Translate

Saturday, September 30, 2017

ፓትርያርኩ፡- ለኢትዮጵያ የደኅንነት፣ ለምእመናን የድኅነት ሥጋት !( ዲያቆን ዳንኤል ክብረት)

Image may contain: 2 people, people sitting, beard and text
‹የክርስቶስ አንዲት በግ መከራን ስትቀበል ከማይ እኔ የበጉ እረኛ መከራ መቀበልን እመርጣለሁ›
ይህንን የተናገረው ዮሐንስ አፈወርቅ ነበር፡፡ የቁስጥንጥንያዋ ንግሥት አውዶቅስያ የአንዲት ክርስቲያን ምእመንን መሬት ወስዳ ባሰቃየቻት ጊዜ ለተግሣጽ የተናገረው ነው፡፡ እንዳለው አልቀረም አውዶቅስያ ባደረሰችበት መከራ ተግዞ በዚያው ሞትን ተቀብሏል፡፡

Friday, September 29, 2017

በሚስጢር የተያዘው ኩዴታ!!!


(አባጨብሳ ከአዳማ)
—–
የአማራ ተጋድሎ እና የኦሮሞ አብዮት በፈጠረው ምቹ ሁኔታ ኦሮሚያ አዲስ አመራር አግኝታለች። በባለፈው ክረምት በህውሃት ላይ የደረሰውን ድንጋጤ እና መዳከም ተጠቅሞ አመራሩን የጨበጠው የአባዱላ ቡድን አንድ አመት ሊሞላው ነው። የነአባዱላ ቡድን መለስ ዜናዊ ከሞተ ጀምሮ የኦፒዲኦን ሊቆጣጠር ሲሞክር የአደባባይ ሚስጢር ነው። በመጨረሻ ተሳክቶለት እጁ ሲያስገባ የቄሮ ተቃውሞ ኦሮሚያን እያናወጠ ስለነበረ ህዝብ የሰለቻቸው ከህውሃት ጋር ሲሰሩ የኖሩ ግለሰቦችን ከፊት ማስቀመጥ ፈራ። እና ብዙም የማይታወቀውን ከክልሉ ውጭ ሰርቶ የማያውቀውን ለማ መገርሳ ከፊት አስቀምጠው ኦሮሚያን ከጀርባ ሊያሽከረክሩ ታቀደ።

አዜብ መስፍን 54 ደቂቃ ሙሉ በደህንነቱ ሹም ተጋለጠች



“…የጉሊት ነጋዴዎች በላባቸው የሚያድሩ የዕለት ኑሯቸውን ለማሸነፍ የሚደክሙ እንጂ እንደነሱ የሕወሓት ባለስልጣናትና ቤተሰቦች አየር በአየር የሕዝብና የአገር ሀብት ዘርፈው በአንድ ቀን ጀምበር ሚሊየነርና ቢሊየነር አልሆኑም…አዜብም ሆነች ሌሎቹ የሕወሓት ባላስልጣናት ውሸት በመናገራቸው ልንገረም አይገባም ።

Thursday, September 28, 2017

እምቢተኝነት በተግባር!

“ሕዝቡን ካፈንከው እና ከመቃወም ሌላ አማራጭ ካሳጣኸው ይፈነዳል፤ ወጣቱ በሙሉ ዓመጽ ላይ ነው፤ ትውልድ አምጿል”። የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጠኛ JEFFREY GETTLEMAN በኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ በተነተነበት ጽሁፍ ላይ ከተናገረው። ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ

የአለም ባንክ እውነትና ኩሸት | ከኤርሚያስ ለገሰ

ሰሞኑን ይፋ የተደረገው የአለም ባንክ ሪፓርት ብዙ የሚነግረን ቁምነገሮች አሉ። በአንድ በኩል የሕውሐት አገዛዝ የገባበትን ማጥ ያሳየናል ። ይህም አገዛዙ ጊዜውን ጠብቆ ተፈጥሮአዊ ሞቱን ሊሞት መቃረቡን ሐገራዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች የሚያሳዩበት ነው። በሌላ በኩል አለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት እና ምእራባውያን በሚያካሂዱት ስውር ደባ ስርአቱን ለማስቀጠል የሚያደርጉትን አገም ጠቀም እንመለከታለን ። እነዚህ የውጭ ሐይሎች እውነትና ውሸት እየመጋገቡ የሚያቀርቡት በዚህ ምክንያት ነው። የሰሞኑ የአለም ባንክ ሪፖርት ለዚህ አባባል ጥሩ ምሳሌ አድርጌ ወስጀዋለሁ። ለዚህ ብዙ ማስረጃዎች ከሪፖርቱ ውስጥ መጥቀስ ይቻላል። ለዛሬው አንድ ኩሸት እና እውነት እንውሰድ።
ኩሸት አንድ: ” ዳታ ማጣጣም!”

