Translate

Wednesday, April 30, 2014

ዓባይ እንደ ዋዛ–ኢትዮጵያዊነትን አጥፍቶ ዓባይን ለመታደግ ይቻላልን?

አክሎግ ቢራራ (ዶር)

ክፍል ሁለት

Click here for PDF

“ውኅ እየጠማው ያባዪን ልጅ
እሚያዘጋጅለት ቢጠፋ

እሚያበጃጅ ለልማት የሚያመቻች ዓባይን
አኮላሽቶለት ፈንጂውን”

ሰይፉ መታፈሪያ ፍሬው፤ ዐባይ–ፈንጅ የቀበረ ውሃ
ኢትዮጵያ ታላቅና ሃብታም ለመሆን የምትችል አገር ናት። የተፈጥሮ ሃብቷ፤ አቀማመጧና የሕዝብ ስርጭቷ ለታላቅነቷ የማይገኙ ምሰሶዎች (Social Pillars) ናቸው። ሆኖም፤ ይህ የአገርና የማህበረሰብ ታላቅነት መሰረት ጎሳዊና አምባገነናዊ የሆነ ስርዓት ባመጣው ጦስና ቀውስ እየባከነ ነው። ህወሓት ከተመሰረተበት ጀምሮ የተካውን መንግሥትና ሌሎችን በማዋረድ፤ በማጋለጥ፤ በማጥላላት፤ በማሰር፤ በመግደልና ከሃገር በማባረር ሃያ ሶስት ዓመት ገዝቷል። የጥቂቶችን ኪስ በሚያሳፍር ደረጃ ሞልቶ፤ ቢያንስ ሃያ አምሥት ቢሊዮን ዶላር ከሃገር ተዘርፎ ወደ ውጭ ሃብታም አገር ባንኮች እንዲዘዋወር አድርጓል። ይኼን ሲያደርግ ደጋግሞ የሚነግረን ተግባሩ ሁሉ ለጭቁን ሕዝቦች፤ ለድሃዎች ጥቅም የሚል ፕሮፓጋንዳ እየተጠቀመ ነው። ኢትዮጵያ የብዙ ምሁራን፤ ጠበብቶች፤ ሰራተኞች፤ አገር ወዳዶች ወዘተ አገር ብትሆንም ዛሬ የተማረና አገሩን ለማልማት የሚችል የተማረና የሰለጠነ የሰው ኃይል ድሃ ሆናለች። በሃያ አንደኛው መቶ ክፍል ዘመን ተቀባይነት የሌለው በኢትዮጵያ ተከስቷል።

የአባቶች ስንብት … (ጋዜጠኛ ተመሰገን ደሳለኝ )


Temesgen Desalegn "Fact" Ethiopian Amharic newspaper editorከ97ቱ በእጅጉ የተቀዛቀዘው የ2002ቱ ምርጫ የቀናት ዕድሜ ብቻ ቀርተውታል፤ ከመቼውም በላይ የፖለቲካ ምህዳሩን ያጠበበው ገዢው ግንባር፣ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር የሚያደርገውን የምረጡኝ ክርክር እንደ 97ቱ በቀጥታ ስርጭት እንዲተላለፍም ሆነ በአዳራሹ ታዳሚዎችና ታዛቢዎች እንዲገኙ አልፈቀደም፤ በዚህ ክርክር ላይ ኢህአዴግ እንደተለመደው ለመጀመሪያ ጊዜ ካቀረባቸው ጥቂት አፈ-ቀላጤዎቹ መካከል የተመልካችን ትኩረት በመሳብ ጎልማሳው የወራቤ ፍሬ ሬድዋን ሁሴንን የሚተካከል አልነበረም፡፡ ሬድዋን ዕድሉን ካገኘ እንደ ‹‹ጓድ›› መንግስቱ ኃ/ማሪያም ለሰዓታት ሳያቋርጥ ቃላቶችን እንደ መትረየስ አከታትሎ ማንጣጣት ጎልቶ የሚታወቅበት ባህሪው ነው፤ ‹ከሎጂክ› ይልቅ የተዋቡ አረፍተ ነገሮችን መደርደር ይቀናዋል፤ በየመሀሉም የመድረክ ተወካዮችን ‹‹ራዕይና የጠራ ፖሊሲ የሌላቸው››በማለት ይዘልፋል፤ መልሶ ደግሞ ‹ፀረ-ኢትዮጵያዊና ፀረ-ሰላም ናቸው›› ሲል ይኮንናል፡፡ በየሰከንዱ በአስደንጋጭ እና በአደገኛ(Inflammatory) የቃላት ሰይፍ ይመትራቸዋል፡፡ ይህ ‹‹ታጋይ››ነቱም ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ በጉምቱ የድርጅቱ ሰዎች ዘንድ ሞገስን አስገኝቶለታል፡፡ ይሁንና ከዕለታት በአንዱ ቀን በዛው አድናቆት በተቸረበት የክርክር መድረክ፣ እንደልማዱ ቃላት ስንጠቃው ላይ ተጠምዶ የነገር ጦሩን ሲያወናጭፍ ድንገት አዳልጦት ታላቅ ‹‹ስህተት›› ፈፀመ፡፡

Monday, April 28, 2014

ሠማያዊ ፓርቲ የነፃነት ትግልና የሃበሻ ጀብዱ

ዳኛቸው ቢያድግልኝ

በቅርቡ የሴቶችን ቀን አስመልክቶ በተደረገ የሩጫ ዝግጅት ወቅት የሚኒሊክና የጣይቱ ልጆችነ ነን ያሉ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣት ሴቶች “አትለያዩን! አትከፋፍሉን! ነፃነት እንሻለን! ለድሃው ይታሰብለት! ኑሮ ከበደን! ውሃ ጠማን! መብራት ናፈቀን!” በማለት በጣም ሰብዓዊና እናታዊ ጥሪ ጮክ ብለው አሰምተው ነበር። ይህም መልካም ድርጊታቸው ለፍትህና ለአንድነት የሚደረግ ህዝባዊ ጥሪ በሚያስበርግጋቸው የወያኔ ባለስልጣናት ሁከት ፈጠራ ተብሎ ተወነጀሉ። ፕሮፌሰር አልማርያም በተቆጣው ብዕራቸው

… ያገሬ ወይዛዝርቶች በምህረት አልባ ጨካኞች ሲንገላቱና ሲወገሩ ከዳር ቆሜ ማየትን ህሊናዬ ፈጽሞ አይፈቅድልኝም። ይልቁንም የእንግልታቸው ምክንያት ሰብዓዊ በሆነው መብታቸው ድምፃቸውን ስላሰሙ በመሆኑ የነሱና የመሰሎቻቸውን ጥሪ በዚህም ሳቢያ የሚደርስባቸውን አበሳ ሁሉ ለአለም አሳውቅ ዘንድ ድምጼን ከፍ አድርጌ እጮሃለሁ…

ብለው ነበር። ከርሳቸው ድምጽ ጋር በማበር የሚያስተጋቡ ድምጾች ይኖሩ ዘንድ እውነት ነውና የኔንም ድርሻ እነሆ እጮሃለሁ።

Saturday, April 26, 2014

ከሰማያዊ ፓርቲ የሰላማዊ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ለሚዲያ ማህበረሰቡ የተላለፈ ጥሪ

Ethiopia's Semayawi (Blue) party logoውድ የሚዲያ ማህበረሰብ አባላት፡- ባለፉት 23 ዓመታት ህወሓት/ኢህአዴግ በህገ መንግስቱ የሚዲያ ነጻነት እንደሚፈቀድ ቢደነግግም በተግባር ግን የራሱን ፕሮፖጋንዳ ከሚነዛባቸው ሚዲያዎች ውጭ ሌሎቹን ሲዘጋና ሲያሸማቅቅ ኖሯል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ህዝባችን ከገዥው ፓርቲ ፕሮፖጋንዳ ውጭ አማራጭ መረጃ ማግኘት አልቻለም፡፡ ጋዜጠኞች እየታሰሩ፣ እየተሰደዱ፣ ሚዲያዎች እየተዘጉም ቢሆን የተቻላችሁን ያህል ለህዝብ መረጃ ለማድረስ የሚዲያው ማህበረሰብ አባላት ለምታደርጉት ሁሉ ከፍ ያለ ክብር አለን፡፡ የታፈነውን የህዝብ ድምጽ ለማሰማት የምታደርጉትን ጥረትም እናበረታታለን፡፡ ሆኖም አሁንም ቢሆን በገዥው ፓርቲ አፋኝነት ምክንያት ህዝባችን የሚገባውን መረጃ እያገኘ አይደለም፡፡ እናንተም በሰበብ አስባቡ ጫና እየደረሰባችሁ እንደሆነ ፓርቲያችን ይገነዘባል፡፡

ገዥው ፓርቲ ላይ የሰላ ትችት የሚያደርሱ ጋዜጠኞች ‹‹አሸባሪ›› ተብለው ታስረዋል፡፡ ጋዜጦችና መጽሄቶች በስርዓቱ ተዘግተዋል፡፡ በርካታ ጋዜጠኞች አገራቸውን ጥለው ተሰደዋል፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ድብደባ፣ ማስፈራሪያና ዛቻ ደርሶባቸዋል፡፡

Friday, April 25, 2014

ሰበር ዜና፡ “ሰማያዊ ፓርቲ የእሁዱን ሰልፍ በታቀደው መሰረት ለማከናወን በሙሉ ቁርጠኝነት ላይ ይገኛል!!!”

ሰበር ዜና፡ “ሰማያዊ ፓርቲ የእሁዱን ሰልፍ በታቀደው መሰረት ለማከናወን በሙሉ ቁርጠኝነት ላይ ይገኛል!!!”

