Translate

Monday, June 30, 2014

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን ባለሥልጣናት እገታ ላይ መሆኑን በማስመልከት የወጣ መግለጫ ሰኔ 23 ቀን 2006 ዓ.ም

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን ባለሥልጣናት እገታ ላይ መሆኑን በማስመልከት የወጣ መግለጫ
ሰኔ 23 ቀን 2006 ዓ.ም
የግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓም ለሥራ ጉዳይ በየመኒያ አየር መንገድ አይሮፕላን ተጉዞ በትራንዚት ሰንዓ ከተማ እያለ በየመን መንግሥት ፀጥታ ኃይሎች በሕገወጥ መንገድ ታግቷል። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን የጉዞው መዳረሻ አልነበረም፤ ከየመን ጋርም የሚያገናኘው ምንም ጉዳይ አልነበረውም። የየመን መንግሥት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አግቶ ለአንድ ሰዓት እንኳን ለማቆየት ምንም ምክንያት የለውም። በዚህም ምክንያት ያለአግባብ የታገተብን የንቅናቄያችንን አመራር በአስቸኳይ እንዲፈታ በተለያዩ መንገዶች ላለፈው አንድ ሣምንት ያደረግነው ጥረት እስካሁን አልተሳካም። እንዲያውም የየመን ባለስልጣናት አምባገኑን ወያኔ ለመርዳት ባለው ፍላጎት ሳቢያ መሪያችንን አሳልፎ ሊሰጠው ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት አድሮብናል።
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ በሀገራችን በኢትዮጵያ ውስጥ ፍትህ፣ ነፃነትና ዲሞክራሲ እንዲሰፍን ጊዜውን፣ እውቀቱንና ጉልበቱን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን አሳልፎ ለመስጠት የተዘጋጀ፤ ዝግጁነቱንም በተግባር ያሳየ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው። የየመን መንግሥት ከዘረኛውና ፋሽስታዊው ወያኔ ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ታጋይ መሪያችን ላይ እየፀመ ያለውን ደባ የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲያውቅ የንቅናቄዓችን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ወስኗል።

አንጋፋው የነጻነት ታጋይ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን የፀጥታ ሃይሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ግንቦት 7 ዛሬ አስታውቋል::

Breaking News: አንጋፋው የነጻነት ታጋይ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን የፀጥታ ሃይሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ግንቦት 7 ዛሬ አስታውቋል
ግንቦት 7 ዛሬ ለጋዜጠኞች እና ለአባላቶቹ በላከው መግለጫ የድርጅቱ ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ለስራ በሚንቀሳቀሱበት ሰአት ትራንዚት በአደረጉበት በየመን አውሮፕላን ጣቢያ ውስጥ በፀጥታ ሃይሎች መወሰዳቸውን አስታውቋል።

Sunday, June 29, 2014

እያበበ የመጣዉ ህዝባዊ ትግል

ኢትዮጵያ ህዝብ ለብዙ ዘመናት እንወድሀለን በሚሉት ነገስታት ተረግጧል፤ ህብረተሰብዓዊነት አመጣንልህ ባሉት ወታደራዊ አምባገነኖችም ለ17 አመት እጅና እግሩን ታስሮ ተገዝቷል። እነዚህ ሁለት ለህዝብ ደንታ የሌላቸዉ መንግስታት ተራ በተራ በህዝብ ትግል ተንኮታኩተዉ የታሪክ ቅርጫት ዉስጥ ገብተዋል፤ ሆኖም ሁለቱንም መንግስታት በመራራ ትግል አሸንፎ የጣለዉ የኢትዮጵያ ህዝብ የትግሉን ዉጤት ማስጠበቅ ባለመቻሉ ይህ ኃያልና የረጂም ዘመን ታሪክ ባለቤት የሆነ ህዝብ ዛሬም ነፃ አወጣንህ በሚሉት ዘረኛ አምባገነኖች እየተረገጠ ነዉ። አዎ! የኢትዮጵያ ህዝብ ዛሬም እየተረገጠ ነዉ። ዛሬም አየታሰረ ነዉ። ዛሬም እየተገደለ ነዉ። ዛሬም ይህንን ሁሉ በደል የሚያደርሱበትን የአንድ ወንዝና የአንድ መንደር ምርት የሆኑ ዘረኛ አምባገነን ገዢዎችን ከጭንቅላቱ ላይ ለማዉረድ እየታገለ ነዉ። በእርግጥም የኢትዮጵያ ህዝብ ከምን ግዜም በተለየ መልኩ የወያኔን ዘረኛ አገዛዝ አምርሮ እየታገለ ነዉ፤ በተለይ በዚህ በያዝነዉ አመት ወያኔንና ሃያ ሁለት አመት ሙሉ የገነባዉን ዘረኛ ስርዐቱን ለመደምሰስና ኢትዮጵያ ዉስጥ በፍትህና በእኩልነት ላይ የተመሰረተ ስርዐት ለመገንባት የሚደረገዉ የሞት የሽረት ትግል ተጠናክሮ ቀጥሏል።

መዝገቦቹ መልሰው ተቀራረቡ የእምነት ክህደት ቃል በኃይል አስፈርመዋቸዋል

Tsion Girma's photo. 
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በስድስቱ ጦማሪያንና በሦስቱን ጋዜጠኞች ላይ የፌደራል ፖሊስ የተለያየ ምክንያት እየሰጠ ቀጠሮ የሚያራዝመውን ሁለት መዝገብ አንዴ ሲያቀራርበው መልሶ ደግሞ ሲያራርቀው ቆይቶ አሁን ደግሞ መዝገቦቹን መልሶ አቀራርቧቸዋል፡፡እስረኞቹ ራሳቸውን መከላከል በማይችሉበት ኹኔታ ፖሊስ ያረቀቀውን የእምነት ክህድት ቃል ተገደው እንዲፈርሙ አድርጓቸዋል፡፡
የሦስቱ ብሎገሮች አቤል ዋበላ፣በፍቃዱ ኃይሉና ማኅሌት ፋንታሁን ቀጠሮ ለዛሬ ሰኔ 22 ቀን 2006 ዓ.ም እንዲቀርቡ የሚል የነበረ ሲኾን ከጠዋት ጀምሮ ችሎቱን ለመታደም የመጣውን ቤተሰብ፣ጓደኞቻቸው፣ጋዜጠኞች፣ዲፕሎማቶችና የወጣቶች ደጋፊዎች በአጠቃላይ ወደ ሦስት መቶ የሚጠጋ ሰው ከችሎት ውስጥ የሚሰማውን አዲስ ነገር ለመጠበቅ በግቢው ውስጥ ቆመው ነበር፡፡ ከጠዋቱ አራት ሰዓት አካባቢ የእስረኞቹ ጠበቃ አቶ አመኃ መኮንን ተጠርተው የመዝግብ ቤት ጸሐፊዋ ስለሌለች ችሎቱ ለከሰዓት በኋላ እንደተዛወረ ይነገራቸዋል፡፡ እርሳቸውም ችሎቱን ለመከታተል ለቆመው ሰው መልዕክቱን ያስተላልፋሉ፡፡ ጥቂት ሰዎችም ይህን መልዕክት ሰምተው ግቢውን ለቀው ይወጣሉ ብዙኃኑ ግን እዛው እንደቆሙ መጨረሻውን ለማየት መጠባበቅ ይጀምራሉ፡፡

የቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ጥፋቱ ምንድን ነው?

"ቴዎድሮስን ነጥሎ የማጥቃት ዘመቻ ምክንያቱ ምንድን ነው?"

teddyafro t

ቴዎድሮስ ካሣሁንን በአካል አላውቀውም፤  በዘፈንና በጭፈራ በእውነት ተደሳች መሆን ካቃተኝ ቆይቷል፤ ከ ኅዳር 1967 ጀምሮ ነው የቆረቆረኝ፤ ይህ ሰው እንደሰውና እንደ ኢትዮጲያዊ በየጊዜው የሚደርስበትን ወደ ግፍ የሚጠጋ በደል ስመለከት ያው የለመድነው ምቀኝነት ነው እያልሁ ሳልፈው ቆየሁ፤ ግን በደሉ አላቆም አለ፤ ማንም ሊደርስለት አለመቻሉ ይበልጥ ያሳዝናል፣ በእሱ ላይ ተከታታይ  የደረሰበት በደል የሕግ ያለህ የሚያሰኝ ነው፤ በቴዎድሮስ ካሣሁን ላይ በተቀነባበረ መንገድ የሚፈፀመው ማሰቃየት ማንንም ሰው የሚያሳስብ ነው፤ ምክንያቱ ምንድን ነው? በግልጽ የታወቀ ነገር የለም።

ኢትዮጵያዊው-ኖርዌጂያን ኦኬሎ ኦካይ ኦቻላ ”ሞት ሊበየንበት ይችላል” -በሽብርተኝነት ክስ ሞት ተፈርዶባቸው ሞታቸውን የሚጠባበቁ 127 ሰዎች ኣሉ

በኖርዌይ ሃገር ውስጥ በኖርዌጂያንኛ የሚታተመው ዳግብላደት የተባለው ጋዜጣና ድረ-ገጽ ”ኢትዮጵያዊው-ኖርዌጂያን” ኦኬሎ ኦካይ ኦቻላ በሚቀጥለው ሳምንት ሞት ሊበየንበት ይችላል” ሲል ኣውጥቶኣል።
”ባለፈው ሳምንት ለማወቅ እንደተቻለው ዕድሜው 52  የሆነና  ኦኬሎ ኦካይ ኦቻ  የተባለ ኖርዌጂያን ኢትዮጵያ ውስጥ በሽብርተኝነት ተከሶ በእስር ላይ ይገኛል።” tiltalt for terror በማለት የጀመረው የኖርዌዩ ዳግብላደት ሲቀጥልም…”የኢትዮጵያ መንግስት ቃለ ኣቀባይ እንደሚለው ገንዘብ ኣሰባስቦና ኣጥቂ ቡድን መልምሎ ኣደጋ ለማድረስ ሲሞክር ያዝነው በማለት መከሰሱን ያትትና በበኩላቸው የኖርዌዩ የሰብኣዊ መብት ጥበቃም ሆኑ የዓለም ኣቀፉ ሰብኣዊ መብት ተሟጋቾች ድርጊቱን በጥብቅ ያወገዙት ሲሆን፣ ኣያይዘውም ለዚሁ ድረ-ገጽ ታሳሪው ግለሰብ ያለበት ሁኔታ ከወትሮው የከፋ እንደሆነም ስጋታቸውን እንደገለጹለት ያወሳል።
 ኢትዮጵያንም ሆነ የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት፣ በኣሁኑ ወቅት በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ውስጥ የሚገኙትን  ኦኬሎ ኦካይ ኦቻ ”በሚገባ ያውቃሉ” ያሉዋቸውን የሰብኣዊ መብት ተሟጋችና ኖርዌጂያን ፈሊክስ ሆርነ ን  ኣነጋግሮ ድረ-ገጹ ያገኘው መልስ ”ኖርዌጂያኑን ኦኬሎ በሚቀጥለው ሳምንት የሚሰየመው ችሎት ሞት ሊበይንበት ይችላል” በማለት የገለጹ ሲሆን ኣክለውም፣
”በሃገሪቷ ውስጥ በሽብር ወንጀል የሚከሰሱት ዜጎች የሚገጥማቸው የሞት ፍርድ ነው። ነገር ግን እነዚህ ሞት የሚፈረድባቸው ዜጎች ምንም ማስረጃ ያልቀረበባቸው ናቸው። በሽብር ክስ ስለተከሰሱ ብቻ ዕድላቸው ይሄው ነው። በሞት ቀጠና የሚገኙትን ዜጎች የሚዘግበው ዓለም ኣቀፉ ድርጅት በኢትዮጵያ በእስር ቤት ውስጥ በሞት ቀጠና (ሴል) የሚሰቀሉበትን ወይም የሚገደሉበትን ጊዜ የሚጠባበቁ 127  ዜጎች  ይገኛሉ ሲል ፈሊክስ ሆርነ ለድረ- ገጹ ገልጸዋል።

Thursday, June 26, 2014

የወያኔን የጥፋት ድግስ እናምክን!

