ-ሐበሻ) ጎንደር በሰላማዊ ሰልፍ በተቀወጠበት በዛሬው ዕለት ምስራቅ ሐረርጌ አወዳይ ከተማም እንዲሁ ሕዝባዊው ተቃውሞ ገንፍሎ መውጣቱ ተሰማ::
ሕዝቡ በሰላማዊ መንገድ ወጥቶ ተቃውሞን ባሰማበት በዛሬው የአወዳይ ከተማ ተቃውሞ በስፍራው የነበረው የአጋዚ ሰራዊት 4 ሰዎችን ክፉኛ ማቁሰሉ ተሰምቷል::
የሕዝባዊ ተቃውሞው እጅግ በመጠንከሩ ሕዝቡ ከአዲስ አበባ ሃረርና ጅጅጋ የሚያገናኘውን መንገድ በድንጋይ; በ እንጨትና በተለያዩ ቁሳቁሶች እንደዘጋጋቸው የደረሱን መረጃዎች ይጠቁማሉ:: በዛሬው ተቃውሞ በአጋዚ ጥይት ከቆሰሉት መካከል አህመድ የሱፍ; ሙአዝ አብዱልሃሚድ ኡመር; ባርክሌና በየነ ደሜሾ የሚባሉ ወጣቶች እንዳሉበት ታውቋል::

በገደብ አሳሳ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ወደሙ | ሰልፈኞች የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ደኤታ መኖሪያ ቤትን አቃጠሉ

gedeb asasa2
Gadab asasa
(ዘ-ሐበሻ) በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች የተጀመረው ሕዝባዊ አመጽ እንደቀጠለ ነው:: ሕዝብ በመንግስት እና በመንግስት ደጋፊዎች ንብረት ላይ የበቀል እርምጃውን እየወሰደ መሆኑም ተሰምቷል::
ምዕራብ አርሲ በገደብ አሳሳ ቲጆ ዋቄንተራ ከተማ ዛሬ በተደረገ ተቃውሞ በአጋዚ ጥይት ወገኖቹ የተቆሉበት ሕዝብ ቁጣውን የመንግስት መስሪያ ቤቶችን ሰባብሮ በመግባት ሰነዶችን በመበታተንና በማቃጠል የበቀል እርምጃዎችን ወስዷል::
በዛሬው የገደብ አሰሳ ቲጂ ዋቄንተራ ከተማ ቤታቸው ከተቃጠለባቸው የ ስር ዓቱ ባለስልጣናት መካከል የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ደኤታው አቶ ዳዋኖ ከድር መኖሪያ ቤት እንደሚገኝበት ታውቋል:: እንደደረሰን መረጃ ከሆነ ተቃሟቸውን ሊገልጡ የወጡ ሰልፈኞች የምታስፈጀን አንተ ነህ በሚል የአቶ ዳዋኖ ከድርን መኖሪያ ቤት በ እሳት አንድደውታል::
Gadab asasa 2

Wednesday, July 27, 2016

ምስለ – ብአዴን

ብአዴን የብረት አከሉ ህዝባዊ አመጽ መሀንዲስ?

gondar uprising
ለፖለቲካ ስልጣን ሁለተኛነት ሁሌም የሚጫወተዉ ብአዴን፤ ኢሕኢፓ በገጠመው የመበታተን አደጋ ለኢሕዴን ጥንሰሳ ምክንያት የሆነው የበለሳ ንቅናቄውን በመጀመር ብዙዎች ወደ ደርግ ሲኮበልሉ፣ እልፎች ወደ ሱዳን ሲሰደዱ ‹‹ጥቂቶች ቆራጦች›› ህዳር 11/1973 ዓ.ም በህወሓት አጋፋሪነት ኢሕዴንን እንደመሰረቱ በግነታዊ ቃላት የታጀበው የድርጅቱ ታሪክ ያትታል፡፡

Tuesday, July 26, 2016

ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ “ስለ ኦሮሞና አማራ ትክክለኛ የዘር ምንጭ” ያብራራሉ!!


ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ “ስለ ኦሮሞና አማራ ትክክለኛ የዘር ምንጭ” ያብራራሉ!!
ፕሮፌሰር Fikre Tolossa ሰሞኑን ባሳተሙት ‹‹የኦሮሞና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ›› በተሰኘው መፅሀፋቸውና ተያያዥ ጉዳዮች ቅዳሜ እለት ከታተመው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ጋር ያደረጉትን ቃለመጠይቅ ሁላችሁም ታነቡት ዘንድ እዚህ ለጥፌዋለው፡፡ ትምህርት ሰጪ ስለሆነ አንብቡት

Friday, July 22, 2016

ሰበር መረጃ – በሕወሃት የመከላከያ ሰራዊት ዉስጥ የነበረዉ ጉምጉምታ ወደ ተግባራዊ ተቃውሞና ፍጥጫ ተሸጋገረ

በልኡል አለም
የወታደራዊ ፖለቲካ መምሪያ እና የፕሮፓጋንዳ ክፍሎች ምንጭ እንደሚያመለክተዉ በሰሞኑ ጎንደር ላይ የተገደሉትን የመከላከያ ሰራዊት አባላት ወደ ትዉልድ ቦታቸዉ ተወስደዉ በክብር መቀበራቸዉ ተንተርሶ በሰራዊቱ ዉስጥ ቅራኔ ተፈጥሯል!TPLF security members killed in Gondar
ይህዉም፣

Wednesday, July 20, 2016

ጥርስ ኣልባው ሃይለማርያም ደሳለኝ ስልጣን ቢለቅ ለሕወሓት ትልቅ ኪሳራ መሆኑ እየተነገረ ይገኛል :

ለወልቃይት የማታለያና የጊዜ መግዣ እንዲሆን ጊዜያዊ የራስ ገዝ ኣስተዳደር ሊሰጥ ይችላል::
Minilik Salsawi's photo.የኣማራ ክልል መሳሪያ ማስፈታት ካልቻለ ፌዴራል መንግስቱ መሳሪያ ያስፈታ የሚል ስልጣን የሚሰጥ ኣዋጅ እየተረቀቀ እንደሆነ መረጃዎች ኣሉ። ይህም ለፓርላማ ይቅረብ ኣይቅረብ ኣልታወቀም።አማራ ክልል ባለስልጣናትን ያላከተተ ዝግ ስብሰባ በሃይለማርያም ደሳለኝ እየተመራ ባህርዳር ላይ ተቀምጧል። የወያኔ ጅቦች ሊበሉ ያሰቧቸው የብአዴን ሰዎች እንዳሉ ኣመላካች ነው።(ከሐምሌ ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን የሚጠበቀውን የገቢ ግብር አዋጅ እና ሌሎች ለቋሚ ኮሚቴ ተመርተው ያልተጠናቀቁ አዋጆችን ለማፅደቅ ??? )
 ኢትዮጵያ ከፍተኛ የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ እየዋዥቀች ነው።ለፓርላማው ስለወቅታዊ የሃገሪቱ ሁኔታ እንዲያነብ በሕወሓት ተጽፎ የመጣለትን ንጝግር እንዲሻሻል ቢጠይቅም ተቀባይነት ኣላገኘም።በሃይለማርያም ደሳለኝና በደህንነት ቢሮው ሃላፊ እንዲሁም በሕወሓት ጄኔራሎች መካከል ኣለመግባባት የተከሰተ መሆኑ እየተነገረ ሲሆን ሕወሓት ሃይለማርያም ኣርፎ እንዲቀመጥ ኣስጠንቅቃዋለች፥ ወታደራዊ እና የደሕንነት ሪፖርት የፈለገው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ የሕወሓት ባለስልጣናትን መልስ ተከትሎ ሃይለማርያም ደሳለኝ በጥርስ ኣልባነቱ ቢጮሕም የሚሰማው ኣላገኘምበስልጣን የመቆየት ፍላጎት እንዳሌለው የሚያስነግረው ሃይለማርያም በነዱት የሚሄድ በግ መሆኑን ሕወሓቶች ራሳቸው መስክረውበታል።