Wednesday, September 27, 2017

የቀድሞ የአማራ ክልል የደህንነት ኃላፊ በርካታ ምስጢሮችን ዘረገፉ | ልደቱ አያሌውን ጨምሮ ማታ ማታ ስለሚታሰረውና ቀን ሰዎችን ስለሚያሳፍነው የግንቦት 7 ‘አባል’ የሚናገሩት አላቸው

“የአገር ውስጥ ደህንነት ሀላፊ የነበረው ወልደስላሴ በደህነት ውስጥ ቅጥል ስሙ ኦሮሞ ገዳይ እንደውም የሕወሃት አባላት የሆኑት …ገዳይ ነው የሚሉት”

“ዒላማ የተደረጉ እስረኞች መርዝ እንዲሰጣቸው ይደረጋል የውሻ መግደያን ጨምሮ ሚሰጡት መርዞች ሶስት አይነት ናቸው” 

“የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ባለሃብቶች የንግድ ተቋመኖቻቸውን፣ህንጻዎቻቸውን ለደህነቱ ድብቅ ማሰቃያነት ይፈቅዳሉ ለምሳሌ በጎንደርና በባህርዳር ካሉት ጥቂቶቹን በምሳሌ ብጠቅስ…”

“አቶ ልደቱ ከመጀመሪያም የደህነቱ አባል ነበር።  ልደቱ ብቻ ሳይሆን ለደህነት መስሪያ ቤቱ እንዲሰሩ የሚመለመሉ የተቃዋሚ መሪዎችና አባላት አሉ። አንዳንዶቹ ብዙ ካሳሰሩ በሁዋላ እኔኔም እንዳይነቃብን እሰሩኝ ይሉ ነበር”

“የአዲስ አበባ የግንቦት ሰባት አባል የነበረ ከግንቦት ሰባት የተሰጠውን ተልዕኮ ቀን ቀን ከደህነቱ ጋር ተገናኝ የተባለውን እየተገናኘ ሲያሳፍን ይቆይና  ማታ ማታ እስር ቤት ያድር ነበር በሁዋላ ተጠቅመው ሲጨርሱ ግን… በአገር ውስጥም በውጭም አሉ ተቃዋሚዎች ራሳቸውን መፈተሽ አለባቸው…”

Tuesday, September 26, 2017

ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ላይ የቀረበ ክስ

Image may contain: 1 person, standing
(ይህ ክስ በሚገባ ለህዝብ ደርሷል የሚል ግምት የለኝም። ምን አልባት ኮሎኔሉ በፀረ ሽብር አዋጁ ያውም ከ15 አመት እስከ ሞት የሚያስቀጣ አንቀፅ እንደተጠቀሰበትና ስለ ዝርዝሩንም ብዙ ሰው መረጃ ላይኖረው ይችላል። አማራ ክልል (ከጎንደር አልፎ እስከ እንጅባራ) ለነበረው ህዝባዊ ንቅናቄ ኮሌኔሉን ተጠያቂ አድርገውታል። የክሱ ዝርዝር ኮሎኔሉን ከግለሰብም በላይ አድርጎ አቅርቦታል። በሌሎች ክስ መዝገቦች የተጠቀሱ ጉዳዮችም በኮሎኔሉ ላይ ክስ ሆነው መጥተዋል። ለአብነት ያህል ወደመ የተባለው ንብረት በብዙ መዝገቦች በክስነት ቀርቧል። በሌላ ክስ መዝገብ ተከሳሽ የሆኑት የኮሚቴው ባላት እንደ አባሪ በስፋት ክሱ ላይ ስማቸው ተጠቅሷል። አላስፈላጊ የመሰለኝን የክስ ዝርዝር አላካተትኩትም።)
ለአማራ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍ/ ቤት
ባህርዳር
ቀን 25/02/ 2009 ዓም (ክስ የተመሰረተበት)
የፌ/ጠ/ዐ/ወ/መ/ቁ 157/09
የፌ/ፖ/ ወ/ መ/ቁ 04/09
ከሳሽ_ የፌ/ ጠቅላይ ዐ/ህግ
ተከሳሽ_ ኮለኔል ደመቀ ዘውዱ አየለ፣ እድሜ 45 አመት
አድራሻ _አማራ ክልል ጎንደር ከተማ ቀበሌ 18፣ የመ•ቀ _አዲስ
1ኛ ክስ
በ1996 ዓም የወጣውን የወንጀለኛ ህግ አንቀፅ 32/1/ሀ ፣ ለ ፣ 38 እና በ2001 የወጣውን የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/ 2001 አንቀፅ 3(1)፣(2)፣(4) እና (6) ስር የተመለከተውን በመተላለፍ፣

