Translate

Tuesday, May 29, 2018

በአዲስ አበባ፣ አውሮፓና አሜሪካ ለ“ዘመቻ ዓቢይ” የስውር ምልመላ ተጀምሯል!

የ“ዘመቻ ዓቢይ” - አዝማቾችን ዓቢይ ያውቋቸዋል?



  • ኃይሌ ገብረሥላሴ መልማይ መሆኑ ታወቀ
የሰሜን አሜሪካ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በዳላስ ሊያካሂድ ያሰበው ሰላሳ አምስተኛ የስፖርት ፌስቲቫል ከወዲሁ እጅግ ጥንቃቄ በሚያሻው ጉዳይ ተወጥሯል። የጎልጉል የመረጃ አቀባዮች እንዳሉት በአገር ውስጥ፣ በአሜሪካና በአውሮፓ የሕዝብ ግንኙነት የሚሠሩ ክፍሎች በምሥጢር እየተመለመሉ ነው። ኃይሌ ገብረሥላሴ አገር ውስጥ ሆኖ ይህንኑ የምልመላ ሥራ እየሠራ ነው። አነጋጋሪ የሆነው ይህንን ዘመቻ የሚያከናውኑት ክፍሎች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ እውቅና ይኑራቸው አይኑራቸው አለመታወቁ ነው።

Wednesday, April 4, 2018

ቀጣዬ 100 ቀናት!(ኤርሚያስ ለገሰ)

Ermias Legesse, author and ESAT TV and Radio contributor
መንደርደሪያ
የትግራይ ነፃ አውጪ በገጠመው ሕዝባዊ ማእበል፣ እንዲሁም የሕዝቡን ተቃዉሞ በተከተለበት ጫና ዶክተር አቢይን ወደ ጠቅላይ ሚኒስትርነት አምጥቷል። የዶክተር አቢይ ወደ ፊት መምጣት በብዙ መልኩ የተደበላለቀ ስሜቶችን ፈጥሯል። በህውሓት ደጃፍ ከፍተኛ ቁዘማና ንዴት የፈጠረ ሲሆን በለውጥ ፈላጊው ዘንድ የተከፋፈለ አስተያየቶች በመስተናገድ ላይ ናቸው። በተለይም ዶክተሩ በበአለ ሲመቱ እለት ያቀረበው ንግግር የብዙ ኢትዬጲያውያንን አንጀት ቅቤ ያጠጣ ነበር። በታሪካዊነቱም ተመዝግቧል።

Sunday, March 18, 2018

ዛሬ ልወቅስ ነው፣ ራሴን ጨምሬ…

መሳይ መኮንን
Waldeba monastery priests, political prisoners in Ethiopia.
ዛሬ ልወቅስ ነው። ራሴን ጨምሬ በጽሁፍ ጅራፍ ልጋረፍ ነው። በእውነት ይህን ጽሁፍ ስሞነጫጭር ውስጤ በእልህና ቁጭት ድብን እያለብኝ ነው። በዚህም አሰብኩት። ወደዚህም ወሰድኩት። አገለባብጬ ተረጎምኩት። ዝምታችን ከፍርሃት በቀር ምክንያታዊ አልሆንልህ አለኝ። መቼም የትግራዩ አገዛዝ ስልጣን ላይ ከወጣ በኋላ የሞራል ልኬታችን ፈሩን ስቷል። የህሊና ፍርዳችን ተዛብቷል፡፡ ሰው የመሆን ሚዛናችን ጎድሏል።

Tuesday, March 13, 2018

የነዳጅ አቅርቦት ማስተጓጎል ዘመቻ()

Mesay Mekonnen, ESAT journalist
መሳይ መኮንን
ቄሮ ቃሉን አያጥፍም። ባለፉት ሁለት ዓመታት በቄሮ ተጠርቶ ያልተሳካ የአድማም ሆነ የተቃውሞ ሰልፍ ከነበረ አላስታውስም። ከሁሉ የሚደንቀኝ በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት፡ የኦሮሚያን ክልል ከዳር እስከዳር ባናወጠው ህዝባዊ እምቢተኝነት በቄሮዎች እጅ ህይወቱን ያጣ ሰላማዊ ሰው አለመኖሩ ነው። የሚጠራው አድማ፡ የሚካሄደው ዘመቻ፡ የሚወሰደው እርምጃ የአገዛዙን የማፈናና የመግደል አቅም ከማላሸቅ ያለፈ የትኛውንም የህብረተሰብ ክፍል ለጉዳት የዳረገበት አጋጣሚ አልተፈጠረም። በእውነት የቄሮዎች ትግል እነመሀተማ ጋንዲ የእንግሊዝ የቅኝ ግዛት ዘመን እንዲጨልምና ከነግሳንግሱ ከምድር ገጽ እንዲጠፋ ያደረጉበትን አስደናቂ የእምቢተኝነት ትግል የሚያስታውስ ነው።

በእርግጥ ቄሮዎች ዛሬ ላይ ላቀጣጠሉት እምቢተኝነት እርሾው ቀደም ተብሎ የተዘጋጀ መሆኑን እዚህ ላይ መጥቀስ ያስፈልጋል። ኢትዮጵያ ውስጥ የትግራይ አገዛዝ ቤተመንግስት ከገባ ጀምሮ ትግል ነበር። በተለያዩ አካላት ሲደረግ የነበረው እልህ አስጨራሽ የነጻነት ተጋድሎ በቅብብሎሽ እዚህ ዘመን ላይ ደርሷል።

Saturday, March 10, 2018

“የክርስቲያን አገር በሆነችው ሙስሊሞች ሊነግሡባት ነው” ህወሓት ለአሜሪካ እንደራሴዎች


  • የአስራ ሰባት ታዋቂ ኦሮሞ ሙስሊሞችን ስም ለማስረጃነት አቅርቧል
  • ከዝርዝሩ ውስጥ የዶ/ር አቢይ አህመድ ስም ይገኝበታል
ህወሓት ከፊቱ የተጋረጠበትን የፖለቲካ ቀውስና ቀውሱን ተከትሎ ከጌቶቹ የተነሳበትን ተቃውሞና ግፊት አቅጣጫ ለማስቀየር ሃይማኖትን የተንተራሰ ስልት ተግባራዊ ማድረጉ ተሰማ። የሚካሄደው ህዝባዊ ተቃውሞ አገሪቱን ለእስልምና አክራሪ አሳልፎ ለመስጠት ያለመ እንደሆነ ህወሓት በወኪሉ በኩል ስም ዘርዝሮ አቅርቧል።