ርላማው መጠራቱ ለምንድን ነው ? ግርማ ካሳ

547መቀመጫ ያለው ፓርላማ ከሰኔ 30 ቀን በኋላ መስከረም እስኪጠባ ድረስ የማይሰበሰብ አካል ነው። አባላቱ እረፍት ላይ ነው የሚሆኑት። (እንደ ትምሀርት ቤቶች ማለት ነው)። በሌላውም አገር የፓርላማ አባላት የማይሰበሰቡባቸው ቀናቶች በዛ ይላሉ። ይሄም የሆነበት ምክንያት አለው። አባላቱ በፓርላማ መቀመጥ ብቻ ሳይሆን፣ የሕዝብ ተወካዮች እንደመሆናቸው ከሕዝብ ጋር መነጋገር አለባቸው። በዚህ ወቅት ነው የተለያዩ ስብሰባዎች በተመረጡበት ቦታ እየጠሩ ሕዝቡ ያለውን ብሶት፣ መሻሻል አለባቸው የሚለው እንዲነገራቸው የሚያደርጉት። የበኢትዮጵያ ያሉ የፓርላማ አባላት ግን ከተመረጡ በኋላ መንግስት በአዲስ አበባ ከሚሰጣቸው ቤት ፈቀቅ አይሉም። ይሄ ማለት የሕዝብ ተወካዮች የሚባሉት ሕዝብን እንደማይወኩሉ በገሃድ የሚያረጋግጥ ነው።

ሌ/ጀነራል ገዛኢ አበራ ቤተሰቦቻቸውን ሰብሰበው ስዊድን ገቡ!!


(ዘ-ሐበሻ) የጦር ሃይሎች የሎጂስቲክስ ዋና ሐላፊ የነበሩት ሌ/ጀነራል ገዛኢ አበራ ቤተሰቦቻቸውን ሰብስበው ስዊድን መግባታቸውን አብርሃ ደስታ ከመቀሌ ባስተላለፈው መረጃ አመለከተ። አብርሃም ገዛኢ ከሃገር የወጡት በጡረታ ለተገለሉ በኋላ ነው  በማላት  ”የህወሓት ሃላፊዎችማ የያዙትን ይዘው ከሀገር እየወጡ ነው። የተቸገሩ ታችኞቹ ካድሬዎች ናቸው። እንደ አለቆቻቸው ወደ ዉጭ በመኮብለል የግል ደህንነታቸው መጠበቅ አይችሉም።” ሲል ትችቱን አስፍሯል።

Friday, July 15, 2016

ይድረስ ለጎንደር ሕዝብ – ከቅስቀሳና አደራጅ አካላት የተሰራጨ አስቸኳይ ባለ 8 ነጥብ መልእክት

Gonder
ሃምሌ 8 2008
1. ወያኔ የሚንበረከከው በሃይል ብቻ ስለሆነ የተጀመረው አኩሪ ህዝባዊ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንዲቀጥል። ያ ካልሆነ የታሰሩ ወገኖችን ማስፈታት አይቻልም።

Thursday, July 14, 2016

በጎንደር የተቀሰቀሰው አመጽ ለሁለተኛ ቀን ቀጥሏል፣ በርካታ ሰዎች ተገድለዋል፣ ከወያኔ ወገን የወደቁት አስክሬናቸው አልተነሳም

“የወልቃይት ሕዝብ የማንነት ጥያቄ ኮሚቴ አባላትን” ከጎንደር ከተማ አፍነው ለመውሰድ ፊታቸውን ጭምብል በመልበስ ሸፍነው ከትግራይ ክልል በመጡት የሕወሃት አፋኞችና እነርሱን በመርዳት ላይ ካሉት የፌደራል ፖሊሶች ጋር የጎንደር ሕዝብ ለሁለተኛ ቀን እየተዋጋ ይገኛል።Colonel Demeke Zewdu
ወያኔዎቹን በመፋለም ላይ ያሉት አብዛኛዎቹ ወጣቶች ምንም አይነት የጦር መሳሪያ ያልታጠቁ ናቸው። ይሁንና ምንም እንኳን ከሕዝብ ወገን “የወልቃይትን ሕዝብ የማንነት ጥያቄ የኮሚቴ አባላትን” ጨምሮ ብዙ ሰዎች የወደቁ ቢሆንም በአንጻሩ ከወያኔዎቹ ጎራም በርካታ ታጣቂዎች ተገድለዋል።

Wednesday, July 13, 2016

አርበኞች ግንቦት 7 ለጎንደር ህዝብ አጋርነቱን እየገለጸ እንደሚገኝ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናገሩ

Image result for dr berhanu negaአርበኞች ግንቦት 7 መስዋዕትነት እየከፈለ ለሚገኘው የጎንደር ህዝብ አጋርነቱን እየገለጸ እንደሚገኝ ሊቀመንበሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተናገሩ። የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በምስልና ድምፅ ከኤርትራ ረቡዕ ዕለት ባስተላለፉት መልዕክት የአማራም ህዝብ ሆነ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ አጋርነቱን እንዲያሳይ ጥሪ አቅርበዋል።
የወልቃይት ህዝብ ማንነቱን በተመለከተ በህጋዊና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ያቀረበው ጥያቄ በህወሃት በኩል የሃይል ምላሽ መሰጠቱ የቀሰቀሰው ተቃውሞ ወደግጭት ማምራቱን በጥሪያቸው ያስታወሱት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ በጎንደር የታየው ህዝባዊ ዕምቢተኝነት በስርዓቱ ሰለባ ለሆኑትና ለውጥ ለሚሹ ሁሉ መነቃቃትን የፈጠረ እንደሆነ አመልክተዋል።

የአርማጭሆ ሕዝብ ተነስቷል – በጎንደር ከተማ 4 ሆቴሎች ወድመዋል * 2 ደህነንቶች ተገደሉ (ዜና ጎንደር)

ፎቶ ፋይል
(ዘ-ሐበሻ) በሕወሓት ደህንነቶች ተንኳሽነት; በጎንደር ሕዝብ ቁጣ የተቀጣጠለው ሕዝባዊ አመጽ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል:: የጎንደር ከተማ በአሁኑ ወቅት ከሕወሓት መንግስት ቁጥጥር ውጭ መሆኗን የሚገልጹ ምንጮች ወታደሮች አሁንም ወደ ሕዝቡ እየተኮሱ ቢሆንም ሕዝቡም የአጸፋ ምላሹን በተለያዩ መንገዶች እየገለጸ ነው::

ሰበር ዜና – የአርበኞች ግንቦት 7 ጀግኖች የነፃነት ታጋዮች ጓንጋ አሳግላ ላይ ከቀኑ ስድስት ሰዓት እስከ ሰባት ሰዓት ከ24ኛ ክፍለ ጦር ጋር ተፋልመው በትንሹ 15 ወታደሮችን ገድለው 10 አቁስለዋል

ሰበር ዜና! ትንቅንቁ አሁንም በመረረ ሁኔታ እንደቀጠለ ነው!!
Arbegnoch Ginbot 7
የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት የጥቃት አድማሱን አስፍቶ በአማራ ክልል አዋሳኝ ከተሞች ላይ በሰፈረው የሕወሓት ጦር ላይ ጥቃት እየፈፀመ እንደሚገኝ ተሰምቷል!!

Tuesday, July 12, 2016

መንግስት የጎንደሩን የሕዝብ ቁጣ ያቀጣጠሉት ኤርትራ ከመሸጉ ኃይሎች መመሪያ እየተቀበሉ ነው ሲል ከሰሰ


(ዘ-ሐበሻ) የወልቃይት ጠገዴ ማንነት አስተባበሪዎችን ለማሰር ከትግራይ የመጡ ደህንነቶች ላይ እርምጃ በመውሰድ ተጀምሮ; በጎንደር የሕዝቡ ቁጣ አይይሎ ከተማውን መቆጣጠሩንና አንገዛም ማለቱ መዘገቡ ይታወሳል:: በዚህም ጉዳይ መንግስት በሰጠው ምላሽ “በኤርትራ ከመሸጉ ሀይሎች መመሪያ በመቀበል የተከፈተ ነው” አለ:: መንግስት በራድዮ ፋና በኩል እንዳለው “በሰሜን ጎንደር ዞን ጠገዴ ወረዳ ሶሮቃና ኩርባ አካባቢ የሚያልፉ የህዝብና የመንግስት ተሽከርካሪዎች ላይ ተደጋጋሚ ተኩስ በመክፈት ጥቃት በመፈፀም የህብረተሰቡን ሰላማዊ እንቅስቃሴ አደጋ ላይ እንዲወድቅ ሲያደርጉ የነበሩትን አስሬያለሁ” ብሏል::

