Translate

Thursday, December 28, 2017

ለማና ገዱ በአስቸኳይ ኢህአዲግን አፍርሱ(መሳይ መኮንን)

Image may contain: 3 people, people smiling, people standing
የዘንድሮው ህወሀት በሁለት መልኮች ይገለጻል። አንደኛው በፍርሃት የሚናጥ፡ በማያባራ ህዝባዊ ማዕበል ወንበሩ የተናጋ፡ ወድቀቱን በቅርበት እያየ በስጋት እየተርገፈገፈ የሚገኝ፡ ሳር ቅጠሉ የተጠየፈው፡ ድርጅት ነው። ሌላኛው መልኩ ደግሞ መቃብር አፋፍ ላይ ሆኖ የሚፎክር፡ በመጨረሻው ሰዓት ንሰሀ መግባት ሲገባው ሃጢያቱን የሚከምር፡ ሞት ደጃፍ ቆሞ የሚሸልል፡ ዕብሪትና ጥጋብ በስተርጅናም ያለቀቀው፡ ለአንድም ቀን ቢሆን በስልጣን ለመቆየት ሀገር ከማፍረስ ወደኋላ የማይል፡ ሃላፊነት የጎደለው፡ ሞራል የደረቀበት፡ ''እኔ ከሞትኩ....'' መስመር ላይ ወጥቶ ወደግዙፍና መጠነ ሰፊ ጥፋት የሚጋልብ ድርጅት ነው።
ለጊዜው ወደተቋረጠው የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባ ላምራ። የደህነንቱ ሹሙ ቦግ ብሏል። ተቆጥቷል። ፊቱ ቲማቲም መስሏል። ዓይኑን ያጉረጠርጣል። እንደልማዱ ማስፈራራት ላይ ነው። ባሳደግን ተናቅን፡ ባጎረስን ተነከስን ዓይነት ስሜት ውስጥ ሆኖ በንዴት ይወራጫል። ወዲያውኑ ደግሞ ይቀዘቅዛል። ስሜቱ ይበርዳል። “ከሀይ ስኩል ጀምሮ ያሳደግናችሁ እኛ ነን። በጣም ጠንካሮችና ጎበዞች በመሆናችሁ እኔ በግሌ እኮራባችኋለሁ። ብዙዎች አገር ትተው ሲሰሹ እናንተ ግን በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ከሕዝብ ጎን በመቆማችሁ ምስጋና ይገባችኋል፤ ሆኖም ግን አገር ሲመራ መቸኮል አያስፈልግም፤ ሰከን ማለት ይገባል” ዓይነት ምክር ለመስጠት ይሞክራል። ጭንቀት። ስጋት። ፍርሃት። ደግሞም ትዕቢት፡ ድንቁርና፡ እየተፈራረቁ ያንገላቱታል።

Wednesday, December 27, 2017

ለማ መገርሳ “አውሬውን አቁስለነዋል፤ ይህ ግን በቂ አይደለም” እያሉ ነው

ክንፉ አሰፋ
Lemma Megersa
“አውሬው ቆስሏል*። ቆስሎ ስላልተኛ፣ ማቁሰሉ ብቻ በቂ አይደለም። ተመልሶ እንዳይመጣ እርግጠኞች መሆን አለብን።” የሚለው ቃል የወጣው ከ”ጽንፈኛው ዲያስፖራ” ወይንም ከተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች አይደለም። ከአውሬው ጋር አጋር ሆኖ ከሚሰራ ድርጅት መሪ ነው። ያውም በገዥው ፓርቲ ልሳን። የ26 ዓመቱ ፖለቲካ እየተንከባለለ እዚህ ላይ ደርሷል። አንድ ሰው እውነትን በመናገሩ ጀርባው ተጠንቶ፣ ደሙ ተለክቶ፣ ግንባሩ ተገላልጦ፣  በሽብር በሚፈረጅባት ሃገር ውስጥ፣ ጥቂቶች የእድሜ-ልክ ፈራጅ ሆነው በተሰየሙበት ሃገር ይህ ተከሰት። እነ እስክንድር ነጋ፣ ተመስገን ደሳለኝ፣ አንዷለም አራጌ ከዚህ የባስ ነገር አልተናገሩም። በፍትህ ስም የሚቀለድባቸው እነ ፕ/ር መረራ ጉዲና እና በቀለ ገርባ ይህችን ያህል እንኳን አልተነፈሱም።