Thursday, March 1, 2018

ህወሓት፡ የHR 128 ፍርሃቻ እና የማግኒትስኪ ሕግ

ከዚህ በፊት በአሜሪካ ምክርቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በረቂቅ ሕግነት ከቀረቡት መካከል ህወሓት/ኢህአዴግ HR 128 እጅግ ፈርቶታል። ይህንን ረቂቅ ሕግ ለማክሸፍም የውትወታ (ሎቢ) ሥራ ከመሥራት ጀምሮ የአሜሪካ ባለሥልጣናትንና የፖለቲካ መሪዎችን በ“አልሻባብ ምስራቅ አፍሪካን ይወራል” ድራማ ለማስፈራራት ተደጋጋሚ በርካታ ሙከራዎችን ቢያደርግም አልተሳካለትም። ላለፉት በርካታ ወራትም (በቅርቡ ወደ አሜሪካ የመጡትን እነ ወርቅነህን ጨምሮ) ሊያሳምኑ ይችላሉ የሚላቸውን ሹሞቹን በመላክ ረቂቅ ሕጉ በተግባር እንዳይውል የአሜሪካ ባለሥልጣናትንን – ጊዜ ስጡን፣ ሁሉን እናስተካክላለን፣ … የመሳሰሉ ተማጽንዖዎችን ሲያቀርብ ቆይቷል። በግምባር ቀደምትነትም የህወሓት ወዳጅ የሆኑት ሴናተር ኢንሆፍ ህወሓት/ኢህአዴግን ለመታደግ ኢትዮጵያ ድረስ እስኪሄዱ ያደረሰ የውትወታ ሥራ ተካሄዷል።

Tuesday, February 27, 2018

“ታሪክ ራሱን ቧልት በሆነ መንገድ ሲደግም!”

ኤርሚያስ ለገሰ
Ermias Legesse, author and ESAT TV and Radio contributor
አንድ safegurding Tegaru lives በሚል ስያሜ የሚጠራ  ካድሬ ” ደኢህዴን ከኃይለማርያም ወደ ሽፈራው ሽጉጤ ያደረገው ለውጥ የጥልቅ ተሃድሶ እድገት ነው፣ ወይንስ ከድጡ ወደ ማጡ ነው?” በሚል ያነሳሁት ጥያቄ ላይ አስተያየት ሊሰጥ ወደ ገፄ መጥቶ ነበር።  ከላይ ከተጠቀሰው ኮካ በተጨማሪ በለውጥ ሀይል ዙሪያ ያሉ ወገኖች ” ሲራጅ ፈርጌሳ የደኢህዴን ሊቀመንበር ሆነ ብለህ ነበር!” የሚል ጥያቄ ስላነሳችሁልኝ ሁኔታውን ትንሽ ልበልበት። በትግራይ ነፃ አውጪ ደጃፍ ታሪክ እራሱን ስለሚደጋግሞ መለስ እያሉ ማስታወሱ ሳይበጅ አይቀርም። ከላይ የተጠቀሰው አይነት ሾርት ሜሞሪ ያላቸውን ኮተታም ካድሬዎች አፍ ማዘጋት የሚቻለው በዚህ መልኩ ነው። በሚያገኙት መረጃ ወደ ሰው ይመለሳሉ ብሎ ተስፋ ማድረግ ታማኝ እንዳለው ” እባብ ለመደ ተብሎ በኪስ አይያዝም!” ቢሆንም እባብነታቸውን እንዳይረሱ ያደርጋቸዋል። እናም እንደሰሞኑ በጅምላ ግድያ በርሜላቸውን እስኪሞሉ አድብተው እንዲቀመጡ ያደርጋቸዋል።

Thursday, February 22, 2018

ወርቅነህ ገበየሁ ቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆን ህወሃት ወስኗል

ክንፉ አሰፋ
Workneh Geeyehu, Ethiopia's Minister of Foreign Affairs.
ወርቅነህ ገበየሁ ቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆን በህወሃት ተሹሟል። ይህ ከታማኝ ምንጭ የደረሰን መረጃ ነው። መረጃው እንደሚጠቁመው፤  እነ ዶ/ር ደብረጽዮን  ሹመቱን ያጸደቁለት፤ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ  ገና በስልጣን ላይ እንዳሉ ነበር። የህወሃት ሰዎች “የኦሮሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መሆን ሃገሪቱ አሁን የገባችበትን አስከፊ ችግር ይፈታል”  የሚል ቅኝት ይዘው ወደ ምዕራቡ አለም እንዲሰማሩም ተደርጓል። 

Monday, February 19, 2018

የጠቅላይ ተጠቅላይ ጨዋታ

ኤርሚያስ ለገሰ
Image result for ermias legesse
ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ቀጥሎ የኢትዬጲያን የፓለቲካ አየር የሞላው የሚቀጥለው " ጠቅላይ/ ተጠቅላይ" ማን ይሆናል የሚለው ነው። ይህንን ጉዳይ ሰዎች በተለያዩ አቅጣጫዎች ይመለከቱታል። በተለይም በማህበራዊ ድረገጾች ካሉት ፍትጊያዎች አንዱ በዚህ ዙሪያ ያለው እሰጣ ገባ ሆኗል። በአንድ በኩል ስርነቀል የስርአት ለውጥ ለማምጣት እየታገልን ባለንበት ሰአት በዚህ አነስተኛ አጀንዳ ዙሪያ ለምን ጊዜያችንን እናጠፋለን የሚሉ ብዙዎች ናቸው። በሌላ በኩል ከራሳቸው እምነት፣ ጥቅም እና ፍላጐት በመነሳት " እከሌ ጠቅላይ መሆን አለበት!" የሚለውን የሚገፋም አልታጡም።

Sunday, February 18, 2018

የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ህወሀት ክፉኛ ቆስሏል። ከእንግዲህ በመንግስትነት የመቆም እድል የለውም። ኳሷ በኢትዮጵያውያን እግር ስር ገብታለች።

Mesay Mekonnen, ESAT journalist
መሳይ መኮንን
ያለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ትልልቅ ክስተቶች የተሰተናገዱበት ነው። ተስፋና ስጋት፡ ብርሃንና ጽልመት፡ አንድነትና መነጣጠል፡ ከፊታችን ተደቅነው ጉዟቸንን እንድናሳምር፡ መንገዳችንን እንድንመርጥ፡ አካሄዳችንን እንድናስተካክል፡ እድል እጣፈንታችንን እንድንወስን ከሚያስችለን ዋናው ምዕራፍ የተጠጋን ይመስላል። የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ህወሀት ክፉኛ ቆስሏል። ከእንግዲህ በመንግስትነት የመቆም እድል የለውም። ኳሷ በኢትዮጵያውያን እግር ስር ገብታለች። የጊዜ ጉዳይ ነው። በጣም ጥንቃቄ የሚያስፈግበት ወቅት ላይ ነን። ጥሞና ያስፈልገናል።
አዎን! እስረኞች ተፈተዋል- የሚቀሩ ቢኖሩም። አቶ ሃይለማርያም ስልጣን ለቋል- ስልጣን ባይኖረውም። አስቸኳይ አዋጅ ተደንግጓል- ለውጥ ባያመጣም። ህዝባዊ ትግሉ ተጠናክሯል- በፈረቃ መሆኑ ባይቀርም። ይህ ሁሉ የሆነው በዚህ ሳምንት ውስጥ ነው። በኢትዮጵያ የ27 አመታት የትግራይ ነጻ አውጪ የአገዛዝ ዘመን እንደዚህ ሳምንት ክስተቶች በፍጥነት ተደራርበው የመጡበት ጊዜ ያለ አይመስለኝም። እነኚህ ክስተቶች ወዴት ይመሩናል? በእርግጥ ቁልፍ ጥያቄ ነው።
የእስረኞች መፈታት