Monday, September 25, 2017

ህዝብ የሚጠየፋቸው ገዢዎች እና ክፉ በሽታቸው

ግዛቸው አበጋዝ ፤ ሳሰካችዋን ካናዳ፣መስከረም 2010
 Ethiopia, TPLF officials 
በኢትዮጲያ ታሪክ ውስጥ እንደወያኔ በህዝብ የሚጠላ ገዢ አላየሁም፤ አልሰማሁም እንዲሁም አላነበብኩም፡፡ በዚህ ወቅት ኢህአዴግን ሀገሪቱን የሚያስተዳድር መንግስት ብሎ እና ሹማምንቱን ደግሞ ህዝቡን የሚመሩ መሪዎቹን ብሎ መጥራት አይደለም መስማት ህሊናን የኮሰኩሳል፡፡ ምክንያቱም በሀገሪቷ እና በህዘቧቿ ላይ ያደረጉት እና የሚያደርጉትን ስትመለከት፡፡ ከተራ ወንበዴነት እስከ ሀገርን እና ህዝብን ለዘርፍ የመጣ የውጪ ጠላት የሚፈፅመውን ፈፅመዋል፡፡

የህወሃት አጀንዳ + የዘር ፖለቲካ + የሜንጫ ፖለቲካ – መጨረሻው ተያይዞ …

የኢትዮጵያ ህወሓት ሰራሹ “ፌደራሊዝም” ወደ ተፈራው ቀውስ እየተንደረደረ መሆኑንን የሚያሳዩ የዜና ዘገባዎች የተሰሙት ገና ከጅምሩ ነበር። በርካታ ባለሙያዎችና የተቀናቃኝ ፖለቲካ መሪዎች በተደጋጋሚ ስጋታቸውን ቢገልጹም ተቀባይነት ሊያገኙ ባለመቻላቸው የጎሣና የብሄርተኛነት በሽታ እያደር ኢትዮጵያን እየበላት አሁን ያለችበት ደረጃ አድርሷታል።

Sunday, September 24, 2017

የወደፊቱን መጠራጠርና መፍራት ካንዣበበብን አደጋ አያድነንም፤ መፍትሔው በቆራጥነት እውነታውን መጋፈጥና ትግላችንን ማጠናከር ብቻ ነው!!!

ሁላችንም ልናነበው የሚገባ ከሰማያዊ ብሔራዊ ሸንጎ የተሰጠ መግለጫ 
Image may contain: 2 people

(ከሰማያዊ ብሔራዊ ሸንጎ የተሰጠ መግለጫ)

ዛሬ በሀገራችን ከላያችን በተጫነው አገዛዝ ምክንያት በዜግነታችን እና በሉዓላዊነታችን ላይ ያልተጋረጠ የችግር ዓይነት የለም፡፡ የችግሩ ስፋትና ጥልቀት ከሀገር መፍረስ አደጋ ጀምሮ እስከ ዘር ፍጅትና የማያባራ የእርስ በእርስ ጦርነት ይደርሳል፡፡ በእነዚህ ችግሮች ፍርሃትና ጭንቀት ውስጥ ሆነን ምንም ሳናደርግ በየዕለቱ በአገዛዙ አረመኒያዊ ተግባር በዜጎች ላይ የተፈፀመው ግድያ፣የጅምላ እስር እና መፈናቀል በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ጥልቅ ሀዘንና የልብ ስብራት ጥሎ አልፏል፡፡

Friday, September 22, 2017

‘አጃኢብ’ ያሰኘው የአዜብ መስፍን ወሬ

ክንፉ አሰፋ
Azeb Mesfin on Zami Radio
“አከ’ሲ” አለ ያገሬ ሰው፣ ከሰሞኑ ‘አጃኢብ’ ያሰኘውን የአዜብ መስፍን ወሬ ሲሰማ። አዜብ ልምድ ያላት ውሸታም እንጂ ልምድ ያላት ኮሜዲ አትመስልም ነበር። ከሚሚ ስብሃቱ ጋር በያዝነው ሳምንት የተወኑት ድራማ ግን ጦሽ አርጎ ያስቃል። መቼም ጥርስ እንጂ ልብ አይስቅ። ፈንድሻም’ኮ ልቧ እየተቃጠለ ነው ፊትዋ ሚፈካው።