Saturday, December 23, 2017

የኢህአዴግ ስብሰባ

መሳይ መኮንን
EPRDF Addis Ababa meeting
ህወሀት አድብቷል። አንገቱን የሰበረ መስሏል። ሆደ ቡቡ ሆኗል። መሪዎቹ በየምክንያቱ ያለቅሳሉ። ”እንዲህ መሆናችንን አናውቅም ነበር—ለካንስ በድለናችኋል” ይላሉ በየዕረፍት ሰዓቱ። በኢሳት እጅ የገባው ግርድፍ መረጃ ላይ እንደተመለከተው፡ ህወሀት በመከላከያ ሰራዊቱ የአዛዥነት ቁልፍ ቦታዎችን ሊያካፍል ተሰማምቷል። በደህንነት መስሪያ ቤቱ ውስጥ የሚገኙ የተወሰኑ የሃላፊነት ወንበሮችን ለመልቀቅ ቃል ገብቷል። በርስትነት ይዞአቸው የቆያቸውንና በሌሎች በፌደራል ደረጃ የሚገኙ ወሳኝ የሚኒስትር መስሪያ ቤቶችን ለአባል ፓርቲዎች በኮታ ሊያከፋፍል ፍቃደኝነቱን አሳይቷል።

Thursday, December 21, 2017

ወያኔን ማፍረስ አገራችንን ከመፍረስ መታደግ ነው! – የአርበኞች ግንቦት 7 መግለጫ

No automatic alt text available.
December 21, 2017
የወያኔው ጦር በጨለንቆ በኦሮሞ ወገኖቻችን ላይ ባደረሰው የጅምላ ጭፍጨፋና እንዲሁም በምዕራብ ሃረርጌ ሃዊ ጉዲና እና ዳሮ ወረዳዎች ውስጥ በኢትዮጵያ ሶማሊ ወገኖች ላይ በደረሰው እልቂት ንቅናቄያችን አርበኞች ግንቦት7 የተሰማውን ከፍተኛ ሃዘን ለመግለጽ ይወዳል። ለእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ህይወት ከፍተኛ ዋጋ የሚሰጠውና ለዜጎች የህይወት ዋስትናና ነጻነት እውን መሆን ሌት ተቀን የሚታገለው ድርጅታችን፣ እንዲህ አይነት የጅምላ ጭፍጨፋ መርዶዎችን ሰምቶ በዝምታ ለማለፍ የሚያስችለው ትዕግስት የለውም።

የአለም ህዝብ አገራችንን በድህነቷ ይወቃት እንጅ፣ ድህነት ያልበታተነው የህዝብ አንድነትና ፍቅር ያላት አገር መሆኗንም ጠንቅቆ ያውቃል። ይህ በዘመናት የተገነባው ፍቅርና አንድነት የውዷ አገራችን ልዩ መለያ እሴቷ ነው።

መረጃዎች የሚጠቁሙት የህወሀት ፍጻሜ ከሚጠበቀው በላይ ፈጣንና ቅርብ መሆኑን ነው።(መሳይ መኮንን)

Image may contain: 1 person, hat
መረጃዎች ጅረት ሆነዋል። ይፈሳሉ። በጥንቃቄ የተመረጡትን ለቅመን ስንመረምራቸው የሚሰጡን ምስል የህወሀት ፍጻሜ ከሚጠበቀው በላይ ፈጣንና ቅርብ መሆኑን ነው። በቀናት የሚጠብቅ ሳይሆን በሰዓታት የሚለዋወጥ የፖለቲካ ንፋስ ከወዲህ ወዲያ እያጎነን ነው። ህወሀት ጥርሱ ወላልቆ ማየት የሚናፍቀው ኢትዮጵያዊ መሽቶ በነጋ ቁጥር አዲስ ነገር እየሰማ ነው።

በፓርላማው የኦህዴድና ብአዴን አባላት አቶ ሃይለማርያም ለጥያቄዎቻችን መልስ ካልሰጡን መደበኛ ስብሰባ አንሳተፍም ማለታቸው ዛሬ ተሰምቷል። ይህ ቀላል ለውጥ አይደለም። ቤቱ ታሪክ ሊሰራበት ከሆነ እሰየው ነው። ባለፈው የህወሀት ጄነራሎች መጦሪያ የሆነውን ሜቴክን የተመለከተ የፓርላማ ስብሰባ ላይ አባላቱ በድፍረት የተናገሩት ያልተጠበቀ ነበር። ''አሁንስ የፓርላማ አባል መሆን አሳፈረን'' ነበር ያሉት። ይሄው አሁን ደግሞ በሰፊው ደገሙት። ያለፈው ሳምንት ሁለት የፓርላማ ስብሰባዎች ያልተካሄዱት በአባላቱ አድማ መሆኑን ሰማን። ጥሩ ነው። ህወሀት በቁሙ ተስካሩን ሊበላ መድረሱን የሚያሳይ ነው።