ሰበር መረጃ — የትምህርት ሚኒስተር፣ የፈተናዎች ኤጀንሲ ኮምፒውተሮች ሃክ ተደረጉ

በልኡል አለም
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና አፈትልኮ መዉጣትን ተንተርሶ ብዙዎች የራሳቸዉን አስተያየት ሰጥተዋል ነገር ግን ፈተናዉ ትክክለኛ መሰረቁን የሚያረጋግጥ አካል አልተገኘም ነበር። ኢሳት ጉዳዩን ለማጣራት ብዙ ጥረት አድርጎአል ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ተመሳሳይነት ያለዉ መግለጫ የሰጡጠም ግለሰቦች አለጠፉም።የትምህርት ሚኒስተር፣ የፈተናዎች ኤጀንሲ ኮምፒውተሮች ሃክ ተደረጉ
እዉነቱ ከሕወሃት መንደር ሲነገር መስማቱ ብዙም ባያስደነቅ የሐገራችንን ብሐራዊ ደህንነት አደጋ ላይ የጣለዉ እራሱ የብሐራዊ ደህንነት ፈተናዉ የተሰረቀበትን መንገድ አገኘሁ እያለ ባለበት ሁኔታ የ12ተኛ ክፍል ተፈታኞች እና መምህራን ያፈተለከዉ ፈተና ትክክለኛ መሆኑን እያረጋገጡ ይገኛሉ።

Monday, July 11, 2016

በፈተና ስም ማህበራዊ ሚዲያው አፈና ተካሄደበት

Image result for social media
ሐምሌ ፬( አራት ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በመላ አገሪቱ የፌስ ቡክ፣ ትዊተር፣ ኢንስታግራም እና ቫይበር የመልክት መለዋወጫ ዘዴዎች የተዘጉ ሲሆን፣ ገዢው ፓርቲ እርምጃውን የወሰድኩት የአስራ ሁለተኛ ክፍል ተማሪዎች ተረጋግተው ፈተና እንዲፈተኑ ለማስቻል ነው ብሎአል። ይሁን እንጅ እርምጃው በአገሪቱ ውስጥ እየተባባሰ ከመጣው የፖለቲካ ቀውስ ጋር እየተያያዘ ነው። ገዢው ፓርቲ ለፈተና በሚል አለማቀፍ ገጽታውን አያበላሽም የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች፣ ምክንያቱ የማህበራዊ ሚዲያው እየፈጠረ ካለው ተጽኖና በአገሪቱ እየታዬ ካለው አለመረጋጋት ጋር የሚያያዝ ነው በማለት አስተያየት ይሰጣሉ። ተማሪዎች ፈተናውን ተረጋግተው እንዲወስዱ ለማድረግ እንዲሁም ካላስፈላጊ ውዥንብር እንዲድኑ በማሰብ የተወሰደው እርምጃ ጊዜያዊ ነው ሲሉ የመንግስት ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ ተናግረዋል። ማህበራዊ ሚዲያ ተማሪዎችን የሚያዘናጋ መሆኑ ተረጋግጧል በማለት ቃል አቀባዩ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ዜጎችን ማፈናቀል መግደልና ማሰደድ የህወሃት አይነተኛ መግለጫዎች ናቸው

Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracyህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ወደ ስልጣን ከመጣበት ጊዜ አንስቶ በአገራችንና በህዝባችን ላይ ሲፈጽም የቆየውና እየፈጸመ ያለው ግፍና ስቃይ ተዘርዝሮ የሚያልቅ አይደልም። አፈና፣ እስር፣ ግድያና ዜጎችን ማፈናቀል አይነተኛ መግለጫዎቹ የሆነው ይህ የህወሃት አገዛዝ፣ ሰፋፊ የእርሻ መሬቶችንና የከተማ ቦታዎችን በመቸብቸብ ሃብት ለማካበት ባለው ዕቅድ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን እትብታቸው ከተቀበረበት ቀዬና የትውልድ መንደሮቻቸው በግፍ እንዲፈናቀሉ አድርጎአል። አሁንም እያደረገ ነው። ሰሞኑን በአዲስ አበባ በንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ ቀርሳና ኮንቶማ በተባሉ ቀበሌዎች ከ30 ሺ በላይ የሚገመት ህዝብ ለአመታት ከኖረበት መኖሪያ ቤቶች በሃይል ተገፍትረው በመውጣት ጎዳና ላይ እንዲበተኑ ተደርጎአል። በዚህም እርምጃ ምክንያት አቅመደካማ የሆኑ አዛውንቶች፤ ነፍሰጡሮችና ከወለዱ ገና ሳምንታት ያልሞላቸው እመጫቶች፤ የሚያጠቡ እናቶች፤ ህጻናትና ለጋ ወጣቶች ለከፋ ችግር ተዳርገው ለቅሶና ዋይታ በማሰማት ላይ ናቸው። በስንት ልፋትና ድካም ከሰሩዋቸው ቤቶች ተለዋጭ ቦታ ሳይሰጠን ወይም ካሳ ሳይከፈለን አንወጣም በማለት ለማንገራገር የሞከሩ 10 ሰዎች በፖሊስ ጥይት ተገደለዋል፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ደግሞ ለእስር ተዳርገዋል።