ከአመራሩ በተጨማሪም የታሰሩ አባላት ዝርዝርSemyawi party leaders arrested
የካ ክፍለ ከተማ ሾላ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩ
1. ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት -የፓርቲው ሊቀመንበር
2. ስለሽ ፈይሳ- ምክትል ሊቀመንበር
3. ብርሃኑ ተክለያሬድ-የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ
4. ዳዊት ጸጋዬ
5. አወቀ ተዘራ
6. ኢብራሂም አብዱሰላም
7. ሁሴን
8. ሙሉጌታ መኮንን

Thursday, April 24, 2014

ሰበር ዜና፣ ፖሊስ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን ማሰሩን ቀጥሏል

ሰበር ዜና፣ ፖሊስ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን ማሰሩን ቀጥሏል

በዳንኤል ሃረጋዊSemayawi party members on action
ፖሊስ ቀስቃሾቹን እያሰረ ነው ፖሊስ የእውቅናው ደብዳቤ አልደረሰኝም በሚል በተለያዩ የአዲስ አበባ ክፍሎች ቅስቀሳ ላይ የተሰማሩትን የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች እያሰረ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት በየካ፣ ካሳንቺስና አቧሬ ሲቀሰቅሱ የነበሩ ወጣቶች በፖሊስ ተይዘው ታስረዋል፡፡ ቀስቃሾቹ ሰልፉ እውቅና እንደተሰጠው የሚያመለክተውን ወረቀት ለፖሊስ ቢያሳዩም ፖሊሶች የእውቅናው ደብዳቡ አልደረሰንም በሚል አስረዋቸዋል፡፡ ቀስቃሾቹ የያዙት የእውቅና ደብዳቤ ግልባጭ ለፖሊስ የተጻፈበት በመሆኑ ሰልፉ እውቅና አግኝቶ እያለ ሆን ተብሎ ለማደናቀፍ እንደሆነ ምክትር ሊቀመንበሩ አቶ ስለሽ ፈይሳ ገልፀዋል፡፡
በላም በረት፣ ቦሌ ድልድይ፣ ኮተቤ፣ መገናኛ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የነበሩ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ቅስቀሳቸውን በተሳካ መልኩ አጠናቀዋል፡፡ በሌሎች አካባቢዎች የተሰማሩት አባላት ቅስቀሳውን አጠናክረው ቀጥለዋል፡፡ በሌላ በኩል በየካ፣ ካሳንቺስና አቧሬን ጨምሮ በሌሎች የከተማይቱ ክፍሎች ፖሊስ ከ20 በላይ አባላትን ማሰሩ ታውቋል፡፡

በሱዳን ያሉ ስደተኞች በምጥ ቀጠና ውስጥ… (በግሩም ተ/ሀይማኖት)

ሰሞኑን ሱዳንም እንደ ሳዑዲ አረቢያ ኢትዮጵያዊያኖችን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ደፋ ቀና እያለች ነው የሚል ወሬ ተናፍሶ ብዙዎች ምጥ በቁናን አስበው እህህህህን እያቀነቀኑ ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንግስትም ተስማምቷል፡፡ (ደህና ነገር አዘጋጅቶ ረግጠው የወጡ ይመስል ለማስመለሱ ፍጥነቱ ይገርማል፡፡ ከሰዑዲ ተመላሾች ምን ተደረገላቸው?) ታዲያ ሲስማማ የዜጎቹን መብት ለማስጠበቅ ቅንጣት ያህል እንደማይደራደር የብዙዎች ፍርሃት ነው፡፡ አሁን የስደተኛው ፍርሃቱ እውን ሆኗል፡፡ ይፋም ተደርጓል፡፡ ኢህአዴግ ዳግም ሊሳሳት የማይገባው በሳዑዲ አረቢያ እንደተደረገው ዜጎቻችንን በአደባባይ መጨፍጨፍ እና ማሰቃየት እንዳይከሰት ጥንቃቄ መደረግ አለበት፡፡ ቢሆንም ተቃዋሚ የሚባሉ በችግር ከሀገር የወጡ ስደተኞችና ኢህዴግን የማይደግፉ ግን እንኳን ወደ ሀገር መመለሱ እየተደረገ አይደለም አሁንም ጉሸማና እስር እንዳልቀረላቸው ይነገራል፡፡

ዋና ኦዲተር ለብክነት የተጋለጡ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ሒሳቦችን አጋለጠ

ዋና ኦዲተር ለብክነት የተጋለጡ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ሒሳቦችን አጋለጠ

-ከ1.5 ቢሊዮን ብር በላይ ያልተሰበሰበ ሒሳብ አለ -785 ሚሊዮን ብር ሕጋዊ ያልሆነ ወጪ ታይቷል -ከ2.3 ቢሊዮን ብር በላይ ያልተሠራበት በጀት ተገኝቷል የፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ላለፉት በርካታ ዓመታት ለፓርላማ ሲያቀርበው እንደቆየው ሁሉ፣ ለብክነት የተጋለጠ በቢሊዮኖች የሚቆጠር የመንግሥት ሀብት መኖሩን ባለፈው ሚያዝያ 14 ቀን 2006 ዓ.ም. ለፓርላማው ይፋ አድርጓል፡፡

ባርያ ነጻ የሚወጣው መቼ ነው? እሱ ሲፈቅድ ነው? ወይስ ጌታው ሲፈቀድለት?

ክፍል አንድና ሁለት ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

freedom


አንድ

በአለፈው ሳምንት (ፋክት ቁጥር 36) ወይዘሮ መስከረም የተለያዩ መጻሕፍትን በመጥቀስ በሴቶች ላይ ያለውን መጥፎ ጫና በደንብ ያስመሰከረች ይመስለኛል፤ ግን እኮ በሴቶች ላይ ያለው ጫና የቆየ፣ ክፉና ጎጂ መሆኑን ማንም ያውቀዋል፤ ቁም-ነገሩ ያለው ከዚያ የባህል ጭነት በራስ ጥረት ወጥቶ፣ ነቀፌታንም ሆነ እርማትን ለመቀበል ሳይፈሩና ሳያፍሩ እንደመስከረም በአደባባይ ሀሳብን በመግለጽ በአገርና በወገን ጉዳይ መሳተፍና ሌሎችም እንዲሳተፉ የተቻለን ሁሉ ማድረጉ ላይ ነው፤ ለዚህ ነው ይህንን መልስ የምጽፈው፤ ወይዘሮ መስከረም በአጋጠሟትና በምታያቸው እንቅፋቶች ላይ ማተኮርዋ እንደርስዋ መንፈሳዊ ወኔው የሌላቸውን ያስፈራራቸዋል እንጂ አያበረታታቸውም፤ የማንንም አፍአዊ ጫና ተቋቁመው በራሳቸው የውስጥ ኃይል እንዲመሩ እናድርግ።

አስፈላጊው ለውጥ ፣ መጭው ምርጫና የተቃዋሚዎች “መሳተፍ” ጉዳይ

(ናትናኤል ካብትይመር ኖርዌይ)

ethiopian_election_ballot_box

የሰው ልጅ ግላዊና ማህበራዊ ህይወቱን ለማሻሻል እንዲሁም የለት ተለት ህይወቱን የተሻለ ለማድረግ በአካባቢው ወይም በሚኖርበት ሃገር ያለውን አካባቢያዊና መንግስታዊ ስርዓት ጤናማ መሆኑ ግድ ነው። የማህበረሰቡም የለት ተለት ህይወት ከግዜ ወደ ግዜ አስቸጋሪ እየሆነ ሲሄድ የዛ ማህበረሰብ መንግስት ወይም አገዛዝ መቀየሩ አንደኛው መፍትሄ ነው። እንደሁለተኛ አማራጭ መፍትሄ  የሚወሰደው ደግሞ የነበረውን አገዛዝ ለአነስተኛና ከፍተኛ ለውጦች ካለው ምቹነት አንፃር ተመዝኖ አስፈላጊ የሚባሉ የፖሊሲና የመንግስታዊ አወቃቀር ለውጦችን መተግበር ሲሆን ይህም በሌሎች ሃገራት ተሞክሮ ጥሩ ሊባል የሚችል ለውጥ ሲያስገኝ ተስተውሏል።

Wednesday, April 23, 2014

ከሰማያዊ ፓርቲ የሰላማዊ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ለንግዱ ማህበረሰብ የተላለፈ ጥሪ!

በንግዱ ዓለም ለተሰማራችሁት ኢትዮጵያውያን በሙሉ፤

A call from Semayawi party April 2014
በአሁኑ ወቅት ስልጣን ላይ ያለው ፓርቲ ሁሉንም የኢኮኖሚ መስክ ጠቅልሎ በመያዙ በአገሪቱ ኢኮኖሚ የሚገባችሁን አስተዋጽኦ እያደረጋችሁ እንዳልሆነ እንረዳለን፡፡ ለይስሙላ ብቻ ነጻ ገበያን ‹‹ፈቅጃለሁ!›› የሚለው ገዥው ፓርቲ ኢኮኖሚውን በራሱ ድርጅቶች ተቆጣጥሮ ለስልጣን መቆያ መሳሪያ አድርጎታል፡፡ የመንግስት ድርጅት የሚባሉትም ቢሆኑ ኢኮኖሚው ጠቅልለው ለተመሳሳይ አላማ መሳሪያ በመሆን ላይ ናቸው፡፡ ይህን ተከትሎም አገራችን ነጻ ገበያና የግል ባለሃብቶች የተዳከሙባት ግንባር ቀደም አገር ሆናለች፡፡
ይህ በአንድ ኃይል የተጠቀለለ የኢኮኖሚ ስርዓት እናንተ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት በነጻነት እንዳትሰሩ ከማድረጉም ባሻገር ህዝባችን በኑሮ ውድነት እንዲታመስ አንድ ምክንያት ሆኗል፡፡ በተለይ በቅርብ አመታት ከስርዓቱ ጋር አብሮ መሄድ ያልቻለውን የንግዱን ማህበረሰብ ለስርዓቱ እጁን እንዲሰጥ ለማድረግ እንዲመች ከሚሰራው ስራ ጋር የማይመጣጠን ግብር በመጫን ላይ መሆኑን ለመረዳት ችለናል፡፡ ሱቅ በደረቴ የሚሰሩ፤ እንጀራ ጋግረው የሚሸጡ እናቶች፤ የጀበና ቡናና ሌሎቹንም አነስተኛ ስራዎች የሚሰሩ ወጣት ኢትዮጵያውያን ሳይቀሩ የማይችሉት ግብር ተጨኖባቸዋል፡፡ የንግድ ፈቃድ እድሳት፤ የመስሪያ ቦታና ሌሎችም ነጋዴው በኢትዮጵያዊነቱና ለህዝብ በሚሰጠው ጥቅም ሊያገኛቸው የሚገባቸው መብቶች በሙስና ለፓርቲ ባለው ቅርበትና በሌሎች በዚህ ስርዓት በተሳሳቱ አሰራሮች የንግዱን ማህበረሰብ አስረው ይዘውታል፡፡

ከሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ለኢትዮጵያ ዳያስፖራ የተላለፈ ጥሪ!

ከሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ለኢትዮጵያ ዳያስፖራ የተላለፈ ጥሪ!

Semayawi Party- Ethiopia
ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዙ ምሁራን መፍለቂያ ለመሆኗ አለም ይመሰክርላታል፡፡ አንቱ የተባሉ ምሁራንን በማፍራት ለዓለም አበርክታለች፡፡ ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በአለም ካሉ ታላላቅ ዩንቨርስቲዎች እና የምርምር ተቋማት እስከ አመራነት ድረስ ኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች መገኘታቸው ነው፡፡ እነዚህ ምሁራን በተሰማሩበት ስራ መስክ የሚያስመዘግቡት ውጤት እና በስራቸው ተሸላሚ መሆን ላነሳነው ሀሳብ ማጠናከሪያነት ያገለግለናል፡፡ እጅግ የሚያሳዝነውና ልብ የሚሰብረው ግን ሀገራችን ከእነዚህ ውድ ልጆቿ ተገቢውን ዋጋ አለማግኘቷ ነው፡፡ ሀገራችን የወላድ መካን እየሆነች ነው፡፡ ይህ ደግሞ ሆነ ተብሎ የሚቀነባበር ሴራ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡
ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዙ ምሁራን መፍለቂያ ብትሆንም ቅሉ በተከታታይ ስልጣኑን የጨበጡት ጭፍን አንባገነኖች በሚያራምዱት አግላይ ምሁር ፖሊሲ ምክንያት እውቀታችሁን እና ገንዘባችሁን በምትወዷት ሀገራችሁ ኢንቨስት አድታደርጉ ሁኔታዎች ባለመመቻቸታቸው የስደትን መራራ ጽዋ እንድትጨልጡ ተገዳችኋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በተለይ ባለፉት 10 አመታት በተቃዋሚዎች መዳከም የሚያታግል ኃይል አጥታችሁ እንደቆያችሁም እናምናለን፡፡

ህወሓት እስከመቼ ደም ማፍሰሱን ይቀጥላል ? (አቶ ሀብታሙ አያሌው UDJ)

Ato Habtamu Ayalew (UDJ)ሀገር የመገንጠል ዓላማ ይዞ የተነሳው የህወሓት ጁንታ በስውር እና በአደባባይ የጫካ ልማዱን መሰረት አድርጎ ሲገድል መኖሩ አዲስ ባይሆንም ከሰሞኑ መረር ያለ እርምጃ ‹‹ግድያ›› ማሰቡን ከጓዳው የወጣ የወሬ ምንጭ ደረሰን፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በአዲስ አበባ አስተዳደር ጽ/ቤት ተገኝቼ ነበር፡፡ የመገኘቴ ዓላማም የፊታችን እሁድ ሚያዚያ 26 የሚደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ የዕውቅና ደብዳቤውን ለመስጠት የተያዘውን ቀጠሮ በማክበር ነበር፡፡ የሰላማዊ ሰልፍ እውቅናን በተመለከተ ኃላፊ የሆኑት አቶ ማርቆስ ፎርም እንዲሞላ አዘዙ፤ የተባለውን ፎርም ሞላን፤ ያን ጊዜ የአቶ ማርቆስ የቢሮ ስልክ አንቃጨለ፤ አነሱት ……ቀጭን ትዕዛዝ ከወዲያ ማዶ…………… ‹‹የአንድነትን ሰላማዊ ሰልፍ በተመለከተ ዕውቅናው እንዳይሰጥ ይቆይ›› አቶ ማርቆስ ፊቱ ተለዋወጠ ‹‹ ይቅርታ አድርግልኝ የኔ ችግር አይደለም›› ሌላ ቃል ካፉ አልወጣም፡፡

የወያኔዎች አስቂኝ መመሪያዎችና ዐዋጆች

ነፃነት ዘለቀ (ከአዲስ አበባ)

በመጀመሪያ የክርስትና እምነት ተከታይ አንባቢዎች እንኳን ለ2006ዓ.ም የትንሣኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡
ሕወሓት ወደ ሥልጣን መጥቶ በዓይነቱ የተለዬ የጥቁር አፓርታይድ ሥርዓትን በዓለማችን ለመጀመሪያ ጊዜ በኢትዮጵያ ካቆመ ወዲህ እጅግ ብዙና ለመቁጠርም የሚያዳግቱ መመሪያዎችንና ዐዋጆችን ቀርፆአል፡፡ አንዳንዶቹን በዘፈቀደና በነሲብ እየቸከቸከ በፈለገው ሰዓትና ወቅት ራሱ ተግባራዊ በማድረግ፣ አንዳንዶቹንም ለማስመሰል ያህል በእንቅልፋምና ደናቁርት የ“ፓርላማ” አባላቱ አማካይነት በዐይን ጥቅሻ በሚታዘዝ የሆዳም ማይማን ጭብጨባ “አጸድቆ” ሥራ ላይ በማዋል ሀገርንና ሕዝብን ማተራመስ ከያዘ ሁለት ዐሠርት ዓመታትን ጨርሶ የሦስተኛውን ዐሠርት አንድ ሦስተኛ ያህል ጊዜ ለማገባደድ ጥቂት ወራት ብቻ ይቀሩታል፡፡
ከቅርቦች ልጀምር፡፡ ቅድም ቡና ስጠጣ እንዲህ የሚል ወሬ ሰማሁ፡፡ እውነት ይሁን ሀሰት ገና አላረጋገጥሁም – ይሁን እንጂ የወያኔን ባሕርይ ለሚያውቅ ይህን ወሬ ሀሰት ነው ማለት የሚያስችል አዲስ ነገር አይገኝም፡፡ ከዚህ የበላለጡ አስቂኝና አስገራሚ መመሪያና ዐዋጆችን እየታዘብን 23 የመከራና ፍዳ ዓመታትን ስላቀናን ይህኛውን የተለዬ አያደርገውም፡፡ የሰማሁት ምን መሰላችሁ – ልማታዊ የወያኔ ሙዚቀኞችና ዳንኪረኞች በኮፒራይት መቸገራቸውን ስላመለከቱና ለዚህም ችግር መባባስ ትልቁን ሚና እየተጫወቱ የሚገኙት የስልኮች ሚሞሪዎችና ብሉቱዝ በመሆናቸው እነዚህን አገልግሎቶች የሚሰጡ ማናቸውም የቴክኖሎጂ ውጤቶች ወደ ሀገር እንዳይገቡ መንግሥት ማገጃ አውጥቷል የሚል ነው፡፡ በዚህም ሳቢያ የእጅ ስልኮችና የመሳሰሉት የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ማዕቀብ ሊጣልባቸው እንደሆነ እየተነገረ ነው፡፡

Tuesday, April 22, 2014

ነገረ ኢትዮጵያ ቁጥር 9 ወቅታዊና አገራዊ ጉዳዮችን ይዛ ቀርባለች

Negere Ethiopia Semayawi party's newspaper issue 9

ነገረ ኢትዮጵያ ቁጥር 9 ወቅታዊና አገራዊ ጉዳዮችን ይዛ ቀርባለች፡፡ በተለያየ ምክንያትጋዜጣዋን ኮፒ በዕለቱ ያላገኛችሁ ይኸው መረጃ ይደርሳችሁ ዘንድ በፒዲ ኤፍ (PDF) ለቀናታል፡፡

ስለፍትህ ሲባል ስርዓቱ ይፍረስ! ክፍል ሶስት (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ)

Temesgen Desalegn "Fact" Ethiopian Amharic newspaper editorልዕለ ኃያሏ ሀገረ-አሜሪካን ዛሬ ለተጎናፀፈችው የሕግ የበላይነት የተከበረበት ሥርዓት መሰረት የጣሉት እነ ቶማስ ጃፈርሰን በነፃነት አዋጃቸው ላይ ‹‹ሁሉም ሰዎች በእኩልነት የተፈጠሩ ናቸው›› በማለት ሲደነግጉ፤ እንግሊዛዊው ደራሲ ጆርጅ ኦርዌል ደግሞ “Animal Farm” በሚለው መፅሐፉ፣ ጉልበታም ‹‹ገዥ›› አድርጎ በሳላቸው ገፀ-ባሕሪያት አማካኝነት ‹‹…አንዳንድ እንስሳት (ሰዎች) ግን የበለጠ እኩል ናቸው›› ይለናል፡፡ በርግጥ ሁለቱም አይነት አስተዳደሮች መሬት ወርደው ዓለማችንን ዲሞክራት እና አምባ-ገነን በማለት በሁለት ጎራ የከፈሉ የመሆናቸው ጉዳይ አከራካሪ አይደለም፡፡ ራሷ አሜሪካንን ጨምሮ አብዛኛው የአውሮፓ አገራት ከሞላ ጎደል በዜጎች እኩልነት ላይ የተመሰረተ ማሕበረሰብ መገንባት ከቻሉት ውስጥ ሲመደቡ፤ ብዙሃኑ የአፍሪካ እና የእስያ መንግስታት ደግሞ ‹‹አንዳንድ ሰዎች ይበልጥ እኩል ናቸው›› በሚል መንፈስ የተቃኘ አገዛዝ አንብረው፣ የትኛውንም ተግዳሮት በጠብ-መንጃ ዓይን መመልከትን ፈቅደዋል፡፡ ከእነዚህኞቹ መካከል የእኛይቷ ኢትዮጵያ ዋነኛዋ ናት፡፡

ሁለት : ባርያ ነጻ የሚወጣው መቼ ነው? እሱ ሲፈቅድ ነው? ወይስ ጌታው ሲፈቀድለት? (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)


