Translate

Thursday, May 4, 2017

በዶ/ር መረራ ጉዲና የክስ መቃወሚያ ላይ ዓቃቢ ህግ መልስ ሰጠ፤ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ መቅረባቸውን ለማረጋገጥ የመሐል ዳኛው በተደጋጋሚ ስማቸውን ጠርቷል

Dr. Merera Gudina, Prof. Berhanu Nega and Feyisa Lilesa
በሰማያዊ ብሔራዊ ሸንጎ የህዝብ ግንኙነት ንዑስ ኮሚቴ
በፌደራል ጠቅላይ ዓ.ህግ የወንጀል ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸውን በእስር ሆነው እየተከታተሉ ያሉት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ሊቀመንበርና የመድረክ ከፍተኛ አመራር ዶ/ር መረራ ጉዲና ለቀረበባቸው ክስ ባቀረቡት መቃወሚያ ላይ ዓቃቢ ህግ ዛሬ ሚያዚያ 26 ቀን 2009 ዓ.ም ምላሽ ሰጠ፡፡

የፈደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት ተከሳሽ ዶ/ር መረራ ጉዲና ያቀረቡትን መቃወሚያና ዓቃቢ ህግ የሰጠውን መልስ መሰረት በማድረግ በቀረበው መቃወሚያ ላይ ብይን ለመስጠት ለግንቦት 25 ቀን 2009 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
በዚሁ መዝገብ ሌላው ተከሳሽ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ መቅረብ አለመቅረባቸውን ለማረጋገጥ የመሐል ዳኛው በችሎት ስማቸውን በተደጋጋሚ ቢጠሩም ተከሳሹ አልቀረቡም፡፡

No comments:

Post a Comment