Translate

Monday, October 31, 2016

Sunday, October 30, 2016

ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ያደረጉት ጥሪ በመከላከያ ሰራዊቱ ዘንድ ከፍተኛ ተደማጭነትን እያገኘ መምጣቱ ታወቀ!

ናትናኤል ኃይለማርያም
4814177_7
የአርበኞች ግንቦት ሰባትሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሀኑ  ለመከላከያ ሰራዊት አባላት፣የፌደራለ እና የክልል ፖሊስ አባላት፤ለአጋዚ ልዩ ጦር አባላት እና ለሌሎች ስርአቱ ታጣቂዎች ያደረጉት  ጥሪ  በሰራዊቱ ዉስጥ ከፍተኛ መነጋገሪያ  ከመሆኑም በተጨማሪ ሰራዊቱ ከህዝብ ጋር ለመቆም የመጨረሻ ዉሳኔ ላይ እንዲደርስ ያደረገዉ ጥሪ ነዉ ሲሉ እነዚሁ ምንጮች ጠቅሰዋል።የተደረገዉን ጥሪ መቀበላቸዉን ለማመላከት ሀሳባቸዉን የገለጹት የሰራዊቱ አባላት እንዳሉት “ መከላከያዉ የህዝብ ሳይሆን የህዉሀት ቡድን አገልጋይ እየሆነ መምጣቱን ሙሉ በሙሉ ያወቁበት ደረጃ ላይ መድረሳቸዉን እና ሊቀመንበሩ እንዳሉት ሰራዊቱ የቁም እስረኛ ሲሆን በተለይ ህዝባዊ እምቢተኝነቱ ከተጀመረ ጀምሮ ምን እንደሚያደርግ እና ወዴት እንደሚሄድ የጠራ አቅጣጫ ባለማግኘቱ እና ባለበት ከፍተኛ ጫና የተነሳ አማራጭ በማጣት በሰራዊቱ ዉስጥ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

Saturday, October 15, 2016

የአርበኞችግንቦት 7 ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መግለጫ


የአርበኞችግንቦት 7 ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መግለጫ
October 14, 2016
ጥቅምት 1 ቀን 2009 ዓ.ም.
የአርበኞች ግንቦት 7 ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባውን ከመስከረም 28 እስከ ጥቅምት 1 ቀን 2009 ዓ.ም. አካሂዶ በወቅቱ የአገራችን ሁኔታዎች ተነጋግሮ ውሳኔዎችን አሳልፏል፤ ሠራዊቱንም አነጋግሯል።
ሥራ አስፈፃሚው የአገራችን ፓለቲካዊ ሁኔታዎች በፍጥነት እየተለዋወጡ መሆኑና ተከታታይነት ያለው ወቅታዊና ውጤታማ አመራር መስጠት የሚገባ መሆኑ አጽንዖት ሰጥቶበታል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው እምነት፣ በአገራችን የተለያዩ አካባቢዎች የተቀሰቀሰው ሕዝባዊ እምቢተኝነት በህወሓት የአገዛዝ ዘመን ደርሶ ወደማያውቅበት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል። ሕዝብ ለሚያቀርባቸ ጥያቄዎች ሁሉ ምላሹ ጥይት፣ እስርና ጉልበት የሆነው የህወሓት አገዛዝ በሚሰጣቸው ፋሽታዊ ምላሾች ሳቢያ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎቻችንተሰውተዋል፤ በአስር ሺዎች የሚገመቱት ደግሞ ለእስር ተዳርገዋል። በዚህም ምክንያት ለውጥ ፈላጊው ሕዝብ ሕዝባዊ እምቢተኝነት ከሕዝባዊ አመጽ ጋር ለማቀናጀት ተገዷል፤ ሰላማዊ ዜጎች ራሳቸውን ለመከላከል መሣሪያ ለማንሳት ተገደዋል። ለፖለቲካ ችግሮች ፖለቲካዊ መፍትሄ ከመስጠት ይልቅ ችግሩን በኃይል እወጣዋለሁ ብሎ እየሄደበት ያለው መንገድ ፈጽሞ እንዳይሳካ ማድረግና ይልቁንም ውድቀቱን የሚያፋጥን እንዲሆን ማድረግ የንቅናቄዓችን የጊዜው አብይ ተግባር መሆኑን ሥራ አስፈፃሚው አምኖበታል።ይህን እውን ለማድረግድርጅታችን የሕዝቡን ትግል በአግባቡ ማቀናጀትና መምራት ቀዳሚ ሥራው እንደሆነ የአርበኞች ግንቦት 7 ሥራ አስፈፃሚ ስምምነት ላይ ደርሷል።

Friday, October 14, 2016

ከሰሞኑ አስደናቂ የፕሮፖጋንዳ ዘመቻዎች ሁለቱ !