Prof. Mesfin Woldemariamአንድ በሀርቫርድ የኒቨርሲቲ ያጋጠመኝን ነገር መግቢያ ላድርገውና ልቀጥል፤ በአንድ ሴሚናር (የጥናት ውይይት) ላይ አንድ ጥቁር አሜሪካን ፕሮፌሰር ወደአሜሪካ በባርነት በመጡት አፍሪካውያን ላይ የተፈጸመውን ግፍ በመዘርዘር አስረድቶ አሁን ለእነሱ ልጆችና የልጅ ልጆች ካሣ መከፈል አለበት የሚል ክርክር አነሣ፤ ካሣውን የመክፈል ግዴታ የሚጣለው ማን ላይ ነው? ካሣውንስ የመቀበል መብት የሚሰጠው ለማን ነው? የሚሉ ጥያቄዎችን ሳናነሣ ብዙ ሌሎች ጥያቄዎች ይኖራሉ፤ — እነዚያ ከአፍሪካ በባርነት ተይዘውና ተሸጠው የመጡት ሰዎች ዛሬ የሉም፤ እነሱ በባርነት ሞተዋል፤ ዛሬ በሕይወት የሚገኙት ጥቁር አሜሪካውያን ነጻነታቸውን አግኝተው ባለሙሉ መብት ዜጎች ሆነዋል፤ በአንጻሩ ደግሞ ለባሪያዎች ነጻነት የተጋደሉ ነጮች አሉ የእነዚህ ልጆች ከባሪያዎቹ ወይንስ ከጌቶቹ ወገን ይመደባሉ? ዛሬ ለልጆቻቸው ካሣ ይከፈል ማለት ልጆቹ የራሳቸውን ነጻነት ችላ ብለው ከአባቶቻቸው ባርነት ጋር እንዲቆራኙ ማድረግ አይሆንም ወይ? የባርነት ምልክቶችን ሁሉ ደምስሰው ነጻ ሰዎች ለመሆን የመጀመሪያው ግዴታ ራስን ችሎ በሁለት እግሮች መቆም ነው፤ ካሣ ክፈሉን ማለት አንደኛ ዋጋ ለማይሰጠው ነጻነት ዋጋን በማውጣት ማርከስ ነው፤ ከሰውነት ወደቤት እንስሳነት መውረድ ነው፤ ሁለተኛ በጌታና በባርያ መሀከል ያለው ግንኙነት መልኩን ለውጦ እንዲቀጥል መድረግ ነው፤ የውይይቱ ባለቤት እኔ ያቀረብሁትን ሀተታ እንዳላሰበበት ቢናገርም የእኔ ጥያቄ የተወደደ አልመሰለኝም፤ ካሣ ተቀባዮች ባርነታቸውን ካሣ ከፋዮች የባሪያዎች ባለቤትነታቸውን ጠብቀው እንደተቆራኙ መቀጠላቸው ባርነትን አያጠፋም፤ ለእኔ ጤናማ አልመሰለኝም።

Monday, April 21, 2014

ቴሌፎኑ ‘ለግዜው’ ጥሪ አይቀበልም

ክንፉ አሰፋ

Ethio Telecom the worst service in Africa
“የደወሉላቸው ደምበኛ ለግዜው ጥሪ አይቀበሉም።…” የምትለዋ አሰልቺ የቴሌ መልእክት ያላጋጠመው ቢኖር ወደ ኢትዮጵያ ስልክ ደውሎ የማያውቅ ሰው ብቻ መሆን አለበት። ኮ/ል መንግስቱ ሃይለማርያም ወደ ቀድሞ ወዳጆቻቸው መደዋወል ጀመሩና በመሃል ተስፋ ቆረጡ አሉ። አስር ለሚያህሉ አርሶአደሮች እና የሰራዊቱ አባላት ዘንድ ደውለው አልተሳካለቸውም። ለሁሉም ጥሪ ያገኙት ምላሽ “የደወሉላቸው ደምበኛ ለግዜው ጥሪ አይቀበሉም።” የሚል ሲሆንባቸው ራሳቸውን ነቀነቁ። ሰው ሁሉ የጨከነባቸው መሰላቸው። እንዲህም አሉ። “የሃገሬ ሰው እንኳን የስልክ ጥሪ፤ የእናት ሃገር ጥሪስ መች ተቀበለ።”
ለአመታት በተከታታይ በሁለት ድጅት እያደገች ያለች ሃገር የስልክ መስመር ችግር ይገጥማታል ብሎ ማሰብ ይከብዳል። ችግሩን በደንብ ላልተረዳው፣ ሰው የሞባይል ስልክ የሚገዛው እንዲሁ ይዞ ለመታየት ነው ያስብል ይሆናል። ይህ አባባል በከፊል ትክክል ነው። ዘመናዊ ስልክ በመያዝ ለላንቲካነት ብቻ የሚጠቀሙበት ሰዎች አይጠፉም። የቻይናው ቀፎ ከሞዴል አርሶ አደሮች አልፎ ተራው አርሶ-አደር እጅ ላይም ገብቷል። አብዛኞቹ ግን ተንቀሳቃሽ ስልካቸውን አይጠቀሙበትም። ለዚህም ይመስላል በርካታ ተንቀሳቃሽ ስልክ የሚይዙ ሰዎች እንዲሁ ለእይታ እና ለላንቲካ ብቻ የሚመስላቸው። አገልግሎቱን በተመለከተ ግን 99 በመቶ የሚሆነው ችግር የመዋቅር ችግር ነው።

ከሰማያዊ ፓርቲ የሰላማዊ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ለመምህራን የተላለፈ ጥሪ

ለተከበራችሁ የኢትዮጵያ መምህራን በሙሉ!!! ለአንድ አገር ብልጽግና ትምህርት ቁልፍ ስለመሆኑ ለማንም አጠያያቂ አይደለም፡፡ ለዚህም ሲባል መንግስታት ለትምህርት የሚሰጡት ትኩረት በቀዳሚነት ቦታ ላይ ይገኛል፡፡ በአገራችን ያለው ነባራዊ ሁኔታ ግን ከዚህ ጋር በእጅጉ የሚቃረን ነው፡፡ የትምህርት ፖሊሲ ከመቸውም ጊዜ በባሰ ሁኔታ ለእናንተ ለመምህራኖች የማያሰራ፣ ብቁ የተማረ ዜጋ የማይፈራበትና ለአገርም የማይጠቅም ሆኗል፡፡ ሁሉንም ነገር ለስልጣናቸው በሚያመች መልኩ የሚዘውሩት የወቅቱ ገዥዎች ትምህርት ከንጉሱና በደርግም ጊዜ ከነበረው በባሰ ደረጃ እንዲገኝ አድርገውታል፡፡

Ethiopia's Semayawi (Blue) party logo
ውድ የአገራችን መምህራኖች፤ በአሁኑ ወቅት መምህር በደርግና በኃይለስላሴ ዘመን ከነበረው ክብር ስለመውረዱ ከእናንተ ውጭ እማኝ መጥራት አያስፈልግም፡፡ መምህራኖች በማስተማር ብቃታቸውና ትምህርት ደረጃቸው፣ በስራ ዘመናቸው፣ በአጠቃላይ ለቀጣዩ ትውልድና ለአገራቸው በሚያበረክቱት ሳይሆን ለስርዓቱ ባላቸው ቅርበትና ርቀት እንደሚመዘኑም እናንተው ራሳችሁ የምታሳልፉት የዕለት ተዕለት ጭቆና በመሆኑ ሀቁ ከእናንተ የተደበቀ አይደለም፡፡
በስራችሁ ላይ የሚደረግባችሁ ጣልቃ ገብነት ተባብሶ መቀጠሉም የአደባባይ ሚስጥር ሆኗል፡፡ የገዥው ፓርቲ ያልተማረ ካድሬ ከእናንተ የተሻለ ተጠቃሚ በሆነበት አገር መጭውን ትውልድ የምትቀርጹት እናንተ መምህራን ግን ኑሮን ለመግፋት ተቸግራችኋል፡፡ በደሞዝ ጭማሬ ስም የ70 ብር ያልበለጠ ጭማሪ ልክ እንደ ቀሪው ጭቁን የኢትዮጵያ ህዝብ በእናንተም ላይ ስርዓቱ እየቀለደ ቀጥሏል፡፡ በነጻነት ለማስተማር አለመቻላችሁና እንዲሁም የሚገባችሁን ክብርና ክፍያ ባለማግኘታችሁ ተሸማቅቃችሁ እንደምትኖሩ የታወቀ ሀቅ ነው፡፡

Saturday, April 19, 2014

ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ የሚደረግ ሽግግርና የባህር በር አለመኖር ፈተና

ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪ የሚደረግ ሽግግርና የባህር በር አለመኖር ፈተናየጀቡቲ ወደብ።    ወያኔ አሰብና ምጥዋን  ለኤርትራ ካስረከበ በ  ኃላ እጅና እግሩ ታስረዋል።<<<የጀቡቲ ወደብ።  ወደብ አያስፍልግም ባዩ ወያኔ  አሰብና  ምጥዋን  ለኤርትራ  ካስረከበ  በ ኃላ  እጅና  እግሩ ታስረዋል።

በ   |  ሪፖርተር ጋዜጣ
ደቡብ ኮሪያ ከ30 ዓመታት በፊት ኢትዮጵያ አሁን በምትኝበት የኢኮኖሚ ደረጃ ላይ ትገኝ እንደነበር ይነገራል፡፡ ሆኖም የአምስት ዓመት የኢኮኖሚ ልማት ፕሮግራም በመንደፍ በፍጥነት ከድሆች ተርታ በመውጣት በዓለም ላይ ግዙፍ ከሚባሉ ኢኮኖሚዎች አንዷ ለመሆን በቃች፡፡ 

የኢሕአዴግ የደህንነት ሚ/ር አቶ ጌታቸው አሰፋ በአጭር ጊዜ ቢሊየነር ሆነዋል * ዘረፋው ቀጥሏል

በኢትዮጵያ ውስጥ በከፍተኛ ስልጣን እርከን ላይ የተቀመጠ እና በሙስና አልተዘፈቀም የተባለ ቢኖር ደፍሮ ይህ ነው የሚል የለም። ከራሳቸው ስም ጀምሮ እስከ ዘመድ አዝማዶቻቸው ወዳጅ ጓደኞቻቸውን ሳይቀር በዘረፋ ውስጥ በማመሳጠር ያሰማሩት የወያኔ ባለስልጣናት ተቆጥረው አያልቁም። ከትንሽ የቀበሌ ካድሬ ጀምሮ ልከክልህ እከክልኝ ብላ እንብላ መውደቂያህን አሳምር ወዘተ እየተባለ የህዝብ ሃብቶች የሃገር ውስጥ እና የውጪ ባንኮችን አጨናንቀዋል።
የወያኔ ባለስልጣናት የሆኑና ከቤተሰቦቻቸው ከዘመድ ወዳጆቻቸው ጀርባ ሆነው ከፍተኛ የዘረፋ ስራ ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ የሚተገብሩ በአደባባይ ግን እንደ ንጹሃን ምንም እንዳሌለባቸው መታየት የሚፈልጉ ያሻቸውን ነገር በስልክ ቲዛዝ አሊያም በተላላኪ ደህነንቶች የሚያስፈጽሙ እንደ ደብረጺሆን ገ/ሚ ሳሞራ የኑስ አባይ ወልዱ በረከት ስምኦን ሃይለማርያም ደሳለኝ እና የተወሰኑ 3 % የሚሆኑ የሕወሓት አመራሮች ሃገሪቷን እየዘረፉ ይገኛሉ።