የትግላችን መጨረሻ ነፃነታችን ብቻ ነው! (የዲሲ የጋራ ግብረ ሃይል)

የዲሲ የጋራ ግብረ ሃይል
Ethiopians demonstration against the Amhara eviction
የዋሽንግተን ዲሲ የጋራ ግብረ ሃይል ከፈጣሪ በታች የምንመካበት የኢትዮጵያ ህዝብ ክንዱን አስተባብሮ ስለነፃነቱ በጋራ በመቆም ለነፃነቱ ገፋፊዎች ባሳየው ማንነቱ አንገታችንን እንድናቀና ስላደረገን ምስጋናችን ከልብ የመነጨ ነው።

Wednesday, February 14, 2018

“ሁሉንም ባለድርሻዎች ያካተተ የሽግግር መንግስት ሂደት” አቶ ንአምን ዘለቀ

ሁሉንም ባለድርሻዎች ያካተተ – ማለትም የፓለቲካ ሃይሎች፡ የሲቪክ ማህበረሰቡን፡ ታዋቂ ምሁራንን፣ የሀገር ሽማግሌዎች የሚገኙበት ማንንም ያላገለለ የብሔራዊ ዉይይትና ከዚህም የሚወጣ ሁሉን አቀፍ የሽግግር መንግስት ሂደት
  • ሁሉንም ባለድርሻዎች ያካተተ – ማለትም የፓለቲካ ሃይሎች ፡ የሲቪክ ማህበረሰቡን፡ ታዋቂ ምሁራን ፣ የሀገር ሽማግሌዎች የሚገኙበት ማንንም ያላገለለ የብሔራዊ ዉይይትና ከዚህም የሚወጣ ሁሉን አቀፍ የሽግግር መንግስት ሂደት ብቻ ነው ተቀባይነት የሚኖረው፡፡

Tuesday, February 13, 2018

የኦጋዴን ነፃ አውጪ ግንባርና የወያኔ ድርድር በኢትዮጵያ አንድነት ላይ የተቃጣ ሴራ!

ከዶ/ር ዲማ ነገዎ፣ ፕ/ር ጌታቸው በጋሻው እና ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ
Ogaden is the unofficial name of the Somali Region of Ethiopia
ከታማኝ ምንጮች እንደተረዳነው በወያኔና በኦብነግ መካከል ሲካሄድ የቆየው ውይይት በመጠናቀቅ ላይ ነው:: በናይሮቢ ተጀምሮ በዱበይ ከተማ ሲካሔድ ቆይቶ አሁን እንደገና ወደ ናይሮቢ ተመልሶ ፍፃሜ ላይ መድረሱን ምንጮቻችን ገልፀዋል:: ይህ ሤራ ወያኔ ኢትዮጵያን ረግጦ  ገዝቶ ለመኖር ካልቻለ ኢትዮጵያን ሽብር  ውስጥ  ከቶ ትግራይን ለመገንጠልና የትግራይን ሪፑብሊክን ለማቋቋም ያለውን ግልፅ አቋም በተግባር እየተረጎመ መሆኑን ያሳያል::

Sunday, February 11, 2018

የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ህወሀት ከኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጪ ግንባር ጋር በኬኒያ ሸምጋይነት ድርድር ጀምረዋል።

 በመሳይ መኮንን
Ogaden National Liberation Front
የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግንባር ህወሀት ከኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጪ ግንባር ጋር በኬኒያ ሸምጋይነት ድርድር ጀምረዋል። የሶማሌ ክልል ፕሬዛዳንት አብዲ ኢሌና በሶማሊያ የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ተወካይ ጄነራል ገብሬ የህወሀትን መንግስት ወክለው በድርድሩ እየተሳተፉ መሆናቸው ተገልጿል። የሚጠበቅ ነው። በዚህን ወቅት፡ የህዝብ ንቅናቄ ሲጠነክር፡ ፖለቲካዊ ትኩሳት ሲጨምር የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ከሚወስዳቸው የተለመዱ እርምጃዎች አንዱ የኦጋዴን ነጻ አውጪ ግንባርን ደጅ መጥናት ነው። ድርድር።

Thursday, February 8, 2018

ፋሽስታዊው የሕወአት አገዛዝ የቆመበትን ኢኮኖሚያዊ ምሰሶዎች ለማሽመድመድ አለም አቀፍ የሃዋላ ተአቅቦ ዘመቻ አካል እንሁን!!

በነአምን ዘለቀ
Ethiopians Remittance Embargo.
ከፋሽስቱ የወያኔ አገዛዝ ጋር በሚደርገው ሁለገብ ትግል ስልቶች መካከል የኢኮኖሚያዊ ጦርነት (Economic Warfare) አንዱ ነው። ስርአቱ የቆመበትን ምሰሶ የማዳከም የኢኮኖሚያዊ ጦርነት ስልቶች እንዱ የሃዋላ ተአቅቦ ነው። የሃዋላ ተአቅቦ ለአጠቃላይ ትግሉ ከፍተኛ እገዛ የሚያደርግና ስርአቱን ለማዳከም ያለው ሚና ከፍተኛ ነው።

ህወሓትና ኢትዮጵያን የማፈራረስ ዓላማው!

የአዘጋጆቹ ማስታወሻ፤ ባለፉት ዓመታት ከህወሓት እየኮበለሉ የወጡ የቀድሞ አባላት በርካታ ናቸው። እንዳንዳቸው የሚወጡበት ምክንያት ቢኖራቸውም ህወሃትን በማጋለጥና ማንነቱን ለኢትዮጵያ ሕዝብ በማሳወቅ የአቶ ገብረመድኅን አርአያን ያህል ታላቅ ሥራ የሠራና መስዋዕትነት የከፈለ አለ ለማለት ያስቸግራል። አብዛኛዎቹ የቀድሞው አባላቱ የህወሓትን ምሥጢራዊ አሠራር እና እጅግ አረመኔያዊ ግፍ፤ ኤፈርት በኢትዮጵያ ሐብት ላይ የፈጸመውንና እስካሁንም እየፈጸመ ያለውን የኢኮኖሚ ግፍ፣ ዝርፊያ፣ ሌብነት፣ … የመሳሰሉ ጉዳዮች በአደባባይ ከመናገር ሲቆጠቡ ተስተውለዋል። አንዳንዶቹም በህወሓት ከፍተኛ አመራር ላይ የነበሩ የቀድሞ አባላት ቢሆኑም፤ ኤፈርትም ሲያስተዳድሩ የቆዩ ቢሆኑም ስለጉዳዩ ሲጠየቁ የሚሰጡት ምላሽ አባይ ጸሐዬ ወይም ስብሃት ነጋ ከሚሰጡት ምላሽ ያልተለየ ሆኖ ተገኝቷል።

Monday, February 5, 2018

የንግድ ስርአቱና “የቲም ለማ” ግኝት!