Tuesday, December 19, 2017

እነለማ መገርሳ በፍፁም የማይሸነፉበት ምክንያት

መኮንን ሀብተጊዮርጊስ ብሩ (ዶ/ር)
Lemma Megersa
ከጥቂት ዓመታት በፊት ቅንጅት መንፈስ ነዉ ሲባል ይሰማ ነበር። እዉነት ነበር ፣ እዉነትም ነዉ። አብሮነት ከፈጣሪዉ ለሰዉ ልጅ የተ ሰዉ የመሆን መንፈስ ነዉ። ሴይጣ ጥለቀቱ ዉስጥ እስኪገባ ድረስ ያን የፍቅር መንፈስ አሳንሶና አኮስሶ ደቀ መዛሙርቱንም ሲቻለዉ በየ እስር ቤቱ አጉሮ ሳይቻለዉ ከተፈጠሩባት ምድር አሳዶና አስወጥቶ ቤተ መቅደሱንም ቤተመርገም ሊያደርገዉ ቢፍጨረጨርም፣ መቼም ሊሸነፍ የማይችለዉ የአብሮነት መንፈስ በቁጣ መቅደሱን ሊረከብ ተዘጋጅቷል። እነ ለማ፡፣ አዲሱና፣ገዱ ወደ ደማስቆስም ይሁን ባሕር ዳርሲጓዙ ያ ሊሸነፍ የማይችል የአብሮነት መንፈስ የተገናኛቸዉ ይመስላል። ፈጣሪ ያኔ አሳደህኛልና ሲል ጳዉሎስን ከማዉገዝ ይልቅ ደቀ መዝሙሩ አድርጎ መሾሙን እዚህ ጋ አንድ ይሉሃል።

Monday, December 18, 2017

ሰበር መረጃ – ሕወሃት በጠረጴዛ ዙሪያ እየተሸነፈ ነው | ኃይለማርያም ደሳለኝን ‘ስልጣንህን’ ልቀቅ አሉት

ገረሱ ቱፋ እንደዘገበው
zehabesha አሁን እየተካሄደ ባለዉ የኢህአዲግ ሥራ አስፈጻሚ ውይይት ላይ ሕወሃት በጠረጴዛ ዙሪያ እየተሸነፈ እንደሆነ ከውስጥ የወጣ መረጃ ደርሶኛል። ኦህዴድ እና ብአዴን በጋራ በመቆማቸው በሕወሃት ላይ ድል እየተቀዳጁ እንደሆነ መረጃዎቼ ያስረዳሉ። በመሆኑም ሁለቱ እስከመረሻው በዚሁ ህብረት ከቀጠሉ ለተሻለ ድል እንደሚበቁ ምንጮቼ ያላቸዉን ጠንካራ እምነት ጨምረው ገልፀውልኛል።ስብሰባው ዛሬ ማምሻውንም ይቀጥላል።
በሌላ በኩል ኃይለማርያም ደሳለኝ የሕወሃት ሰዎች ሁለቱ ድርጅቶች ቀሪዉን ሁለት አመት ሳትጨርስ ስልጣንህን ሊቀሙህ ነው ሲላሉት የኦሮሞንና የአማራን ጉዳይ እንደሁለተኛ ዜጋ ጉዳይ እየተመለከተው ነዉ። በትላንትናው ዕለት በቴሌቪዥን ቀርቦ ያነበበው መግለጫ የዚሁ ነጸብራቅ እንደሆነና መግለጫዉ አስቀድሞ በሕወሃት ተፅፎ እንደተሰጠው ምንጮቼ ጠቁመዋል። ኃይለማርያም የተፈጠሩ ችግሮችን ያቀረበበት ቅደመ ተከተልና በንባቡ ውስጥ በኦሮሞ ላይ የደረሰውን እልቂት አኮስሶ በሶማሌ ላይ ደረሰ ያለውን ግዲያ አፅንኦት ሰጥቶ ያቀረበበት ሂደት አቋሙን ግልጽ እንደሚያደርገዉ ምንጮቼ አልሸሸጉም።

