Translate

Saturday, May 27, 2017

የቴዲ አፍሮ… ተሞክሮ! (ከኤርሚያስ ለገሰ – ቁጥር አንድ)

ከኤርሚያስ ለገሰ (ቁጥር አንድ)
Teddy Afro, by Ermias Legesse
የዛሬ ሁለት አመት በጸደዩ ወራት የኢሳት ስድስተኛ አመት ለማክበር በፍሎሪዳ ግዛት ታምፓ ከተማ ተጉዤ ነበር።-የአጋጣሚ ነገር ሆኖ በዝግጅቱ ላይ ከድምጻዊ ቴዎድሮስ ጋር አብሮ የሰራ ድምጻዊ አብሮኝ ተጉዟል ። ይህ የሚወዳት አገሩን ተቀምቶ በሰሜን አሜሪካ ቨርጂኒያ የከተመ አርቲስት ጋር በነበረን ወግ መሃል ስለ አርቲስት ቴዲ አፍሮ አንስተን የተጫወትንበት ነበር። ቴዲ አፍሮን በቅርበት የሚያውቀው ይህ የኪነጥበብ ሰው እንዳጫወተኝ ከሆነ የቴዲ አፍሮ የስኬት ምክንያቶች በዘፈቀደ የመጣ አይደለም። ይልቁንስ የቴዲ የስኬት ምክንያቶች የስራ ዲሲፕሊኑ፣ ትጋቱ፣ ለራሱና ለሙያው የሚሰጠው ዋጋ፣ በየጊዜው ብቃቱን ለማሳደግ የሚያደርገው ጥረት፣ ትላንት የነበረውን አስተሳሰብ ዕድገት ለማምጣት ያለው ዝግጁነትና የጠለቀ የአሸናፊነት ስሜት ሰንቆ መጓዙ እንደሆነ ያምናል። በህይወቴ ጥንቅቄ የሚያውቅ እንደ ቴዲ አፍሮ አላጋጠመኝም ይላል።

Monday, May 15, 2017

የኮሌራው ምሥጢር! የቴድሮስ “የጥቅምት ዱብ ዕዳ”?


በህወሃት/ኢህአዴግ ከፍተኛ የገንዘብ ድጎማና ድጋፍ ለዓለም የጤና ጥበቃ ድርጅት ዳይሬክተርነት የሚወዳደረው ቴድሮስ አድሃኖም የመመረጡ ጉዳይ አደጋ ገጥሞታል፡፡ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በነበረበት ወቅት ሦስት የኮሌራ ወረርሽኞች በምሥጢር እንዲያዙ ማድረጉ ለዳይሬክተርነት እንዳይበቃ ያደርገዋል ተብሏል፡፡ እንደ አሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ይህ ጉዳይ የቴድሮስ “የጥቅምት ዱብ ዕዳ” ሊሆን እንደሚችል ተገምቷል፡፡

Thursday, May 4, 2017

በዶ/ር መረራ ጉዲና የክስ መቃወሚያ ላይ ዓቃቢ ህግ መልስ ሰጠ፤ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ መቅረባቸውን ለማረጋገጥ የመሐል ዳኛው በተደጋጋሚ ስማቸውን ጠርቷል

Dr. Merera Gudina, Prof. Berhanu Nega and Feyisa Lilesa
በሰማያዊ ብሔራዊ ሸንጎ የህዝብ ግንኙነት ንዑስ ኮሚቴ
በፌደራል ጠቅላይ ዓ.ህግ የወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸውን በእስር ሆነው እየተከታተሉ ያሉት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ሊቀመንበርና የመድረክ ከፍተኛ አመራር ዶ/ር መረራ ጉዲና ለቀረበባቸው ክስ ባቀረቡት መቃወሚያ ላይ ዓቃቢ ህግ ዛሬ ሚያዚያ 26 ቀን 2009 ዓ.ም ምላሽ ሰጠ፡፡