ኢትዮጵያን የሚገዛው ጉጅሌ ሀገራችንን እየወሰደበት ያለው አደገኛ አቅጣጫ አሳሳቢ ከመሆን አልፎ የአደጋውን መራራ ፍሬ ማየት ከጀመርን ሰነበትን። የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች ወሳኝ ከሆነው የወደፊቱ የጋራ ጥቅማቸውና ህልውናቸው በበለጠ ልዩነታቸውና ያለፈ ታሪካቸው እንደዋናው ነገር እየተቆጠረ ለሚሰበከው ስብከት የኢትዮጵያ ህዝብ አስተዋይ ባይሆን ኖሮ እስካሁን ብዙ ጥፋት በደረሰ ነበር።
ህወሃት በህዝቡ ውስጥ የኖረውን ልዩነት የጠብ፣ የግጭትና የመፈራራት መሰረት በማድረግ በሥልጣን ላይ ለመቆየት ካለው ምኞት የተነሳ በመደዴ ካድሬዎቹ አማካኝነት ለዘመናት አብሮ የኖረውን ህዝብ በማቃቃር እኩይ ተግባር ላይ ተጠምዶ ይገኛል።
ህወሃት ይህን የማጋጨት ስራ በተለይ በስልጣን የመቆየት ፍርሃት ባባነነው ቁጥር የሚጠቀምበት መሳሪያ አድርጎታል። በባህርዳር ላይ የብሄረሰቦች ኳስ ጭዋታ ውድድር ምክንያት አድርጎ፣ መደዴ ካድሬዎቹን አሰማርቶ ስታዲዮም ውስጥ ኦሮሞዎች እንዲሰደቡ ካደረገ በኋላ ነገሩን ከማረጋጋት ይልቅ በኦሮሞኛ የቴሌቪዥንና ሬድዮ፣ ኦሮሞዎች በአማራዎች ተሰደቡ ብሎ ያስነገረው ለምንድን ነው? ከዚያ በኋላ በኦሮሚያ የተለያዩ አካባቢዎች ቁጣና ጠብ ለመቀስቀስ ብሎም በዚህ ጠብ ውስጥ ገላጋይ በመምሰል የአንዱ ብሄር ጠባቂ መስሎ ለመታየት ጉዳዩን ባልተረዱ የዋሆች ውስጥ ለመግባት ይፈልጋል። በአማራ ተወላጆች አካባቢ እኛ ከሌለን ኦሮሞ ይፈጇቹኋል፤ በኦሮምያም በሶማሊያም እንዲሁ በተዘጋ በር ውስጥ በተቃራኒው ዘረኝነትንና መከፋፈልን በመስበክ ንጹሃኑ ህዝብ ከፍርሃት ተነስቶ ተገዥ ደጋፊዎቹ እንዲሆኑ በማድረግ ላይ መሆኑንም ያልገባቸው የዋሆች ይኖራሉ። ህወሃትንና ባህርዩን በቅጡ ለምናውቀው ወገኖች ግን ይህ ተንኮሉ ትልቅ ሚስጥር አይደለም።

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሠራዊት ሰኔ 16/2006 ዓ/ም በወልቃይት አድነጣ በተሰኘ ስፍራ ድል ተቀዳጀ!

Image
አምባገነኑ የወያኔ አገዛዝ የይስሙላውን ምርጫ በመጪው ዓመት እንደተለመደው ግልጽና ፍትሃዊ ባልሆነ መልኩ ለማከናወን ሲል ገና ከአሁኑ ለለውጥ የተነሳሱ ዜጎችን በማሰርና በማሳደድ ብሎም ደብዛቸውን እያጠፋ በሚገኝበት በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሠራዊትየወገን ደራሽ ጥቃቱን በጎጠኛው ቡድን ታጣቂዎች ላይ መውሰዱን ቀጥሏል።
በሰኔ 16/2006 ዓ/ም በወልቃይት አድነጣ በተሰኘ ስፍራ በስርዓቱ የሚሊሻ ታጣቂ ላይ በወሰደው ወታደራዊ እርምጃ አስራ ስምንት(18) ገድሎ ሁለት(2) ማርኳል የምርኮኞቹ ስም1ኛ- ቻለው ሲሳይ 2ኛ- ተጫነ ንጉሱ ሲሆኑ ሠራዊቱ ለሁለቱም ምርኮኞች ስለወቅቱ የኢትዮጵያ ሁኔታና ስለ ድርጅቱ አላማና ግብ በማስተማር ለቋቸዋል።

Wednesday, June 25, 2014

በደቡብ ክልል እየታየ ያለው መንግስታዊ አፈናና ፀረ-ሕግ አቋም እንዲገታ ትግላችንን አጠናክረን እንቀጥላለን! (UDJ)

UDJ
June 24, 2014
ከአንድነት ፓርቲ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ
ባለፉት 23 ዓመታት የኢትዮጵያ ሕዝብ ስርዓቱ አምጦ የወለዳቸው ሀገራዊ አፈና፣ ማዋከብ፣ የመኖር ዋስትናን መንፈግ፤ ዜጎችን ማሰደድና ማሰር የተለመዱ ድርጊቶ ሆነው ኖረዋል፡፡ አሁንም በዚህ አስከፊ የአፈና መንገድ ጉዞውን ቀጥሏል፡፡ የስርዓቱ መንግስታዊ አፈናና ፀረ-ሕዝብ አቋም በመላ ኢትዮጵያ የተዘረጋ ቢሆንም ፓርቲያችን በእንቅስቃሴዎቹ ውስጥ እንደታዘበው በደቡብ ክልል በተለየ ሁኔታ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ በተለይም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በክልሉ የሚገኙ የተለያዩ ሹማምንቶች ባደረባቸው የገዥነት መንፈስ ሰላማዊ እንቅስቃሴዎችን በማፈንና ብሎም ያለምንም ማስረጃና ምክንያት ሰላማዊ ታጋዮችን ወደ እስር ቤት በመክተት ተግባራዊ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡UDJ/Andinet party logo
ከዚህ በፊት በክልሉ በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ የፓርቲያችን ከፍተኛ አመራሮች ከዞኑ አመራሮች ጋር ውይይት ሲያካሂዱ ድንገተኛ ወረራ ተደርጎና የግቢ በር ተሰብሮ ወደ እስር ቤት ተወስደው ነበር፤ ቁጫ ላይ ጠርተነው የነበረው ሰላማዊ ሰልፍም እንዲሁ በጉልበት፣ በእስርና አፈና እንዳይካሄድ ተደርጓል፤ ይባስ ብሎ ደግሞ የክልሉ ዋና ከተማ በሆነችው አዋሳ የጠራነው ሰላማዊ ሰልፍ ተገቢውን ህጋዊ ሂደት ቢያልፍም በህገ-ወጥ እስር እንዲጠናቀቅ ሆኗል፡፡ ይህ እውነትም በክልሉ በተለየ ሁኔታ መንግስታዊ አፈናና ፀረ-ሕግ አቋም እንዳለ ያረጋገጠ ነው፡፡

በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብትን የደፈጠጡ አገር አልባ ናቸው!


ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
32451fd6d49697411375563081ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ወንጀል ፍፃሜ መሪ ተዋንያን ሆነው ከቆዩ በኋላበመሰደድ በአሜሪካ እራሳቸውን ደብቀው በተቀመጡ የሰብአዊ መብትደፍጣጮች ላይ የዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ የፍትህ መምሪያ ጥቆማእንዲቀርብለት ኢትዮጵያውያንን/ትን በማበረታታት ላይ ይገኛል፡፡
እነዚህ በሰው ልጆች ላይ ወንጀልን የፈጸሙ ጨካኞች በሰው አገር ሄደው ተደብቀዋል፡፡ እነዚህ ወንጀለኞች በዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ በበማታለል ገብተው ለ30 ዓመታት ተደብቀዋል፡፡ እነዚህ በሰው ደም የተዘፈቁ ወንጀለኞች በቀላሉ ሊያዙ በሚችሉበት አገር በመሄድ ለድፍን ሶስት ዓመታት የተደበቁም አሉ ፡፡

‹‹ …ያኔ በምወደው የጋዜጠኝነት ሙያ እየሰራሁ እቀጥላለሁ›› ጀግናው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ (ከቃሊቲ እስር ቤት)

በጋዜጠኛ ኤሊያስ ገብሩ
ቅዳሜ ሰኔ 14 ቀን 2006 ዓ.ም ከታች በፎቶግራፍ የምንታይ [ፎቶግራፉን ያነሳው አብነት ረጋሳን ጨምሮ] fጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በዓለም የጋዜጠኞች እና የዜና አታሚዎች ማኅበር የዓመቱ የወርቅ ብዕር የ “pen Golden of freedom 2014″ ተሻላሚ በመሆኑ ‹‹እንኳን ደስ ያለህ›› ለማለት ኬክ አስጋግረን ወደቃሊቲ አምርተን ነበር፡፡
press
ቁጥራችን መብዛቱ በቃሊቲ ያሉ ፖሊሶችን ግር ማሰኘቱ አልቀረም ነበር፡፡ ተፈትሸን ስንገባ አንድ የፖሊስ ኃላፊ አስቁመውን ‹‹የመጣችሁበትን ነገር አውቀነዋል፣ ቀለበት ይዛችኋል›› አሉን – ቆጣ በማለት፡፡ እኛ አስክንድር ነጋን እና አንዷለም አራጌን ልንጠይቅ እንደመጣን አስረዳናቸው፡፡ በዕለቱ አንዲት በቃሊቲ የታሰረች ሙስሊም እና በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ታስሮ የሚገኝ ሙስሊም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የጋብቻ ሥነ-ሥርዓት የሚያደርጉበት ፕሮግራም በመኖሩ መረጃው ለፖሊሶች በመድረሱ ነበር ፖሊሱ እኛን እንዲጠየቁ ያስገደዳቸው፡፡ [የሙሽሮቹን ጉዳይ ጋዜጠኛ ዳዊት ሰለሞን በፌስ ቡክ ገጹ ከሁለት ቀን በፊት ጽፎታል]

ለጂቡቲ በነፃ የተሰጠው ውኃ የሁለቱ አገሮች ስትራቴጂካዊ የውህደት አካል መሆኑን መንግሥት አስታወቀ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ በጠረፍ አካባቢ ለጂቡቲ በነፃ ለውኃ ቁፋሮ የሚውል መሬት መስጠቱ፣ ኢትዮጵያና ጂቡቲ የጀመሩት ስትራቴጂካዊ የመዋሀድ አካል መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ሰኔ 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ለአገር ውስጥ ጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ ባለፉት ሁለት ሳምንታት የኢትዮ-ጂቡቲ የጋራ ኮሚሽን 12ኛ ስብሰባውን ያካሄደ መሆኑን፣ ሁለቱም አገሮች የጀመሩትን የልማትና የውህደት ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ለማፋጠን የሚያስችሉዋቸው የጋራ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ተናግረዋል፡፡ አምባሳደሩ እንዳሉት ፍትሕ፣ ኢምግሬሽን፣ ትምህርት፣ ጤና፣ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ የሠራተኞች ልውውጥ፣ ንግድና ኢንቨስትመንትና የድንበር ንግድ የስብሰባው ዋነኛ አጀንዳዎች ነበሩ፡፡ 
አምባሳደር ዲና በቅርቡ ለጂቡቲ በነፃ የተሰጠው የውኃ ቁፋሮ ከወዳጅነት በዘለለ ለኢትዮጵያ ምን ጠቀሜታ ይሰጣል በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፣ ውሳኔው ቀደም ሲል ስምምነት ላይ የተደረሰበት የስትራቴጂካዊ የውህደት ዕቅድ ሒደት አካል መሆኑን አስረድተዋል፡፡
በ‹‹ስትራቴጂክ ኢንትግሬሽን›› ዕቅዱ ስምምነት መሠረት ሁለቱም አገሮች በኢኮኖሚና በመሠረተ ልማት የተደገፈ የፖለቲካ ውህደት ለማምጣት በኢትዮጵያ በኩል ለጂቡቲ ዜጎች የተለየ ጥቅም (Preferential Treatments) ለማስጠበቅ የተወሰነ መሆኑን፣ ለጂቡቲ በነፃ የተሰጠው የውኃ ቁፋሮ የዚሁ ውሳኔ አካል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ‹‹እንደ ኢምፔርያል ዘመን አንድ አገር ሌላ ሉዓላዊ አገር በኃይልና በጦር ወደ ግዛቱ ማስገባት አይችልም፡፡ የጂቡቲ ዜጎች ግን ወደውና ፈልገው ወደ ቀድሞ ቤታቸው የሚመጡበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም፤›› ብለዋል ዓላማውን ሲያብራሩ፡፡