ኤርሚያስ ለገሰ
#1: መግቢያ
በአቶ ለማ መገርሳ ሊቀመንበርነት የሚመራው የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ በአዳማ የ10 ቀን ዝግ ስብሰባ ለማድረግ ተቀምጧል። በዚህ ስብሰባ ላይ የተለያዩ ድርጅታዊ፣ ክልላዊ፣ አገራዊ እና አለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን በመመርመር ታላላቅ ውሳኔዎችንና የቀጣይ አቅጣጫዎችን እንደሚያስቀምጥ በግምገማው ቃል አቀባይ ተነግሯል። የድርጅቱ ስራ አስፈፃሚ እና የግምገማው ቃል አቀባይ አቶ ሐብታሙ ሐ/ ሚካኤል ለየኦሮሞ ብዙሃን መገናኛ ( OBN) በሰጠው መረጃ መሰረት ግምገማው በአሁን ሰአት ወደ አቢይ አጀንዳዎች ተሸጋግሯል።
Lemma Megersa, with his team, was in Bahir Dar.
Lemma Megersa
ከእነዚህ አቢይ አጀንዳዎች መካከል በአገሪቱ የንግድ ስርአት ላይ ውይይት እየተደረገ መሆኑ ቃል አቀባዩ ተናግሯል። የንግድ እንቅስቃሴው ስልጣንን ተገን በማድረግ በተወሰኑ አካላት ተይዞ የኦሮሚያን ኢኮኖሚ እያቀጨጨው መሆኑ በጥልቀት መታየቱን ገልጿል። ስልጣንን መሰረት በማድረግ በተወሰኑ አካላት የሚለውን በቀይ ብዕር አስምሩልኝና ወደ ቃል አቀባዩ መግለጫ እንመለስ። አቶ ሐብታሙ ለOBN በሰጠው መግለጫ ላይ፣
” የአገሪቱ የንግድ ስርአት ከአድሎነት የፀዳ ነወይ? የንግድ ስርአቱ በፍትሐዊነት ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል እኩል ተጠቃሚ እያደረገ ነወይ? ወይንስ የተወሰኑ አካላት ብቻ ከድንብር ድንበር እየተዘዋወሩ እንደፈለጉት ተጠቃሚ የሚሆኑበት ነው? በሚለው ጉዳይ ላይ በጥልቀት ተወያይተናል። በአገሪቱ የንግድ ስርአቱ ውስጥ ትልልቅ ችግሮች አሉ። ስልጣንን ተገን በማድረግ በተወሰኑ አካላት ተይዞ ያለ የኮንትሮባንድ እንቅስቃሴ አራማጆች ላይ ታግለን መስመር እንዲይዙ በማድረግ ረገድ ምን እንደምንመስል ፈትሸናል” ብሏል።

Friday, February 2, 2018

“የህውሓት የአዲስ አበባ ልዩ ዞን!” እና የ HD አዲሱ ዲስኩር

በኤርሚያስ ለገሰ
መንደርደሪያ አንድ:- 1998 
Ermias Legesse, author and ESAT TV and Radio contributor
የመለስ ትሩፋት ባለቤት አልባ ከተማ መፅሐፍ ” የአዲስአባ ፓለቲካ ምህዳር” በሚል ርእስ ስር በገፅ 252 ላይ የሚከተለውን ትለናለች፣

Sunday, January 28, 2018

ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ ጆሮና አይኔ ወሎ ላይ ተተክሎ ሰንብቷል

መሳይ መኮንን
ከወልዲያው ጭፍጨፋ፡ ከቆቦዎች አይበገሬነት እስከመርሳዎች ጀግንነት፡ ክስተቶችን እዚያው አጠገባቸው እንዳለ ሆኜ ነበር ስከታተል የቆየሁት። ስሜቴ ከወዲህ ውዲያ ሲላጋ፡ ቅጭም ሲል፡ በሀዘን ሲመታ፡ ደግሞም በጀግንነታቸው ልቤ ሲሞቅ፡ ወዲያኑም በሚደርስባቸው የግፍ በትር ውስጤ ሲደማ፡ በሞታቸው ኩምትር ስልበወርቃማ መስዋዕትነታቸው ስጽናና፡ እንዲሁ ላይ ታች ስል ሰነበትኩ። አሁንም ከዚያው ነኝ። ከወልዲያ ምድር፡ ከቆቦዎች መንደር፡ ከሮቢት ሰፈር፡ ከሀራ ገበያ፡ ከጎቢዬዎች ሀገር፡ ከመርሳዎች መንደር፡፡ የማያውቁት ሀገር አይናፍቅም የሚለው አባባል አይገባኝም። ወሎን ባላውቀውም ይናፍቀኛል።
Mesay Mekonnen, ESAT journalist
መሳይ መኮንን (የኢሳት ጋዜጠኛ)
ፖለቲካው ግሏል። ሙቀቱ ጨምሯል። ህወሀቶች መቀሌ ላይ የቀመሙትን መርዝ በእጅ አዙር ሊረጩት ተሰማርተዋል። የዘርዓይ አስገዶም ያልተጠና ዲስኩር የህወሀቶችን ቀጣይ አካሄድ እርቃኑን ያጋለጠው ሆኗል። አንጻራዊ የህዝብ ድምጽ በማሰማት ቀና ማለት የጀመሩትን የኦሮሞ ብሮድካስት ኔትወርክና የአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅትን ወደ ቀድሞ አገልጋይነታቸውና በቀቀንነታቸው ለመመለስ በህወሀት አማካኝነት የተዘጋጀውና እነዘርዓይ የተላኩበት ዘመቻ ድባቅ ሲመታ ለመታዘብ ችለናል። አፋቸው ተሎጉሞ የከረሙት ወይም ከህወሀት አገልጋይነት መላቀቅ አቅቷቸው ህዝባቸውን ሲያሳዝኑ የምናውቃቸው እነንጉሱ ጥላሁን እንኳን አፍ አውጥተው፡ ወኔ አግኝተው፡ ድፍረት ተላብሰው ”በዘረኝነት ትዕቢት የተወጠረውን” ዘርዓይን እሳት እንዳየ ላስቲክ ኩምሽሽ ሲያደርጉት አይተናል።

Wednesday, January 24, 2018

አዲስ ድራኮኒያን ህግ! ( በቅርብ ቀን ይጠብቁ!)

