Translate

Tuesday, October 31, 2017

ህወሓት የኦህዴድን የበላይነት በመቀበል ኦሮሞ ጠ/ሚኒስትር ሊሾም ነው

  • ጉዳዩ በህወሓት ዘንድ መጠነኛ መከፋፈል ፈጥሯል
“ኃይለማርያም ደሳለኝ የመስዋዕት በግ?” ሲሉ የመረጃው ሰዎች አዲሱን ዜና ይጀምራሉ። የጎልጉል ታማኝ መረጃ አቅራቢዎች በኦሮሚያ ከአሁን በኋላ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ኃይል – ህወሓት ዕድል ፈንታ እንደሌለው ማመኑን ይጠቁማሉ። የኦሮሞ ጥያቄ የወንበር መሆኑን ህወሃት እንዳመነና ይህንኑ እምነቱን ተግባራዊ ለማድረግ መነሳቱን ለ“ወዳጆቹ”፣ ጌቶቹና አሳዳሪዎቹ ማሳወቁንም ይጠቁማሉ። በሌላ ወገን ደግሞ ይኸው ሁኔታ በህወሓት ውስጥ መጠነኛ መከፋፈልን እንደፈጠረ ይነገራል።

የመጀመሪያ መጨረሻው

Image may contain: 1 person, sitting and indoor
[በኤርሚያስ ለገሰ]
የሕውሓት አገዛዝ የመጨረሻውን መጀመሪያ ጐዳና ጀምሮታል። ይህ ምዕራፍ እውነተኛው የስርአቱ ባህሪ በማያወላዳ መንገድ የሚገለጥበት ሆኗል ። በተለይም የትግራይ ተወላጆችን በፍራቻ በመሸበብ ከሌሎች ኢትዬጲያውያን ጋር ደም እንዲቃቡ የማይቆፍረው ጉድጓድ እንደማይኖር በግልፅ የታየበት ነው። የሰሞኑ አስደንጋጭ ክስተቶች ዝም ብለው የመጡ ሳይሆን ከአገዛዙ ውስጣዊ ባህሪ የሚመነጩ ናቸው።
ሰለሆነም የኢትዮጵያ ህዝብ የሚያደርገው የስርአት ለውጥ ትግል ህውሓት ትግሉን ወደ ሌላ አቅጣጫ በመውሰድ እንዳይቀለብሰው የሚያደርጉ ስትራቴጂ እና ስልቶችን መከተል እንደሚያስፈልግ ግላጭ የወጣበት ሆኗል። ለዛሬው በኦሮሚያ እየተካሄዱ ያሉ ሕዝባዊ ትግሎችን ለማገዝ ይረዳሉ የምላቸውን ጥቂት ቁምነገሮች ለመጠቆም እፈልጋለሁ።
# የቅድሚያ ቅድሚያው ህዝባዊ እምቢተኝነቱንና ተቃውሞውን አጠናክሮ መቀጠል ይሆናል። ሰልፎችን አለማቋረጥ፣ መንገድ መዝጋት፣ የቀበሌና ወረዳ እንዲሁም የመንግስት ቢሮዎችን ማጨናነቅ፣ የፓርቲ ጽሕፈት ቤቶችንና ኩባንያዎችን ማገት ያስፈልጋል። ከህውሓት/ ኢህአዴግ ጋር ባላቸው የጥቅም ትስስር የሚንቀሳቀሱ ባለሃብቶችን ንብረት ቆጠራ ማካሄድና ከአገዛዙ ጋር ያላቸውን ትስስር ፍቺ እንዲፈጽሙ ማስጠንቀቅ ያስፈልጋል። የኤፈርት ምርቶችን የሚቀበሉ ነጋዴዎች ውላቸውን እንዲያቋርጡ ማስጠንቀቂያ መላክ ያስፈልጋል። የጉና ኢንተርፕራይዝ የጅምላ እና ችርቻሮ ሱቆች ተለይተው መዘጋት ይኖርባቸዋል። የአንበሳ፣ ወጋገን ባንክና የአፍሪካ ኢንሹራንስን ህዝቡ እንዳይጠቀም ማድረግ ያስፈልጋል። እንደዚህ አይነት እርምጃዎች ተጠናክረው መቀጠል ያለባቸው ነው።

Sunday, October 29, 2017

“ሁሉንም ፈንቅል HR 128ን አምክን” – በሶማሊያ ዕልቂት የህወሓት ሥውር እጅ?

ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ /ህወሓት/ የተነሳበትን ዓላማ ለማሳካት የማይፈነቅለው ድንጋይ የለም የሚለው አስተያየት አሁን አሁን አከራካሪ ሊሆን አይችልም። በብዥታ ውስጥ የነበሩት እንኳን አሁን “ምን እየሆነ ነው” በሚል ራሳቸውን እየጠየቁ ያለአስረጂ ምላሹን እያገኙ ህወሓትን በጥርጣሬ የሚያዩበትን መነጽር አውልቀዋል። ይህ እንግዲህ በውጪውም ዓለም ጭምር እየሆነ ነው።

Tuesday, October 24, 2017

በሁለቱ ድርጅቶች ጥምር መንግስቱ ሊመሰረት ይችላል። ( በኤርሚያስ ለገሰ)

የቀጣይ ግማሽ አመት እቅድ
በብዙዎች ዘንድ ኦህዴድ አሁን የያዘውን አቋም አስመልክቶ የተለያዩ አስተያየቶች ይሰጣሉ።በአንድ በኩል አባዱላ የወሰደውን እርምጃ እና የለማ መገርሳ ካቢኔ ከአንደበታቸው የሚወጣውን ኢትዬጲያዊነት በመመልከት እድል ሊሰጣቸው ይገባል የሚሉ አሉ። በሌላ በኩል አሁንም ከጀርባ ያለው ህውሓት ስለሆነ የተቀነባበረ ድራማ ነው የሚሉ ይገኙበታል። ከዚህ በተጨማሪም ” ፌንጣ ብትቆጣ ክንፏን ለመጣል ነው” በሚል የሚተርቱ አልጠፉም።
የራሴን ቦታ ስመለከተው ኦህዴድ ዋነኛ የለውጥ ሐይል ባይሆንም በኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ አመኔታ የሚፈጥሩ እርምጃዎችን መውሰድ ከቻለ ሊበረታታ እንደሚገባይሰማኛል።
ኦሕዴድን ምንም ሳናስጨንቀው ህውሓት ከቀየሰው ህጋዊ ማእቀፍ ሳይወጣ የሚፈፅመው ቁልፍ ተግባራት የመበረታታቱ መነሻ ሊሆን እንደሚገባ እምነት አለኝ።
በመሆኑም የሚከተሉትን ቀላልና ሕጋዊ ተግባራት በሚቀጥሉት ስድስት ወራት ( ህዳር – ሚያዝያ) ይፈፅምና ማበረታታቱን ወደ ድጋፍ እንቀይርለት።
አንደኛ:-የኢህአዴግ ሕገ ደንብ በግልፅ እንዳሰፈረው አባል ድርጅቶቹ በማንኛውም ወቅት ከግንባሩ ለቀው መውጣት ይችላሉ።በመሆኑም ኦሕዴድ በግንባሩ ሕገ ደንብ መሰረት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ፍቺውን በሚቀጥለው ጉባኤ ላይ አቅርቦ መፈፀም ይኖርበታል። ይሄን ማድረግ ሕጋዊ ነው። ቀላልም ነው።

የህወሃት ጣእረሞት ባጭሩ ሲዳሰስ (መስቀሉ አየለ)

መስቀሉ አየለ
Meles Zenawi on fire
ለዘር ፖለቲካ የበላይነት በመስጠት ኢትዮጵያዊነትን ለማዳከም የቋንቋ ባቢሎን ገንብቶ ክልላዊ አድረጃጀትን ሲገነባ የኖረው ወያኔ የዘራው ዘር ፍሬ አፍርቶ ዛሬ የሱን ልሳን የሚናገሩ ሚሊዮኖች በየአቅጣጫው እንደ እንጉዳይ መፍላት ጀምረዋል። በዚህም የተነሳ ማእከላዊ መንግስቱ ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ግባተ መሬቱ ተፈጽሟል ማለት ይቻላል።