ወይዘሮ አዜብ መስፍን በድጋሚ ሙልጭ ያልኩ ደሃ ነኝ አሉ

 የቀድሞ የህወሓት መሪ አቶ መለስ ዜናዊ ባለቤት ወይዘሮ አዜብ መስፍን ምንም የሌላቸው ደሃ መሆናቸውን በድጋሚ ተናገሩ፡፡ በሀገር ውስጥ ከሚገኝ አንድ የሬድዮ ጣብያ ጋር ቃለ መልስል ያደረጉት ወይዘሮ አዜብ መስፍን፣ ስማቸው ከሙስና ጋር ተያይዞ መነሳቱም አግባብ እንዳልሆነ ገልጸዋል፡፡ ከዚህ ቀደም ከሙስና ጋር በተያያዘ ስማቸው ሲነሳ እንደነበር ያስታወሱት ወይዘሮዋ፣ ይህ ጉዳይ ጋዜጠኞች ያናፈሱባቸው ወሬ እንጂ ትክክለኛ ነገር እንዳልሆነ በቃለ ምልልሳቸው ወቅት ተናግረዋል፡፡ ወይዘሮዋ ከዚህ ቀደም በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ ደሃ በመሆናቸው ልጆቻቸውን የሚያስተምሩት የእሳቸውን እና የባለቤታቸውን ደሞዝ አጠራቅመው እንደሆነ መናገራቸው ይታወሳል፡፡
‹‹በሙስና የሚጠረጠር ሀብት ካለኝ ምድረ ጋዜጠኛ ያጋልጥና የኢትዮጵያ ህዝብ ይውረሰው፡፡›› በማለት የተናገሩት ወይዘሮ አዜብ መስፍን፣ እንዲህ ዓይነቱ ወሬ የሚናፈስባቸው ለምን እንደሆነ ግራ እንደሚያጋባቸውም አክለው ገልጸዋል፡፡ ወይዘሮ አዜብ ባለቤታቸው ከማለፋቸው አስቀድሞ በሰጡት አንድ ቃለ ምልልስ ላይ፣ ልጆቻቸውን የሚያስተምሩት እሳቸው እና ባለቤታቸው የሚያገኙትን የመንግስት ደሞዝ እያጠራቀሙ እንደሆነ ተናግረው ነበር፡፡ ሆኖም ከወይዘሮ አዜብ ሶስት ልጆች ሁለቱ ማለትም ሰምሃል መለስ ዜናዊ እና ሰናይ መለስ ዜናዊ በአሜሪካ እና በእንግሊዝ በሚገኙ ውድ ዩኒቨርሲቲዎች የተማሩ ናቸው፡፡

Wednesday, September 20, 2017

አቶ አባይ ጸሀዬ ለሕክምና ከሀገር መውጣታቸው ተሰማ

Image may contain: 1 person, sitting

(ኢሳት ዜና–መስከረም 10/2010) በኢትዮጵያ ውስጥ በሚካሄደው ሌብነት በግንባር ቀደምትነት ሲጠቀሱ የነበሩትና ከሀገር እንዳይወጡ እገዳ ተጥሎባቸው የቆየው አቶ አባይ ጸሀዬ ለሕክምና ከሀገር መውጣታቸውን ምንጮች ለኢሳት ገለጹ።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ራሳቸውን በኮሚቴ ያደራጁ የትግራይ ምሁራንና የሀገር ሽማግሌዎች በሌብነት ላይ የተጀመረው ዘመቻ እንዲቆምና የታሰሩትም እንዲፈቱ መጠየቃቸው ተሰምቷል።

የቴዲ አፍሮ ጉዳይ እና የካናዳው ፓርላማ አባል ለፕሬዝዳንት ሙላቱ የጻፉት ግልጽ ደብዳቤ – አሉላ ከበደ (ቪኦኤ)

“ኢትዮጵያ በየጊዜው ከፍተኛ መጠን ያለው እርዳታ ከካናዳ መንግስትና ሕዝብ ታገኛለች። በቅድሚያ ያ እርዳታ በረሃብ አለንጋ ለሚገረፉት ለእነኚያ ለታሰበላቸው ተረጂዎች መድረሱንና የሰዎች መብት መጠበቁን ማረጋገጥ እንሻለን። በእርግጥ የምናየው የሰብዓዊ መብት ረገጣ ግን በተዘዋዋሪም ቢሆን ያን ዓይነት አመኔታ እንድናሳድር የሚያግዝ አይደለም።” ለኢትዮጵያው ፕሬዝዳንት ሙላቱ ተሾመ ግልጽ ደብዳቤ የጻፉት የካናዳ ፓርላማ አባል አሌክስ ናዳል።

Tuesday, September 19, 2017

ግዜ እየጠበቀ የሚፈነዳው የመለስ ቦንብ (ይገረም አለሙ)

ይገረም አለሙ
ye meles zskrenአንተ መለስ ዜናዊ ነፍስህን አይማረው- እግዚአብሄር ይይልህ
ቀብረህ በሄድከው ቦንብ ታጫርሰናለህ፤
ሰሞኑን ከምሥራቁ የሀገራችን አካባቢ የምንሰማው ወሬ  ሰው ለሆነ ፍጡር ሁሉ ለአእምሮ የሚከብድ ነው፡፡ ሁል ግዜ ነገሮች አዲስ ለሚሆኑባቸው ትናንትን በመርሳት ስለነገም በማሰብ ለማይደክሙ ለእለት ለእለቱ ብቻ ለሚጮሁት ካልሆነ በስተቀር ይህ አሁን እየተፈጸመ ያለው ነገር መች እንደሚሆን ለማወቅ አልተቻለ ካልሆነ በስተቀር አንድ ቀን  ያውም ከዚህ በከፋ መልኩ ሊፈጸም እንደሚችል ወያኔ ሥልጣን በያዘ ማግስት የተረዱ ብዙዎች ነበሩ፡፡ ጩኸዋል፣  ስጋታቸው ገልጸዋል፣ ፍራቻቸውን ሊያጋሩን ሞክረዋል፡ማን ሰምቶ እንጂ፡፡

የህወሓት ፕሮግራም፤ የመለስ ሌጋሲ – ዜጎችን ማፈናቀል፤ ማጋደል!