Sunday, July 10, 2016

የትምህርት ሚኒስትሩ የፈተና ወረቀት አልተሰረቀም አሉ

የትምህርት ሚኒስትሩ የፈተና ወረቀት አልተሰረቀም አሉ
ከሰኞ ሐምሌ 4 ቀን የሚጀመረው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተሰረቀ በሚል በተለያዩ የማህበራዊ ድረ-ገፆች የተሰራጨው ወሬ ሃሰተኛ መሆኑን የት/ት ሚኒስትሩ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ አስታወቁ፡፡ 26 የፈተና ወረቀቶች ተሰርቀው መውጣታቸውን አንዳንድ ድረ ገፆች ያስታወቁ ሲሆን በማህበራዊ ሚዲያዎችም የእንግሊዝኛ ፈተና መሰረቁን የሚያመላክት መረጃዎች ተሰራጭተዋል፡፡ በጉዳዩ ላይ አዲስ አድማስ ያነጋገራቸው የትምህርት ሚኒስትር አቶ ሽፈራው ሽጉጤ፣ ፈተናው ተሰርቋል የተባለው “ውሸት ነው፤ የራሳቸውን የውሸት የፈተና ወረቀት አዘጋጅተው ነው ወሬውን ያሰራጩት” ብለዋል፡፡
 ቀደም ሲል ፈተናው ግንቦት 22 ቀን እንዲካሄድ ታስቦ በነበረበት ወቅት የፈተና ወረቀቶች ስለመሰረቃቸው በተለያዩ ድረ ገፆችና ማህበራዊ ሚዲያዎች ሲገለፅ እንደነበረ የሚታወስ ነው፡፡ መንግት መረጃውን እያስተባበለ ቆይቶ፣ በፈተናው መስጫ እለት ነው በድንገተኛ መግለጫ ፈተናው እንዲቋረጥ የወሰነው፡፡

“ከ4 ሚሊዮን አምፖሎች ውስጥ 15 ሚሊዮኑ ለተጠቃሚ ደርሷል”

አዝናኝ እና አሳዛኝ የመንግስት ሪፖርቶች - በአዲስ መፅሀፍ
ስኳር፣ ኮንዶሚኒዬም፣ ወርቅ፣ ኤሌክትሪክ፣ አውቶቡስ …

   ባለፈው ዓመት፣ የስኳር ምርትን 22 ሚሊዮን ኩንታል ለማድረስ ታቅዶ አልነበር? ለዚህም፤ ከ200ሺ ሄክታር በላይ አዲስ የእርሻ መሬት ተዘጋጅቶ፣ የስኳር አገዳ ይለማል ተብሎ ነበር - በትራንስፎርሜሽን እቅድ፡፡ ግን አልተሳካም፡፡ የለማው ተጨማሪ መሬት፣ 35ሺ ሄክታር ነው፡፡ 
ከእቅዱ ጋር ሲነፃፀር፣ 15 በመቶ ብቻ ነው፡፡ ከእቅዱ ውስጥ፣ ሩብ ያህሉን እንኳ ማሳካት አልቻለም፡፡ 
ነገር ግን፣ ይህንን ውድቀት እንደ ስኬት አስመስዬ ማቅረብ ብፈልግስ? በአምስት አመታት ውስጥኮ፣ በድሮው 30ሺ ሄክታር ላይ 35ሺ ሄክታር ተጨምሯል፡፡ ስለዚህ፣ የ115% እድገት ተመዝግቧል ማለት ይቻላል፡፡
በእርግጥ፣ በቅርቡ የታተመው አመታዊ የመንግስት ሪፖርት ላይ “215%” ተብሎ ተጽፏል፡፡ ግን ይሄ አይገርምም፡፡ ለምን ብትሉ፤ “ገና ምኑን አያችሁና!” እላችኋለሁ፡፡ ገና ብዙ ስህተቶችን ታያላችሁ፡፡ ለምን? 
አገሩን ካጥለቀለቁት ብዙ አይነት እጥረቶች መካከል፣ “የቁጥር እውቀት እጥረት” (የሂሳብ እጥረት) አንዱ ነዋ፡፡ 
የመጀመሪያው ስህተት፣ ቁጥሩን ማሳሳት ነው (115% መሆን የነበረበት 215% ብሎ መፃፍ)፡፡ ሁለተኛው ስህተት፣ በ200ሺ ሄክታር (በ700%) ለማሳደግ ታቅዶ እንደነበር ሳይጠቀስ ይታለፋል፡፡ 