Saturday, October 21, 2017

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ - ስለ ማረሚያ ቤት ቆይታው

  ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ - ስለ ማረሚያ ቤት ቆይታው 
• “እንደ ፍርደኛ ሳይሆን እንደ ጦር ምርኮኛ ነበር የምታየው”
         • “በሃገሪቷ ላይ ምን እየተካሄደ እንዳለ አላውቅም ነበር”
         • “እናቴ እውነተኛ ኢትዮጵያዊ መንፈስ ያላት ነች”

   ባለፈው አርብ ጥቅምት 3 ቀን 2010 ዓ.ም ከእስር እንደሚለቀቅ ሲጠበቅ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ፤በግልጽ ባልታወቀ ምክንያት በዕለቱ ሳይፈታ በመቅረቱ ቤተሰቦቹ ማዘናቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ጋዜጠኛው ከሁለት ቀን በኋላ ግን የ3 ዓመት እስሩን ያለ አመክሮ አጠናቅቆ፣መፈታቱ ይታወቃል፡፡ ለመሆኑ የማረሚያ ቤት ቆይታው ምን ይመስል ነበር? ወደፊትስ ምን አቅዷል? የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ፤ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን አነጋግሮታል፡፡

Thursday, October 19, 2017

የሕወሃት የበላይነት በውዴታ አሊያም በግዴታ ያበቃል! | ስዩም ተሾመ

በሕገ መንግስታዊ የፌደራል ስርዓት በምትመራ ሀገር፣ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት በአራቱ የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች፤ ህወሓት፥ ብአዴን፥ ኦህዴድ እና ደኢህዴን ጥምረት የሚመራ ሆኖ ሳለ፣ በሀገሪቱ ለሚስተዋሉ ፖለቲካዊ ችግሮች ህወሓትን ብቻ ተጠያቂ ማድረግ አድሏዊነት ሊመስል ይችላል። ነገር ግን፣ ይሄ እውነታ እንጆ አድሏዊነት አይደለም። ሌሎች የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች፣ የፌደራል ስርዓቱና ተቋማት፣ እንዲሁም የክልል መንግስታትና ተቋማት የሚተዳደሩበት ሕግ፥ ስርዓትና መዋቅር በህወሓት የፖለቲካ መርህና አመለካከት ላይ የተመሰረተ ነው።

Monday, October 16, 2017

በረከት ስሞዖን መልቀቂያ ማስገባታቸው ተነገረ

ትናንት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቦርድ ሊቀመንበርነታቸው መባረራቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ በዘገበ ማግስት የብአዴን/ኢህአዴግ ከፍተኛ አመራር የነበሩት አቶ በረከት ስምዖን ከድርጅታቸውና ከሥራቸው የሥራ መልቀቂያ ማስገባታቸው እየተነገረ ነው::
የጠቅላይ ሚኒስተሩ አማካሪ ሆነው እየሰሩ የሰነበቱት አቶ በረከት ስምዖን መልቀቂያ ያስገቡበት ምክንያት እስካሁን አልተገለጸም:: ሆኖም ግን በዚህ መረጃ ዙሪያ የተለያዩ አክቲቭስቶች አስተያየቶችን እየሰነዘሩ ይገኛሉ::

Friday, October 13, 2017

ተመስገን ደሳለኝ የተፈረደበትን የእስር ጊዜ ያለ አመክሮ የጨረሰ ቢሆንም እስርቤቱ ሊፈታው ፍቃደኛ አልሆነም

Temesgen Desalegn "Fact" Ethiopian Amharic newspaper editor
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የወያኔ አገዛዝ የፈረደበትን የሦስት አመት የእስር ጊዜ (ያለ አመክሮ) ሙሉ ለሙሉ ጨርሶ የሚፈታበት ቀን ዛሬ ቢሆንም የዝዋይ እስርቤት ተመስገንን ሊፈታ ፍቃደኛ አለመሆኑን በእስርቤቱ ተገኝቶ የተመስገንን መፈታት ሲጠባበቅ የነበረው ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ ገልጿል።

የሴናተር ኢንሆፍ ህወሓትን የመታደግ ዘመቻ ቀጥሏል!