Tadesse Biru Kersmo
ከሰሞኑ አስደናቂ የፕሮፖጋንዳ ዘመቻዎች ሁለቱ !
1. በ1997 ምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የአመጽ አማራጮችን ሁሉ ይቃወም የነበረው ሰላማዊ ታጋይ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አሁን የአመጽ ጥሪ ማቅረቡ በንጽጽር እየቀረበ ትናንት “ሰላምን በመስበክ ሲያሞኘን የነበረ ሰው ዛሬ ይኸው በይፋ ጦርነት አወጀብን” እያሉን ነው። በህወሓት ፕሮፖጋንዲስቶች ትንተና መሠረት፣ ይህ የአቋም ለውጥ የመጣው ስልጣን ፈላጊ ስለሆነ ነው።
ፕ/ር ብርሃኑ ከመነሻው የትጥቅ ትግል አማራጭን አለመስወዱ፤ ለሰላማዊ ትግል እድል መስጠቱ፤ በሰላማዊ መንገድ ታግሎ ለውጥ ለማምጣት በሙሉ እምነትና ጉልበት መንቀሳቀሱ ያስመሰግነዋል እንጂ እንዴት ሊያስወስቅሰው ይችላል? ትንሽ የማሰላሰል ችሎታ ያለው ሰው “ለመሆኑ በ 1997 ምን ሆነ? ከ 1997 በኋላ የዚህን ሰው አቋም የሚያስቀይር ነገር ምን ተፈፀመ?” ብሎ አይጠይቅም ብለው ለማመን እንዴት ቻሉ?
ምርጫ 97 ለፕ/ር ብርሃኑ ያረጋገጠለት ህወሓት በሰላማዊ ምርጫ ስልጣን እንደማይለቅ ነው። ባይሆን “በ97ስ እንዴት በምርጫ ይለቃል ብሎ አመነ?” ቢባል እንኳን ትንሽ ወግ ያለው ጥያቄ በሆነ። ይኸ ጥያቄም ብዙ ጊዜ ተጠይቆ መልስ ሰጥቶበታል “ወያኔ በሰላም ለመልቀቅ ተፈጥሮው አይፈቅድለትም ከሚል ነቢባዊ ውሳኔ በተግባር ተፈትኖ የሚሰጥ ውሳኔ ይሻላል” ዓይነት ምላሽ ሲሰጥ ብዙ ጊዜ ሰምቸዋለሁ።
ይኸ ጉዳይ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ታህሳስ 4 ቀን 2002 ዓ. ም. (December 10, 2009) የኖቤል የሰላም ሽልማት ሲቀበሉ ያደረጉት ንግግር ያስታውሰኛል። እንዲህ ብለው ነበር።
“እውነቱን በመቀበል እንጀምር − ብጥብጥ ያለበት ቅራኔን በእኛ እድሜ ማስቀረት አንችልም። ለወደፊቱም ሕዝቦች − በግልም ሆነ በጋራ − ኃይልን መጠቀም አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን ከሞራል አንፃርም ተገቢ የሚሆንበት ሁኔታ ይኖራል። ... አንሳሳት! ክፋት በዓለም ላይ አለ። በሰላማዊ ትግል ሂትለርን መግታት አይቻልም ነበር። ... አንዳንዴ ጉልበት መጠቀም ያስፈልጋል ማለት ከሃቅ የራቀ ምፀት አይደለም፤ ይልቁንስ ታሪክን በቅጡ መረዳት፤ የሰውን ልጅ ድክመቶችን ማወቅ እና የምክንያታዊነት ውስንነትን መገንዘብ ነው። ... ሰላም ተመራጭ መሆኑ መታመኑ ብቻውን ሰላምን ለማስገኘት አይበቃም።”