የከሸፉት የህወሓት የተስፋ ቃላት

(ለምለም ሀይሌ ኖርዌይ)

promise failed
lemlem


የደርግ መንግስት ከወደቀ በኋላ በእግሩ የተተካው ህወሓት ይኸው ሥልጣን ላይ ከወጣ 23 ዓመት ሊሆነው ነው። ህወሓት ወደ ሥልጣን ሲመጣ ዲሞክራሲን አሰፍናለው፣ ሰብአዊ መብት አክብሬ አስከብራለው፣ የብሔር ብሔረሰቦች መብትና እኩልነት ይከበራል፣ ልማት ይመጣል የኢትዮዽያ ሕዝብ ስደት ያበቃል፣ በቀንም ሦስት ጊዜ ይበላል የሚሉት ዋንኞቹ ነበሩ። እስኪ አንድ በአንድ እንያቸው።

የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹ ‘ሮሮና ስጋት

“ምላሽ ካልተሰጠን የትምህርት ማቆምና ሰላማዊ ሰልፍ እናደርጋለን!”

addis ababa university

የትምህርት ሚኒስትር በ2006 ዓ.ም በአገሪቱ በተፈጠረው የመምህራን እጥረት ምክንያት በተለ ያዩ የትምህርት ዘርፎች የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ያገኙ ኢትዮጵያውያንን ለአንድ አመት ሙሉ ወጫቸውን ችሎ የማስተማር ስነ ዘዴ (ፔዳጎጅ) በማስተማር ወደ መምህርነት እንዲገቡ ማስታ ወቂያ ያወጣል፡፡ በወጣው ማስታወቂያ መሰረ ትም ለማጣሪያነት የቀረበውን ፈተና በመፈተን መልምሎ ለስልጠና እንዲገቡ ይደረጋል፡፡ በዚህ መሰረት በ10 ዩኒቨርሲቲዎች (መቀሌ፣ ባህር ዳር፣ ወሎ፣ ወለጋ፣ ጅማ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ዲላ፣ ሀሮማያ፣ ሀዋሳና አዲስ አበባ) እንዲሰለጥኑ ይደረጋል፡፡

Thursday, April 17, 2014

ሰማያዊ ፓርቲ በፌደራል መንግስቱና በቡለን ወረዳ የመሰረተው ክስ ሀሙስ ፍርድ ቤት ይቀርባል!

ሰማያዊ ፓርቲ በቤንሻንጉል ጉምዝ በህገ ወጥ መንገድ የተፈናቀሉ ኢትዮጵያውያን ወደ ቦታቸው በአስቸኳይ እንዲመለሱና ተገቢው ካሳ እንዲከፈላቸው በተደጋጋሚ ባካሄዳቸው ሰላማዊ ሰልፎችና ባወጣቸው መግለጫዎች የጠየቀ ሲሆን መንግስት ለጥያቄው ምላሽ ባለመስጠቱ ዜጎቹ የተፈናቀሉበትን ቡለን ወረዳና የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር እንዲሁም የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ላይ ክስ መስርቶ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ክሱን ታዋቂው የዓለም አቀፍ የህግ ባለሙያ ዶክተር ያእቆብ ኃይለ ማሪያም ይዘውት የነበረ ቢሆንም በተለያዩ ቢሮክራሲያዊ ምክንያቶች መዝገብ ሳይከፈትለት እንደቆየ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸዋል፡፡

Amhara Ethnic group members Ethiopiaይሁን እንጂ ሰማያዊ ፓርቲ ባደረገው ተደጋጋሚ ግፊት ክሱ በአሁኑ ወቅት መዝገብ ተከፍቶለት፣ የዳኝነት ክፍያ ተከፍሎ በቀጣይ ሀሙስ ሚያዝያ 9/2006ዓ/ም ክሱ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ስምንተኛ ፍትሃብሄር ችሎት ላይ መታየት እንደሚጀምር ኃላፊው ገልጸዋል፡፡

‹‹ሰማያዊ ፓርቲ በጉዳዩ ላይ አቋም ወስዶበት ከሰላማዊ ሰልፉም ባሻገር ዜጎቹ ወደ ቀዬአቸው እንዲመለሱና ካሳ እንዲሰጣቸው ተግባራዊ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡

Tuesday, April 15, 2014

ሰማያዊ ፓርቲ በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ጠራ


አዲስ አበባ፡- ሰማያዊ ፓርቲ ‹‹የተነጠቁ መብቶችን እናስመልስ!›› በሚል መሪ ቃል ሚያዚያ 19/2006 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ጠራ፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ከአሁን ቀደም የተለያዩ ጥያቄዎችን በማንሳት ምላሽ እንዲሰጣቸው ቢጠይቅም ጥያቄዎቹ ምላሽ ያልተሰጣቸው ከመሆኑም ባሻገር ጭራሹን እየተባባሱ በመምጣታቸውና ህዝብም እየተማረረ በመሆኑ ሰላማዊ ሰልፉን መጥራት እንዳስፈለገ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 25 2005 ዓ.ም ያደረገውን ጨምሮ በአዲስ አበባና ሌሎች አካባቢዎች ሰላማዊ ሰልፎችንና ህዝባዊ ስብሰባዎችን ባደረገበት ወቅት የኑሮ ውድነት፣ የእምነት ጣልቃ ገብነት፣ ሉዓላዊነት፣ ዜጎችን ከቀያቸው ማፈናቀልና ሌሎችም መሰረታዊ ጥያቄዎችን አንስቶ የነበረ ቢሆንም ጥያቄዎቹ ምላሽ ሊያገኙ እንዳልቻሉ የህዝብ ግንኙነቱ ገልጸዋል፡፡ ከዚህ በተቃራኒ በእስልምና እና ኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታዮች ላይ የሚደረገው ጣልቃ ገብነት፣ ዜጎችን ከቀያቸው ማፈናቀሉ፣ የኑሮ ውድነት፣ ሙስና አሁንም ድረስ ተባብሰው መቀጠላቸው ሰላማዊ ሰልፉን በመጥራት ህዝቡ እነዚህን የተነጠቁ መብቶች እንዲያስመለስ ማስተባበርና ማታገል የግድ በማለቱ ነው ብለዋል፡፡

Monday, April 14, 2014

አንድ ባርያ ነጻ የሚወጣው መቼ ነው? ሲፈቅድ ነው? ወይስ ሲፈቀድለት? (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)

Prof. Mesfin Woldemariam : is an Ethiopian Human Rights activist and philosopherበአለፈው ሳምንት (ፋክት ቁጥር 36) ወይዘሮ መስከረም የተለያዩ መጻሕፍትን በመጥቀስ በሴቶች ላይ ያለውን መጥፎ ጫና በደንብ ያስመሰከረች ይመስለኛል፤ ግን እኮ በሴቶች ላይ ያለው ጫና የቆየ፣ ክፉና ጎጂ መሆኑን ማንም ያውቀዋል፤ ቁም-ነገሩ ያለው ከዚያ የባህል ጭነት በራስ ጥረት ወጥቶ፣ ነቀፌታንም ሆነ እርማትን ለመቀበል ሳይፈሩና ሳያፍሩ እንደመስከረም በአደባባይ ሀሳብን በመግለጽ በአገርና በወገን ጉዳይ መሳተፍና ሌሎችም እንዲሳተፉ የተቻለን ሁሉ ማድረጉ ላይ ነው፤ ለዚህ ነው ይህንን መልስ የምጽፈው፤ ወይዘሮ መስከረም በአጋጠሟትና በምታያቸው እንቅፋቶች ላይ ማተኮርዋ እንደርስዋ መንፈሳዊ ወኔው የሌላቸውን ያስፈራራቸዋል እንጂ አያበረታታቸውም፤ የማንንም አፍአዊ ጫና ተቋቁመው በራሳቸው የውስጥ ኃይል እንዲመሩ እናድርግ።
አንድ መጽሐፍን በመጥቀስ ወይዘሮ መስከረም የሚከተለውን ጽፋለች፡–

የኢትዮጵያን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ እና የዲያስፖራውን ሚና በተመለከተ በኖርዌይ ኦስሎ ሕዝባዊ ውይይት ተካሄደ

የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ

Ginbot7 meeting in Norway
በዲምክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ  የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አዘጋጅነት አፕሪል ቅዳሜ 12/2014  በኖርዌይ ኦስሎ ከተማ  የኢትዮጵያን ወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታ እና የዲያስፖራውን ተሳትፎ በተመለከተ ታላቅ ሕዝባዊ ስብሰባ ተካሄደ:: በሕዝባዊ ስብሰባው ላይ ቁጥራቸው ወደ ሁለት መቶ የሚጠጉ በኖርዌይ የሚኖሩ ኢትዮጵያኖች ከኦስሎ እና ከተለያየ ከተማ በመምጣት በስብሰባው ላይ የተገኙ ሲሆን  የግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር አባል አቶ ቡዙነህ ፅጌ የስብሰባው ተጋባዥ እንግዳ በመሆን ሰፋ ያለ ንግግር አድርገዋል::

የሽብርተኝነት እንቆቅልሽ

የኢትዮጵያው አዋጅ ትርጓሜና ክፍተቶቹ

terror
መንግስታት በተለያየ መልኩ ትርጉመው ያቀረቡትን ሽብርተኝነት ለመዋጋት በሚል ህግ ያወጣሉ፡፡ በእርግጥ በአዲስ መልክ በሽብር ላይ የታወጀው ዘመቻ በአሜሪካ ግፊት የመጣ ነው፡፡ እ.ኤ.አ በ2001 አሜሪካ ከደረሰባት የሽብር ጥቃት በኋላ “war on terror” እንዲሁም “counter ter­rorism” የተሰኙ ዘመቻዎችን ነድፋ ተንቀሳቅሳለች፡፡ አሜሪካ ወዳጅም ሆነ የቀዩ ባላንጣዎቿን ሳይቀር ደልላም ሆነ ተማጽና የጀመረችው ይህ “ጸረ ሽብር ዘመቻ” መንግስታት በየ አገራቸው የራሳቸውን ጥቅም የሚያስጠብቁ አፋኝ “የጸረ ሽብር” ዘመቻ እንዲያወጡ እድል ሰጣቸው፡፡

