Translate

Tuesday, October 4, 2016

በሰበታ፣ ዓለም ገና፣ በፉሪና አየር ጤና የሕዝብ ቁጣ ገነፈለ – የትግራይ ነጻ አውጪ ወታደሮች እየተኮሱ ነው

(ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ ዙሪያ ባሉት በሰበታ፣ ዓለም ገና፣ በፉሪና አየር ጤና ሕዝብ ግልብጥ ብሎ አደባባይ በመውጣት በመንግስት ላይ ተቃውሞውን በማሰማት ላይ መሆኑ ተሰማ:: ለዘ-ሐበሻ የመጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በነዚህ ከተሞች የንግድ እንቅስቃሴዎች ቆመዋል::: ሕዝቡን ለመበተን የትግራይ ነጻ አውጪ ወታደሮች እየተኮሱ መሆኑ ተሰምቷል::
14591847_1848685248699812_7965544009936441995_n
በቅድሚያ በፉሪ የጀመረው ተቃውሞ ወደ አየር ጤና የተዛመተ ሲሆን ዓለም ገና እና ሰበታም በሕዝብ ተቃውሞ እየተደበላለቁ ይገኛሉ::
ከፉሪ እስከ ጆሞ ድረስ የፌደራል እና የኦሮሚያ ክልላዊ ፖሊስን ዩኒፎርም የለበሱ የትግራይ ነጻ አውጪ ወታደሮች እንደወረሩት ሲሰማ ሕዝቡን ለመበተንም ተኩስ ከፍተዋል::
በፉሪ ሱቆች እና ካፌዎች በአጠቃላይ ንግድ እንቅስቃሴ መቆሙም ተዘግቧል:: ጆሞ አካባቢ ልጆቻቸውን የሚያስረምሩ ወላጆች ወደ ትምህርት ቤት በመሄድ ልጆቻቸውን እያወጡ ሲሆን በነዚህ አካባቢዎች ትራንስፖርት መቆሙም ታውቋል::

14463066_310740835948819_8569296370625295351_n
14492452_1090605974340964_151446872303695216_n
በአዲስ አበባ አለምገና በሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ንብረቶች ላይ እርምጃ የተወሰደ ሲሆን የአካባቢው ወጣቶች መንገዶችን በመዘጋጋት ትግሉን በማቀጣጠል ላይ ነው::
አሁን በደረሰን መረጃ የትግራይ ነጻ አውጪ መንግስት ወደ ሕዝብ በመተኮስ በርካታ ወጣቶችን አቁስሏል::

No comments:

Post a Comment