በኤርሚያስ ለገሰ
Ermias Legesse, author and ESAT TV and Radio contributor
በቅርቡ የፀረ ሽብርተኝነት ህግ ተስተካካይ የሆነና ከሌሎች ጨቋኝ ህጐች (የፕሬስ ህግ፣ የፀረ ሽብርተኝነት ህግ) ጋር እርስ በራስ የሚመጋገብ አዋጅ ሊወጣ ያቆበቆበ ይመስላል። የአዋጁም ስያሜ ” የማህበራዊ ሚዲያ ህግ” ሊባል ይችላል። ይሄ ህግ ህውሓት የአርማጌዶ ፍልሚያ ጀምሬያለሁ በማለት በድርጅታዊ መግለጫው የገለፀውን ወደ ተግባር ለመቀየር የታሰበ ነው። እንደታዘብኩት ከሆነ ለዚህ አደገኛ ህግ ለመውጣት የሚያስችል ቅድመ ሁኔታዎች እየተሰሩ ነው። አንዳንድ ማሳያዎችን አንስተን ጉዳዩን እንመልከተው።

Tuesday, January 23, 2018

የእኛ ስሜት እና የቴዲ አፍሮ ቁስል

Image may contain: 1 person, standing
~አንድ እርምጃ ወደኋላ ሁለት እርምጃ ወደፊት!
(ጌታቸው ሺፈራው)
ቴዲ አፍሮ ባህርዳር ላይ "ጃ ያስተሰረያል!"ን ዝፈንልን ተብሎ ሳይዘፍን ከመድረክ ወረደ፣ ሕዝብም ቅር ተሰኘ አሉ። ይህን ስሰማ በሁለቱም ጫማ ውስጥ ገብቼ አየሁት። የኮንሰርት ተሳታፊ እና ዘፋኙን ሆኜ!
ሕዝብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ቁስሉ እየጠዘጠዘው ነው። ቴዲ የብሶቱን እንዲዘፍንለት ይፈልጋል። ባህር ዳር ደም ያልደረቀባት ከተማ ነች፣ ቁስሉ ያልጠገገ፣ በየጊዜው እየደማ ያለ ሕዝብ ነው። ትናንት እንኳ ሕዝን የወልዲያን ሰቆቃ ሰምቶ ነው ወደ ኮንሰርቱ የገባው። ሕዝብ የፍቅር ሳይሆን የትግል ዜማ፣ የብሶት ዜማ ነበር መስማት የሚፈልገው።
በሌላ በኩል ደግሞ ቴዲ አፍሮ "ይህን ከዘፈንክ አይቻልም" እየተባለ ፍዳውን አይቷል። ገንዘብ ከስሯል። ዋናው ገንዘቡ አይደለም። አድናቂዎቹን ማግኘት አልቻለም። ሌላው ቀርቶ ስለ መተባበር፣ ስለ ሕዝብ ፍቅር በአካል ተገኝቶ መስበክ አልቻለም! ከ "ጃ" አንፃር ካላየነው በስተቀር አብዛኛው የቴዲ ዘፈን ፖለቲካ ነው። ሀገር የመሰረቱትን እንደሰይጣን የሚጠሉ ገዥዎች ባሉበት ሀገር "ጥቁር ሰው"ን ያህል ፖለቲካ ያለ አይመስለኝም። ቴዲ በቅርቡ ያወጣው አልበም የተወደደው "ጃ ያስተሰራልን"ስላካተተበት አይደለም። ዝም ብሎ ዘፈን ስለሆነም አይደለም። ፖለቲካም ስለሆነ ነው። ተወዳጁ ቴዎድሮስ ካሳሁን ስለዘፈነውም ጭምር ነው!
በመከራ ያለ ሕዝብ ስሜት ለማንም ሊያስቸግር ይችላል። የባሰው ሕዝብ በስልት፣ ቀስ እያልክ ከምትነግረው አፍርጠህለት ግንባርክን ብትባል "ወንድ" ይልሃል። እውነቱን ተናግሮ ከመሸበት ማደር የሚለውም ይህንኑ ነው። ይህ የሕዝብ ስሜት ከበደል ብዛት የመጣ ነው። የብሶት ነው!

Saturday, January 20, 2018

የህወሀት ጸሀይ እየጠለቀች ነው

Image may contain: 1 person
መሳይ መኮንን
ብዙ ምልክቶች በመታየት ላይ ናቸው። ተመልሶ የሚያንሰራራበት እድል ያለ አይመስልም። እየተንፏቀቀ ጊዜ ሊወስድ ይችላል። እግሮቹ ተሰብሮ በደረቱ እየተሳበ ከቤተመንግስት የተወሰነ ጊዜ ሊቆይ ይችላል። ስጋው አልቆ በአጥንቱ ቆሞ ጥቂት ጊዜያት መቆየቱ የማይቀር ነው። በዘላቂነት ግን አልቆለታል ማለት ይቻላል። የህዝቡ ተቃውሞ ሳይቋረጥ ከቀጠለ፡ ከያቅጣጫው የበረታው ግፊት ጉልበቱን ጨምሮ ይበልጥ ከገፋ የሚንፏቀቀውን፡ እግሮቹ የተሰበረውን፡ በአጥንቱ የቀረውን ህወሀት ከታሰበው ጊዜ በጣም በቅርብ ዘላለማዊ ሞቱን የሚጨልጥ ስለመሆኑ አያጠራጥርም። እስቲ ምልክቶቹን አንድ በአንድ እንመልከታቸው፥-
የትግራይ ህዝብ
ህወሀት ከ2010 ዓም ዋዜማ ጀምሮ መቀሌ ከቷል። ላለፉት አምስት ወራት በስብሰባ፡ በኮንፈረንስ፡ በግምገማ፡ በህንፍሽፍሽ፡ በጉባዔ ተጠምዶ ከርሟል። አሁንም እንደሚኖር ይጠበቃል። ትግራይ የህወሀት የመጨረሻ ምሽግ ናት። ስልጣን ላይ ከወጣበት ጊዜ አንስቶ የኢትዮጵያ ልብ ማግኘት ያቃተው ህወሀት አክ እንትፍ፡ ተብሎ መተፋቱን አረጋግጧል። የኢትዮጵያን ህዝብ በፍቅርም፡ በጉልበትም መምራት እንደማይችል ተረድቶታል። ከእንግዲህ ወርቅ እንኳን ቢያነጥፍ የሚቀበለው እንደሌለ አውቆታል። ስለዚህ ወደ መጨረሻ ምሽጉ ፊቱን አዙሯል። ይህ ምሽግ የተወሰነ ዕድሜ እንደሚያዘልቀው ተማምኗል። በኋላ ኪሱ የሸጎጣትን ''የትግራይ ሪፑብሊክ'' ምስረታ ከተሳካለትም ይሞክራል። በኢትዮጵያ ማዕከላዊ መንግስት በበላይነት መቆየት ካልቻልኩ ያሉኝ አማራጮች ብሎ ከያዛቸው እርምጃዎቹ አንዱ ወደ ትግራይ ጠቅልሎ ገብቶ ምሽጉን ማጠናከር ነው።ለዚህም የትግራይን ህዝብ ልብ ሙሉ ለሙሉ ለማግኘት ቃል በመግባት ተግቶ እየሰራ ነው።