ገና ከመነሻው በበረሃ ያወጣው ፕሮግራሙ በግልጽ እንደሚያመለክተው የህወሓት ዋንኛ ዓላማ ኢትዮጵያን አዳክሞና በጎሣ ከፋፍሎ ትግራይን ታላቅ በማድረግ ሪፑብሊክ መመሥረት ነው። ባለፉት 26 ዓመታት ይህንን ለማሳካት በኢትዮጵያ ውስጥ ያልፈነቀለው የጎሳ ድንጋይ የለም፤ ያላጋጨው ሕዝብ፤ ያላጋደለው ወገን የለም፤ ትግራይን ሳይጨምር!

Sunday, September 17, 2017

የቅማንት ካርድ (መሳይ መኮንን)

መሳይ መኮንን
Gondar, Qimant election
ዛሬ የሰሜን ጎንደር ሰማይ ያረገዘው ዳመና ምን ሊያዘንብ እንደሚችል አይታወቅም። ህዝብ አማራ፡ቅማንት የሚል ልዩነት ሳይገድበው ግልብጥ ብሎ ወጥቶ ድምጹን እየሰጠ ነው። አንድን ሰው ለሁለት እንደመክፈል የተቆጠረው፡ ስጋና አጥንትን የመለያየት ያህል የተወሰደው ህዝበ ውሳኔ ህወሀት ስለፈለገው ብቻ እየተካሄደ ነው። የህዝቡ አንድነት የሚያስደስት ቢሆንም ውጤቱ የሚወሰነው በህወሀት በሚመራው ምርጫ ቦርድ ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ምርጫ የሚባል ነገር ከተጀመረ አንስቶ አሸናፊ የሚሆነው ድምጽ የሚሰጠው ሕዝብ ሳይሆን ድምጹን የሚቆጥረው አካል ነው። ያ ደግሞ ህወሀት ነው።

Friday, September 15, 2017

የትግራይ ህዝብ ሆይ አገርና ህዝብ እያጠፉ ላሉት ልጆችህ መሸሸጊያ ዋሻነትህ ይብቃ



No automatic alt text available.
መስከረም 5 ቀን 2010 ዓ• ም
ወልቃይት፣ አማራ
ኢትዮጵያ
********
የተከበርከውና ኢትዮጵያን ከሌሎች ወንድሞችህ ጋር በመሆን ለዘመናት ከወራሪ በመጠበቅ ታላቅ ውለታ የሰራኸው የትግራይ ህዝብ ሆይ ስማኝ፣ ልጆችህ ክደውሃል፣ ልጆችህ ለዘመናት በሰላምና በፍቅር ከኖርክበት ኢትዮጵያዊ ማንነትህ አፋተውሃል፣ ልጆችህ አባቶችህ ያቆዩልህን የባህር በር አሳጥተውሃል፣ ልጆችህ በመላዋ ኢትዮጵያ በነፃነትና በፍቅር ተዘዋውረህ የምትኖርበትን የነገ የከበረ ኢትዮጵያዊ አንድነት ንደው አንተን ከኢትዮጵያዊ ከፍታ አውርደው በትግራይ ምድረ በዳ የዘር ቡትቶ አልብሰው ያንከራትቱሃል፣ ልጆችህ በደምና በክህደት በተጨማለቀ ማንነት የመንግስተ ሰማያት ኑሮ ሲኖሩ አንተ ነገ ምን ይዞ ይመጣ ይሆን በሚል ፍርሃት ታስረህ ትሰቃያለህ፣

Thursday, September 14, 2017

ህልውናውን በህዝቦች ቅራኔ ላይ የገነባ ዘረኛ ቡድን (በያሬድ አውግቸው)

በያሬድ አውግቸው
Ethiopia, TPLF officials
“Whoever sows injustice will reap calamity.”
በአሁኑ ወቅት የህወሃት  ዋነኛ  ስራ  በህዝቦች መካከል ቅራኔዎችን መፍጠር የሚመስልበት ደረጃ ላይ ደርሰናል። እንደ ጥሩ ምግባር ለቅራኔዎችም እቅድ ተዘጋጅቶና በጀት ተመድቦ  የህዝቦች ደም ሲፈስ ይታያል። ለዚህም የወቅቱ የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ልዩ ሃይልና የአጎራባች የኦሮሚያ ወረዳዎች ነዋሪዎች መካከል ያለው ጦርነት መሰል ግጭት አንዱ ማሳያ ነው።  ግጭቱ በመንግስት ዝም ባይነት አንዳንዴም መሪነት ሲቀጣጠል የወቅቱ አደገኛ ደረጃ ላይ ደርሶአል። ይህ ክስተት ለብዙዎች ግራ አጋቢ ሆኖ ቆይቶአል። 

ከወልቃይት ጠገዴና ጠለምት የአማራ ብሄር የማንነት ጉዳይ አስተባባሪ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ

ሸክሙን ሲፈሩ መደላድሉን!!

