Translate

Thursday, September 7, 2017

ሳባ (የአባይ ጸሐዬ የእንጀራ ልጅ) ከ’ወዛመይ’ እስከ በቻይና የሚገኘው የኢትዮጵያ ሬስቶራንት ባለቤትነት * ከሞላ አስገዶም ጋር ምን ታደርጋለች?


ሳራ ከሞላ አስገዶምና ከጓደኞቹ ጋር በመሸታ ቤት










 ከውስጥ አዋቂ ለዘ-ሐበሻ የተላከ መረጃ
በሕወሓት ውስጥ የተፈጠረው መፈረካከስ ያሰጋቸው ባለስልጣናት ልጆቻቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን ወደ ውጭ ማሸሹን ተያይዘውታል:: በሙስና እስር ስጋት ውስጥ ያሉት አስራ ሁለቱ የአባይ ጸሐዬ ልጆች አሜሪካ ገብተዋል:: በሃገር ቤት የቀጠለው እርስ በ እርስ የሕወሓቶች መበላላት ጉዳዩ እስኪረጋጋ እዚህ ይቆያሉ:: ካልተረጋጉም እዚህ ያፈሩትን ንብረት ይዘው ይቀጥላሉ::
ከአባይ ጸሐዬ ልጆች መካከል አንዷ ቢቢ አንዷ ናት:: በአዲስ አበባ የ7 ህንጻዎች ባለቤት ናት:: በ እናት ከምትገናኛትና ለአባይ ጸሐዬ የ እንጀራ ልጅ ሳባ ወርቁ ጋር አብረው ዱባይ ቆይተው ሳባ ወደ ቻይና እንዲሁም ባቢ ከ12ቱ እህት ወንድሞቿ ጋር አሜሪካ ትገኛለች::(አቡዳቢ  ውስጥ ስለነበረውና ስላለው ጉዳይ ወደፊት ሰፋ ያለ መረጃ ይቀርባል)

ትናንት በዘገባዎች ላይ ሳባ የአባይ ጸሐዬ ልጅ ተብላ ከተለጠፈች በኋላ የሥርዓቱ ሰዎች “ሳባ የአባይ ልጅ አይደለችም” ለማለት ቃትቷቸው ነበር:: የእንጀራ አባት እንደ አባት ካልተቆጠረ አዎ አባቷ ላይሆን ይችላል:: ግን የአባይ ጸሐዬ ልጅ እህት ናት:: ለዚህም ነው ስለዚህች ወጣት ሚሊየነር ነገሮችን መረጃዎችን እንድንፈለፍል ያደረገን::
  ወዛመይ የተሰኘው የዳዊት ነጋ የሙዚቃ ክሊፕ ትግራይ ውስጥ የሚገኘው መኖሪያ ቤቷ ተቀርጿል:: በክሊፑ ላይም ተውናለች:: በጓደኞቿ ዘንድ “የወርቅ ዘር” በሚል የምትታማው ሳባ ቴዎድሮስ አድሃኖም የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተርነትን ካሸነፈ በኋላ ሳቢና የተሰኘው ሬስቶራንት በቻይና የተሰኘ የኢትዮጵያ ሬስቶራንት ቻይና ውስጥ ተከፍቶላታል::
የኢትዮጵያ ሕዝብ ሃብትና ንብረት በየመሸታ ቤቱ አርቲስቶችን በመጋበዝ ይበተናል::
ቻይና በርካታ የሕወሃት ባለስልጣናት ልጆች እንደሚማሩ ይታወቃል:: በዚሁ ቻይና ውስጥ አምባሳደር ሲሾም እንኳ የሚሾመው ከሕወሓት ተመርጦ ነው:: በቻይና የተለያዩ ኢትዮጵያውያን ነጋዴዎች ይመላለሳሉ:: ይህ ሬስቶራንት ነጋዴዎች የሚሰለሉበት እንደሆነ የሚናገሩት የውስጥ ምንጮች ከኢምባሲው ጋር ብዙ የሚሰራቸው ምስጢራዊ ጉዳዮች እንዳሉ ምንጮቹ ይናገራሉ:: አብዛኞቹም የሚሰሩት ምስጢራዊ ነገሮች እናንተ አንባቢዎች የምትገምቱት ዓይነት ነው::
ሳባ ከተለያዩ ኢትዮጵያውያን አርቲስቶች ጋር ግንኙነት አላት:: በሃገር ቤት አርቲስቶችን ባገኘች ቁጥርም በየመሸታ ቤቱ ጋባዥ እርሷ ናት:: ዱባይ በነበረችበት ወቅትም ተዋቂ ሰዎች እዚያ ሲመጡ ተቀባይና ሃገር አሳይ በመሆን ጀርባቸው ምን እንዳለ የምታጠናው እርሷ ነበረች እየተባለ በሰፊው መረጃዎች ይነገሩባታል::
ሳባ መቀሌ በነበረችበት ወቅት
ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ የገባው የትህዴን መሪ ሞላ አስገዶም ጋርም በተደጋጋሚ በየመሸታ ቤቱ መታየቷን የሚናገሩት ምንጮቹ ፎቶዎችን አስደግፈው ልከዋል:: ከሞላ ጋር የነበራቸው ግንኙነት እስከምን ድረስ እንደሆነ የሚታወቅ ባይሆንም ሆኖም ግን አብረው በብዛት ታይተዋል::
ሳባ ዛሬ በስሟ ቻይና ውስጥ ሬስቶራንቱን ተከፍቶላት እየሰራች ነው:: የወደፊቱ የሕወሓት መሪዎች መኖሪያ በምትባለው ቻይና እንዲህ ያለው ሬስቶራንት መከፈቱ ጥቅሙ ለሕወሓት ሰዎች ሳይታለም የተፈታ ነው::
ቻይና ለንግድ የሚሄዱ ከሕወሓት ጋር ንክኪ የሌላቸው ነጋዴዎች ሊያስቡበት የሚገባውን ጉዳይ እዚህ ጋር ጠቆም አድርገናል::
__________________________
ተጨማሪ መረጃዎችን እያሰባሰብን ለሕዝብ እናቀርባለን::
በሌሎችም የውጭ ሃገራት የሚገኙ የህወሃት ባለስልጣናት ንብረቶችና መረጃዎች እየደረሱን ሲሆን እያጣራን ማቅረባችንን እንቀጥላለን::

1 comment:

  1. The best lie of the year!!! It just dhows how deep you succumbed in despaier, and how detached you are with the country you claim are from.

    ReplyDelete