Wednesday, October 12, 2016

ለመለስ የተፃፈ ደብዳቤና የመለስ መልስ

ፍቃዱ ጌታቸው ለመለስ ወለላዬ ለመለስ መልስ

meles-z


ከፍቃዱ ጌታቸው ለመለስ
እንደምን አለህ ጋሼ እንደምን ነህ መለስ
ትመጣለህ ስንል ቀረህ ሳትመለስ
እኛማ ይሔውልህ
ባንተ ሌጋሲና ባንተ ትልቅ ራዕይ
በየአደባባዩ እንላለን ዋይ ዋይ
ዛሬም ጀነራልህ ተኩስ ነው ትዕዛዙ
ወገን ያጋድማል የግፍ አፈሙዙ
ለምንድን ነው ስንል ስምክን አስቀድመው
ከክርስቶስ በላይ ምስልህን አትመው
ቅዱስ መጽሐፍ ይመስል
ባንተ ራዕይና በሌጋሲህ ምለው
ቢረፈርፉንም አላለቅንምና
ደብዳቤ ላክንልህ ከሞት የተረፍነው!

ህወሃት “አስከሬን ልግዛችሁ” አለ!

የኦሮሚያ 2.4 ቢሊዮን ብር የት ገባ?

blood birr

በሙት መንፈስ አገር እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በይስሙላነት ባስቀመጠው ፕሬዚዳንት አማካኝነት ፓርላማ ብሎ በሰየመው የራሱ ስብስብ በኢትዮጵያ ያለ አንዳች ልዩነት ለገደላቸው ወገኖች አስከሬን መግዣ ብር ሰይሜአለሁ ብሏል፡፡ ከዚህ በፊት በኦሮሚያ ላፈሰሰው መድቤአለሁ ያለው 2.4 ቢሊዮን ብር እስካሁን የት እንደገባ አይታወቅም፡፡

“ህወሃት በእስረኞች ላይ አጥንት የሚያመነምን መርዝ ይጠቀማል” እማኝ

"የባዮሎጂካል መሣሪያ ጥቃት ነው፤ ቤተሰብ ለልጆቻችሁ ድረሱ"

bio-bone

በኢትዮጵያ እስረኞች አጥንትን ቀስ በቀስ በሚያፈርስ መርዝ እየተጠቁ መሆኑን ታውቁ ኖሮዋል?
ከጥቂት ዓመታት በፊት የግንቦት ሰባት መሪዎች እና አባላት መታሰራቸው ይታወሳል። ብዙዎቹ ቃሊቲ የሚገኘው እስር ቤት ነበሩ። በእስር ቤት እያሉ በደረሰባቸው ያልታወቀ ሕመም ምክኒያት ሕይወታቸውን ያጡ መሪዎችም ነበሩ።ታዲያ አንዴ ከሜክሲኮ ወደ ሃያሁለት በታክሲ ተሳፍሬ ስሔድ በግምት የሃያ ዓመት ዕድሜ ያለው ልጅ ታክሲው ውስጥ ገብቶ አጠገቤ ተቀመጠ።

Tuesday, October 11, 2016

ኢንጂነር ይልቃል ታሰሩ

(ዘ-ሐበሻ) የሰማያዊ ፓርቲን እስከባለፈው ሳምንት ድረስ ሲመሩ የቆዩት ኢንጂነር ይልቃል መታሰራቸው ተሰማ:: ከርሳቸው ጋር አብረው ሌሎች የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች መታሰራቸው ተሰምቷል::
መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አውጥቻለሁ; እየታደስኩኝም ነው ባለ ማግስት ተቃዋሚዎችን እየጠራረገ ማሰሩን ተያይዞታል::
hiber-radio-interview-with-eng-yilkal-getnet.jpg
ከኢንጂነር ይልቃል በተጨማሪ አቶ ወረታው ዋሴ; ወይንሸት ሞላ እና ብሌን መስፍን እንዲሁም እያስጴድ ተስፋዬ በተለያዩ ቦታዎች በደህንነቶች ተይዘው መታሰራቸውን የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታውቀዋል::
ሰማያዊ ፓርቲ ባለፈው ሳምንት ባደረገው ጉባኤ ኢንጂነር ይልቃልን ከሊቀመንበርነት ማንሳቱ ይታወሳል::