Tuesday, June 24, 2014

የመጨረሻዉ መጀመሪያ

በቅርቡ በተከታታይ አገር ቤት ዉስጥ ቅርጽና ይዘት እየያዙ የምናያቸዉና ማንም አሌ የማይላቸዉ ግዙፍ እዉነታዎች ሁሉም በአንድነት የሚጠቁሙት አይቀሬዉ የወያኔ መጨረሻ መጀመሩን ነዉ። ከዚህ ቀደም በግልጽ እንዳየነዉ ወያኔ አንድ ቦታ ሲሸነፍ ሌላ ቦታ እያሸነፈ በጉልበትም በተንኮልም የፖለቲካ የበላይነቱን እንደያዘ ከሃያ ሁለት አመት በላይ ቆይቷል። ወያኔ ለአመታት ህዝብን ያታለለባቸዉ የዉሸት ክምሮችና ህዝባዊዉን ትግል ወደ ኋላ ለመጎተት የተጠቀመባቸዉ ስልቶች ዛሬ ሁሉም ሙጥጥ ብለዉ አልቀዉበት ዬኔ ነዉ ብሎ በሚመካበት ትግራይ ዉስጥ ጭምር መግቢያና መዉጪያዉ የጠፋዉ የተከበበ አዉሬ መስሏል። በያዝነዉ የ2006 ዓም ሁለተኛዉ አጋማሽ ወያኔ ጨካኙን የአግአዚ ኃይል እዚህም እዚያም አሰማርቶ ከሚቆጣጠራቸዉ ጥቂት አደባባዮች ዉጭ እንደቀድሞዉ በግልጽ ወጥቶ ወያኔን የሚያሞግስ ወይም የወያኔን የሌለ ገድል የሚናገር ሰዉ የለም። በሌላ በኩል ደግሞ በተለያዩ የትግል ስልቶች ወያኔን የሚታገሉ ኃይሎች አገር ዉስጥና ከአገር ዉጭ ኃይላቸዉና ቁርጠኝነታቸዉ እየጨመረ መጥቶ ወያኔ ያንን የተለመደ የቀቢፀ ተስፋ እርምጃዉን እዲወስድና የራሱን የመጨረሻ እሱ እራሱ ሳይወድ በግዱ እንዲያፋጥነዉ እያደረጉት ነዉ።
የአገራችንን አንድነት ሊያላሉና ኢትዮጵያ የሚለዉን ታሪካዊ ስም ከታሪክ ዉጭ ማድረግ ከሚችሉ አደገኛ የወያኔ ባህሪዮች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ ዘረኝነቱና ለአገር አንድነትና ዳር ድንበር መከበር ያለዉ የግድየለሽነት ባህሪይ ነዉ። ዛሬ ወያኔ በአራቱም ማዕዘን በየቀኑ አየጨመረና እያየለ የሚሄደዉን የህዝብ ቁጣ ለማብረድና አፋፍ ላይ ለደረሰዉ ስርዐቱ ተጨማሪ ግዜ ለመግዛት የሚወስዳቸዉ እርምጃዎች ከዚሁ ከዘረኝነት ባህሪይዉ የሚመነጪ እርምጃዎች ናቸዉ።

የደገሃቡር የጸጥታ አዛዥ ተገደሉ

ከሶስት ቀናት በፊት የኦጋዴን ነጻ አውጭ ድርጅት ታጣቂዎች በደጋሃቡር ላይ ድንገት በፈጸሙት ጥቃት ከሞቱት 7 የመንግስት ታጣቂዎች በተጨማሪ የደጋሃቡር የጸጥታ ጉዳዮች ሃላፊ የሆኑት አቶ አሻር ፣ በታጣቂዎች ጥይት ቆስለው ወደ ደጋሃቡር ሆስፒታል ከተወሰዱ በሁዋላ ዛሬ ጠዋት ሰኔ 17 ቀን 2006 ዓም ማረፋቸውን የደረሰን ዜና አመልክቷል።

የአካባቢው የልዩ ሚሊሺያ አዛዥ የሆኑት ሙሃመድ ዳይክ ክፉኛ ቆስለው አሁንም በሆስፒታሉ በመታከም ላይ ሲሆኑ፣ አማጽያኑ ጥቃቱን ፈጽመው ከአካባቢው መሸሻቸው ታውቋል።
ኢህአዴግ በክልሉ እየተባባሰ የመጣው የጸጥታ ሁኔታ ስጋት ላይ መጣሉን ተከትሎ ከኦብነግ ጋር ሊያደርገው ያሰበው ድርድር ሁለት የኦብነግ አመራሮች ናይሮቢ ኬንያ ላይ ተይዘው ከተወሰዱ በሁዋላ ተደናቅፏል። መሪዎቹ እጃቸውን በፈቃዳቸው እንደሰጡ መንግስት ቢገልጽም፣ እስካሁን ድረስ የታፈኑት መሪዎች ቀርበው እጃቸውን በፈቃዳቸው መስጠታቸውንና አለመስጠታቸውን አልተናገሩም።

መርህ አልባነት – ከደሞዝ ጭማሪው ጀርባ

መንግስት “የዋጋ ንረትን በማይቀሰቅስ ሁኔታ” “የተጠና” የመንግስት ሰራተኞች የደሞዝ ጭማሪ ከሀምሌ ወር 2006 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚያደርግ ጠቅላይ ሚንስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ መግለፃቸው የሰሞኑን አበይት ዜና ሆኗል። አቶ ኃይለማሪያም “ሌጋሲያቸውን የሚያስቀጥሉላቸው” አቶ መለስ በምርጫ ወቅት ምንም አይነት የደሞዝ ጭማሪ እንደማይደረግ በህይወት በነበሩበት ወቅት ተናግረው እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡ ከመንግስት ምንጮች (በተለይም ከስርአቱ የዳታ መጋገሪያ – ማዕከላዊ ስታትስቲክስ ባለስልጣን) የሚወጡትን በፖለቲከኞች የሚፈበረኩ አሐዞችን ወደጎን ብለን አሁን ባለው ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ሲቪል ሰርቫንቱ ህልውናውን ማስቀጠል በገመድ ላይ እንደመጓዝ እጅግ አስቸጋሪ ሆኖበታል፡፡ ወሩን በአግባቡ ከማያሳልፍ ገቢ ጋር የገዢው ፓርቲ ፖለቲካዊ ጫና ሲደመር የመንግስት ሠራተኛ መሆን “ካለመኖር አንድ ደረጃ ብቻ ከፍ ብሎ ያለ” የኑሮ ደረጃ ሆኗል፡፡ የአንድ ለአምስት ጥርነፋው፣ ከሥራ ብቃት ይልቅ ፖለቲካዊ ታማኝነትን የሚያስቀድመው የዕድገት መሠላል፣ በየጊዜው የሚመጡ በቅጡ ሳይላመጡ የተዋጡ የአሠራር ስርአቶች (BPR, BSC, ካይዘን ወዘተ)፣ የማይመች የስራ አካባቢ ወዘተ ሲቪል ሰርቫንቱን የሥራ ፍላጎቱ የተቀዛቀዘ፣ ማምለጫ አማራጭ ፈላጊ እና ስልቹ ማድረጉ የማይታበል ሐቅ ነው፡፡

Monday, June 23, 2014

የሶማሊው ክልል መሪ የመንግስት ደህንነቶች ሊገድሉዋቸው እንደሚችሉ በመጠቆም ጠባቂዎቻቸውን ቀየሩ

የሶማሊ ክልል መሪ አብዲ ሞሃመድ ኡመር የፌደራሉ መንግስት የደህንነት ሰዎች ሊገድሉኝ ይፈልጋሉ በማለት ቀድሞ ሲጠብቁዋቸው የነበሩ ጠባቂዎቻቸውን በመቀየር አካባቢው በታማኞቻቸው በአይነ ቁራኛ እንዲጠበቅ እያደረጉ ነው።

ካለፉት ሳምንታት ጀምሮ ወደ የፕሬዚዳንቱ ቢሮ ወደሚገኝበት አካባቢ የሚዘዋወሩ ሰዎች ልዩ ፍተሻ እየተደረገባቸው ነው።
አቶ አብዲ ባለፈው ሳምንት ከ9 ዞኖችና ከ68 ወረዳዎች የተውጣጡ 1 ሺ 500 የሚሆኑ ከመላው ኦጋዴን የተውጣጡ የአገር ሽማግሌዎችን ሰብስበው ማእከላዊውን አስተዳደር የሚተቹ ንግግሮችን ተናግረዋል።
የደህንነት ሃላፊው ጌታቸው አሰፋ በሙስና የተበለሻ “ሌባ ነው” ሲሉ የፈረጁት አቶ አብዲ፣ ለፓስፖርት ማውጫ በሚል ከኦጋዴን ተወላጆች ገንዘብ እንደሚቀበሉ ለተሰብሳቢው ተናግረዋል።
“አትፍሩ የኢህአዴግ የደህንነት ሃይል በሙሉ ከክልላችን ተጠራርጎና ተሰባብሮ እንዲወጣ አድርጌዋለሁ፣ በክልሉ ያለሁት እኔ ነኝ” በማለት የተናገሩት አቶ አብዲ፣ ማንኛውም የአገር ሽማግሌ የኢህአዴግን የደህንነት ሃይሎች  እንዳይተባበር ጥሪ አቅርበዋል።
“ኢትዮጵያውያን አይወዱንም፣ መሬታችን እንጅ እኛን አይፈልጉንም፣ እንደሁለተኛ ዜጋም ያዩናል” ያሉት አቶ አብዲ፣ ህገመንግስቱ እስከመገንጠል የሚደርስ መብት ያጎናጸፋቸው መሆኑን ለሽማግሌዎቹ አስረድተዋል።

የ2007 የመንግሰት በጀት ሚስጥር

ከግርማ ሰይፉ ማርይ
(የኢትዮጵያ ፓርላማ አባል)
የኢትዮጵያ በጀት በደንብ አድርጎ ለመረመረው ሀገሪቱ ያለችበትን ፖለቲካ ሁኔታ የሚያሳይ ነው፡፡ ይህም ማለት በበጀቱ ውስጥ የቻይና፣ ምዕራባዊያን ሀገሮች እንዲሁም የምዕራብ ሀገሮች ይዞታ የሚባሉት አለም አቀፍ ባንኮች እጅ በግልፅ የሚታይ ነው፡፡ እንደምታውቁት መንግሰት ለ2007 ዓመተ ምህረት ያቀረበው በጀት ብር 178.6 ቢሊዮን ነው፡፡ ዘጠኝ ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር አካባቢ ማለት ነው፡፡ መደበኛው ወጪ እና የክልሎች ድጋፍ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ የሚሸፈን ሲሆን ዋና ዋና የካፒታል በጀት ደግሞ ከመደበኛ ወጪ እና ክልሎች ድጋፍ ከሚተርፈው አነሰተኛ የሀገር ውስጥ ገቢ እና ለበጀት ጉድለት ለመሸፈን ከታሰበው ከሀገር ውስጥ ባንኮች ብድር ይሸፈናል ተብሎ የሚጠበቅ ነው፡፡ ከአጠቃላይ በጀቱ 19.2 በመቶ ከእርዳታና ብድር ይሸፈናል በዝርዝር ሲታይ ግን የመደበኛ በጀቱ 21.8 ከመቶ፣ የካፒታል በጀቱ ደግሞ 36.5 ከመቶ የሚሸፈነው ከብድርና እርዳታ ነው፡፡
ስንት ሰው እንደሚያስታውስ ባላውቅም የቀድሞ አዲስ ጉዳይ ጋዜጣ (ሁሌም ጋዜጣ ሳስብ የሚናፍቀኝ) በአንድ ወቅት የቀረበን በጀት ይህ በጀት ኢትዮጵያዊ በጀት ነው ወይ? የሚል ጥያቄ አንሰቶ ነበር፡፡ የበጀትን ዜግነት የጠየቀበት ገፊ ምክንያት በዚያን ሰሞን መወያያ፤ በአሁኑ ጊዜ ጠርናፊ ህግ የሆነውን የሲቪል ማህበራት ህግ ነበር፡፡ ይህ አፋኝ ህግ ማነኛውም በኢትዮጵያ ውስጥ የሚንቀሳቀስ ሰቪል ማህበር በጀቱ ከአስር በመቶ በላይ ከውጭ ከሆነ ኢትዮጵያዊ አይደለም ነው የሚለው፡፡ አሁን በሀገራችን የሚንቀሳቀሱት ብዙዎች መንግሰታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የተመዘገቡት በኢትዮጵያዊነት ሳይሆን “ረዚደንት” በሚል ቅፅል ነው፡፡

Sunday, June 22, 2014

ድርብ አኃዝ ዕድገት ወይስ ድርብ ድህነት?


poor1

በኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ የዓለምአቀፍ ልማት ትምህርት ክፍል ሥር የኢኮኖሚ ጥናት የሚያካሂደው የኦክስፎርድ የድህነትና የሰብዕ ልማት ማዕከል (The Oxford Poverty and Human Development Initiative (OPHI)) ሰሞኑን ባወጣው የ2014 የጥናት መረጃ ደሃ ከሚባሉት አገራት ዝርዝር ኢትዮጵያ ከመጨረሻው ሁለተኛ መሆኗን ገለጸ፡፡ የጥናቱ ዘገባ ኢህአዴግ በየጊዜው ከሚያቀርበው የዕድገት ስሌት ጋር በግልጽ የሚጋጭ መሆኑ ተነገረ፡፡