መስከረም 1 ቀን 2010ዓ/ም
Map of Gondar, Ethiopia
የገዥው ቡድን በኃይል አዳፍኖ ለመያዝ የሞከረው ድንገት እንደ እሣተ ገሞራ የፈነዳውና ከአንድ ዓመት በላይ በመላው ኢትዮጵያ በተለይም “የአማራ ክልል” በሚባለው ለገዥው ቡድን የእግር እሣት የሆነበትና ሀገሪቱ ለአንድ ዓመት ያህል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ ያስገደደው አላስቀምጥ አላስተኛ ያለው እርስ በርሳቸው እንዳይተማመኑ በጥርጣሬ እንዲተያዩ ያደረገው፤ የአማራን ተጋድሎ የወለደው የወልቃይት ጠገዴና ጠለምት የአማራ ብሔር የማንነት ጉዳይ አስተባባሪ ኮሚቴ ራሳቸው በጻፉት ሕገ- መንግሥቱ በሚፈቅደው መሠረት አንቀጽ 39 ንኡስ አንቀጽ 5ን መሠረት በማድረግ ያቀረቡትን ሕጋዊና ሕገ መንግሥታዊ የመብት ጥያቄ እንደ ሆነ የአደባባይ ምሥጢር ነው።

Wednesday, September 13, 2017

የአርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ፣ አንደኛ መደበኛ ጉባኤን በሚመለከት የወጣ መግለጫ፣

Image may contain: one or more people and people sittingImage may contain: 2 people
የአርበኞች ግንቦት 7፣ ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ንቅናቄ፣ ከጳጉሜ 1 ቀን 2009 ዓ.ም ጀምሮ እስከ መስከረም 1 ቀን 2010 ዓ.ም ድረስ ባደረገው የመጀመሪያው ጉባኤ፣ የሀገራችንን ወቅታዊ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣የማህበራዊ ሁኔታዎችንና በአሁኑ ሰዓት የሚትገኝበትን የደህንነት ስጋት በስፋትና በጥልቀት ፈትሿል። በፍተሻው ሀገራችን ኢትዮጵያ በረጅም ታሪኳ የገጠሟት እጅግ ፈታኝ ወቅቶች እንዳሉ አስታውሶ፤ በአሁኑ ወቅት የምትገኝበት ሁኔታ ግን ከዚህ በፊት ገጠሟት ከነበሩ አስቸጋሪ ሁኔታዎች ሁሉ እጅግ የከፋ እንደሆነ ጉባኤው ድምዳሜ ላይ ደርሷል። አገራችን አሁን ለደረሰችበት አሳዛኝ አደጋ ደረጃ ላይ ለመድረስ ዋነኛው ምክንያት ላለፉት 26 ዓመታት በወያኔ የበላይነት የተዘራው መርዛማ የዘር ፖለቲካ መሆኑን አረጋግጧል።
በአሁኑ ወቅት የወያኔ መርዛማ የዘር ፖለቲካ በተለያዩ የህብረተሰቡ ክፍሎች ውስጥ የዘራው የጠላትነት፣ የፍራቻና የጥርጣሬ ወረርሽኝ በራሱና የህወሀት/ኢህአዴግ ግንባር ድርጅቶች ውስጥ ጭምር ገብቶ፣ እርስ በእርስ በውስጥ ሽኩቻ እና የግንባር ድርጅቶቹ ደግሞ ከሌሎች የግንባር ድርጅቶች ጋር ወደ ጥፋት ጎዳና በፍጥነት በሚጓዝ የትንንቅ ሂደት ውስጥ ገብተዋል። የሀይለማሪያም ደሳለኝ አሻንጉሊት መንግስትም ለዚህ የጥፋት ሂደት፤ የአጋፋሪነት ሚናን በመጫወት ላይ ይገኛል። ይህ ሂደት በምን ሁኔታ ሊጠናቀቅ እንደሚችልና ሊያስከትል የሚችለውም እጅግ አስፈሪ ሀገራዊ ሁኔታ ጉባኤውን እጅግ አሳስቦታል።

Saturday, September 9, 2017

መንግስት ከህወሓት የንግድ ድርጅቶች የመኪና ግዢ ሊፈጽም ነው

Image may contain: 4 people, people smiling, outdoor
መንግስት ከህወሓት የንግድ ድርጅቶች የመኪና ግዢ ሊፈጽም መሆኑ ታወቀ፡፡ ሰሞኑን በስራ ላይ የዋለው የመንግስት መመርያ አስቀድሞ የነበረውን የመኪና ግዥ ስርዓት አፍርሶ በአዲስ ተክቶታል፡፡ በአዲሱ የመንግስት መኪና መግዣ ህግ እና ደንብ ስርዓት መሰረት፣ ከዚህ በኋላ መኪና መገዛት ያለበት ከውጭ ሀገር ሳይሆን ከሀገር ውስጥ እንዲሆን ተደንግጓል፡፡ አሁን ባለው የሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ መኪና የመገጣጠም እና የማምረት ኢንዱስትሪውን ተቆጣጥረው የያዙት የህወሓት የንግድ ድርጅቶች በመሆናቸው፣ መንግስት መኪና ሊገዛ የሚችለው የግድታ ከህወሓት ድርጅቶች መሆኑን መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡

Thursday, September 7, 2017

ሳባ (የአባይ ጸሐዬ የእንጀራ ልጅ) ከ’ወዛመይ’ እስከ በቻይና የሚገኘው የኢትዮጵያ ሬስቶራንት ባለቤትነት * ከሞላ አስገዶም ጋር ምን ታደርጋለች?