Saturday, July 9, 2016

ሰበር ዜና… በወያኔ ወታደራዊ ደህንነት አባላት ላይ እርምጃ ተወሰደ

በልኡል አለም
በሰሜን የሐገራችን ክፍል በህቡእ የተደራጁ የዉስጥ አርበኞችና የትግል አጋሮች በአንድነት በመተባበር ቀንደኛ እና አደገኛ በሆኑ በትግራይ ነጻ አዉጪ ቡድን የመከላከያ ሰራዊት የደህንነት አባላት ላይ እርምጃ ወስደዋል። ቢያንስ ከ6 ወራት በላይ የፈጀዉን ድርጊት ከመራዉ የህቡእ ኃይል ህበረት ወስጥ የወጣዉ መረጃ እንደሚጠቁመዉ።
TPLF security officers killed in Gondarወታደር አሳምን ሃለፎም፣
ወታደር በረከት ድረስ፣
ወታደር ሰይድ ይማም፣
ወታደር የትናየት ላቀዉ፣
ወታደር ጀምበሩ ዘለቀ።
የተባሉ እነዚህ እርምጃ የተወሰደባቸዉ አባላት የሕዝብ ጠላትነታቸዉን በግልጽ ያስመሰከሩ ያለ አግባብ የሚያስሩ፣ የሚገድሉና ወገኖቻችንን የሚያሳድዱ በተለይም በጎንደር አካባቢ መሬታችንን ለሰሜን ሱዳን አሳልፎ ለመስጠት ደፋ ቀና የሚለዉ የወያኔ አገልጋዮች በወልቃይት ጠገዴ አፋኞችና ገዳዮች ሲሆኑ በተለያዩ ወቅቶችና ግዜያቶች ከሰፊዉ ህዝብ ጎን እንዲቆሙ ትእዛዝ ቢሰጣቸዉም አሻፈረኝ በማለታቸዉና በእኩይ ተግባራቸዉ በመቀጠላቸዉ ነዉ።

Friday, July 8, 2016

ፈተናው… ከፈተና በፊት እንደገና ተሰራጨ (መረጃውን ይዘናል)