Thursday, June 19, 2014

ጦማሪያኑን እና ጋዜጠኞቹን በተመለከተ ችሎቱ ለፖሊስ ጠንካራ ትዕዛዝ አስተላለፈ


በቁጥጥር ስር ከዋሉ ባለፈው ቅዳሜ (ሰኔ 7 ቀን 2006 ዓ.ም) 50ኛ ቀናቸውን በእሰር ያሳለፉት ስድስቱ ጦማሪያንና ጋዜጠኞች ለአራተኛ ጊዜ የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተፈቅዶባቸዋል። ለአራተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረቡት ከዞን 9 ጦማሪያን መካከል ዘላለም ክብረት፣ ናትናኤል ፈለቀና አጥናፉ ብርሃኔ ሲሆኑ፤ ጋዜጠኞቹ ደግሞ ተስፋለም ወልደየስ፣ ኤዶም ካሳዬ እና አስማማው ወ/ጊዮርጊስ ናቸው። በዕለቱ ችሎቱ መርማሪ ፖሊስ የሚያቀርባቸውን ተደጋጋሚ ምክንያት አጠንክሮ በመፈተሽ በቀጣይ ቀጠሮ ፈፅሟቸው ሊመጣ የሚገቡ አራት ተግባራትን በግልፅ በማስቀመጥ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

የአቶ ሬድዋን ሁሴን የ ”Corporal Interest” ትንታኔ

Redwan Hussein, head of Ethiopia's communication affairs office
በእርሳሱ መሬ---በኢህአዲግ ውስጥ ካሉት ቁንጮ ባለስልጣናት መካካል በሞጋችነታችው እና የተሳካለት የቃላት መደርደር ችሎታቸው አቶ ሬድዋን ሁሴንን የሚተካከላቸው አለ ብዬ አላምንም:: እናም በዚያን ሰሞን የአውራምባው ጋዜጣ ባለቤት አቶ ዳዊት ከበደ እኝሁን ባለስልጣን ቃለ መጠይቅ ሲያደርግላቸው የተለመደውን ባዶና ካድሬያውዊ መልሳቸውን አፈሰሱት:: ታዲያን የእኔን ቀልብ የሳበው ነገር ደጋግመው የጠቀሱት ”Corporal Interest” ብለው የደነቀሩት ቃላትና ስለ ምንነቱም የእኔ መንግስት ጭብጥ ግንዛቤ ነው ብለው ያሉት ነገር ነበር:: አዎን ቃላቱ ልክ እዚህ እንደምታነቡት ነው ጥቅም ላይ የዋለው። ለእንደኔ ብጤው እንግሊዝኛ እንደ ቁምጣ ለሚያጥረው አንድ በቋንቋው ተክኛለሁ የሚል የዚህን ቃል ትርጉምና አጠቃቀም እስካላስረዳኝ ድረስ አባባሉ ሰውየው እንደተጠቀሙበት አይነት አጠቃቀም አንብቤም ሰምቼም ነበር ለማለት ድፍረቱ የለኝም። ትልቁ ትዝብት ያለው ዘጠና ሚሊዮን ህዝብ እየገዛ ካለ መንግስት አፈ ቀላጤ አሳፋሪ ሊባሉ የሚችሉ የአቅም ማነስና የብስለት መታጣት መንፀባረቃቸው ላይ ነው። ለነገሩ በዚያች ሀገር ማፈር ከጠፋ ሰንበትበት ብሏል።ሌላው ቢቀር ቢሯቸውና የስልጣን ቦታቸው የሰጣቸው አጋጣሚና የተመቻቸ ዕድል ከጥቅም ላይ አውለው የራሳቸውን ግላዊና ቡድናዊ የዕውቀት አድማስ ማበልፀግ አለመቻላቸው ወይም አለመፈለጋቸው ዋነኛው አሳዛኝ ነገር ነው። በጣሙን የምንሽማቀቀው ደግሞ ይህን መሰሉ ክስተት ምሁር ነን ፣ ተምረናል ከሚሉ የመንግስቱ ባለሟሎች ጎራም ስናያ ነው።

Wednesday, June 18, 2014

‹‹ይህ ሽልማት የእኔ ብቻ አይደለም፣ የእናንተም ነው›› እስክንድር ነጋ

በኤልያስ ገብሩ ጎዳና
‹‹ይህ ሽልማት የእኔ ብቻ አይደለም፡፡ የእናንተም ነው፡፡ …››
‹‹በእስር ላይ የምትገኙ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያኖች የእኔ ጀግኖች ናችሁ››
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ
‹‹አሁን ደስተኛ ነኝ››
‹‹እስክንድርን ምግብ ማብሰል እያለማመድኩት ነው››
አቶ አንዷለም አራጌ
ከትናንት በስትያ ሰኔ 03 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ላይ ከቅርብ ጓደኛዬ እና የሙያ ባልደረባዬ ጋዜጠኛ አናንያ ሶሪ ጋር ወደቃሊቲ ማረሚያ ቤት [እስር ቤትም ነው] አምርተን ነበር- ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋንና የአንድነት ፓርቲ ጸሐፊ የሆኑትን አቶ አንዷለም አራጌን ለመጠየቅ፡፡ የተለመደውን የፖሊስ ፍተሻ አልፈን ወደ ውስጥ ስንዘልቅ የሰማያዊ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፈ አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ፣ አቶ ሳሙኤል የተባሉ አባልና የ‹‹ነገረ ኢትዮጵያ›› ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው እስክንድርን ሊጠይቁ ቀድመውን ደርሰው ነበር፡፡Ethiopian political prisoners Eskinder Nega and Andualem Arage
…እስክንድርን እና አንዷለምን አስጠራናቸው፡፡ ሁለቱም ሲያዩን ደስ አላቸው፡፡ በተለይ በተለይ የእስክንድር ፈገግታ በጣም ደማቅ ነበር፡፡ ተከፋፍለን ከሁለቱም ጋር ሃሳቦችን መለዋወጥ ጀመርን፡፡
እስክንድር በዓለም የጋዜጠኞች እና የዜና አታሚዎች ማኅበር የዓመቱ የወርቅ ብዕር የ “pen Golden of freedom 2014″ ተሸላሚ በመሆኑ ‹‹እንኳን ደስ ያለህ›› አልኩት፡፡ ‹‹አመሰግናለሁ፡፡ ትናንት አንድ ልጅ ሊጠይኝ መጥቶ ነግሮኛል›› ካለን በኋላ ደግመን ስለሽልማቱ በጋራ ሃሳብ መለዋወጥ ቀጠልን፡፡ እስክንድር ሽልማቱ አዲስ መሆኑን አላወቀም ነበር፡፡

ኮካ ኮላ የተባለው መጠጥ አጠገቤ አይደርስም! (ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም)

ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
ኮካ ኮላ ትክክለኛ ነገር አይደለም!
የኮካኮላ ኩባንያ በታዋቂው የኢትዮጵያ ኮከብ ድምጻዊ ሙዚቀኛ በሆነው በቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ላይ ያደረገውን ስነምግባርን የጣሰ፣ የዘፈቀደ እና ፍትሀዊ ያልሆነ ድርጊት በማስመልከት የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበረሰብ በማህበራዊ እና በመገናኛ ድረ ገጾች ተቃውሞውን በመግለጽ የኮካ ኮላ ምርት እንዳይጠጣ ጥሪውን በማስተላለፍ ላይ ይገኛል፡፡ የዲያስፖፈራው ማህበረሰብ በማያያዝም የኮካ ኮላ ኩባንያ ተንኮልን ባዘለ መልኩ ቴዲን ነጥሎ በማውጣት የአድልኦ ሰለባ እንዲሆን አድርጓበታል በማለት ላይ ነው፡፡ የኮካ ኮላ ኩባንያ 32 የልዩ ልዩ አገሮች ሙዚቃ የቡድን አቀንቃኞችን ለብራዚል የዓለም እግር ኳስ ፌዴሬሽን/FIFA ዋንጫ የመክፈቻ ስነስርዓት ማድመቂያ ሙዚቃ አንድያቀነባበሩ አድርጎ ነበር፡፡ የኮካ ኮላ ኩባንያ በቴዲ አፍሮ ከተቀነባበረው የኢትዮጵያ ሙዚቃ በስተቀር የሁሉንም ዓይነት መሰል ሙዚቃዎች ለቅቋል!boycott coca-cola
አሁን የኮካ ኮላ ምርት እንዳይጠጣ የሚለውን መርህ እቀላቀላለሁ፡፡ ባለፉት ስምንት ዓመታት ሳቀርባቸው የነበሩትን ትችቶቸን ስትከታተሉ ለቆያችሁ በሚሊዮኖች ለምትቆጠሩ አንባቢዎቸ አሁን የኮካ ኮላ ምርት እንዳይጠጣ የሚለውን ቡድን እንድትቀላቀሉልኝ በአክብሮት እጠይቃለሁ፡፡
የኮካ ኮላ ኩባንያ እና ተወካዮች በቴዲ ላይ ስህተት የፈጸሙ መሆናቸውን ከጥርጣሬ በላይ ተገንዝቢያለሁ፡፡ ስሙን አጥፍተዋል፣ ስብእናውን ዝቅ አድርገዋል እናም በአደባባይ በህዝብ ፊት አዋርደውታል፡፡ ይዞት የቆየውን ዝና እና ክብር ነፍገዋል፣ ስሙን ጥላሸት ቀብተዋል፣ እናም በስራው እና በጥሩ ስነምግበሩ ተጎናጽፎት የቆየውን ጥሩ ስሙን አጉድፈዋል፡፡ ፍትሀዊ ያልሆነ፣ ጨካኝነት የተሞላበት እና የሞራል ስብዕናን ባልተላበሰ ሁኔታ አስተናግደውታል፡፡

Tuesday, June 17, 2014

የጀኔራሎቹ የጓዳ ሽኩቻ! – ቀጣዩ ኢታማዦር ማን ነው?



‹‹ደመወዝ አነሰኝ ብሎ ጭማሪ የሚጠይቅ ካለ አሁንኑ ከሰራዊቱ መልቀቅ ይችላል፡፡›› ይህ የጦር ኃይሎች ኢታማዦር ሹምየሆነው ጀኔራል ሳሞራ የኑስ ሁለተኛው የሰራዊት ቀን በተከበረበት ሰሞን ባህር ዳር ከተማ ሙሉዓለም አዳራሽ ከተሰበሰቡት የሰራዊቱ አባላት መካከል የደመወዝ ጭማሪን በተ መለከተ ለተነሳለት ጥያቄ ምላሽ ሲሰጥ የተናገረው ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከአጼ ኃይለስላሴ ዘመነ መንግስት ጀምሮ ዘመናዊ ውትድርናና የጦር ስልት ሰልጣኝ ወታደሮችንና መኮንኖችን በተደራጀ ስልጠና ማፍራት መጀመሯ ይጠቀሳል፡፡ በሀረርና ሆለታ የጦር አካዳሚዎች በመታገዝ ዘመናዊ የውትድርና ሳይንስ ትምህርት መሰጠት የተጀመረው በዚሁ በንጉሱ ዘመን ነበር፡፡ በዚህ መልኩ እየተደራጀ የመጣው የሀገሪቱ ሰራዊት እስከ ኢህአዴግ ወደ ስልጣን መምጣት ዘመን ድረስ የሀገሪቱ ብሄራዊ ሰራዊት ሆኖ ለመዝለቅ ችሏል፡፡ ሆኖም የደርግ ውድቀትን ተከትሎ በነበረው ጊዜ አያሌ የሰራዊቱ አባላት ለስደትና ሞት እንዲሁም ለብተና ለመዳረግ በቅተዋል፡፡

የትግራይን መስቀል ስለመሸከም (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ)