Monday, October 10, 2016

ህወሃት/ኢህአዴግ ዕድሜዬ ከ6 ወር አይበልጥም አለ

"ህወሃት የመቀበሪያ ጉድጓዱን በጥልቅ የቆፈረበት አዋጅ ነው"

soilders

ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም የሚገዛው ህወሃት ላለፉት 25ዓመታት መብት በገፍ ሲሰጥ የቆየ ይመስል ህገመንግሥታዊ መብቶችን የሚገፍ ያስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጇል። አዋጁ ለስድስት ወር ይቆያል ማለቱ የህወሃት ዕድሜ ከስድስት ወር እንደማይቆይ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል፡፡

Thursday, October 6, 2016

አዲስ አበባ ተቆላልፋለች – ፖሊስ እና ሰራዊቱ በሕዝብ ላይ አልተኩስም ብለዋል (ወቅታዊ ሪፖርታዥ)

ክንፉ አሰፋ 
መግቢያ የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ብሄራዊ እርቅ እና ድርድር እንዲደረግ ጥሪ ማድረጉ ይታወሳል። አምስቱ የሕወሃት ቁንጮዎች ትእቢት የተሞላበት ምላሽ ነው የሰጡት። ከድርድር ይልቅ ከሕዝብ ጋር ጦርነት መግጠምን መርጠዋል።

Soldiers in Addis Ababa, Ethiopia አብዛኛው የፖሊስ እና የሃገር መከላከያ ሰራዊቱ “ሕዝብ ላይ አልተኩስም” ማለታቸው የህወሃት አመራርን ጭንቅ ውስጥ አስገብተውታል።

 አዲስ አበባ ተቆላልፋለች። በአራቱም አቅጣጫ በኩል የሚገባም የሚወጣም የለም።  መንገዶች በሙሉ ተዘጋግተዋል።  ስልክ እና ኢንተርኔት ጠፍቷል።

 በአዲስ አበባ ዙርያ ባሉ ከተሞች ሰኞ መስከረም 23 ቀን የተጀመረውን ሕዝባዊ አመጽ ለማዳፈን በህወሃት የተወሰደው የአፈሳ እርምጃ አመጹን አላቆመውም። ሰኞ ማምሻውን በሺዎች የሚቆጠሩ ዘጎች ታፍሰው ወዳልታወቀ ስፍራ በወሰዳቸው ሳብያ አመጹ በዛሬው እለት ተባብሶ ቀጥሏል።  የአካባቢ ፖሊሶችም ከሕዝብ ጋር በመሆን በአመመጹ እየተሳተፉ በመሆኑ የስራአቱን ቁንጮዎች ጭንቀት ውስጥ ከቷቸዋል።

Tuesday, October 4, 2016

በሕዝብ አቆጣጠር አሁን ሁሉም ነገር አበቃ ህወሃት - ቄጤማና ቅጠል የያዘን ህዝብ ረሸነ


irreecha74
irreecha55
ዛሬ ጨለሞ ዋለ። ዛሬ አገር ማቅ ለበሰች። ዛሬ የሆነውን ማመን ይከብዳል። ቄጤማና ቅጠል ይዘው የወጡ ሰላማዊ ዜጎች በጅምላ ተረሸኑ። “Down! Down! Woyane … Down! Down TPLF! …” በማለት ቁጣውን የገለጸ ሕዝብ እገዛሃለሁ በሚለው የትግራይ ህዝብ ተገንጣይ ቡድን (በህወሃት) ተጨፈጨፈ። ከአየርና ከምድር ጭስና ጥይት የተረጨበት ህዝብ፣ የሚገባበት ጠፍቶት የውሃ ራት ሆነ። ሞተ። ቆሰለ። በውሃ ተበላ።

“አሁን ደም ተቃብተናል፤ ዕርቅ የለም፤ ሌላ ሳይከተል ልቀቁልን”፤ “ከህወሃት ጋር ድርድርና እርቅ ብሎ ነገር የለም” የሕዝብ ምላሽ ሃይለማርያም ውረድ ተባለ!