  • ጉብኝቱ “ከHR 128 … ውጪ ሊሆን አይችልም” ኦባንግ
የአሜሪካ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት አባል ሴናተር ጀምስ ኢንሆፍ ህወሓት/ኢህአዴግን ለመታደግ በአዲስ አበባ ላይ ከኢህአዴግ ሹሞች ጋር መከሩ። አቶ ኦባንግ ሜቶ ጉብኝቱ “ከHR 128 የተያያዘ ነው፤ ከዚህ ውጪ ሊሆን አይችልም” ይላሉ።

Thursday, October 12, 2017

ወሊሶ: በአንድ ቀን “ከሱናሚ ወደ ሰላም!”

በትላንትናው ዕለት በአንዳንድ የኦሮሚያ አከባቢዎች ሕዝባዊ ተቃውሞ ሲካሄድ እንደነበር ይታወሳል። ሰላማዊ ሰልፉ በተለይ በአምቦ ከተማ በሰላም ሲጠናቀቅ፣ በሻሸመኔ ደግሞ የስምንት ሰዎች ሕይወት ጠፍቷል። በተቃውሞ ሰልፉ ላይ “Down Down Woyane” የሚል መፈክር ሲሰማ እንደነበር በማህበራዊ ሚዲያዎች ተገልጿል። 

ለኢትዮጵያ የመከላከያና ፖሊስ ሠራዊት አባላት የተደረገ ጥሪ !! ከፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

የአርበኞች ግንቦት7 ሊቀመንበር በድጋሚ የቀረበ ።
የተከበራችሁ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት አባላት፤ የፌደራልና የክልል ፓሊስ አባላት፤ የአጋዚ ልዩ ኮማንዶ ጦር አባላትና ሌሎች የሥርዓቱ ታጣቂዎች። አገራችን በለውጥ ሂደት ውስጥ ባለችበት በዚህ ወሳኝ ወቅት ለእናንተ ቀጥታ መልዕክት ማስተላለፍ የሚገባ ሆኖ ስላገኘሁት ይህንን አጭር መልዕክቴን በጥሞና እንድታዳምጡኝ፤ የሰማችሁ ላልሰሙት እንድታደርሱልኝ እጠይቃለሁ።

Wednesday, October 11, 2017

አባዱላ ወደ ጨፌ ወይስ ወደ ሸቤ?

የሰበር ዜና ልክፍት የተጠናወተው የዘመኑ “ሚዲያ” የአባዱላን ከአፈጉባኤነት መልቀቅ በሰበር ዜናነት ማናፈሱ ቆም ብሎ ላየው ራስን ትዝብት ላይ የሚጥል ነው። የአባዱላ መልቀቂያ ማስገባት “ምስጢር” በቅርቡ የሚለይለት ቢሆንም በህወሓት ተለክቶና ተጠፍጥፎ የተሠራ ድርጅትና ስብዕና ያለው ለዚህ ዓይነት የሞራል ልዕልና ይደርሳል ብሎ መገመት ህወሓትን ካለማወቅ ወይም ራስን ከመሳት የሚመነጭ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም።

የሕወሓት ደህንነት የኦህዴድ ባለስልጣናትን አስጠነቀቀ | መልቀቂያ ያስገቡ ባለስልጣናትን በሽምግልናም በማስፈራሪያም እያጣደፋቸው ነው

(ዘ-ሐበሻ) የኢህአዴግ አባል የሆነው ኦህዴድ አመራር ለሕወሃት አልታዘዝም ማለቱን ተከትሎ ድርጅቱ በደህንነቱ በኩል የኦህዴድ ባለስልጣናትን እያስፈራራ ሲሆን በሌላ በኩልም በሽምግልና ወጥሮ እንደያዛቸው የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታወቁ::

Monday, October 9, 2017

አልተገናኝቶም (መስቀሉ አየለ)