Temesgen Desalegn "Fact" Ethiopian Amharic newspaper editor…ዕለቱ የሁለት ሺ ሶስት ዓመተ ምህረት የመስቀል በዓል የተከበረበት ማግስት፤ ሰሜናዊቷ የኤርትራ አዋሳኝ ወልቃይት ገና ከእንቅልፏ ሙሉ ለሙሉ ባለመንቃቷ፣ እስከ አፍንጫቸው የታጠቁ ጎፈሪያቸው የተንጨ(ባረረ ፋኖዎች በውስጧ ካሉ ተቋማት ወደ አንዱ እያመሩ ስለመሆኑ የጠረጠረች አትመስልም፤ ከኤርትራ የተነሱት ፋኖዎች መዳረሻ በወረዳዋ ታዋቂ የሆነው አወርቅ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በመሆኑ፤ ማንም ልብ ሳይላቸው ልክ እዚያው እንደደረሱ፣ ከፊሎቹ በሰለጠነ ወታደራዊ ስልት ትምህርት ቤቱን ከአጥር ውጪ በመክበብ ድንገተኛ ጥቃት የሚሰነዝር ኃይል ከመጣ ለመከላከል ሲያደፍጡ፤ የተቀሩት ደግሞ ወደ ውስጥ በመግባት በግቢው የሚገኙ መምህራን ሜዳው ላይ እንዲሰበሰቡ ቀጭን ትዕዛዝ አስተላለፉ፤ በጥቂት ደቂቃዎችም ውስጥ ሁሉም በተባለበት ቦታ ተሰበሰበ፤ እያንዳንዷን እንቅስቃሴ በዕቅዱ መሰረት መፈፀሙን በጥንቃቄ ሲከታተል የነበረው የቡድኑ መሪ በቅድሚያ ስለራሱና ጓደኞቹ ማንነት እና ስለወከሉት ድርጅት አጭር ማብራሪያ ከሰጠ በኋላ፣ የትግሉን ዓላማ በስፋት አብራርቶ አስረዳ፤ ሌሎች ጓዶቹም የፖለቲካ ፕሮግራማቸውን ዋና ዋና ርዕሶች የሚገልጹ በአማርኛና ትግርኛ ቋንቋ የተዘጋጁ በራሪ ወረቀቶችን የማደል ስራቸውን በማጠናቀቃቸው እንደአመጣጣቸው በሽምቅ ተዋጊ ስልት ከአካባቢው ተሰወሩ፡፡ ይህ በሆነ በአስራ ሁለተኛው ቀን (መስከረም 30) ደግሞ እዛው ወረዳ ወደሚገኝ ሌላ ትምህርት ቤት ለተመሳሳይ ዓላማ ድንገት ተመልሰው መጥተው ነበር፤ ሆኖም መንገድ ላይ ካደፈጡ ፖሊሶችና ታጣቂዎች ጋር ፊት ለፊት ተገጣጥመው በተፈጠረው ግጭት ሳቢያ ከእነርሱ ወገን አንድ ሲሰዋ፤ ከፖሊስ አባላት አንድ ቆስሏል፤ አንድ መምህርም በገዛ ቤቱ በተቀመጠበት በተባራሪ ጥይት ቆስሏል፤ ፋኖዎቹም የዚያ ቀን ዓላማቸው ከሽፎ ወደመጡበት የኤርትራ በርሃ ተመልሰው ለመሄድ ተገድደዋል…

Monday, June 16, 2014

ለምን የሳሙኤል ዘሚካኤል ጉዳይ ያን ያህል ያስደንቀናል?

ከበትረ ያዕቆብ
ሰሞኑን በማህበራዊ ድረ ገፆች አካባቢ የህዝብን ቀልብ መሳብ የቻለና አሁንም ዋና መወያያ አጀንዳ ሆኖ የቀጠለ ጉዳይ ተከስቷል፡ የሳሙኤልዘሚካኤልየሀሰትዶክተር እናኢንጂነርነት፡፡ ጉዳዩ ብዙዎችን አጃኢብ አስብሏል ፤ አሁን በርካቶች ብስጭታቸዉን እና ቁጣቸዉን በተለያየ መንገድ እየገለፁ ይገኛል፡፡ ብዙ ሰዎች በአንድ ወቅት የስኬት ምልክታቸዉ እስከ መሆን የደረሰና አድናቆታቸዉን ያጎረፉለት ሰዉ ድንገት የሀሰት ሆኖ ሲያገኙት መደናገጣቸዉ አልቀረም፡፡
እርግጥ ነዉ ነገሩ ትንሽ የሚያስገርም ነዉ፡፡ ወጣቱ የሄደበት እርቀት ግራ የሚያጋባና ድፍረቱ የሚያስገርም ነዉ፡፡ ሌላዉን ትተን በሀገር ዉስጥ የሚገኙትን ዩንቨርሲቲዎች ስም ደጋግሞ እያነሳ ይህንን ሸለሙኝ ፣ ይህንን ሰጡኝ ፣ የረዳት ፐሮፌሰርነት ማዕረግ ተበረከተልኝ ወዘተ ማለቱ በእርግጥም ከማሰገረም አልፎ ብዙ ያስብላል፡፡ ያም ሆኖ ግን እኔን ይበልጥ ያስገረመኝ ጉዳዩ የዚያን ያልህ  እንደ ተዓምር የመታየቱ ነገር ነዉ፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ እየተደረገ ያለዉን ዉይይት ስመለከት እንዴ ነዉ ነገሩ ብየ መደነቄ አልቀረም፡፡

አሸባሪው አቃቤ ህግ በአሜሪካ (ቪዲዮ ቅንብር፣ አበበ ገላው)

ህወሃቶች የፈጠራና የሐሰት ክስ እየፈበረኩ በርካታ ለወገንና ለአገር የሚቆረቆሩ ኢትዮጵያውያንን በአገር መክዳት፣ ዘር ማጥፋት እና ሽብር ፈጠራ ወንጀሎች በመክሰስ እና በማሰር ለከፍተኛ ፍዳና መከራ ዳርገዋቸዋል።
የእነ ሽመልስ ከማልን አርአያ እንዲከተሉ ተመልመለው እንደነ እስክንድር ነጋ፣ ርዮት አለሙ፣ ውብሸት ታየ አንዱዓለም አራጌ፣ ናትናኤል መኮንን፣ በቀለ ገርባ፣ የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን እንዲሁም በርካታ ኢትዮጵያውያንን ለእስርና ለሰቆቃ ከዳረጉት አቀብያነ ሕግ መሃል ቴዎድሮስ በሃሩ፣ ዘርሰናይ ምስጋናው፣ ብርሃኑ ወንድምአገኝ በዋነኛነት የሚጠቀሱ ናቸው።
ቴዎድሮስ በሃሩ በአሁኑ ግዜ በአሜሪካን አገር በሰላም የተረጋጋ ኑሮ ለመመስረት ደፋ ቀና እያለ  ይገኛል። ይሁናና በሲልቨር ስፕሪንግ፣ ሜሪላንድ፣ የሚኖረው ግለሰብ ፍርድ ቤት ስላቀረበው መረጃና የሐሰት ክስ ለመናገር ፍቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል። ይህ ቪዲዮ ቴዎድሮስና ተባባሪዎቹ የህወሃቶችን ግፍ በፍርድ ቤት ሽፋን ለማስፈጸም የሰሩትን ወንጀል፣ በንጹሃን ዜጎች ላይ ያደረሱትን መከራና ፍዳ ለማሳየት ይሞክራል።
ህወሃቶች እና ሎሌዎቻቸው በጸረ ሽብር ሕግ ሽፋን በሐሰት ክስ በበርካታ ንጹሃን ዜጎች ላይ ሽብርና ግፍ መፈጸማቸውን የሚያሳዩ ብዙ መረጃዎች መኖራቸውን በቀላሉ መካድ አይቻልም።
Tewodros Beharu served as trusted prosecutor in Ethiopia
Tewodros Beharu served as one of TPLF’s trusted prosecutors that terrorized political prisoners in Ethiopia with false accusations using the globally ridiculed anti-terrorism law.

Sunday, June 15, 2014

ጄኔራል ሰዓረና ጋዜጠኛ እስክንድር

ከኢየሩሳሌም አርአያ
ሰኔ 1 ቀን 1997ዓ.ም፤ በአዲስ ከተማ ት/ቤት የተጀመረው ተማሪዎችንና ንጹሃን ዜጐችን በግፍ የመግደል እርምጃ ተከትሎ አብዛኛው ባለስልጣናት ልጆቻቸውን ከየት/ቤቱ በአጃቢ ያስወጡ ነበር። ወደ ካቴድራል ት/ቤት በሁለት ኮብራ ተጭነው የተላኩ 20 ልዩ የፌዴራል ፖሊሶች የጄ/ል ሰአረና የጄ/ል ብርሃነ (ወዲ መድህን) ሴት ልጆችን አጅበው ሄዱ። ሁለቱ ሴት ልጆች በማግስቱ አሜሪካ ኤምባሲ ቪዛ ተመቶላቸው ዓርብ ሰኔ 3 ቀን በረሩ። የብዙ ባለስልጣናት ልጆች በተመሳሳይ እንዲወጡ ተደረገ። ..29ሺህ የአሜሪካ ዶላር በተርም እየተከፈለላቸው መማር ቀጠሉ። የአዜብ ልጅና የእህቷ ልጅ፣ (በነገራችን ላይ አርአያ መኮንን ይባላል፤ በ1995ዓ.ም ቦሌ ከሩዋንዳ ፊት ለፊት ጥቂት ገባ ብሎ አዜብ ለዚህ ወጣት በ7 ሚሊዮን ብር ቪላ ቤት ገዝታ በስጦታ አበርክታለች። የቪላው ኪራይ ሂሳብ በስሙ ባንክ ይገባለታል) ..የአርከበና ስብሃት ልጆች በቨርጂኒያ፣ የሽፈራው ጃርሶ ልጆች በካሊፎርኒያ፣ የፖሊስ ኮሚሽነር የነበረው ወንጀለኛውና 5ሚሊዮን ዶላር ሰርቆ የወጣው ተስፋዬ መረሳ ልጆች በኒዮዎርክ….ወዘተ በተቀማጠለ ኑሮና በውድ ክፍያ መማር ያዙ። ባለፈው አመት በነርስ የተመረቀችው የጄ/ል ሰአረ ልጅ ሐመልማል ሰዓረ የምርቃት ፕሮግራም ላይ ጄኔራሉ ተገኝተው ነበር።…ወደ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እንለፍ።
Eskinder Nega's son Nafkot
በፎቶው ጄ/ል ሰዓረ ሴት ልጃቸውን አቅፈው ሲያስመርቁና ሲደሰቱ- በአንፃሩ እስር ቤት ከጋዜጠኛ ሰርካለም የተወለደው የእስክንድር ነጋ ልጅ ሕፃን ናፍቆት እስክንድር በጨቅላነቱ በስደት ያለ አባት እንዲያድግ ተፈርዶበት ይታያል..
እስክንድር በላባቸው ሰርተው ሃብት ካፈሩ ጥሩ ቤተሰቦች የተገኘ ልጅ ሲሆን የተማረው በሳንፎርድ ት/ቤት ነው። ከዚያም አሜሪካ መጥቶ ትምህርትና ህይወቱን ቀጠለ። “አገር አማን” ብሎ በዘመነ ኢህአዴግ አገር ቤት ገባ። ተደጋጋሚ እስርና ድብደባዎችን አሳለፈ። እነሆ “አሸባሪ” ተብሎ ከሌሎች ንፁሃን ጋር በእስር እየማቀቀ ይገኛል። እነ ጄ/ል ሰአረና መሰሎቻቸው በመቶ ሺህ በሚቆጠር ዶላር ልጆቻቸውን በአሜሪካና አውሮፓ ሲያስተምሩና ሲያንደላቅቁ፣ እንዲሁም ልጆቻቸውን ለማስመረቅ ሲገኙና ሲደሰቱ በአንፃሩ በመፃፉና ሃሳቡን በመግለፁ ብቻ እስር ቤት የተወረወረውና ናፍቆት ልጁን እንዳያሳድግ የተደረገው እስክንድር ነጋ ጭራሽ ቤተሰቡ ያወረሱትን ቤት በግፍ እንዲነጠቅ ተደረገ።

በሳጥናኤል መንገድ ነጎዱ!

በቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

ሕዝበ ክርስቲያን በጰራቅሊጦስ መንገድ ሲሄዱ፤ፓትርያርክ፤ሊቃነ ጳጳሳት፤መነኮሳትና ቀሳውስት በሳጥናኤል መንገድ ነጎዱ።

The Ethiopian Orthodox Union church…ዓላማው፤ ሐዋርያት ከክርስቶስ ጋራ በቆዩበት ጊዜ የተማሩትንና የሰሙትን እንዳይረሱ፤ በጥበብ በማስተዋል በቅድስናና በድፍረት ሰውን ከሀሰት ወደ እውነት፤ ከክህደት ወደ እምነት፤ ከበደል ወደ ደግነት፤ ከኃጢአት ወደ ጽድቅ፤ ከግለኝነት ወደ ህዝባዊነት፤ በጠቅላላው ከዲያብሎስ ወደ ክርስቶስ ለማምጣት ነው። እነዚህን ነገሮች በተግባር የሚያውሉት ሰዎች ክርስቲያኖች ተባሉ። ከክርስቲያኖች መካከል በእውቀታቸው፤ በችሎታቸውና በመንፈሳዊነታቸው ተመርጠው በአመራር ላይ ያሉ ደግሞ ጳጳሳትና ቀሳውስት ተባሉ። የነዚህ ሁሉ ክምችት ቤተ ክርስቲያን ተባለች። ይህች ቤተ ክርስቲያን በምድር ያለች “ትምጣ” እያልን የምንመኛትን በሰማይ ያለችውን መለኮታዊት መንግሥት የምታንጸባርቅ ምሳሌና ምልክት የሆነች ድርጅት ናት።… [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

በዞን 1 የሚገኙት ጀግኖቻችን በዛሬው እለት ተበታትነው እንዲደለደሉ ተደረገ! በህዝበ ሙስሊሙ ወኪሎች ላይ በማረሚያ ቤት እየተደረገ ያለው ወከባ በአስቸኳይ ይቁም ! (ድምፃችን ይስማ)

Ethiopian Musilmsበሐሰት የሽብር ክስ ህገ መንግስታዊ መብቶችን በጣሰ ሁኔታ መሪዎቻችንን እያጉላላ የሚገኘው መንግስት በማረሚያ ቤት ውስጥ የሚያደርገውን ወከባ ቀጥሎበታል፡፡ ገና ወደማረሚያ ቤት ከተዛወሩበት ጊዜ አንስቶ ጠያቂዎችን በማጉላላት፣ የጥየቃ ሰአትን ከሌሎች በተለየ መልኩ በመገደብ፣ እንዲሁም በጠያቂዎች ቁጥር ላይ ገደብ በማድረግ በተለያዩ ወቅቶች መብታቸውን ሲነግፍ የቆየው መንግስት ዛሬ ደግሞ በታሪካዊው የካንጋሮ ፍርድ ቤት የችሎት ሂደት ምስክሮቻቸውን እያቀረቡና ትክክለኛው የህዝበ ሙስሊሙ ትግል ገጽታ በችሎት እየተመሰከረ ባለበት በዚህ ወቅት በፍርድ ቤት እየደረሰበት ያለውን ሽንፈት ለመቋቋም ወኪሎቻችን ላይ የተለያዩ ወከባዎችን እየፈጸመ ይገኛል፡፡ እስካሁን ድረስ በእስር ቤቱ ታሪክ በምንም መልኩ የማያስጠይቅን፣ ይልቁንም በማረሚያ ቤቱ ደንብ ጥበቃ የተደነገገለትን ገንዘብ የመያዝ መብት እንደወንጀል በመቁጠር በኮሚቴው ሰብሳቢ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ እና በሸኽ መከተ ሙሄ ላይ፣ እንዲሁም በሌሎች ታሳሪዎች ላይ ሲያደርስ የነበረውና በቅርቡ የተረጋጋው ወከባ መሪዎቻችንን የማጥቂያ ሰበብ ፍለጋ እንጂ ሌላ እንዳልሆነ ግልጽ ነበር፡፡

Thursday, June 12, 2014

ናይ ፌስቡክ ተፃረፍቲ (የፌስ ቡክ ላይ ተሳዳቢዎች)

በታደሰ ብሩ

መንደርደሪያ
ፌስ ቡክ ላይ ህወሓትን (ወያኔን) የሚተች ጽሁፍ ሲወጣ ስድቦችን “በብርሃን ፍጥነት” የሚያዥጎደጉዱ ሃያ ያህል ሠራተኞች ሬድዋን ሁሴን ቢሮ ውስጥ መኖራቸውን ሰምቼ ነበር። ይህ ራሱ እየደነቀኝ እያለ ሰሞኑን ሌሎች ዜናዎች ተከታትለው መጡ።Ethiopian's on facebook
በፌስ ቡክና መሰል ማኅበራዊ ሚዲያዎች ለሚቀርቡበት ትችቶች ፈጣን የስድብ ምላሽ የሚሰጡለት 235 “ባለሙያ ተሳዳቢዎችን” ኢህአዴግ አሠልጥኖ ማስመረቁ ከግንቦት 27 ቀን 2006 ዓም የኢሳት ዜና ሰማሁ። ዜናው እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ኢሳት በነበረው መረጃ ሰልጣኞቹ 2, 350 የፊስ ቡክ፣ የቲውተር እና የብሎግ አካውንቶችን ከፍተዋል።
የኢሳት ዜና ከተሰማ ጥቂት ቀናት ቆይታ በኋላ ደግሞ 300 ብሎገሮች ለተመሳሳይ ተግባር በባህር ዳር ሠልጥነው የመመረቃቸውን ዜና ሴቭ አዲና የተባለው የፌስ ቡክ ባልደረባዬ አጋራን። እሱ ባለው መረጃ መሠረት ደግሞ ሠልጣኞች 3 000 የፌስ ቡክ አካውንቶች ከፍተዋል።
ህወሓት ይህን ልምድ ከየት አመጣው? ይህ ነገር የት ያደርሰናል? ለዚህ ምላሻችን ምን መሆን ይኖርበታል? ይህ አጭር ጽሁፍ እነዚህ ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያገለግሉ ውይይቶችን ለመቀስቀሻነት የሚረዱ ሀሳቦችን ይወረውራል።

የኢትዮጵያ ነፃ ጋዜጠኞችንና ጦማርያንን ማን ይፈራቸዋል? (ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም)

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
የእስክንድር ነጋን፣ ርዕዮት ዓለሙን፣ ውብሸት ታዬን፣ የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎችን…የዴሞክራሲያዊ መብት የመጠቀም የትግል እንቅስቃሴ ሲመለከት እንደሚዳቋ እየበረገገ የሚስፈነጠረው ማን ነው?Ethiopian government scared of bloggers and journalists
የኢትዮጵያ የነጻው ፕሬስ እና ጦማርያን ቁንጮ የሆነው እስክንድር ነጋ ሀሳቡን በነጻ በመግለጹ ብቻ በአምባገነኑ የወሮበላ ቡድን ስብስብ የይስሙላው የዝንጀሮ ፍርድ ቤት የ18 ዓመታት እስር ተበይኖበት በገዥው አካል የማጎሪያ እስር ቤት በመማቀቅ ላይ ይገኛል፡፡ ሟቹ መለስ ዜናዊ ልዩ ትዕዛዝ እስክንድር ነጋ በቁጥጥር ስር እንዲውል እና የ18 ዓመቱ የሸፍጥ እስራት እንዲበየንበት ተደርጓል፡፡ መለስ ዜናዊ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ማናቸውም ጋዜጠኞች የበለጠ እስክንድር ነጋን ይፈራዉና ይጠላው ነበር፡፡ ዝሆን አይጦችን “ይፈራል” ከሚለው ኢ-ስነ አመክንዮ አንጻር በተመሳሳለ መልኩ መለስም እስክንድር ነጋን እንደጦር ይፈራው ነበር፡፡
በቅርቡ እስክንድር ከማጎሪያው እስር ቤት ለ8 ዓመት ልጁ ለናፍቆት እንዲህ የሚል ግልጽ ደብዳቤ ጽፏል፣ “እንዲያው ሁኔታውን ሳየው እያለሁ የሌለሁ የዘፈቀደ አባት ሆኛለሁ፣ ምክንያቱም በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ፈረንሳዮች ነጻነት፣ እኩልነት፣ ፍቅር እያሉ ደጋግመው ይጠሯቸው የነበሩትን ሶስት ቀላል ቃላትን በመውሰድ እኔም በሀገሬ ነጻነት፣ እኩልነት እና ፍቅር እንዲሰፍን በማሰብ እነዚህን ቃላት በማስተጋባቴ ነው በሸፍጠኞች ለእስር የተዳረግሁት“ ብሏል፡፡ እስክንድር ለነጻነት፣ ለእኩልነት እና ለአብሮነት ፍቅር ጦማሪ ነው፡፡ ለዚህም ነው ለእኔ የጀግናዬ ተምሳሌት የሚሆነው!

Tuesday, June 10, 2014

“ነጻነትነታችን እንደ ዕርዳታ እህል ከምዕራባውያን የሚለገሰን አይደለም!”

ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በኢትዮጵያ ለሚገኙ የፖለቲካ መሪዎች ያስተላለፈው ግልጽ መልዕክት

የተወደዳችሁ በኢትዮጵያ የምትገኙ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፤
Solidarity Movement for New Ethiopia - logoበቅድሚያ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) የአክብሮት ሰላምታ በማቅረብ በትግሉ መስክ የምትከፍሉትን መስዋዕትነት የሚያደንቅ መሆኑን ይገልጻል፡፡ በተለይ በአሁኑ ጊዜ የፖለቲካ ምህዳሩ እጅግ ጠብቦ የለም የሚባልበት ደረጃ በደረሰበት ወቅት በምታገኙት ስንጥቅ ሁሉ እየተጠቀማችሁ ለህዝባችሁ የብርሃን ጭላንጭል ስለምትፈነጥቁ አኢጋን ሥራችሁን ያደንቃል፤ ያከብራል፡፡ እኛ በሥራችሁ ስኬት የምንመኘው ለቆማችሁለት የፖለቲካ ዓላማ ብቻ ሳይሆን ከህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ራሳቸውን ነጻ ለማውጣት አቅቷቸው መፈናፈኛ ላጡትም የመወሰን ኃይል እንደምትሰጧቸው በማመን ነው፡፡

ሰማዕታትን እንዘክር፤ እራሳችንንም እንጠይቅ! (ግንቦት7)

ሰማዕታትን እንዘክር፤ እራሳችንንም እንጠይቅ! (ግንቦት7)

ሰኔ 1997 በዘረኝነት፣ በአፍቅሮተ ንዋይና አፍቅሮተ ሥልጣን የተለከፉ የትግራይ ገዢ ጉጅሌ አባላት ጭካኔ በይፋ የታየበት ወቅት ነው። ለዓመታት በማስመሰያ ጭንብል ተሸፋፍኖ የቆየው የህወሓት እውነተኛ ባህርይ የዛሬ ዘጠኝ ዓመት በወርሃ ሰኔ አደባባይ ወጣ። በሀውዜን ላይ የደረሰውን የግፍ ጭፍጨፋ ሲያወግዝ የቆየው ቡድን ሌላ ሀውዜን አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ፈጠረ። ይኸኛው ሀውዜን ግን በአንድ ቦታ ተወስኖ የቀረ አልነበረም። ጭፍጨፋው በአዲስ አበባ ተጀምሮ ወደ አዳማ፣ ባህርዳር፣ ጎንደር፣ አዋሳ፣ ሃረር፣ ድሬዳዋ እና ሌሎች ከተሞችና ገጠሮች ተዛመተ። “አግዓዚ” የተሰኘው ገዳይ ሠራዊት በሰላማዊ እናቶችና አባቶች፤ ወጣቶችና ህፃናት ላይ ዘመተ። ደብተርና እርሳሶቻቸውን እንደያዙ ከትምህርት ቤት የሚመለሱ እምቦቃቅላ ህፃናትን ሳይቀር በጥይት ግንባርና ደረታቸውን እየመታ ጣለ።Ginbot 7 Ethiopian opposition party
በ1997ቱ ሚያዝያ መጨረሻና ግንቦት መጀመሪያ ላይ አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ በደስታና ተስፋ ተሞልቶ ነበር። የሚያዝያ 30 ታላቅ ሕዝባዊ ሰልፍ እና የግንቦት 7 ጨዋነት የተላበለው ምርጫ የፈጠሩት ተስፋ ቃላት ሊገልጹት በሚችሉት በላይ ነበር። ሆኖም በህወሓት የተመራው የሰኔው ጭፍጨፋ ያንን ሠናይ ስሜት አደፈረሰው፤ አጨለመው።

Monday, June 9, 2014

የሕዳሴ አብዮት አተገባበር! (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ )


ባለፉት ሁለት ሳምንታት በተከታታይ ባቀረብኳቸው ጽሑፎች ገዥው-ግንባር የመረጠው ስሁት መንገድ፣ ኢትዮጵያችንን ለሳልሳዊው አብዮት እያዘጋጃት መሆኑን ማውሳቴ ይታወሳል፡፡ ይህ የለወጥ መስመርም “የሕዳሴ አብዮት” የሚል ስያሜ ኖሮት፣ ሁሉን አሳታፊ ፖለቲካዊና ማሕበራዊ ንቅናቄ በመፍጠር አገሪቱን በዳግም
ውልደት ለማንፃት ብቸኛ አመራጭ የመሆኑ ጉዳይ በስነ-አመክንዮ ተሰናስሎ ቀርቦበት ነበር፡፡ በዚህ ተጠየቅ ደግሞ አብዮቱን ከዳር ለማድረስ ሊተገበሩ የሚችሉ (በሰላማዊ ትግል ማዕቀፍ ውስጥ ያሉ) ስልቶች እና በመጀመሪያው የንቅናቄው ምዕራፍ ሥርዓቱ ለመመለስ ሊገደድባቸው የሚገቡ ጥያቄዎችን እንዳስሳለን፡፡Temesgen Desalegn "Fact" Ethiopian Amharic newspaper editor
ለምን እንሞታለን?
የዓለም ታሪክ አምባ-ገነኖች እብደታቸውን እንዲተገብሩ የሚያስችላቸው የታጠቀው ኃይል (ጦር ሠራዊት፣ ደህንነት እና ፖሊስ) ስለመሆኑ አያሌ ማሳያዎችን ዘርዝሮ ያስረግጣል፡፡ የኢትዮጵያችን የቅርብ ጊዜ ታሪክንም ብንመለከት፣ የአፄ ኃይለስላሴ ጨቋኝ አስተዳደርን ግማሽ ክፍለ ዘመን አፋፍ ድረስ ተሸክመው የተጓዙት እነዚህ ኃይሎች መሆናቸው ጉዳዩን አምነን እንድንቀበል ያስገድደናል፡፡ የኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም በላኤ-ሰብ ዘመን በታሪክነት ተመዝግቦ ለመታወስ የቻለውም ይህንኑ ክፍል አጥብቆ በመያዙ መሆኑ የትላንት ክስተት ነው፡፡ ባለፉት ሁለት አስርታት ያስተናገድነው የኢህአዴግ ብልጣ ብልጥ አምባ-ገነን አስተዳደርም ከከፋፍለህ-ግዛ ስልቱ በተጨማሪ ዋና መሰረቱ ጠብ-መንጃ አንጋቹ አካል ለመሆኑ ይህ ትውልድ የአይን እማኝ ነው፡፡ አዲሱ የሕዳሴ አብዮታችንም በዚህ ኃይል ላይ ትኩረት ያደርግ ዘንድ የተገደደበት መግፍኤ ይኸው ነው፡፡

በአንድነት እና በመኢአድ መካከል የተደረገው ውህደት በተመለከተ የተሰጠ መግለጫ (የሰሜን አሜሪካ የአንድነት የድጋፍ ማህበራት)

ANDINET NORTH AMERICA ASSOCIATION OF SUPPORT ORGANIZATIONS (ANAASO)

ተሰናክለን ነበር፤ አሁን ግን ጸንተናል!

«ዉጊያዉን ተሸነፍን እንጂ ጦርነቱን አልተሸነፍንም» ነበር ያሉት የፈረንሳዩ የ2ኛው ዓለም ጦርነት መሪ፤ ጀነራል ቻርለስ ደጎል፣ አገራቸው በናዚዎች ሥር በወደቀች ጊዜ። ልክ እንደ ዉትድርናዉም፣ በሰላማዊ ትግል ዉስጥ መሸነፍ፣ መዉደቅ፣ መሳሳት አለ። መነሳትም እንዲሁ፡፡ ታላቁ የነጻነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ እንዳሉትም፤ «በሕይወት ውስጥ ትልቁ ነገር ፈትሞ አለመውደቅ ሳይሆን፤ በወደቁ ቁጥር መነሳት ነው»
በአገራችን የሰፈነዉን አምባገነንነት በመቃወምና በአገራችን ሰላም፣ ዴሞክራሲ፣ የሕግ የበላይነት እንዲሰፍን፣ ላለፉት አያሌ አመታት ትእግስት አስጨራሽ ትግል ቢደረግም፤ የተደረጉ ጥረቶች የተፈለገውን ዉጤት ሳያመጡ ቀርተዋል፡፡
በተለይ በምርጫ ዘጣና ሰባት ወቅት፣ በአገር ዉስጥና ከአገር ዉጭ ያለውን ኢትዮጵያዊ ሁሉ የሚያነቋንቅ ትልቅ ሥራ ተሰርቶ የነበረ ቢሆንም፣ ቅንጅትን በመሰረቱ ድርጅቶች መካከል ልዩነቶች ስለተፈጠሩ፣ የቅንጅት አመራር አባላትም በተለያዩ ምክንያቶች ስለተከፋፈሉ፣ የአገዛዙ አፈናና የረቀቀ ከፋፋይ ሴራ ተጨምሮበት፣ ያኔ የነበረዉ የቅንጅት አብዮት እንዲቀዘቅዝ ሆኗል፡፡። ይህም የአምባገነኖች ደስታ ሆኖ ቆይቷል።

በአገሩ ጉዳይ የሚያገባው ትውልድ ፍለጋ!! (zone9)

‹‹የአሁን እኛ?››

Zone 9 bloggersበሳምንቱ መጨረሻ ቀናት ምሽቶችን የሚያደምቁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጫወታዎን የሚታደሙ፣ ከዚያም አልፈው ጎራ ለይተው የሚሰዳደቡና የሚወቃቀሱ፣ የባሰ ዕለት ደግሞ በትልልቅ ጫወታዎች መልክ ጎራ ለይተው የሚቧቀሱ ወጣቶችን ማየት የከረመ አገራዊ ትዕይንት ሆኗል፡፡ ቅጥ ባጣ የፈረንጅ እግር ኳስ ፍቅር፣ ‹‹ከብርሃን ፍጥነት›› በላይ እየተስፋፉ ባሉ ‹‹የሱስ መሰረተ ልማቶች›› ውስጥ በመጥፋትና በቸልተኝነት የሚታማው ይህ ትውልድ ከላይ በተጠቀሱ ‹‹አደንዛዥ›› ጉዳዮች ተጠልፎ ካልወደቀም በጥልቅ ‹‹ራስን የማዳን›› ስሜት በመዋጥ አገሩን የረሳ፣ ፖለቲካ የማይገደው፣ ምርጫ የማያሳስበው ትውልድ ነው ተብሎ ይታማል፤ አለፍ ሲልም ደግሞ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በስደት ወደተገኘው አገር ለመጓዝ ልቡ የቆመ፣ በአገሩ ተስፋ የቆረጠ፣ በየትኛውም አጋጣሚ አገር ጥሎ ለመሄድ ጓዙን ጠቅልሎ የተሰናዳ ወጣት እንዴት አገርን ይረከባል? ሊረከብስ ቢዘጋጅ ከማን እና እንዴት ይረከባል? ይህችን አገር ከእኛ የሚወስዳት ማነው የሚሉ ‹‹አባቶችም›› መኖር ሌላው ነባራዊ ሐቅ ነው፡፡

Sunday, June 8, 2014

“አባ” ግርማ! እንኳን ለግንቦት ፳ አደረሰዎ! ይኽቺ ጎንበስ-ጎንበስ ዕቃ ለማንሳት ነው!

ወንድሙ መኰንን – ከብሪታኒያ ሚያዝያ ፴ ቀን ፪ሺ፭ ዓ. ም (7 June 2014)

Aba Girma celebrating Ginbot20 with TPLF
ወያኔ አሁን ደኅና ልማታዊ መነኵሴ አገኘች! ጎሽ! የለንደኑ ኤምባሲዋ፣ አዲሱን ወዶ-ገባ ለግንቦት ፳ አሰልጥና አስመረቀች! በድንኳን ባደረገቸው ድግስ ላይ በግልጽ ለዕይታ አበቃች።

እየራበንም ቢሆን በምግብ እራሳችንን ችለናል – ኃ/ማሪያም ደሳለኝ

(ግንቦት7 ዜና) – ወያኔ ስልጣን በያዘባቸዉ አመታት በተለይም ባለፉት አስር አመታት የኢትዮጵያ ኤኮኖሚ በድርብ አኃዝ አደገ፤ ኢትዮጵያ በ2015 ዓም መካከለኛ ገቢ ካላቸዉ አገሮች ተርታ ትሰለፋለች፤ በኤሌክትሪክ ኃይል እራሳችንን ችለን ለጎረቤት አገሮች እንተርፋለን፤ በቅርቡ ደግሞ በምግብ ምርት እራሳችንን ቻልን የሚሉ በአይን የማይታዩና በእጅ የማይዳሰሱ የ”ላም አለኝ በሰማይ” ክምሮች እየከመረ የኢትዮጵያን ህዝብ ለመደለል ሞክሯል። የአገሩ ኤኮኖሚ በእጥፍ አደግ ሲባል ችግርና መከራዉ በሦስት እጥፍ የጨመረበት የኢትዮጵያ ህዝብ ግን እንኳን መካከለኛ ገቢ ካላቸዉ አገሮች ተርታ ሊሰለፍ ከሦስቱ ዕለታዊ ምግቦች አንዱን በቅጡ መብላት ተስኖት መብራት በሳምንት አንድ ቀን ብቻ እያገኘ “ጽድቁ ቀርቶብኝ በወጉ በኮነንከኝ” እያለ ጨለማ ቤት ዉስጥ ቁጭ ብሎ የመከራ ዘመን መቁጠር ጀምሯል።

Ethiopian PM Hailemariam Desalegn on Al Jazeera
የኢትዮጵያ ህዝብ እንመራሀለን ከሚሉት የወያኔ መሪዎች እጅ እጅ ብሎ የሰለቸዉ ነገር ቢኖር እንደሰዉ በእግሩ ቆሞ የሚሄደዉ ዉሸታቸዉና ቅጥፈታቸዉ ነዉ። የወያኔ መሪዎችና እዉነት አንድ ላይ ታይተዉ ስለማያዉቁ ህዝብ አይኑ እያየ የሆነዉን ነገር አልሆነም ወይም ጭራሽ ያልተሞከረዉን ነገር ሆነ ብለዉ ሲዋሹ ለአፋቸዉም ለሰብዕናቸዉም አይሳሱም። ለምሳሌ ሠላማዉ ዜጎችን በጅምላ ገድለዉ ብርድልብስ ጠቅልለዉ እየቀበሩ ማንንም አልገደልንም፤ መብቱን የጠየቀ ሰላማዊ ሰልፈኛ በጥይት እየጨፈጨፉ – ባንክ ተዘረፈ፤ መሬታችንን ለምነዉ ለሱዳን እየሰጡ – የተሰጠ መሬት የለም፤ አኝዋክን ከመሬቱ አፈናቅለዉ መሬቱን ለባዕዳንና ለቤተሰቦቻቸዉ በርካሽ እየቸበቸቡ ኢትዮጵያ ዉስጥ የመሬት ቅርሚያ የለም እያሉ የዋሿቸዉ ግዙፍ ዉሸቶች ከብዙዎቹ ቂቶቹ ናቸዉ።

Friday, June 6, 2014

የደህንነት ኃይሎች በጋዜጣ አዙዋሪዎች ላይ እርምጃ መወሰድ ጀመሩ

Reading newspapers in Addis Ababa, Ethiopia

(ነገረ-ኢትዮጵያ፣ ሰበር ዜና) – በቅርቡ ገዥው ፓርቲ የግሉን ሚዲያ ለማፈን እንዲያስችል ጋዜጣ አዙዋሪዎችና አከፋፋዮችን በጥቃቅንና አነስተኛ ለማደራጀት የሚያስችል አሰራር እንደጀመረ ታውቋል፡፡ በዚህ አሰራር መሰረት ገዥው ፓርቲን የሚተቹ ጋዜጦችና መጽሄቶች ከገበያ በማስወጣት በቀጣዩ ምርጫ የሚደርስበትን ጫና ለመቀነስ እንደፈለገም ሲነገር ቆይቷል፡፡

የእናት ሀገር የድረሱልኝ ጥሪ ???…

(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)

ethio poor

ባለፈው ሰሞን ወያኔ ኢሕአዴግ ላለመው የጥፋት ተልእኮ ወሳኝ ክንውኑን መተግበሩ ይታወሳል፡፡ ወያኔ ለጥፋት ተልእኮው በእጅጉ የሚረዳውን ወሳኝ የጥፋት ሥራ የመሥራቱን ያህል ከእምነተ-አሥትዳደር (ፖለቲካ) ፓርቲዎች (ቡድኖች) አንሥቶ እስከ ሕዝባዊ ማኅበራት (Civic organizations) ድረስ ያሉ ሁሉ ልብ ሳይሉት ወይም በቅጡ ሳይረዱት ቀርተው ይሁን ምን አላውቅም ተገቢውን ትኩረት ሳይሰጡት ሲቀሩ ሳይ እጅግ ተገርሜያለሁ፡፡

የኢትዮ-ኤርትራ የድንበር ጉዳይ ለምን አይቋጭም?