“ዶክተሩ” ደብረጽዮን ምላሽ አለው

“… የአመራሩ ድክመት ድርጅቱን ጎድቷል፤ … የበላይ አመራሩ ሥራውን ሲገመግም ብዙ ጉድለት ተገኝቶበታል” በማለት ለፋና ቃለምልልስ የሰጠው አዲሱ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር የወንበዴዎች ቡድን መሪ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ነው። በበፊቱ አመራር ውስጥ ምክትል ሊቀመንበር የነበረው ደብረጽዮን፤ 35 ቀናት በፈጀውና ዋናው ችግር አመራሩ መሆኑን በገመገመው ስብሰባ መሠረት መባረር ሲገባው ይልቁንም ሊቀመንበር ሆኗል።

ኦህዴድ በህወሓት ላይ ላወጣው መግለጫ ሃይለማርያም ምላሽ ሠጠ


በጨለንቆ በተፈፅመው የጅምላ ግድያ በስተጀርባ ማን ነው ያለው ? 
የኢፌዲሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 87 (3) ስር የአገር መከላከያ ሰራዊት የአገርን ሉዓላዊነት ለማሰከበር ነው የተቋቋመው። በዚሁ ንዑስ አንቀፅ 4 እና 5 ስር የአገር መከላከያ ሰራዊት በማንኛውም ጊዜ ለህገመንግስቱ ታዛዥ በመሆን ለፖለቲካ ፓርቲዎች ውግንና ሳያሳይ ነፃ ሆኖ የአገር ደህንነት የመጠበቅ ስራውን እንደሚሰራ ይደነግጋል። ይሄው የመከላከያ ሰራዊቱ ከውጭ የሚመጣውን የአገሪቱን ጠላት ለመከላከል በአገሪቱ ብሄር ብሄረሰቦች የተገነባ ከተቋቋመለት አላማ ውጭ ታሪካዊ ስህተቶችን በህዝቦች ላይ ሲፈፅም ታይቷል።

Saturday, December 16, 2017

የኢትዮጵያ ሃገራዊ ንቅናቄ የሽግግር መንግስት ሰነድ ማዘጋጀቱን ገለጸ

አባይ ሚዲያ ዜና

ናትናኤል ኃይለማርያም
የኢትዮጵያን ጉዳይ አስመልክቶ በአውሮፓ ፓርላማ የተጠራ ስብሰባ ላይ የኢትዮጵያ አገራዊ ንቅናቄ አመራሮች በቦታው በመገኘት ኢትዮጵያ አሁን ስለገጠማት ፈታኝ እና አስፈሪ ጉዳዮች በማንሳት ሰፊ ማብራሪያ መስጠታቸውን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለኢሳት በሰጡት ቃለ መጠይቅ ለማወቅ ተችሏል።

Wednesday, December 13, 2017

ከ424 ዜጎች ጭፍጨፋ፤ ከ14 ዓመት መሬት ነጠቃ በኋላ የጋምቤላ “ኢንቨስትመንት” 9ቢሊዮን ብር ያህል ከስሯል

ጋምቤላን በረሃ አድርጎ፤ ሕዝቧን ገድሎ፤ በተለይ የአንድ ክልል “ዜጎችን” ብቻ ጠቅሞ በጋምቤላ የተተገበረው “ኢንቨስትመንት” ዘጠኝ ቢሊዮን ብር ያህል የማይከፈል ዕዳ ውስጥ መዘፈቁን ህወሓት/ኢህአዴግ አመነ።

“እንጨርሳቸው፤ አንድም አኙዋክ መትረፍ የለበትም”


  • እነዚህም የህወሓት ነፍሰበላዎች ይፈለጋሉ!
የሰላም ሰዎች የሆኑት አኙዋኮች ከህወሓት ጋር መቃቃር ውስጥ የገቡት ገና ከጅምሩ ነበር። የቀድሞው የአኙዋክ ምክርቤት ኃላፊ የነበሩት አቶ ኦባንግ ሜቶ እንደሚሉት ችግሩ የተያያዘው ህወሓት የጋምቤላን ለም ምድር የራሱ ለማድረግ ከመፈለጉ ጋር ነው። ህወሓት ሥልጣን ላይ እንደተቆናጠጠ የጋምቤላን ብቸኛ ጄኔሬተር በመንቀል ከመውሰድ አልፎ በአሎሮ ግድብ ላይ የነበሩትን ወደ 400 የሚሆኑ ማሽነሪዎች እና የእርሻ መሣሪዎች በምሽት ወደ ትግራይ ነቅሎ ወስዷል ይላሉ አቶ ኦባንግ። በመቀጠልም ተዝቆ የማያልቀውን የጋምቤላን ድንቅ ሃብት በረኸኞቹ ህወሃቶች ለመዝረፍ ውሳኔያቸው አደረጉ