irreecha79
ኦሮሚያ ብቻ ሳትሆን ድፍን አገርን ማቅ ያለበሰው የጅምላ ጭፍጨፋ እያደር አጥንት የሚያደቅ መረጃ እየወጣበት ነው። ህወሃት የእርቅ መንገዶችን በሙሉ አሟጦ የቀበረበት ይህ “ይቅርታ የሌለው ወንጀል” እስካሁን የ678 ንጹሃንን ህይወት አጥፍቷል። የትዳር ጓደኛውን አስከሬን በግል ተሽከርካሪ ጭኖ እያነባ ወደ ቤተሰቡ የወሰደ አለ። ገንዘብ ተዋጥቶለት የሚስቱን አስከሬን ጭኖ ወደ ሱሉልታ የተጓዘ መኖሩ ተሰምቷል። እናትና ልጅ ባንድነት ቀብራቸው ተከናውኗል። በአንድ ቀን ሁለት ወይም ከዚያ በላይ ወገኖች ከቤተሰባቸው ጎድለዋል። አስከሬን አሁን ድረስ እየተቆፈረ እየወጣ ነው። ሃይቅ ላይ የተንሳፈፉ አስከሬኖች እየተለቀሙ ነው። ህዝብ ቁጣው ገንፍሎ በተለያዩ ስፍራዎች እምቢተኛነቱን እየገለጸ ነው። ህወሃት ግን አሁንም ይዋሻል።

በሰበታ፣ ዓለም ገና፣ በፉሪና አየር ጤና የሕዝብ ቁጣ ገነፈለ – የትግራይ ነጻ አውጪ ወታደሮች እየተኮሱ ነው

(ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ ዙሪያ ባሉት በሰበታ፣ ዓለም ገና፣ በፉሪና አየር ጤና ሕዝብ ግልብጥ ብሎ አደባባይ በመውጣት በመንግስት ላይ ተቃውሞውን በማሰማት ላይ መሆኑ ተሰማ:: ለዘ-ሐበሻ የመጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በነዚህ ከተሞች የንግድ እንቅስቃሴዎች ቆመዋል::: ሕዝቡን ለመበተን የትግራይ ነጻ አውጪ ወታደሮች እየተኮሱ መሆኑ ተሰምቷል::
14591847_1848685248699812_7965544009936441995_n
በቅድሚያ በፉሪ የጀመረው ተቃውሞ ወደ አየር ጤና የተዛመተ ሲሆን ዓለም ገና እና ሰበታም በሕዝብ ተቃውሞ እየተደበላለቁ ይገኛሉ::
ከፉሪ እስከ ጆሞ ድረስ የፌደራል እና የኦሮሚያ ክልላዊ ፖሊስን ዩኒፎርም የለበሱ የትግራይ ነጻ አውጪ ወታደሮች እንደወረሩት ሲሰማ ሕዝቡን ለመበተንም ተኩስ ከፍተዋል::
በፉሪ ሱቆች እና ካፌዎች በአጠቃላይ ንግድ እንቅስቃሴ መቆሙም ተዘግቧል:: ጆሞ አካባቢ ልጆቻቸውን የሚያስረምሩ ወላጆች ወደ ትምህርት ቤት በመሄድ ልጆቻቸውን እያወጡ ሲሆን በነዚህ አካባቢዎች ትራንስፖርት መቆሙም ታውቋል::

Saturday, October 1, 2016

“ኦጋዴን፤ የኢትዮጵያ [የህወሃት] ድብቅ ኃፍረት”

“አንዳችሁንም አናስተርፍም፤ እንጨርሳችኋልን” የህወሃት ነፍጠኞች

Ogaden 15
ሰዎችን እንደ እህል በዘር ጆንያ እየሠፈረ በፈለገበት ሣጥን ውስጥ ማስገባት ዓላማው የሆነው የትግራይ ሕዝብ ነጻአውጪ ግምባር (ህወሃት)፤ በኦሮሞ ተቃውሞ #oromoprotest እና በአማራ ተጋድሎ #amhararesistance የተነሳውሕዝባዊ እምቢተኝነት ዕንቅልፍ ስለነሳው በተለይም ደግሞ የሁለቱ በኅብረት መቆም ኅልውናው ላይ አደጋ ስለጣለበት ሶማሊና አፋር ክልል መንጎዳጎድ ጀምሯል፡፡