ኢህአዴግ እንደ ናቡከደነፆር

(ወይንሸት ንጉሴ)

Nebuchadnezzar

በአንድ ወቅት የዓለም ገናና ንጉስ የነበረው የባቢሎን ንጉስ ናቡከደነፆር ለ43 ዓመታት ባቢሎንን ገዝቷል፤ በስተሰሜን ሶሪያ በምዕራብ በፍልስጤም እስከ ግብፅ ግዛቱን አስፋፍቷል፡፡ ይህ ንጉስ ህጎችን ከመቀፅበት ይደነግጋል፣ ይለውጣል፡፡ ለእሱ ስርዓት ተገዥ ያልሆኑትን ያስራል፣ ይገርፋል፡፡ ንጉስ ናቡከድነፆር በጣም የሚፈራ እና ኃይለኛ ንጉስ ቢሆንም ከመውደቅ ግን አልዳነም፡፡ ለማንኛውም የዚህ ንጉስ ታሪክና የሀገራችን መንግስት ስርዓት ብዙ የሚያመሳስላቸው ነገሮች ስላሉ እንዲህ አቅርቤዋለሁ፡፡

Saturday, April 12, 2014

አዎ ማኅበረ ቅዱሳንን ተጠንቀቁ! ትልቁ ስጋት እሱ ነውና

አዲሱ ተስፋዬ

መነሻ
ይህንን ጽሁፍ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ሰንደቅ ጋዜጣ በሚያዝያ 1/2006 ዓ.ም እትሙ ማኅበረ ቅዱሳንን በተመለከተ ያወጣው ቃለ መጠይቅና ሀተታ ነው [i] :: ሶስቱም አስተያየት ሰጭዎች “ማኅበረ ቅዱሳን አክራሪ ነው:: ስለዚህም መንግስት ሊያፈርሰው ነው ” የሚለው ወቅታዊ ዜና ምንጩ ከየት እንደሆነ ግልጽ እንዳልሆነ ጠቅሰዋል :: በፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ አበበ ወርቁ ጉዳዩን “በሬ ወለደ ነው” ብለው ሲያጣጥሉት ፣ የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ ደግሞ ” የዚህ ወሬ ምንጩ ከየት እንደሆነ አናውቅም” ሲሉ ተመሳሳይ ነገር ተናግረዋል።Mahibere Kidusan EOTC
ጆሮ ለባለቤቱ ባዳ ነው እንዴ?
በ 1955 እ. ኤ. አ የተመሰረተውና መቀመጫውን በኔዘርላድና በዩናይትድ ስቴትስ ያደረገው Open Doors : Serving Persecuted Christians Worldwide [ii] የተሰኘው ግዙፍ ድርጅት 2013 እ. ኤ. ኣ ባወጣው World Watch List ላይ ክርስትያኖችን በማሰቃየት በ63 ነጥብ ኢትዮጵያ 15ተኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝና ፣ ለዚህም ስቃይ ዋና ተዋናይ ከሆኑት አካላት አንዱ ማኅበረ ቅዱሳን እንደሆነ ጽፎ ፣ ሊስቱንም በመላው ዓለም በትኗል [iii] ። ይሄው በመላው ዓለም በድረ ገጽና በተለያዩ ኤለክትሮኒክ ሚድያዎች (hard and soft copy) የተበተነው ሪፖርት ከመስክ የመረጃ ሰራተኞቼ ፣ ከምሁራንና ከሰላዮቼ አገኘሁ ባለው መረጃ መሰረት አቶ መለስ ዜናዊን ሞት ቀደማቸው እንዲ ማኅበረ ቅዱሳንን እንክትክቱን ሊያወጡት አቅደው እንደነበረ ፣ ቀጣዩም ግዜ ማኅበረ ቅዱሳን የሚገንበት ግዜ እንደሚሆንና ይሄም ለተሐድሶዎች አስቸጋሪ ግዜ ስለሚሆን ከማኅበረ ቅዱሳንን እንዲጠበቁ እንዲህ በማለት ያትታል

በኖርዌ የሚገኙ የወያኔ ሰላዮችን በመቃወም ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በኦስሎ ከተማ ተካሄደ

በኖርዌ የሚገኙ የወያኔ ሰላዮችን በመቃወም ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በኦስሎ ከተማ ተካሄደ


ማርች 11, 2014 በኖርዌ የሚገኘው የኢትዮጵያን የስደተኞች ማህበር ያዘጋጀው ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ከተለያዩ የኖርዌ ከተሞች በመጡ ታዳሚዎች እና በኦስሎ ነዋሪ በሆኑ ኢትዮጵያውያንና በኢትዮጵያ ባንዲራ እንዲሁም በተለያዮ መፈክፎች ታጅቦ በተሳካ ሁኔታ ተከናወነ። 

Friday, April 11, 2014

ለትግራይ ተወላጆች በሙሉ ……. – አብርሃ ደስታ

10155685_627468584000753_4676346970037171962_n‘ዜጎች ነንና ፍትሓዊ ልማት ያስፈልገናል’ ሲንል አሰሩን። ‘ደማችን ገብረናልና ሰለማዊ ሰልፍ የመውጣት መብታችን ይከበርልን’ ስንል ደበደቡን። ‘ብዙ መስዋእት ከፍለናልና ነፃነታችንን አትንፈጉን’ ስንል ትጥቃችንን አስፈቱን። መብታችንን ለማስከበር ስንሞክር ገደሉን።
ግን ይህን ሁሉ ወላጆቻችን፣ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን የከፈሉት መስዋእት ዓላማው ምን ነበር? ደርግን ደምስሶ ሌላ ደርግ መመስረት? ይሄማ ሊሆን አይችልም። ደርግ’ኮ ደርግ ያሰኘው ተግባሩ ነው።
ደርግን የምንጠላው ደርግ ስለሆነ አይደለም። መጥፎ ምግባር ስለነበረው ነው። ጨቋኝ ስለነበረ ነው። ገዳይ ስለነበረ ነው። ገዳዮቹ ቢቀያየሩ እንኳን ተግባራቸው ያው ግድያ መሆኑ አይቀርም። ገዳይ ማን ይሁን ምን ያው ገዳይ ነው። ደርግ እንዲጠላ ያደረገው ገዳይነቱ ነው። ለኛ የገደለ ሁሉ ደርግ ነው። መግደል፣ በሰው ልጅ ላይ ግፍ መፈፀም፣ መጨፍጨፍ ምን ያህል መጥፎ መሆኑ ከልምድ እናውቀዋለን። ስቃዩ ምን ያህል መራራ እንደሆነ ከራሳችን በላይ ማንም ሊያስረዳን አይችልም።

ሰበር ዜና ባህር ዳር ከተማ የሰዎችን ህይወት የነጠቀ ግጭት ተነሳ ተኩሱ አሁንም እንደቀጠለ ነው

በባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 13 ሜትሮሎጂ ጀርባ በተለምዶ ዝንጀሮ ወንዝ በሚባለው አካባቢ የከተማው አስተዳደር የመኖሪያ ቤቶችን በግሬደር ማፍረሱን ተከትሎ በአካባቢው ነዋሪዎችና በታጣቂዎች መካከል  በተነሳ ግጭት ሁለት ሰዎች መሞታቸው ሲረጋገጥ የፍኖተ ነጻነት ምንጮች ከሶስት በላት ሰዎች መሞታቸውን የአይን ምስክሮችን ጠቅሰው ዘግበዋል፡፡  ከስፍራው እየደረሰን የሚገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው ግጭቱ እየተባባሰ የመጣ ሲሆን ተኩሱ አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡ – See more at: http://www.fnotenetsanet.com/

ሒላሪ ክሊንተን ጫማ ተወረወረባቸው

ሒላሪ ክሊንተን ጫማ ተወረወረባቸው

clinton


በመጪው የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ጠንካራ ተፎካካሪ ሆነው ይቀርባሉ እየተባሉ የሚጠበቁት ሒላሪ ክሊንተን ንግግር በሚያደርጉበት ጊዜ ጫማ ተወረወረባቸው፡፡ ጉዳት ባይደርስባቸውም ዜናው ግን የበርካታ ሚዲያዎችን ቀልብ ስቧል፡፡

ስለፍትሕ ሲባል፤ ሥርዓቱ ይፍረስ! (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ )

ስለፍትሕ ሲባል፤ ሥርዓቱ ይፍረስ! (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ )

ባለፉት አራት አስርታት ሀገሪቱ አያሌ ተግዳሮቶችን መጋፈጧ ባይዘነጋም፤ በተለያየ ጊዜ ሚሊዮኖችን ካረገፈው አሰቃቂው ረሃብ በማይተናነስ መልኩ ሕዝቦቿን ዋጋ ያስከፈለ ጉዳይ ቢኖር የፍትሕ አለመከበር ያስከተለው ሁለንተናዊ ምስቅልቅሎሽ ነው ብሎ ለመናገር የሚያስደፍሩ በርካታ ማሳያዎች አሉ፡፡ የየካቲቱን አብዮት ጠልፎ ሥልጣኑን የተቆጣጠረው ወታደራዊው ደርግ፣ የፍርድ ቤት ደጆችን በጓጉንቸር ቆልፎ ሲያበቃ፣ የራሱ አባላት እጃቸውን እያወጡ ድምፅ በመስጠት በአፄው ባለስልጣናትንም ሆነ ግብረ-አበሮቹ በነበሩ መኮንኖች ላይ የሞት ቅጣትን ያህል የመጨረሻ ከባድ ውሳኔ የማሳለፍን አስደንጋጭ ክስተት ጨምሮ፤ ከከተማ እስከ ገጠር ያደራጃቸው የአብዮት ጠባቂዎችና የገበሬ ማሕበራት ከየቤቱ አንቀው እያወጡ “ነፃ እርምጃ” እንዲወስዱ፣ ከየእስር ቤቱ እየለቃቀሙ በጅምላ እንዲረሽኑ በአዋጅ የፈቀደበት ጊዜ የፍትሕ ምኩራቡ ፈርሶ በግላጭ የተቀበረበት ዕለት ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ በርግጥ ይህ የማን-አለብኝነት አረመኔያዊ አገዛዝ የታቃውሞውን ጎራ በማጠናከር ታሪካዊ ውድቀቱ እንዲፋጠን ካደረጉ ምክንያቶች አንዱ እንደነበር ለመረዳት 17 ዓመታትን መውሰዱ አይዘነጋም፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት በረዳት አብራሪ ኃይለመድህን አበራ ላይ ክስ መሰረተ