የተማሪዎች ዓመጽና የየአካባቢው አጫጭር መረጃዎች

አክሱም ዩኒቨርሲቲ
አክሱም ዩኒቨርሲቲ በየግማሽ ቀኑ ሲነሳና ሲበርድ ነው የሰነበተው። በካፌ ሰዓት ብዙ ጊዜ ድንጋይ ይወረወራል። ማምሻውን በራት ሰዓት በተፈጠረው ብጥብጥ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግባትና መውጣት አይቻልም ነበር። በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ትምህርታቸውን አቋርጠው ወደ ቤተሰቦቻቸው ቢሔዱም እስካሁን መውጣት የሚፈልጉ ከሁለት ሺህ በላይ የዐማራ ተማሪዎች አሉ።

Friday, December 8, 2017

በኢትዮጵያ ስም ህወሓት ከሻዕቢያ ጋር የመጨረሻውን የጠቅላይ ጨዋታ ጀመረ



  • አውቀውትም ይሁን ሳያውቁት “የእምነት አባቶች” የክህደቱ ተዋንያን ናቸው
“… ይህ ዜና በተገለበ መልኩ መሰማት ከጀመረ ሰነባብቷል። ዜናው በደባና በተቀነባበረ ሤራ የሚካሄድ ቢሆንም ዜናውን በገደምዳሜ የሚያሰራጩት ክፍሎች ስለ ጉዳዩ የተጨነቁ አይመስሉም። ቅርብ ሆኜ እንደምከታተለው ይህ ዜና አደገኛና ኢትዮጵያን ዳግም ክህደት የሚያከናንባት፤ እንደ አገር የመኖር ኅልውናዋን አደጋ ላይ የሚጥል ነው። ይህንን የሚያውቁ የሃይማኖት አባት መስቀል ተሸክመው የዚህ ሸፍጥ ተዋንያንና አስፈጻሚ መሆናቸው ያሳፍራል። ጉዳዩ በአጭሩ ህወሓት ከሻዕቢያ ጋር በኢትዮጵያ ስም ሊታረቅ ዓለምአቀፍ ዕውቅና የተሰጠው ድርድር መጀመሩ ነው…”

Wednesday, December 6, 2017

የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮች ፈጸምን ያሉትን ጥቃት በተመለከተ ህወሃት ጥቃቱ መፈጸሙን አምኗል

Patriotic Ginbot 7 attack TPLF convoy
የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮች ህዳር 26 – ለህዳር 27/2010 ንጋት ላይ ለወያኔ (አጋዚ) ጦር ሊውል የነበረ ነዳጅ እና ሌሎች ቁሳቁሶችን ጭነው ከሱዳን ወደ ጎንደር ሲጓዙ በነበሩ ተሽከርካሪዎች ላይ በጭልጋ ነጋዴ ባህር በሰነዘሩት ጥቃት ተሽከርካሪዎቹን ሙሉ ለሙሉ ማውደማቸውንና ተሽከርካሪዎቹን አጅበው የነበሩ ወታደሮችን መግደላቸውን ገልጸዋል።

Friday, December 1, 2017

ህዝባችን ለፍትህ እያካሄደ ያለውን ትግል አቅጣጫ ለማስለወጥ ህወሃት የሚሸርበውን ሴራ ማምከን ጊዜ ሊሰጠው የማይገባው ተግባር ነው።


No automatic alt text available.
December 1, 2017
በመንደርና በዘር የተሰባሰቡ የትግራይ ልጆች ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ወይም የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር በሚል ሥም ተደራጅተው በነፍጥ የአገራችንን በትረ ሥልጣን ከተቆጣጠሩ ወዲህ ላለፉት 27 አመታት ከኛ ወዲያ ላሳር በሚል እብሪትና ትዕቢት እያንዳንዱን ማህበረሰብ አዋርደው ገዝተዋል ፤ አሁንም እየገዙ ነው።