"የለዘብተኞችና የእስስት” ፖለቲካ ልዩነት እየፈጠረ ነው


Thursday, June 5, 2014

ዶ/ር ብርሀኑን ለመጀመሪያ ጊዜ እንዳየሁት

ሁኔ አበሲኒያዊ ፒተርቦሮው ዩ.ኬ

Dr. Berhanu Nega Ginbot 7 Chairman
ግንቦት 97 ዓ.ም ለሐገራችን ፖለቲካ ተስፋን ይዞ የመጣ ትልቅ እድል ነበር የምርጫው እለት እኔም በአሁኑ ሠዓት አውስትራሊያ ከሚኖር ወዳጄ ጋር በመሆን በጠዋት ወጥተን በያዝኳት አንድ ካርድ ኢህአዴግን ለመጨረሻ ጊዜ ከስልጣን በማባረሩ ሒደቱ ተሳታፊ ለመሆን ምርጫ ጣቢያ ደርሰናል በድንገት ግን አንድ ተዐምር ተከሠተ ዶ/ር ብርሐኑ ነጋ የሠፈራችን ምርጫ ጣቢያ ለቅኝት ተገኘ አካባቢው በፉጨት ተናጋ እልልታ ጭፈራው ደራ፣ ሰው ሁሉ ዶ/ር ብርሐኑ እየሮጠ ላይ መጠምጠም ጀመረ እኔና ጓደኛዬ ሁኔታውን በአድናቆት መከታተል ያዝን ወዲያውም በአካባቢው ይገኙ የነበሩ ሠዎች ኮተቤ ደጃዝማች ወንድራድ ት/ቤት አካባቢ በሚገኝ አንድ ግሮሠሪ በመውሰድ ምግብ ሊጋብዙት እንደሚፈልጉ ነገሩት ያ ድንቅ ሠው ዶ/ር ብርሐኑ ግን አሻፈረኝ መሄድ አለብኝ ሲል ቢናገርም አንድ አዛውንት ጠጋ ብለው እንዲህ አሉት ”የኛን ግብዣ ንቀህ ካልሆነ በቀር እምቢ የምትልበት ምንም ምክንያት የለም አንተ ነፍስህን ለእኛ ስትል ለመክፈል የተዘጋጀህ ነህ እኛ ለምሳ ብንከፍልልህ ምን አለበት” ሲሉት ዶ/ር ብርሐኑ ላይ የትካዜ እና የፍቅር ፊት አነብ ነበር፡፡

ኢ- ፍትሃዊው እስሬ! እየፈሩ ጋዜጠኝነት የለም! (ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ጎዳና )

(ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብታችን ትልቅ አደጋ ላይ ነው)

Elias Gibruአርብ ግንቦት 15 ቀን 2006 ዓ.ም ከወዳጄ ጋዜጠኛ ዳዊት ሠለሞን ጋር ቀጠሮ ነበረኝ፡፡ ረፋድ 5፡25 ሰዓት ላይ የሞባይል ስልኬ ጠራች፡፡ ከአምባሳደር ወደአራት ኪሎ በሚጓዝ ታክሲ ውስጥ ተሳፍሬ ነበር፡፡ የመስመር (የቢሮ) ስልክ መሆኑን አየሁትና “ሃሎ” አልኩኝ፡፡ ‹‹አቶ ኤልያስ፣ የዕንቁ መጽሔት ዋና አዘጋጅ?›› የሚል የሴት ድምጽ ተሰማኝ፡፡ ‹‹አዎን›› ስል መለስኩላት፡፡ ብዙ ጊዜ አንባቢዎች ስለሚደውሉ፣ ምን ዓይነት ግብረ-መልስ (feed back) ይኖራት ይሆን ነበር ሀሳቤ፡፡ ሳይሆን ቀረ፡፡ ‹‹የምደውለው ከፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ነው፣ በአንድ ጉዳይ ላይ ስለምንፈልግዎት ቃልዎትን መጥተው እንዲሰጡን ነበር፡፡›› …‹‹እሺ፣ ሰኞ ጥዋት ልምጣ?›› በማለት ጠየኳት፡፡ ‹‹ቆይ አንዴ?›› ብላኝ ባልደረቦቿን ካነጋገረች በኋላ ‹‹ይቻላል›› አለችኝ፡፡ ቀጭን የጌታ ትዕዛዝ፡፡ ከዚህ የስልክ ጥሪ በኋላ የመጽሔቱ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ፍቃዱ ማኅተመወርቅ (ፍቄ) ደውሎልኝ ስለጉዳዩ ሐሳብ ተለዋወጥን፡፡ ሰኞ በጥዋት ለመገናኘት ተቀጣጥረን ስልኩ ተዘጋ፡፡

Wednesday, June 4, 2014

ኪነ-ጥበብ አልባ ትግል (የቴዲ አፍሮ ጉዳይ)

አርአያ ጌታቸው

እስከማውቀው ድረስ ቦይኮት ኮካ ኮላ ተብሎ የተጀመረ ይፋዊ ዘመቻ የለም፡፡ ነገር ግን በርካቶች ገና ባልተጀመረ ዘመቻ ላይ ሆነው የወረደ፣ ተራ፣ የዘቀጠ… የሚሉ ቃላትን በመደርደር ለማጣጣል ሞክረዋል፡፡ ቴዲ አፍሮ ላይ ለደረሱበት የሞራል ኪሳራዎች እና ስም ማጥፋቶች ግን ምንም ለማለት አልደፈሩም፡፡ ዛሬ አርቲስት ሁሉ ለሆዱ ባደረበት ወቅት ሀሳቡን ያለምንም ፍርሀት በአደባባይ ጮሆ በመግለጽ ብቻውን በቆመ በዚህ ብላቴና ላይ እየደረሰ ያለውን በደል እና ግፍ ግን አንስቶ መወያያትን በማህበራዊ ድረ ገጽ ላይ ያለውን “የትግል እንቅስቃሴ” አቅጣጫ ያስቀይራል በሚል ለማጣጣል የሚደረግ ሙከራ መልካም አይመስለኝም፡፡Teddy Afro and Coca-Cola
ኪነጥበብ በትግል ውስጥ ከምንም በላይ ጉልህ ሚና ይጫወታል፡፡ ቀደም ባሉት የኢትዮጵያ ፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ እንኳ ብንመለከት በተለይ ከአቢዮቱ ጋር ተያይዞ ምን ያህል ህዝቡን ለማነሳሳት እንደተጠቀሙበት የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው፣ ከዛም በእድገት በህብረት ዘመቻ፣ በኢትዬ ሶማሊያ ጦርነት እና በ17 ዓመቱ የእርስበርስ ጦርነት ወቅት ኪነጥበብ ከጦርቱ ባልተናነሰ በግንባር ቀደምትነት አገልግሏል፡፡

አባ ዱላና ከንቲባ ድሪባ የቁም እስረኛ ሆኑ፣ ፓስፖርታቸው ተቀማ

“የኢህአዴግ በርዕዮተዓለም መበላላት ይፋ እየሆነ ነው”

abadulla and deriba


አባ ዱላ ገመዳና የአዲስ አበባ ከንቲባ ድሪባ ኩማ ፓስፖርታቸውን ተነጥቀው የቁም እስረኞች መሆናቸው ከተለያዩ ምንጮች እየወጡ ያሉ መረጃዎች አመልከተዋል። የጎልጉል ምንጮች ግን ኦህዴድ ውስጥ በከፍተኛ አመራሮች ደረጃ እየተካሄደ ያለው ግምገማ ሲጠናቀቅ በርካታ ባለስልጣኖች ክስ እንደሚመሰርትባቸው ተናግረዋል።

Monday, June 2, 2014

የሕዳሴ አብዮት! (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ )

የዛሬይቱ ኢትዮጵያችን ‹‹አብዮታዊ ሁኔታ›› ላይ ለመድረሷ በብዙሃን ዜጐች ዕይታም ሆነ፤ ሂደቱን በተከታተሉ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ምሁራን ምልከታ የማይታበል ሐቅ ሊሆን መቃረቡ በዚህ ተጠየቅ ለማነሳው አጀንዳ ገፊ-ምክንያት ነው፡፡ በአናቱም ባለፈው ሳምንት ‹‹የ‹ቀለም› አብዮት ናፍቆት›› በሚለው መጣጥፍ ላይ ለማሳያነት የጠቀስኳቸው ፖለቲካዊ፣ ማሕበራዊ እና ነገረ-ንዋያዊ ችግሮች ተደማምረው፣ ሀገሪቷን በርቀት እንደታዘብናት ሶቪየት ሕብረት፣ አሊያም በቅርበት እንዳስተዋልናት ሶማሊያ በመጪዎቹ ጥቂት ጊዜያት የመፈራረሷን አይቀሬነት ማስረገጣቸውን ልብ እንላለን፡፡ ከዚህ ክፉ የታሪክ ዕጣ ለመታደግም ከሁለት አስርታት በላይ ያስቆጠረውን ይሄን አሮጌ ሥርዓት መቀየር ብቻውን ዘላቂ መፍትሔ ሊያመጣ እንደማይችል ዛሬ ግልፅ እውነታ ሆኗል፤ ምክንያቱ ደግሞ ለዘመናት በገዥነት የተንሰራፋው የፖለቲካ ባሕልም አብሮ ካልታደሰ ነገሩ-ሁሉ ‹‹ታጥቦ ጭቃ…›› ከመሆን አለመዝለሉ ነው፡፡

Temesgen Desalegn "Fact" Ethiopian Amharic newspaper editor
እናም ወደዚህ ከፍታ ለመሻገር ሶስተኛው አብዮት ብቸኛ መፍትሔ የመሆኑ ጉዳይ አከራካሪ አይደለም፤ ይህ ታላቅ ንቅናቄ ‹‹የሕዳሴ አብዮት›› በሚል ስያሜ ቢጠቃለል፣ ሂደቱ አንድም ኢህአዴግን ከክፉ ስራዎቹ ከመግታት ባለፈ፣ ኢትዮጵያን በሁለንተናዊ መልኩ የማደስና የተረጋጋ የፖለቲካ ማሕበረሰብ መፍጠርን የመሳሰሉ ተልዕኮዎችን በቀላሉ ወደ መሬት ለማውረድ ያስችላል፤ ሁለትም ከለውጡ ጋር የተያያዙ መሰረታዊ ጥያቄዎችን ከስያሜው አንድምታ አንፃር እየቃኙ በቀላል መንገድ ለመተንተን ጠቀሜታ ይኖረዋል ብዬ አምናለሁ፡፡ አምኜም በአዲስ መስመር የሕዳሴን ታሪካዊ ዳራ፣ አተገባበር እና ተያያዥ ጉዳዮችን እየጠቃቀስኩ ለማብራራት እሞክራለሁ፡፡

Sunday, June 1, 2014

“The Journey to a New Vision for Ethiopia”

Mr. Obang Metho’s Acceptance Speech: At the 22nd SEED Annual Award ceremony

o at seed 1


I would like to deeply thank distinguished members of the Society of Ethiopians Established in Diaspora (SEED) and my fellows’ citizens of Ethiopia for this recognition. I am both humbled and honored to be here tonight as a recipient of this award.

የብርቱ – ካህን ፍሬዎች

አርአያ ጌታቸው

Birtukan Mideksa
የኢትዮጵያ ፖለቲካን በተለይ ከንጉሳዊ ስርዓት ውደቀት በኋላ የነበረው የፓርቲ ፖለቲካ እስከ 1997 ዓ.ም ያለውን መመልከት ብንችል፤ የሴት እህቶቻችን ምንመ እንኳ አልፎ አልፎ በፖለቲካው ውስጥ ተሳትፎ የነበራቸው ቢሆንም ይሄ ነው የሚባል ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አልነበሩም፡፡ ሆኖም ከቅንጅት ውህደት መስከረም 1998 ዓ.ም የብርቱካን ወደ አመራርነት መምጣት በሴቶች የፖለቲካ ህይወት ላይ ትልቅ ተፅእኖ ፈጥሯል፡፡ ብርቱካን ከአንድ ዓመት ከ10 ወር እስር በኋላ ተፈትታ የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ሆና በመመረጥ በኢትዮጵያን ፖለቲካ ውስጥ የመጀመሪያዋ ሴት የፓርቲ መሪ በመሆን በታሪክ መዝገብ ውስጥ ራሷን አሰፈረች፡፡ ሆኖም ብርቱካን ከእድሜዋ ወጣትነት፣ በህግ ያለት እምነት እና ዕውቀት ሴት እና እናት ከመሆኗ ጋር ተደማምሮ በህብረተሰቡ ውስጥ የነበረውን የመሪ ጥማት በቀላሉ ልታሟላ እንደምትችል የተረዳው የወያኔ ስርዓት በ7 ወር የፓርቲ ሊቀመንበር እድሜዋ በዓጭሩ ለመቅጨት በማሰብ በድጋሚ ማንንም ሊያሳምን በማይችል ተልካሻ በሆነ ምክንያት ለእስር ዳረጋት ፡፡ ሆኖም ያልተረዱት ነገር ብርቱካን በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ብዙ ሴቶችን ምንያህል ማርካ እንደነበረ ነው፡፡ ከነዚህም ውስጥ ዛሬ በእስር ላይ የምትገኘው ጀግናዋ ርዕዬት አለሙ አንዷ ነች፡፡