Friday, January 19, 2018

ልክ ያጣው የእነ ገብረ እግዚያብሔር እብሪት

ጌታቸው ሽፈራው
Ethiopian political prisoner Aschalew Desse.
አስቻለው ደሴ የፌደራል ፖሊስ አባል ነበር። አማራ በሰበብ በሚታሰርበትና በሚከሰስበት ግንቦት 7 አባል ነህ ተብሎ ታሰረ። የተለመደውና የሌለው የ”ሽብር” ክስ ተመስርቶበታል። የታሰረው ደግሞ የአማራ ወጣቶች ዘራቸውን እንዳይተኩ ከሚኮላሹበት ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ነው። እንደሌሎቹ ወንድሞቹ አስቻለው ደሴንም ብልቱ ላይ ሁለት ሊትር ሀይላንድ ውሃ አንጠልጥለው ዘሩን እንዳይተካ አድርገውታል። ጆሮውንም ጎድተውታል። ለዚህ ሁሉ ቁስሉ ምንም አይነት የህክምና እርዳታ አላገኘም። በክሱና በማንነቱ ምክንያት ህክምና ተከልክሏል። ጥጋበኞች ላቆሰሉት፣ ለጎዱት አካልና መንፈሱ ምንም አይነት ህክምና አላገኘም።

የመንግስቱ ሃይለማርያም ልጅ ዶ/ር ትዕግስት መንግስቱ አወዛጋቢ ቪዲዮ ለቀቀች – “እንዴት ተደፈርን?”

(ዘ-ሐበሻ) የቀድሞው የኢትዮጵያ መሪ ኮ/ል መንግስቱ ሃይለማርያም ልጅ የሆነችው ዶ/ር ትዕግስት መንግስቱ በግብጽ እና በአባይ ፖለቲካ ዙሪያ አንድ ቪዲዮ ለቀቀች:: ቪዲዮውን የለቀቅችው በፌስቡክ ሲሆን የራሷን አስተያየት “እንዴት ተደፈርን?” ስትል ትጀምራለች:: ይመልከቱትና በአባይ ዙሪያ ያላትን አወዛጋቢ አቋም አስተያየት ይስጡበት::

Thursday, January 18, 2018

ከ23 በላይ ድርጅቶች የተሰባሰቡበት የኢትዮጵያ ማህበረሰባዊ ድርጅቶች ትብብር የውጭ ምንዛሬ “ሬሚታንስ” ተአቅቦ ጥሪን ደገፈ

ጉዳዩ፦ አለም አቀፍ የኢትዮጵያዊያን የጋራ ግበረሀይል እያደረገ ያለውን የውጭ ምንዛሬ ተአቅቦ ዘመቻ ስለመደገፍ
A Call for Worldwide Remittance Embargo Against the Brutal TPLF Regime
የተከበራችሁ ኢትዮጵያዊያን፣
ከዲሴምበር 29 ቀን 2017 ጀምሮ በአለም አቀፍ የኢትዮጵያዊያን የጋራ ግበረሀይል አስተባባሪነት የውጭ ምንዛሬ ተአቅቦ ዘመቻ እየተደረገ ይገኛል። የዘመቻው አላማ የገዳዩ እና ዘራፊው የህወሓት መንግስት በውጭ አገራት ከሚኖሩት ኢትዮጵያዊያን የሚያገኘው የውጭ ምንዛሬ እንዲቀንስ ማድረግ እና የአገዛዙን ኢኮኖሚያዊ አቅም ማዳከም መሆኑን ትብብራችን መረዳት ችሏል። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን የወገናቸውን የነጻነት ትግል የማገዝ ሀላፊነት እና አቅም እንዳላቸውም ትብብራችን ያምናል። ግብረሀይሉ ያወጣው መግለጫ እንደሚያመለክተው እና ትብብራችንም እንደሚያምንበት፣ ኢትዮጵያዊያን ከታች የተዘረዘሩትን ጥሪዎች ተግባራዊ ለማድረግ ከተንቀሳቀሱ፣ በአገዛዙ ላይ ትርጉም ያለው ኢኮኖሚያዊ ጫና ማድረግ ይቻላል።

የበረከት ተመልሶ መምጣት ማረጋገጫ

በኤርሚያስ ለገሰ
Bereket-Simon
የዛሬው አዲስ ዘመን ርዕሰ አንቀፅ የበረከት ስምኦን ተመልሶ መምጣት የሚያረጋግጥ ነው። የአዲስ ዘመን ርዕሰ አንቀፅ የመንግስት አቋም የሚገለፅበት በመሆኑ የሚፃፈው በህውሃት/ኢህአዴግ የፓለቲካ መሪዎች ብቻ ነው። በተለይ በእንደዚህ አይነት የቀውጢ ወቅት አዲስ ዘመን ከስኳር መጠቅለያነት ወጥቶ የፓለቲካውን አቅጣጫ ማሳየት ስላለበት በፕሮፐጋንዳ ክፍሉ ልዩ ትኩረት ይሰጠዋል። የሚፅፈው አሊያም በስልክ ዲክቴት የሚያደርገው ደግሞ በረከት ስምኦን ነው።

Wednesday, January 17, 2018

ከድንዛዜው መውጣት አለብን፣ የህወሀት አጀንዳ እንዲመራን አንፍቀድለት

መሳይ መኮንን
Merera Gudina is a professor and politician in Ethiopia.
Merera Gudina
ሰሞኑን የህወሀት አገዛዝ ከወዲህ ወዲያ እየዘለለ ነው። በፍትህ ስርዓቱ ላይ ጢባ ጢቤ እየተጫወተ ነው። ጠዋት የተናገረውን ከቀትር በኋላ ይሸረዋል። ምሽት ላይ የወሰነውን ንጋት ላይ ይሰርዘዋል። ይፈታሉ፡ አይፈቱም። ይቅርታ ነው። የለም ምህረት ነው። የፖለቲካ እስረኛ የሚባል የለም። ፖለቲከኞች ይፈታሉ። በሁለት ቀናት ውስጥ ይፈታሉ። በሁለት ወር ውስጥ ውሳኔ ያገኛል። ሪፖርተር ሌላ። ሬዲዮ ፋና ሌላ። ዋልታ ወዲህ- ኢቲቪ ወዲያ። ዥዋዥዌ።

Monday, January 15, 2018

የመቀሌው ስብሰባና የ’ፖለቲካ እስረኞች ፍቺ (መሳይ መኮንን)

Few of Ethiopian political prisoners in picture.
ይህን ጽሁፍ በማዘጋጅበት ሰዓት ጠቅላይ አቃቤ ህጉ መግለጫ እየሰጡ ነው። የእስረኞችን መፈታት በተመለከተ ትላንት መግለጫ እንደሚሰጡ ስንሰማ መቀሌ ወሰነች ብለን ነበር። ምክንያቱም የእስረኞች መፈታት ወሬ ከሃይለማርያም አፍ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ በህወሀት መንደር የፈጠረው መንጫጫት የተባለው እንደማይሆን ከምልክትም በላይ ነበርና ነው። ከጠቅላይ አቃቤ ህጉ የዛሬ መግለጫ ለመረዳት እንደተቻለው ግን የሚፈታ የፖለቲካ እስረኛ የለም።