በተመስገን ደሳለኝ

Ethiopian Airlines plane Co-Pilot Hailemedehin Abera Tagegn charged

-ከ253, 336 ከ42 ሳንቲም ዩሮ በላይ ኪሳራ ደርሷል ተብሏል

-የአእምሮ ችግር እንዳሌለበትም ተረጋግጧል

ፍትሕ ሚኒስቴር በረዳት አብራሪ ኃይለመድን አበራ ላይ የካቲት 9 ቀን 2006 ዓ.ም ሌሊት የበረራ ቁጥር ET 702 የሆንን ቦይንግ አውሮፕላንን ከእነ 202 ተሳፋሪዎቹ ወደ ሮም በሚበርበት ወቅት ጠልፎ ሲውዘርላንድ አሳርፏል በማለት በከፍተኛው ፍርድ ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት ክስ መመስረቱን የፍትሕ ሚኒስቴር ምንጮቼ አረጋግጠውልኛል፡፡
በኃይለመድን ላይ የቀረበው ክስ ሁለት ሲሆን፤ የመጀመሪያው በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢፌዴሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 507/1/ ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ፡-

Thursday, April 10, 2014

ከአገር መውጣት የማይችሉ ባለሥልጣናት በጭንቀት ውስጥ ናቸው

"አሁን ያለው ኢህአዴግ ላዩ በቀለም ቀቢ የተዋበ ይመስላል"

stressed


ኢህአዴግ በሙስና ስም የ”ማጥራት ዘመቻ” ማካሄዱን ተከትሎ የተከሰተው አለመተማመንና እርስ በርስ በጥርጥር የመተያየት ችግር ካድሬውን ማስጨነቁ ተጠቆመ። ኢህአዴግን ለመሰናበት የሚፈልጉ በርካታ ካድሬዎች “ለምን” በሚል የሚቀርብላቸውን ጥያቄ በመፍራት የግድ ፓርቲውን መስለው እንደሚኖሩ ተገለጸ።

Wednesday, April 9, 2014

ምስክሮችን ከአደጋ ለመጠበቅ የቀረበ የሀሳብ መርሀ ግብር፣

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም

ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
ፍትህ እንደገና ዘገየችን?
International Criminal Courtእ.ኤ.አ በዚህ ዓመት በጃኗሪ ወር መጨረሻ አካባቢ “ኬንያታ በዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (አይሲሲ/ICC): ዘግይቶ መቅረብ ፍትህ እንደተነፈገ መቆጠር የለበትምን?“ በሚል ርዕስ ትችት አቅርቤ ነበር፡፡ በዚያ ትችቴ ላይ ICC የኡሁሩ ሙጋይ ኬንያታን ጉዳይ አስመልክቶ በሄግ እያደረገ ያለው ተደጋጋሚ የፍትህ ሂደቱን የማዘግየት ስራ፣ በቀጠሮ የማሳለፍ እና “የውሸት ማስረጃዎች” እንዲሁም “የሀሰት ምስክሮች” በማቅረብ እንደገና የመታየት ዕድል ለመፍጠር እየተነገረ እና በተግባር እየተፈጸመ ያለው አጠቃላይ ወደኋላ የመንሸራተት ሁኔታ እንቅልፍ ባያሳጣኝም ክፉኛ ያሳሰበኝ መሆኑን በግልጽ አሳዉቄ ነበር፡፡ በዚህ ድርጊት ላይ ምናልባትም የሆነ የማታለል ስራ እየተካሄደ ያለ መስሎ ታይቶኛል፡፡ ይኸ ነገር ሙሉ በሙሉ ትክክል አይደለም ለማለት ባይዳዳኝም የጥርጣሬ ጠረኑ ግን እየሸተተኝ ነው፡፡ ኬንያታ ከተከሰሱበት የሰብአዊ መብት ጥሰት ነጻ በመሆን ከዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት/አይይሲ መዳፍ ስር እንዲወጡ መድረኩ እየተመቻቸ ነውን? የኬንያታ የፍርድ ሂደት በICC ውሳኔ እንደገና ለሌላ የጊዜ ቀጠሮ እንዲተላለፍ መደረጉ በጉዳዩ ላይ ጥርጣሬን በመፍጠር በአሁኑ ጊዜ ከቀድሞው የበለጠ አሳስቦኛል፡፡

ኢትና አሸሮች የህወሃት የድሜ ልክ እስረኞች

ሳዲቅ አህመድ

ገና ወጣት ሳሉ የደርግን ስርዓት በመሸሽ ወደ ጠረፍ ያቀኑ ናቸዉ። ዲሞክራሲያዊ መሆን ይቃጣዉ የነበረዉ ህወሃት ሁለት አማራጭ የሰጣቸዉም ነበሩ፤ ደርግን በጦር መታገል ወይም ሱዳን ገብቶ ስደተኛ በመሆን ወደ አዉሮፓ፣ዩናይትድ እስቴትስ ወይም ካናዳ በመሰደድ ህወሃትን በገንዘብና በፖለቲካ መርዳት። ወደ ጦርነት አዉድማ የገቡት ኢትና አሸሮች  እንዳሉ ሆነዉ ሱዳን መግባት የመረጡት በተባበሩት መንግስታት (UNHCR) በኩል ወደ ምእራቡ አለም የመጓዛቸዉ ህልም እዉን እስኪሆን ድረስ በሱዳን ዉስጥ “ኢትና-አሸር” የሚባል ህገወጥ (ሐራም) ስራ ነበራቸዉ። ለአያሌ አመታት በዚህ ህገወጥ ስራ በመሰማራት ህወሃትን የደገፉ ሲኖሩ እነዚሁ ኢትና አሸሮች ዛሬም ካሉበት ቦታ የህወሃት የቁም እስረኞች ሆነዉ ህወሃትን እያገለገሉ ይገኛሉ።Twelve O'Clock at mid day
ኢትና አሽር (አስራ ሁለት)የስራ ዘርፍ ምን እንደሆነ ለኔ ለመጻፍ በጣም ያሳፍረኛልና ሱዳን ከነበሩ ኢትዮጵያዉያን ጠይቃቹ ተረዱ። ሰዎችን በሙስና ይዞ ሎሌ ሚያረገው ህወሃት፤ እነዚህንም ኢትና አሽሮች ባሰራቸዉ አሳፋሪ ወንጀል ዛሬም ከርቀት ሆኖ ይቆጣጠራቸዋል።አንዳንዶቹ ንሰሃ አርገዉ ቤተ-ክርስቲያን ወይም ተዉበት አርገዉ መስጊድ ቢገቡም፤ የካድሬነት ስራ ይሰጣቸዋል። ስለ ቤተ ክርስቲያኑ ባላዉቅም ስለ መስጊዱ ትንሽ ልበል…

ዲና ሙፍቲ ይመችዎት – “በነጻው ፕሬስ” ስም

ቀጭኑ ዘ-ቄራ

dina_mufti


ለምሳሌ አንድ አናጢና ግንበኛ የነበረ ሰው ጊዜ ረድቶት ወይም ተምሮ ወይም እድገት አግኝቶ ወይም …. በቃ በሆነ ነገር የጦር ጄኔራል ቢሆንና ተመልሶ ግንበኛ ቢሆን ምን ተብሎ ሊሰየም ነው? ግራ ያጋባል። ግን ደግሞ ላያጋባም ይችላል። የዛሬዎቹ ጄኔራሎች ኢንቨስተር ስለሆኑ ነዋ!! ለምሳሌ አንድ አምባሳደር ተብሎ የ”ተመደበ” ሰው፣ በግምገማ በሉት በገገማ “በቃህ” ቢባልና ቀድሞ ወደነበረው ሙያ ወደ ነርስነቱ ቢመለስ ምን ተብሎ ሊጠራ ነው? “አምባሳደር፣ ነርስ፣ እገሌ …”?

Tuesday, April 8, 2014

ስለፍትሕ ሲባል፤ ሥርዓቱ ይፍረስ! (ተመስገን ደሳለኝ)

ባለፉት አራት አስርታት ሀገሪቱ አያሌ ተግዳሮቶችን መጋፈጧ ባይዘነጋም፤ በተለያየ ጊዜ ሚሊዮኖችን ካረገፈው አሰቃቂው ረሃብ በማይተናነስ መልኩ ሕዝቦቿን ዋጋ ያስከፈለ ጉዳይ ቢኖር የፍትሕ አለመከበር ያስከተለው ሁለንተናዊ ምስቅልቅሎሽ ነው ብሎ ለመናገር የሚያስደፍሩ በርካታ ማሳያዎች አሉ፡፡ የየካቲቱን አብዮት ጠልፎ ሥልጣኑን የተቆጣጠረው ወታደራዊው ደርግ፣ የፍርድ ቤት ደጆችን በጓጉንቸር ቆልፎ ሲያበቃ፣ የራሱ አባላት እጃቸውን እያወጡ ድምፅ በመስጠት በአፄው ባለስልጣናትንም ሆነ ግብረ-አበሮቹ በነበሩ መኮንኖች ላይ የሞት ቅጣትን ያህል የመጨረሻ ከባድ ውሳኔ የማሳለፍን አስደንጋጭ ክስተት ጨምሮ፤ ከከተማ እስከ ገጠር ያደራጃቸው የአብዮት ጠባቂዎችና የገበሬ ማሕበራት ከየቤቱ አንቀው እያወጡ “ነፃ እርምጃ” እንዲወስዱ፣ ከየእስር ቤቱ እየለቃቀሙ በጅምላ እንዲረሽኑ በአዋጅ የፈቀደበት ጊዜ የፍትሕ ምኩራቡ ፈርሶ በግላጭ የተቀበረበት ዕለት ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ በርግጥ ይህ የማን-አለብኝነት አረመኔያዊ አገዛዝ የታቃውሞውን ጎራ በማጠናከር ታሪካዊ ውድቀቱ እንዲፋጠን ካደረጉ ምክንያቶች አንዱ እንደነበር ለመረዳት 17 ዓመታትን መውሰዱ አይዘነጋም፡፡