ሳራ ከሞላ አስገዶምና ከጓደኞቹ ጋር በመሸታ ቤት










 ከውስጥ አዋቂ ለዘ-ሐበሻ የተላከ መረጃ
በሕወሓት ውስጥ የተፈጠረው መፈረካከስ ያሰጋቸው ባለስልጣናት ልጆቻቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን ወደ ውጭ ማሸሹን ተያይዘውታል:: በሙስና እስር ስጋት ውስጥ ያሉት አስራ ሁለቱ የአባይ ጸሐዬ ልጆች አሜሪካ ገብተዋል:: በሃገር ቤት የቀጠለው እርስ በ እርስ የሕወሓቶች መበላላት ጉዳዩ እስኪረጋጋ እዚህ ይቆያሉ:: ካልተረጋጉም እዚህ ያፈሩትን ንብረት ይዘው ይቀጥላሉ::
ከአባይ ጸሐዬ ልጆች መካከል አንዷ ቢቢ አንዷ ናት:: በአዲስ አበባ የ7 ህንጻዎች ባለቤት ናት:: በ እናት ከምትገናኛትና ለአባይ ጸሐዬ የ እንጀራ ልጅ ሳባ ወርቁ ጋር አብረው ዱባይ ቆይተው ሳባ ወደ ቻይና እንዲሁም ባቢ ከ12ቱ እህት ወንድሞቿ ጋር አሜሪካ ትገኛለች::(አቡዳቢ  ውስጥ ስለነበረውና ስላለው ጉዳይ ወደፊት ሰፋ ያለ መረጃ ይቀርባል)

ዜና ጎንደር – ህዝቡ የአፀፋ እርምጃ እየወሰደ ነው

አስናቀው አበበ – ጳጉሜ 2 2009
ጳጉሜ 1 2009 እለት ጎንደር በአድዛ እና ሎዛ ቀበሌወች የወያኔ በአርራና ቅማንት ስም የተደገሰ ህዝብ ከፍፋይ ምርጫ ምዝገባውን ለማስፈፀም የሄዱ ሆምዳ ባለስልጣናት ላይ ህዝቡ የቅጣት እርምጃ ወስዶባውልዋ። ባንዳወቹ ተደብድበው መኪናቸው ተሰባብሯል። ከተመቱት ውስጥ ፖሊስ እና ከጎንደር የሄደች አቃቢ ህግ እንደምትገኝበት ታውቋል።
ትናንት ከሰሜን ጎንደር ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ስለምርጫው ለመዘገብ እና ሁኔታውን ለማየት ሄደው ነበር። አጋጣሚ ለቅሶ ስለነበር ከደንቢያ ጭልጋ እና ላይ አርማጭሆ የመጡ ሰወች ነበሩ። በምርጫው እጅግ ተበሳጭተው ስለነበር መኪናው ላይ ጥቃት አድርሰዋል። የመኪናው መስታውት ሙሉ ተሰባብሯል። የሄዱትም ተላላኪ ተሿሚወች ተደብድበዋል። የቀበሌው ሰወች የተበሳጩበት ምክኒያት ምርጫ የሚካሄዱበት ቦታወች አማራ የሚኖርበት ከመሆኑ አልፎ ለምን ህዝቡን ሊከፋፈሉ መጡ በማለት ነው።
አማራውን በማፅዳት የቅማንት የራስ አስተዳደርን ለማስፈን ወያኔ የያዘውን የመለያየት ተንኮል የተረዱና የተቃወሙ የብአዴን የአካባቢው ባለስልጣን የነበሩ ከአመራርነት እየተነሱ መሆናቸው ታውቋል።