(ኢ.ኤም.ኤፍ) የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በድጋሚ ከፈተናው በፊት መሰራጨት ጀምሯል። ከአንድ ወር በፊት ፈተናው በተመሳሳይ ሁኔታ ወጥቶ በመባዛቱ፤ ተማሪዎች በድጋሚ እንዲፈተኑ በዚህ ሳምንት ቀነ ቀጠሮ ተይዞ ነበር። ከዚህ በፊት ፈተናው ወጥቶ እንዲሰራጭ ምክንያት የሆነው የኦሮሚያ ተማሪዎች ጉዳይ መሆኑ ይታወሳል። በወቅቱ ለፈተናው መሰራጨት ምክንያት የሆነው፤ “ከወራት በፊት በኦሮሚያ በተነሳው ረብሻ ትምህርት ቤቶች ተዘግተው ነበር። በዚህ ምክንያት የኦሮሚያ ተማሪዎች በደንብ አልተዘጋጁም፤ ስለሆነም የፈተናው ግዜ ይራዘምልን።” የሚል ሲሆን፤ መንግስት ጥያቄያቸውን ባለመቀበሉ…. ፈተናው ከመሰጠቱ በፊት፤ እንዲሰራጭ መደረጉ ይታወሳል።
2በወቅቱ የትምህርት ሚንስትሩ ሽፈራው ሽጉጤ፤ “ፈተናው አልተሰረቀም” ሲሉ ቆይትተው፤ ማምሻውን ግን ፈተናው መሰረቁን አምነው፤ ትምህርት ሚንንስቴር ፈተናውን ሙሉ ለሙሉ መሰረዙን ይፋ አድርጎ ነበር። ከዚያ በአፋጣኝ ፈተናውን ለመስጠት ሲጣደፉ፤ “በረመዳን ጾም ወቅት ፈተናውን ብትሰጡ ዋ!” የሚል ማስጠንቀቂያ ከሙስሊም መምህራን አካባቢ በመምጣቱ፤ ፈተናው ከረመዳን ጾም በኋላ እንዲሰጥ ተወሰነ። እንግዲህ ይህ ሁሉ አልፎ ተማሪዎች ፈተናውን ለመውሰድ በዝግጅት ላይ እያሉ፤ ፈተናው ለሁለተኛ ግዜ ተሰርቆ መውጣቱ በሰፊው እየተነገረ ነው።
በአሁኑ ዙር ፈተናው ወጥቶ እንዲሰራጭ ምክንያት የሆነው ደግሞ የገዢው መደብ፤ ኢፍትሃዊ አሠራር መሆኑን አንዳንድ መምህራን እየገለጹ ናቸው። ምክንያቱን ሲዘረዝሩ… “በየአመቱ ፈተናው ሲሰጥ መምህራን በልዩ የአውሎ አበል ክፍያ ይመደባሉ። ይህን የክፍያ ጥቅማጥቅም መምህራኑ አይጠሉትም። ሆኖም በአሁኑ ዙር ፈተናውን እንዲከታተሉ የተደረጉት የኢህአዴግ ደጋፊ ወይም አባል የሆኑ መምህራንን መሆናቸው ቁጣ ቀስቅሷል።” ይላሉ።

Tuesday, July 5, 2016

የአቶ ሀብታሙ አያሌው ባለቤት አራሷን ስታ በመውደቋ ወደ ሆስፒታል ተወስዳለች የአቶ ሀብታሙ አያሌው ባለቤት አራሷን ስታ በመውደቋ ወደ ሆስፒታል ተወስዳለች

Habtamu Ayalew and his wife
ወጣቱ ፖለቲከኛ አቶ ሀብታሙ አያሌው ለከፍተኛ ህክምና ወደ ውጭ ሀገር እንዲጓዝና ፍርድቤት የጣለበትን ከሀገር ውጭ የመጓዝ እገዳ ያነሳል ተብሎ የተጠበቀው ችሎት “ዳኛው ቀርተዋል” በሚል ምክንያት ጉዳዩ ለሌላ ጊዜ በቀጠሮ መተላለፉን ያደመጠችው የአቶ ሀብታሙ ባለቤት እራሷን ስታ ወድቃለች።

ሰበር ዜና: ታማኝ በየነ እና ሲሳይ አጌና ለሕወሓቱ የደህንነት ሚ/ር ጌታቸው አሰፋ ደብዳቤ ፃፉ

Sisay and Tamagn beyene
የሕወሃት ደህንነት ሀገር ቤት ባሉ ቤተሰቦቻቸው አማካይነት ማስጠንቀቂያ መስጠቱን ተከትሎ አክቲቭስት አርቲስት ታማኝ በየነ እና ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ለሕወሓቱ የደህንነት ሚ/ር አቶ ጌታቸው አሰፋ ግልጽ ደብዳቤ ጻፉ:: “ማናቸውም ማሰፈራሪያና መደለያ እንዲሁም ቤተሰቦቻችንን በዕገታ መያዝ ከነጻነት ጉዞ አንዲት ስንዝር እንደማትመልሱን በተግባራዊ ርምጃዎቻችን የምትመለከቱት ይሆናል።” ያሉት ሲሳይ እና ታማኝ ” የደህንነት መስሪያ ቤት ሰራተኞች እንዲሁም የገዢው ፓርቲ ባለስልጣናት በየወላጆቻችን ቤት በመገኘትና በመጥራትበተጠቀሰው ቀን የሰጡት ማሳሰቢያ እና መደለያ እንደደረሰን እየገለጽን፣ እ ንደማንቀበል ለማረጋገጥ ይህን ለመጻፍ ተገደናል።” ብለዋል::