ታዳሚን እንባ ያራጨው የችሎት ውሎ

Image result for torture
(በጌታቸው ሺፈራው)
ዛሬ በጠዋት ሰብሰብ ብለን የገባነው ወደ 4ኛ ወንጀል ችሎት ነበር። ከ4ኛ ወንጀልችሎት ስወጣ 19ኛ ወንጀል ችሎት ታዳሚውን ያስለቀሰ፣ ዳኞቹን ሳይቀር ያሳዘነ ትዕይን እንደነበር ሰማሁ። 19ኛ ወንጀል ችሎት የነበረ አንድ ጓደኛዬን ማስታወሻውን እንዳየው ጠየኩት። የተጀመሩ ዐረፍተ ነገሮች፣ ያልተቋጩ ሀረጎችን አነበብኩ። በእርግጥ እንባ በሚያራጭ ትዕይንት ውስጥ መፃፍ ከባድ ነው። እኔንም ብዙ ቀን አጋጥሞኛል።የጓደኛዬ ማስታወሻ ላይ የሰፈሩ የተቆራረጡትን ዐረፍተ ነገሮች መዝግቤ፣ ጓደኛዬ በችሎት ያየውን እንዲያብራራልኝ ጠየኩት። በአማራ ክልል በነበረው ህዝባዊ ንቅናቄ ሰበብ የታሰሩትና በእነ ታደሰ መሸሻ አሰጌ ክስ መዝገብ ከተከሰሱት መካከል 3ኛ ተከሳሽ የሆነው ዮናስ ጋሻው ደመቀ በሌሎች የአማራ ወጣቶች የሚፈፀመው ጭካኔ ተፈፅሞበታል። አስቻለው ደሴና ሌሎች አማራ ወጣቶች እንዳደረጉት ሱሪውን በችሎት አውልቆ "ህዝብ ይፍረደኝ" ብሏል። ሃይላንድ ያንጠለጠሉበትን ብልቱን አሳይቷል።በዚህ ወቅት ታዳሚው አልቅሷል። ጓደኛዬ ይህን ሰቆቃ እያየ በደንብ መፃፍ አልቻለም። ዳኞች እንኳ አንገት ደፍተዋል። በጠዋቱ ችሎት በተከሳሹ ሰቆቃ ያለቀሱትን ታዳሚዎችም አነጋግሬያቸው ነበር። ከሰዓትም ሀዘኑ ሳይለቃቸው ስለ ሰቆቃው ነግረውኛል።

Saturday, January 13, 2018

የተበላሸው ብድር 3.6 ቢሊየን ብር ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 4/2010)

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለሰፋፊ እርሻዎች ካበደረው 5.6 ቢሊየን ብር ውስጥ 3.6 ቢሊየን ብር የተበላሸ ብድር ሆኗል ሲል አረጋገጠ።
ልማት ባንኩ ለሰፋፊ እርሻዎች መቀበል የጀመረውን የብድር ጥያቄም ማቆሙን አስታውቋል።
በአብዛኛው የትግራይ ተወላጆች ለተሰማሩበት የጋምቤላ የእርሻ ልማት የተሰጠው ብድር ከ63 በመቶ በላይ የተበላሸ ተብሎ የተሰረዘው ባለሀብቶቹ ተጠያቂ እንዳይሆኑ በሚል መሆኑን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው አካላት ይገልጻሉ።
የኦክላንድ የምርምር ተቋም በጋምቤላ የተሰማሩ ባለሃብቶች ከ70በመቶ በላይ የሚሆኑት የትግራይ ተወላጆች ናቸው ይላል።
ራሳቸው ባለሃብቶቹ በተወካያቸው አማካኝነት እንደተናገሩትም በአጋጣሚ የትግራይ ተወላጆች እንበዛለን ነው።

Monday, January 8, 2018

የኤርሚያስ ለገሠ ማስታወሻ ለዶ/ር አቢይ አህመድ

ሰላም ላንተ ይሁን።
ይህን ማስታወሻ የምፅፍልህ የምከትበው ነገር ላታስበው ትችላለህ ከሚል እምነት ተነስቼ አይደለም። በዙሪያህ ያሉ የድርጅቱ ሃላፊዎች እና አማካሪዎችም ያጡታል ከሚል ጥራዝ ነጠቅነት የመነጨ አይደለም። ነገር ግን በፓርቲው የፕሮፐጋንዳ እና ድርጅት እቅድ የማውጣት እና አፈፃፀሙን የመከታተል ስራዎች ላይ ቆይታ አድርጐ እንደነበረ ሰው ቀለል ያሉ ምክረ ሐሳቦችን ለመሰንዘር ነው። እነዚህ አስተያየቶች ቀላልና ህውሃት ቀርጾ ለሩብ ክፍለ ዘመን እየተገበረ ካለው ” ህጋዊ ማእቀፍ” ሳትወጡ ልትፈፅሙት የምትችሉት ናቸው።
ካልተቀየረ በስተቀር የድርጅትና ፕሮፐጋንዳ እቅድ ስታወጡ የሁኔታዎች ትንተና ( SWOT analysis) እንደምታደርጉ አውቃለሁ። ከእነዚህ የሁኔታዎች ትንተና ተነስታችሁ በአመቱ የምትፈፅሟቸው ቁልፍ እና አበይት ተግባራት እንደምትዘረዝሩም እገምታለው። በሌላ በኩል ይህ ከባድ ሃላፊነት በአንተ ጫንቃ ላይ እንደወደቀ ደግሞ ከያዝከው ስልጣን በመነሳት መገመት ይቻላል። መቼም እንደ ሰገሌው ዘመን ህውሓት በትግርኛ እቅድ አውጥቶ በአማርኛ እና ኦሮምኛ ተርጉማችሁ ወደ ስራ አውሉት የሚለው ዘመን ታሪክ የሆነ ይመስለኛል። እርግጥ እነ አባይ ፀሀዬና በረከት ስምኦን ይሄን ሊያደርጉት አይችሉም ብሎ መገመት ግን የዋህነት ነው። ይሁን እንጂ የበላይ አለቃህ የሆነው ለማ መገርሳ ” ቀዳድጄ ቅርጫት ውስጥ ከተትኩት!” እንዳለው አንተም የአለቃህን አርአያነት እንደምትከተል አልጠራጠርም። የፈጠነ አስተያየት ቢሆንም በአጭር ጊዜ ያሳየኸው የአመራር ጥበብ ለዚህ አገላለጤ መነሻ ነው።

Sunday, January 7, 2018

የረቡዕ ዕለት ቃል እስከአሁን አልተከበረም። የተፈታ እስረኛ አላየንም!!