መስቀሉ አየለ
UNREST
ኦህዴድ ብአዴንን ይበልጠዋል የሚለው “ዩኒቨርሳል ትሩዝ” አይነት በመሆኑ ማዎዳደሩ ተገቢ አይመስለኝም። አንድ ቢሉ ምንም እንኩዋን ሁለቱም አሽከርነታቸው ለትግራዩ ገዥ ጉጅሌ ቢሆንም ኦህዴድ ተቦክቶ የተሰራው ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ከኦሮሞ ልጆች ሲሆን ብአዴን ግን አፈጣጠሩ ከጨነገፈው የኢህአፓ ሽል ሲሆን ቀስ ብሎ ኢህአዴን ተብሎ በኢትዮጵያዊ ማንነት ለመምጣት ሞከረና ድህረ ደርግ የዘር ፖለቲካ የበላይነት ሲያገኝ የሚገባበት ቢያጣ አማራ ነኝ ብሎ ባህር ዳር ውስጥ ሄዶ ተወሸቀ። ለዚህም ነው በብአዴን ዋናዎቹ የቀድሞ አመራር ውስጥ አማራ የሆነ ሰው ፈልጎ ማግኘት ችግር የሚሆነው። አዲሱ ለገሰ የሚዛን ተፈሪ ኦሮሞ ነው። ተፈራ ዋልዋ ከጊሚራ ብሄረሰብ ነው። ህላዌ ዮሴፍ ትግሬ ነው። በረከት ኤርትራዊ ነው። አያሌ ጎበዜ ትግሬ ነው። መለስ ጥላሁን ትግሬ እያለ ሲቀጥል የዛሬዎቹ ተተኪዎች እነ ካሳ ተክለ ብርሃን እነ አለምነው መኮንን እንዲሁ ነፍሳቸው ከየት እንደተጋገረ እና እንወክለዋለን የሚሉትን ህዝብ ምን ያህል እንደሚጠሉት ግልጽ ሲሆን ደመቀ መኮንንም ህወሃት አድርግ ያለውን ለማድረግ የቆረበ የከሚሴ ኦሮሞ መሆኑን ወዘተ ማየት ነው። ስለዚህ የብሄር ፖለቲካን በመርህ ደረጃ ተቀብለው ሳለ በማይወለዱበት ይልቁንም በጣም በሚጠሉት ህዝብ ላይ የተሾሙ ጋንግሪኖች በየትኛው ሰብእናቸው እንደ አንድ ኦህዴድ ለኦሮሞ የሚቆረቆረውን ያህል እነሱ ለአማራውሊቆረቆሩ ይችላሉ?

ሽሽት እና የአባዱላ ገመዳ ነገር (ክንፉ አሰፋ)

