Translate

Saturday, April 12, 2014

በኖርዌ የሚገኙ የወያኔ ሰላዮችን በመቃወም ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በኦስሎ ከተማ ተካሄደ

በኖርዌ የሚገኙ የወያኔ ሰላዮችን በመቃወም ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በኦስሎ ከተማ ተካሄደ


ማርች 11, 2014 በኖርዌ የሚገኘው የኢትዮጵያን የስደተኞች ማህበር ያዘጋጀው ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ከተለያዩ የኖርዌ ከተሞች በመጡ ታዳሚዎች እና በኦስሎ ነዋሪ በሆኑ ኢትዮጵያውያንና በኢትዮጵያ ባንዲራ እንዲሁም በተለያዮ መፈክፎች ታጅቦ በተሳካ ሁኔታ ተከናወነ። 

የዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ዋና አላማ በኖርዌ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቀው በሚኖሩበት ሐገር እንደሚሰለሉ እና የወያኔ ሰላዮች በኖርዌይ ምድር መኖራቸውን የኖርዌ የደህንነት ፓሊስ ለሀገሪቱ ትልቅ ጋዜጣ መረጃ መስጠታቸውን እና በተመሳሳይ የሂውማን ራይትስ ዋች በቅርቡ ያወጣውን መረጃ መሰረት በማድረግ የኖርዌ መንግስት ለወያኔ ሰላዬዮች የሚያደርገውን ድጋፍ እንዲያቆም እና አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስድ ለመጠየቅ እና ኖርዌ በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ ያላትን የአሳይለም ፖሊሲ እንድታስተካክል የሚጠይቅ የተቃውሞ ሰልፍ ነበር።

ፕሮግራሙ ከቀኑ 12፡00 የተጀመረ ሲሆን የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌ ምክትል ሊቀመንበር ሰፋ ያለ የወያኔ ሰላዮችን የተመለከተ ንግግር ያሰሙ ሲሆን የዚሁ ድርጅት የሴቶች ክፍል ተወካይ ወ/ሪት ሔለን ንጉሴ አጠቃላይ በኖርዌ ያሉ ሰላዮችን እና በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ሰፋ ያለ ማብራሪያ በመስጠት ሴቶች በሁለገብ ትግል ውስጥ ያላቸውን ጉልህ ሚና እንዲሁም ወደፊት ሊኖራቸው የሚገባውን ሚና ጨምረው በማስረዳት ለትግሉ አጋር መሆናቸውን ገልፀዋል። በመቀጠል የስደተኛ ማህበሩ ፀሐፊ ወ/ሪት የሺሃረግ በቀለ ሰፋ ያለ ማብራሪያ በእንግሊዘኛ ቋንቋ ያቀረበች በመሆኑ የሐገሪቱ ዜጎች መልክቱን በደንብ እንዲሰሙ ያደረገች ሲሆን የኖርዌጅያን ተወላጅ የሆኑትና በስደረኞች ጉዳይ ላይ የሚሰሩ ድርጅቶች ተወካዮች በተመሳሳይ ስለ ኢትዮጵያ አምባ ገነን መንግስት ከስደተኛው በላይ የሚያውቁትን መረጃ በዝርዝር በየተራ በንግግር አሰምተዋል። ይህንን የሰላማዊ ሰልፍ ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ የመሩልን የስደተኛ ማህበሩ የኮሚቴ አባላት የሆኑት አቶ ዮናስ እና አቶ ጌታቸው ናቸው።

በመጨረሻም ከሰላማዊ ሰልፉ በኋላ በወ/ሮ ሰዋሰው እና በባለቤታቸው የተዘጋጀ የምሳ ግብዣ የተከናወነ ሲሆን የስደተኛ ማህበሩም የውይይት ጊዜ አዘጋጅቶ የነበረ በመሆኑ የስደተኛ ማህበሩን የሶስት ወር ሪፖርት ካቀረበ በኋላ በቀጥታ ወደ ውይይት በመግባት ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በኖርዌ ስለሚገኙ የወያኔ ሰላዮች በሰፊው ምክክር አድርገው ወደፊት ምን ማድረግ እንዳለባቸው እንዴት እነኚህን ሰላዮች በምን መልኩ ማጋለጥ እንዳለባቸው ተወያይተው በመቀጠል አጠቃላይ ስለ ኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ውይይት አድርገው ፕሮግራሙ በተሳካ ሁኔታ ከምሽቱ 19፡00 ተጠናቋል። 

No comments:

Post a Comment