Mesay Mekonnen
Image may contain: 1 person
የረቡዕ ዕለት ቃል እስከአሁን አልተከበረም። የተፈታ እስረኛ አላየንም። ብዙውዎች ገናን ለማድመቅ በዚያውም ፖለቲካዊ ነጥብ ለማስቆጠር በገና ዋዜማ የሚፈቷቸው ይኖራሉ ብለው ተስፋ አድርገው ነበር። በዚህም ወደቃሊቲና ቅሊንጦ የሄዱም እንደነበሩ ሰምተናል። ከሸዋሮቢት፡ ዝዋይና ሌሎች ቦታዎች እስረኞች በአውቶብሶች ተጭነው ወደአዲስ አበባ እየገሰገሱ ነው፡ በሚሌኒየም አዳራሽ ልዩ የአቀባበል ፕሮግራም ተዘጋጅቷል.....ብዙ ብዙ ተብሎም ነበር። ግን ወፍ የለም።
እንደሰማነው ህወሀቶች አልተስማሙም። የመቀሌውን የ35 ቀናት ዝግ ስብሰባ የስብሃት ቡድን አሽንፎ ወጥቷል የሚለው ድምዳሜ ወደ ኋላ የተቀለበሰ ይመስላል። አዜብ መስፍን በኢህአዴግ የ18ቀናቱ ጉባዔ መሀል ድንገት በር በርገዳ ገብታ ''መለስ ሞተ ብላችሁ ተጫወታችሁብኝ። የእጃችሁን ታገኛላችሁ'' ዓይነት ማስፈራሪያ አዥጎድጉዳ እንደወጣች ይወራል። ከሷ ጀርባ የተሰለፈውና መከላከያውን በበላይነት የያዘው ሳሞራ ድምጹ ጠፍቶ ቀና ማለት መጀመሩንም የሚያሳዩ ምልክቶች አሉ። እነሃይለማርያም ረቡዕ ዕለት ''የህወሀት/የትግራይ የበላይነት የለም'' የሚል መግለጫ ሲሰጡ አዜብ በዚያው ዕለት ለመሶበ ሲሚንቶ ፋብሪካ የጣሪያ ክዳን ፋብሪካ የ2ቢሊየን ብር ስምምነት ከውጭ ኩባንያ ጋር ተፈራርማለች። ''አለሁ። እጅ አልሰጠሁም'' መልዕክት ነው ብሎ መውሰድ ይቻላል። የአዜብ ዳግም ብቅ ማለት የህወሀት ትርምስ አልበረደለትም- ገና ይናጣል- የሚል ግምትም እንዲሰጠው አድርጓል።

Friday, January 5, 2018

አገራችንን ከተደቀነባት አደጋ መታደግ የሚቻለው የሥርዓት ለውጥ በማምጣት ብቻ ነው። የአርበኞች ግንቦት 7 ርዕስ አንቀጽ !!



የአገራችንን ሉአላዊነት እና የህዝባችንን አንድነት ድርና ማግ ሆኖ አቆራኝቶ ለዘመናት ያቆዩትን እሴቶች ሙሉ በሙሉ በማጥፋት ህወሃት እንደ ድርጅት መሪዎቹም አንደ ቡድን ልዩ ጥቅም እናገኛለን በሚል የፖለቲካ ስሌት ላለፉት 27 አመታት ረጅም ርቀት ተጉዘዋል። በዚህም የተነሳ አብዛኞቹ አመራሮች እና ለአመራሩ ቀረቤታ ያላቸው ካድሬዎች እስከነ ዘመዶቻቸው የአገሪቱን ፖለቲካ ሥልጣን ብቻ ሳይሆን ኢኮኖሚውንም በበላይነት ለመቆጣጠር ዕድል አግኝተዋል። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያቤት ውስጥ የአፍሪካ ጉዳይ ረዳት ሚንስትር እና በተለያዩ አገሮች የአገራቸው አምባሳደር ሆኖ ለረጅም ጊዜ ሲያገለግሉ የኖሩት ሚስተር ሄርማን ኮሄን ሰሞኑን ለሚዲያ በሰጡት ምስክርነት ይህንን ሃቅ በይፋ በማጋለጥ የህወሃት የበላይነት የፈጠረው ችግር የበደሉ ገፈት ቀማሽ ከሆነው ህዝችባን አልፎ በምዕራባውያን ወዳጆቹ ዘንድም እንደሚታወቅ አረጋግጥዋል።

Tuesday, January 2, 2018

ኢህአዴግና እነለማ ከ“ምን ይዤ ልመለስ?” እስከ “መግለጫ” ማጽደቅ!


ህወሓት የሚዘውረው ኢህአዴግ ከሁለት ሳምንታት በላይ ስብሰባ አድርጎ “መግለጫ” ያለውን “ቀጭን ትዕዛዝ” በማውጣት ተጠናቋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በለውጥ አራማጅነት ሲጠቀሱ የነበሩት እነለማ መገርሳ “መግለጫውን” አብረው አጽድቀው ወጥተዋል። “የጨለንቆን ፍጅት የፈጸመው ማነው?” የሚለውም ደፋር አጀንዳ አብሮ የሞተ ጉዳይ ሆኗል። “ምን ይዤ (ወደ ሕዝቤ) ልመለስ?” በማለት ወደስብሰባው የገቡት ኦህዴድና ብአዴን “የተቀናጁ ተጨማሪ እርምጃዎች” እወስዳለሁ (መግደሌን እቀጥላለሁ) ለሚለው የህወሓት “መግለጫ” ይሁንታቸውን ሰጥተው ወጥተዋል።

ሀገርና ወገን ለማዳን አዉሬዉን ማስራብ

ሺፈራዉ አበበ
Remittance Embargo against the repressive Ethiopian government.
ላለፉት ሁለት አመታት የትዉልድ አገራችን በጣም አሳሳቢ በሆነ የፖለቲካና የሰላም ቀዉስ ዉስጥ ትገኛለች። በሺህዎች ሞተዉ፣ ባስር ሺህዎች ታስረዉ፣ በመቶ ሺህዎች ከቤት ከቀያቸዉ ተፈናቅለዉ ያሉበት ወቅት ላይ ነን። መንስኤዉ ግልጽና ቀጥተኛ ነዉ፤ ባንድ በኩል፣ የኢትዮጵያን ህዝብ ስድስት ፐርሰንት ብቻ የሚወክሉ፣ ግን ያገሪቱን የመከላከያ፣ የደህንነት፣ የመንግስት ተቋማትና፣ ቁልፍ የኢኮኖሚ አዉታሮች ለ27 ዓመታት ተቆጣጥረዉ የዘለቁ፣ ለስልጣን ጥማቸዉና ለንዋይ ፍቅራቸዉ ዳርቻ የሌለዉ፣ እንደአገር መሪ ሳይሆን እንደመንደር ወሮበላ የሚያስቡና የሚሰሩ፣ ጸረ-ሀገር ህወሃት-ወያኔዎች አሉ።