ክንፉ አሰፋ
Abadula Gemeda Resigns
ከሰሜን እና ከበስተ-ምስራቅ አቅጣጫ እየነፈሰ ያለው አውሎንፋስ መርከብዋን እያናጋት ይገኛል።  ጫፍ ላይ ጉብ  ያሉትን አስተናጋጆች እያንጠባጠበ የሚገፋው ሃይል እየበረታ መጥቶ፣ አሁን ከካፒቴኑ ቁጥጥር ውጭ የሆነ ይመስላል። ይህ ሁላችንንም የሚያስማማን መራራ ሃቅ ነው። ችግሩ እዚህ ላይ አይደለም። ግን… እየሰመጠ ካለው ከዚህ መርከብ ለማምለጥ የተገኘችውን ቀዳዳ እየተጠቀሙ የሚሾልኩትን ሁሉ “ጀግና” ብለን ለመጥራት እንደምን ይዳዳን?
ራስን ማዳን እና ሃገርን ማዳን፤ በሰማይና በምድር መሃከል ያለ ርቀትን ያህል የተለያዩ ነገሮች ናቸው።
ዘንግተነው ከሆነ ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ይህ ስራዓት “በስብሷል” ብሎ ከተናገረ 10 አመታት አልፈውታል። ከ 26 ዓመታት በኋላ ደግሞ እነሆ ህወሃት ከርፍቶ መርገፍ ጀመረ። ችግሮቹ ግን እጅግ እየተባባሱ እንጂ እየተሻሻሉ አልመጡም። ይህ ስርዓት ዛሬ እንደ ውሃ እና መብራት ያሉ መሰረታዊ የሆኑ የሰው ልጅ ፍላጎቶችን እንኳን ማሟላት ተስኖታል።  “በመለስ ግዜ በፈረቃ፣ ደብረጽዮን ግዜ በደቂቃ” እያለ ከተሜው የስርዓቱን ቁልቁል እድገት የሚነግረን ያለ ምክንያት አይደለም።
ታዲያ በዚህ ሁሉ ረጅም ጉዞ አብረው ዘልቀው፣ አብረው በልተው፣ አብረው ጠጥተው፣ አብረው ዶልተው፣ አብረው ፈስተው፣ አብረው ሰርቀው፣ አብረው ዋኝተው፣ አብረው ቀልተው፣ አብረው አርደው፣ አብረው ቀብረው … አሁን ከድተናል ሲሉ በእርግጥ “ሃገርና ሕዝብን አስበው ነው? ወይንስ ራስን ለማዳን?” ብለን መጠየቅ ግድ ይለናል። ሃገርና ሕዝብ ለ26 ዓመታት እንደ አህያ ሲረገጡ እነዚህ ሰዎች መርከብዋ ውስጥ አብረው ነበሩ። እጃቸውን ሳይጠመዘዙ ከተዳሩበት የህወሃት የጋብቻ ትስስር በኋላ “ሰዎቹ አሜሪካ አገር ሲገቡ ውሉን ለምን አፈረሱት?” ብሎ የሚጠይቅ ብዙ አይታይም።

Sunday, October 8, 2017

የፊንፊኔ ደላላ- ኧረ የገዥ ያለህ፣ ሞጃዎች ሊኮበልሉ ይመስላል (ለዋዜማ ራዲዮ)

ጤና ይስጥልኝ ጌታዬ!

Bilderesultat for ኦቦ አባዱላ
ገረመው እባላለሁ፡፡ እሳት የላስኩ የፊንፊኔ ደላላ ነኝ፡፡ ምስጉን ጉዳይ ገዳይ ስለመሆኔ እግዜርም ሰይጣንም ያውቃሉ፡፡ ኪራይ ሰብሳቢ መሆኔን ድሪባም ኩማም ያውቃሉ፡፡ ዉሎ-አዳሬ ብሔራዊ፣ አመሻሼ አብዮታዊ ሃሃ፣ ላየን ባር ቤቴ፣ ቴሌ ባር ግዛቴ፡፡
እውነት ነው! ጥሎብኝ አልረጋም፡፡ ካዛንቺስ ነው ሲሉኝ ሳሪስ፣ ቀበና ነው ሲሉኝ ባምቢስ ደላላ ምን ቀልብ አለው ብለው ነው፤ጌታው!

HR 128/SR 168 ጸሐይ እየጠለቀችበት ነው!

ለኢትዮጵውያን ታላቅ ተስፋ ይዞ የተነሳው HR 128/SR 168 በሞት አፋፍ ላይ እንደሚገኘ ተነገረ። የህወሃት/ኢህአዴግን ህልውና በማያፈናፍን አጣብቂኝ ውስጥ እንደሚከት ብዙ የተባለለት ይህ ረቂቅ ሕግ ወደ ሕግ መወሰኛ ምክርቤት ቀርቦ ድምጽ ከማግኘቱ በፊት ጊዜውን ጠብቆ እንዲሞት የማቀዛቀዝ ተግባር እየተፈጸመበት ነው። ኢትዮጵያውያን ተባብረው በመታገል ይህ ዕድል እንዳያመልጣቸው ማድረግ እንዳለባቸው ማሳሰቢያ ተሰጠ።

Saturday, October 7, 2017

​አፈ-ጉባዔ አባዱላ ገመዳ ራሳቸውን ከኃላፊነት አነሱ!