Monday, April 7, 2014

በስምምነት ላይ የተመሰረት ባህላዊ ውህደት Vs ህገ-መንግስታዊ ቀናዒነት

(ገለታው ዘለቀ)

2


መግቢያ
 በዚህ ጽሁፍ ሥር ለውይይት ይሆን ዘንድ የምናነሳው ኣሳብ   constitutional patriotism   ወይም ህገ መንግስታዊ ቀናዒነት ወይም ኣርበኝነት የሚባለው ጽንሰ ሃሳብ ባለፈው በተከታታይ ካቀረብኳት የConventional Cultural Unity ወይም በስምምነት ላይ የተመሰረት ባህላዊ ውህደት ካልኩት ኣሳብ ጋር እንዴት እንደሚለያይና  በኢትዮጵያ ሁኔታ ከሁለቱ ኣሳቦች የትኛው ተገቢና ችግር ፈቺ ሊሆን እንደሚችል  ኣሳብ ለማፍራት ነው።

ኖርዌይ ኢህአዴግ ያሰረባትን ዜጋዋን ጉዳይ እየተከታተለች ነው

ማዕከላዊ እስርቤት ከፍተኛ ስቃይ ይደርስባቸዋል በሚል ተሰግቷል

okello


የኢህአዴግን ካዝና የምትሞላዋ ኖርዌይ በማዕከላዊ እስር ቤት የሚገኙትን ዜጋዋን አስመልክቶ በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እየሰራች መሆንዋ ታወቀ። በማዕከላዊ እስር ቤት የታሰሩት ዜጋዋ ድብደባና ቶርቸር እንዳይካሄድባቸው በቅርብ ክትትል እያደረገች መሆንዋን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ክፍሎች ለጎልጉል አስታውቀዋል።

Saturday, April 5, 2014

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ጥሰት ዙሪያ ውይይት አደረገ

ሙሉውን ዝግጅት ለመከታተል ተክታዩን ቪዲኦ የመለከቱ፡፡ 
ኢትዮጵያ መረጃ የሚያወጡትና ጋዜጠኞችን ስሚ” በሚል ርእስ የአውሮፓ ህብረት ሶሻሊስቶችና ዲሞክራቶች ከአለም የጋዜጠኞች መብት ተቆርቋሪ ከሆነው ሲፒጄ ጋር በጋራ ባዘጋጁት የውይይት መድረክ ላይ በቃሊቲ እስር ቤት ከአንድ አመት በላይ ታስሮ የተለቀቀው ስዊድናዊው ጋዜጠኛ ማርቲን ሽብየና በኦጋዴን የተካሄደውን ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት የሚያጋልጥ መረጃ ይዞ የወጣው ወጣት አብዱላሂ ሁሴን፣ የአውሮፓ ህብረት የፓርላማ አባልና የ1997 የኢትዮጵያ ምርጫ የአውሮፓ ህበረት ታዛቢ ሃላፊ፣ የሲፒጄ ጂን ፓወል ማርቶዝ እና የሂውማን ራይትስ ወች ተወካይ የሆኑት ሌስሌ ሌፍኮው ተገኝተው በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ንግግር አድረገዋል።

Friday, April 4, 2014

ረዳት አብራሪ ሃይለመድን አበራ ዛሬም በምረመራ ላይ መሆኑን የስዊዘርላንድ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር መስሪያ ቤት ነገረኝ

593x322xco-pilot_hijacking.jpg.pagespeed.ic.X8fktOpOJtረዳት አብራሪ ሃይለመድን አበራ ዛሬም በምረመራ ላይ መሆኑን የስዊዘርላንድ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር መስሪያ ቤት ነገረኝ
ዛሬ ለምን እነደሁ እንጃ፤ ረዳት አብራሪ ሃይለመድን አበራ በማለዳው በአዕምሮዬ ተመላለሰ። ምን ደርሶ ይሆን… ምን ተብሎ ይሆን… ኢትዮጵያ አየር መንገድ ከመስራት የሰው ሃገር እስራትን ያስመረጠውን በደል የሚነግርን መቼ ይሆን… ወይስ ያቺ እህቱ እና እኒያ ወንድሙ እነዳሉት የስዊዝ ሃኪሞችም ህመምተኛ ነው ብለው ወደ ህክምና ልከውት ይሆን… (ከሆነም ካለሆነም ኢትዮጵያችን ውስጥ ጤነኛው ማነው… መቼስ ነው የምንድነው…) እያልኩ የባጥ የቆጡን ሳንሰላስል ቆየሁና፤ ድንገት የስዊዘረላንድ ወጪ ጉዳይ ሚኒስቴርን ድረ ገጽ ጎግልን ጠየኩት።
የተባረክ ጎግል “ካንተማ አልድብቅህም ደንበኝ!” ብሎ ሰጠኝ። ከድረ ገጹ ላይ የኢሜል አድራሻቸውን ለቅም አደርኩና “Dear Sir Madam…”  ብዬ ሳበቃ (እኔ ከእናነት ሃሳብ እና ናፍቆት በስተቀር ደህና ነኝ) የሚለውለውን ሳላካትት የወንድማችን ሃይለመድን አበራን ነገር ከምን አደረሳችሁት… አሁን በምን ሁኔታ ላይ እነዳለ ለማወቅ ፈለጌ ነው ይህንን የኢሜል መልዕክት ወደ እናንተ መስደዴ ስል በትህትና ጠየኳቸው።

Thursday, April 3, 2014

የማለዳ ወግ… በጨለመው የሳውዲ ወህኒም ይነጋል… (ነብዩ ሲራክ)

ግፍ ከበዛበት ወህኒ የአክብሮት ስላምታየ ይድረሳችሁ! (ነብዩ ሲራክ፣ ከሳውዲ አረብያ ውህኒ ቤት)

Nebiyu Sirak
ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ
እነሆ ለሁለተኛ ጊዜ ለአፍታ ያህል እድሉን አግኝቸ ወህኒ የመውረዴን እውነታ ላስረዳችሁ ግድ አለኝ ። ዛሬ አስረግጨ የምነግራችሁ ወህኒ የመውረዴ ምክንያት ሚስጥር ግምሽ እድሜየን ህግና ስርአቷን አክበሬ የኖርኩባትን የሳውዲት አረቢያን ህግ ተላልፊ አይደለም ! የስደተኛው ጉዳይ ያገባኛል በሚል የማቀርበው መረጃ ቅበላየ የማይመቻቸው ፣ ያመማቸው ከተሴረውና እየተሴረ ካለው እገታ ጀርባ ስለመኖራቸው አልጠራጠርም ። … ዛሬ በዚህ ዙሪያ ብዙ አልልም!
አላወቁትም እንጅ ክፉዎች ጠቅመውኛል ፣ ያላየሁትን እንዳይ አድርገውኛል። መንገዱ የከፋ ቢሆንም በወሰዱኝ መንገድ ተመርቸ እሰማው የነበረውን የወገኖቸ የወህኒ የከፋ ኑሮና ህመም ፣ በተቆርቋሪ ጠያቂ ማጣት ፣ በፍትህ መነፈግ እይሆኑ ያሉትን ከመስማት ማየት ማመን ነውና በአካል ማየት ችያለሁ !
ከመታሰሬ ጥቂት ቀናት በፊት በግፍ ለተደበደበው፣ ሁለት አይኑን ላጣውና “አይሆኑ ከሚሆን ቢሞት ይሻላል” ተብሎ የፎቶ መረጃው ሳይቀር በእጀ የገባውን ወጣት ምንዱብ የወህኒ ህይወትን ተጨባጭ ታሪክ ከአይን እማኞች ቃርሜያለሁ! እሱም ያለው ከታሰርኩበት የቅርብ ርቀት ነው ።… አትጠራጠሩ አገኘውም ይሆናል !

ትንሽ ምላጭ አገር ትላጭ! መጠላለፍ ወደየትኛው ገደል እየመራን ነው? (ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)

Prof. Mesfin Woldemariamየአዲስ አበባን መኪናዎች በተለይም በጫት የሚሽከረከሩት ታክሲዎችን በማንኛውም መስቀልኛ መንገድ ላይ ለአምስት ደቂቃ ቆሞ የተመለከተ ሰው በቀላሉ እንደሚረዳው ‹እኔ ካላለፍሁ ማንም አያልፍም!› በሚል መመሪያ መኪናዎቹ ተቆላልፈው እንዲቆሙ ማድረግ ነው፤ እንደሚመስለኝ የአባቶቻችንን ዕዳ እየከፈልን ነው፤ ዱሮ በደጉ ዘመን ሁለት ኢትዮጵያውያን መስቀልኛ መንገድ ላይ ሲገናኙ አንተ-እለፍ አንተ-እለፍ እየተባባሉ የሰማዕታቱንና የቅዱሳኑን ስም እየጠሩ ይገባበዙ ነበር! ይህ ባህል በጠንካራ የሥልጣኔ ላጲስ ተደምስሶ ጠፍቶ በምትኩ እኔ ካላለፍሁ ማንም አያልፍም መንገዱን ሁሉ መቆላለፍ አዲስ የመጠላለፍ ባህል እየተተከለ ነው፤ የመጠላለፍ ባህል የሚታየው በባቡር መንገዶች ላይ ብቻ አይደለም፤ በብዙ ነገር መጠላለፍ ባህል እየሆነ ነው! የዚህ ዝንባሌ መጨረሻው አሸናፊ የሌለበት ሙሉ ጥፋት ነው።

                                                                         Prof. Mesfin                         Woldemariam
በመንገዶች ላይ ጥቂት በጫት የሚነዱ መኪናዎች በመቶ የሚቆጠሩ መኪናዎች እንዳይንቀሳቀሱ ለማድረግ ይችላሉ፤ ሲያደርጉም በየቀኑ እየታየ ነው፤ በማኅበረሰባዊና በፖሊቲካ ግንኙነትም አንድ ሰው የሚዘራው መርዝ የጊዜው ሁኔታ በሚፈቅድለት ፍጥነት የማኅበረሰቡን አባላት ያዳርሳል፤ እንቆቅልሹ እንደሚለው ትንሽ ምላጭ አገር ትላጭ! ማለት መርዝ፣ እሳት፣ ተላላፊ በሽታ በሕዝቡ ላይ ማሰራጨት ከአምስትና ከአሥር ዓመታት በኋላ ውጤቱ ምን እንደሚሆን መገመት አያቅትም።