አስራ ሁለቱ የአባይ ጸሃዬ ልጆች ወደ ውጭ እንዲሸሹ ተደረገ

 በሙስና ወንጀል ውስጥ እጃቸው አለበት እየተባለ የሚነገረው አቶ አባይ ጸሃዬ ልጆቻቸውን በሙሉ ወደ ውጭ እንዲሸሹ ማድረጋቸውን ከታማኝ ምንጮች የተገኘ መረጃ ለማረጋገጥ ችለናል።
የውጩን ንግድ በሞኖፖል ይዘውት የነበሩት የአባይ ልጆች በአሁን ሰዓት በአሜሪካን ሃገር ውስጥ እንደሚገኙ የተጠቆመ ሲሆን ከሚኖሩበት ስፍራ ሰው በቀላሉ እንዳያጘኛቸው ማህበራዊ ገጾቻቸውን እና ስልኮቻቸውን አጥፍተዋል።
የአስራ ሁለት ልጆች አባት የሆኑት አቶ አባይ ጸሃዬ ከኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን 77  ቢሊየን ብር በማባከን የሚጠቀሱ ሙሰኛ ቢሆኑም እስካሁን ተይዘው ሊጠየቁ ግን አልተቻለም። አቶ አባይ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ በፌደራል ጉዳዮች እና በስኳር ኮርፖሬሽን ውስጥ በሃላፊነት ሲሰሩ የዘረፉትን የሀዝብ እና የሃገር ገንዘብ በልጆቻቸው እና በሚስታቸው ስም በህገወጥ ንግድ ላይ ማዋላቸውንም የደረሰን መረጃ ይጠቁማል።
ከአባይ ጸሃዬ ልጆች ውስጥ ትንሽዋ፣ ቤቢ የተባለችው ልጃቸው በአዲስ አበባ ብቻ 7 ሕንጻዎች  ያላት ሲሆን፤ በዱባይ እና በአሜሪካም ትላልቅ ህንጻዎች እና የንግድ ተቋማት እንዳላት ምንጮቹ ገልጸዋል።  ጤፍ፣ በርበሬ፤ እንጀራ፣ ወዘተ  ወደ አውሮፓ እና ሰሜን አሜሪካ የሚላኩ የእርሻ እና የባልትና ውጤቶች በሙሉ የተያዙት በአባይ ጸሃይ ልጆች መሆኑንም ካገኘነው መረጃ ለመረዳት ችለናል።

Wednesday, September 6, 2017

በምስራቅ ሐረርጌ በአንድ ትምህርት ቤት ላይ በተወረወረ ቦምብ በርካቶች ቆሰሉ

(BBN) በምስራቅ ሐረርጌ ሜኢሶ በአንድ ትምህርት ቤት ላይ በተወረወረ ቦምብ በርካቶች ቆሰሉ፡፡ ከስፍራው የተገኘው መረጃ እንደጠቆመው፣ ቦምቡ የተወረወረው በአካባቢው ጥቃት እያደረሰ በሚገኘው የሶማሊያ ክልል ልዩ ኃይል አማካይነት ነው፡፡ የሶማሊያ ክልል ልዩ ኃይል፣ ባለፉት ተከታታይ ቀናት በምስራቅ ሐረርጌ ሜኢሶ በጦር መሳሪያ የታገዘ ጥቃት ሲፈጽም ቆይቷል፡፡ ከኦሮሚያ ክልል መንግስትም ሆነ ከፌደራሉ መንግስት ምንም ዓይነት ከለላ ያላገኘው የአካባቢው ነዋሪ፣ ባለው አቅም ራሱን ከጦሩ ለመከላከል የአልሞት ባይ ተጋዳይ ትግል እያደረገ ይገኛል፡፡
የአካባቢው ማኅበረሰብ ራሱን ለመከላከል እያደረገ ባለው የአጸፋ ምላሽ የተቆጣው የሶማሊያ ልዩ ኃይል፣ ቦምቡን በትምህርት ቤቱ ላይ እንደወረወረው ከአካባቢው ነዋሪዎች ገለጻ ለመረዳት ተችሏል፡፡ አስተያየታቸውን የሰጡ የአካባቢው ነዋሪዎች ድርጊቱን ‹‹የበቀል እርምጃ›› ሲሉ ገልጸውታል፡፡ የእጅ ቦምቡ ወደ ትምህርት ቤቱ ከተወረወረ በኋላ በርካቶችን ያቆሰለ ሲሆን፣ በጽኑ የቆሰሉት ደግሞ አምስት ህጻናት መሆናቸውን ለመረዳት ተችሏል፡፡ ሌሎችም የጥቃቱ ሰላባ መሆናቸው ታውቋል፡፡

Monday, September 4, 2017

ለብቻው ቤተ-መንግስቱን ያንቀጠቀጠ ብላቴና፣ ቴዲ አፍሮ (ክንፉ አሰፋ)

ክንፉ አሰፋ
Teddy Afro the best Ethiopian singer
በነዚያ የነጠቡ ብዕሮች “ተራራውን ያንቀጠቀጠ” እየተባሉ ሲወደሱ የነበሩ ሁሉ እነሆ በአንድ ብላቴና ሲንቀጠቀጡ ከማየት የበለጠ ምስክር ከየትም ሊመጣ አይችልም። የ”ኢትዮጵያ” ስም ሲጠራ ብርክ እንደያዘው የሚሽመደመዱ፤ አንድ፣ ሁለት፣ ሶስት እየልን በጣት የምንቆጥራቸው የጥላቻና የበቀል ጉግማንጉጎች ለመሆናቸውም ትውልድን ደፍሮ ይናገርላቸዋል።  የዚህ ቡድን አባላት  ከመጠን ያለፉ ጭቃዎች መሆናቸውን እንኳ ለማወቅ ራሳቸውን በመስታወት የሚመለከቱ አይመስልም።