ከስዩም ተሾመ
ሰኞ መስከረም 28/2010 ዓ.ም 5ኛው ዙር የ3ኛ አመት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ይጀመራል። ይህን አስመልክቶ የሪፖርተር ጋዜጣ ሁለት ጥያቄዎች አቅርቦልኝ ነበር። የመጀመሪያው ባለፉት ሁለት አመታት በሀገራችን ከነበረው አጠቃላይ ፖለቲካዊ ሁኔታ አንፃር ሲታይ “የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የሚወክሉትን ሕዝብ በሚገባ እያገለገሉት ነው ወይ?” የሚል ነበር። ይህ ጥያቄ ምክር ቤቱ በሕገ መንግስቱ ከተሰጠው ስልጣንና ኃላፊነት አንፃር መታየት አለበት። በዚህ መሰረት የሚከተለውን ምላሽ ሰጥቼ ነበር፡-
“ባለፉት ሁለት አመታት በተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች ተቃውሞና አድማ ተካሂዷል። ዜጎች ለተቃውሞ አደባባይ የሚወጡት እና የሥራ አድማ የሚጠሩት፤ አንደኛ፡- በሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 30ና 42 ላይ በግልፅ የተደነገገ ዴሞክራሲያዊ መብት ስለሆነ ነው፣ ሁለተኛ፡- ዜጎች የነፃነት፥ እኩልነትና ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ጥያቄ ስላላቸው ነው። ነገር ግን፣ ዜጎች ለተቃውሞ አደባባይ ሲወጡ የፀጥታ ኃይሎች በወሰዱት ከመጠን ያለፈ የኃይል እርምጃ የብዙዎች ሕይወትና ንብረት ጠፍቷል። ይህ ሁሉ የሆነው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 55 መሰረት የተሰጣቸውን ስልጣንና ኃላፊነት በአግባቡ ባለመወጣታቸው ነው።”

Friday, October 6, 2017

አይቀሬው የለውጥ ማዕበል በኢትዮጵያ እና የህወሀት/ኢህአዴግ የቁልቁለት መንገድ! (በኢንጂነር Yilkal Getnet)

Image may contain: 1 person, smiling, standing and suit
ኢትዮጵያ ሐገራችን አሁን ላለችበት ማሕበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ መፍትፌው ምን መሆን አለበት በሚለው አስተሳሰብ ላይ በገዥው ቡድንና በለውጥ ኃይሉ ያለው ልዩነት እንደተጠበቀ ሆኖ ችግሮቹ በተጨባጭ መኖራቸውን በመረዳት በኩል ግን በገዥውም ሆነ በለውጥ ፈላጊዎች መካከል ብዙም ልዩነት ስለሌለ ስለሚደርሰው ግፍ፣ ግድያ፣ አፈናና ሌሎች ቀውሶችን መተንተን አሁን ላይ ብዙም አስፈላጊ ሆኖ ስላልታዬኝ በለውጥ አይቀሬነት፣ የለውጥ ስልቶችና ውጤቱ ላይ አተኩራለሁ፡፡
ለውጥ ተፈጥሯዊ ነው፣ማንኛውም ነገር ይለወጣል፡፡ የሰው ልጅም ይወለዳል ያድጋል ይሞታል፡፡ስልጣኔም ይፈጠራል፣ያብባል ከዚያም ያረጅና በሌላ ስልጣኔ ይተካል፡፡ አገዛዝም የተለያዩ ማደናገሪያዎችንና አስተሳሰቦችን ይዞ በስልጣን ላይ ይቆያል፡፡ ያለውን አመለካከትና አገዛዝ የማይሸከም ህሊናዊና ነባራዊ ሁኔታ ሲፈጠር በስብሶ ይወድቃል፣ በሌላ ሰርዓት ይተካል፡፡
ስለዚህም ህወሀት/ኢህአዴግ ወደደም ጠላም እኛ ተንቀረፈፍንም ፈጠንም በራሱ በተፈጥሮ ህግም ቢሆን ለውጥ አይቀሬ ነው፡፡ የእኛ ሚና ሊሆን የሚችለው ለውጡን በራሱ በተፈጥሮ ከሚሆነው ይልቅ እግዚዓብሄር በሰጠን አዕምሮ ተጠቅመን በታቀደና በተጠና መልኩ በአነስተኛ ወጭና ጊዜ ወደ ተሻለና አስቀድሞ ውጤቱ ወደታወቀ መንገድ መምራት ነው፡፡ ይህንን ካለደረግን ተፈጥሮ በራሱ ለውጥ የሚያደርግብን እንጅ በራሳችን ነገሮችን የምንለውጥ ወይም የመጡ ለውጦችን የምንቆጣጠር ሰብዓዊ ፍጡሮች መሆናችን ይቀርና ደመነፍሳዊ እንስሳ ወደ መሆን እንጠጋለን፡፡ ይህንን ካልኩ በኋል አሁን በሃገራች ያለውን የለውጥ ማዕበል በተመለከተ በሶስት ክፍሎች በአጭሩ ለመዳሰስ እሞክራለሁ፡፡

Wednesday, October 4, 2017

“ታፍኜ እቤት ውስጥ እንድቀመጥ ከተደረኩ በኋላ ተረስቻለሁ” – የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ ፓርቲ ዋና ጸሐፊ አቶ በቀለ ነጋ

በጽዮን ግርማ (VOA Amharic)
በፓርቲያቸው ስም ምንም ዓይነት መግለጫ እንዳይሰጡ፣ ከቤት እንዳይወጡና ሥራ እንዳይሠሩ ከተደረጉ አንድ ዓመት ከዘጠኝ ወር እንደተቆጠረ የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ ፓርቲ ዋና ጸሐፊ አቶ በቀለ ነጋ ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ።
Bekele Nega of Oromo Federalist Congress
አቶ በቀለ ነጋ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ዋና ጸሀፊ
“ከዚህ በላይ መብቴ ሊነካ አይገባም፣ ታፍኜ እቤት ውስጥ እንድቀመጥ ከተደረኩ በኋላ ተረስቻለሁ” ብለዋል።
ፓርቲያቸው አባል የሆነበት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ የሚገኙበትን ሁኔታ ጠቅሶ ደብዳቤ ጽፎ ቢጠይቅም አጥጋቢ ምላሽ የሚሰጥ አካል መታጣቱን ጨምረው ተናግረዋል።
የፓርቲው ጠበቃ አቶ ወንድሙ ኢብሳ በበኩላቸው “ይህን ትዕዛዝ አስተላልፌያለሁ” የሚል አካል መታጣቱን ተናግረዋል። ሁኔታውን ከፖሊሰ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።

Tuesday, October 3, 2017

ክህደትና ድጋፍ መንሳት – የፖለቲከኞች መሰሪ ስልት (ይገረም አለሙ)

Birtukan Mideksa
Birtukan Mideksa is an Ethiopian politician and former judge who was the founder and leader of the opposition party, the Unity for Democracy and Justice (UDJ).
ይገረም አለሙ
ተዋከበና
ወዲህ ዘወር ቢል ሰው የለምና
ገብርዬ ሲሞት ቀኙ ዛለና
አረሩን ስቦ ጠጣው ያ ጀግና

Sunday, October 1, 2017

ታዋቂው አሜሪካዊ አርቲስት ጄይ-ዚ የሞ አንበሳ አርማ ያለበትን የቀድሞ የኢትዮጵያ ባንዲራ ሲያስውለበልብ አመሸ


(ECADF) — ታዋቂው አሜሪካዊ አርቲስት ጄ-ዚ (Jay-Z)… (የታዋቂዋ አሜሪካዊት አርቲስት ቢያንሴ ባለቤት) እና የቦብ ማርሌ የመጨረሻ ልጅ ደሚያን ማርሌ ትላንት ቅዳሜ ምሽት ሳተርደይ ናይት ላይቭ (Saturday Night Live) በመባል በሚታወቀውና እጅግ በርካታ ተመልካች ባለው የቴሌቪዥን ፕሮግራም ላይ እንግዳ ሆነው በመገኘት የሙዚቃ ስራዎቻቸውን ባቀረቡበት ወቅት መድረኩ ላይ የሞ አንበሳ አርማ ያለበት በቀዳማዊ ኃይለስላሴ ዘመን የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ሆኖ ያገለግል የነበረው ባንዲራ ሲውለበለብ አምሽቷል።