Translate

Wednesday, April 9, 2014

ኢትና አሸሮች የህወሃት የድሜ ልክ እስረኞች

ሳዲቅ አህመድ

ገና ወጣት ሳሉ የደርግን ስርዓት በመሸሽ ወደ ጠረፍ ያቀኑ ናቸዉ። ዲሞክራሲያዊ መሆን ይቃጣዉ የነበረዉ ህወሃት ሁለት አማራጭ የሰጣቸዉም ነበሩ፤ ደርግን በጦር መታገል ወይም ሱዳን ገብቶ ስደተኛ በመሆን ወደ አዉሮፓ፣ዩናይትድ እስቴትስ ወይም ካናዳ በመሰደድ ህወሃትን በገንዘብና በፖለቲካ መርዳት። ወደ ጦርነት አዉድማ የገቡት ኢትና አሸሮች  እንዳሉ ሆነዉ ሱዳን መግባት የመረጡት በተባበሩት መንግስታት (UNHCR) በኩል ወደ ምእራቡ አለም የመጓዛቸዉ ህልም እዉን እስኪሆን ድረስ በሱዳን ዉስጥ “ኢትና-አሸር” የሚባል ህገወጥ (ሐራም) ስራ ነበራቸዉ። ለአያሌ አመታት በዚህ ህገወጥ ስራ በመሰማራት ህወሃትን የደገፉ ሲኖሩ እነዚሁ ኢትና አሸሮች ዛሬም ካሉበት ቦታ የህወሃት የቁም እስረኞች ሆነዉ ህወሃትን እያገለገሉ ይገኛሉ።Twelve O'Clock at mid day
ኢትና አሽር (አስራ ሁለት)የስራ ዘርፍ ምን እንደሆነ ለኔ ለመጻፍ በጣም ያሳፍረኛልና ሱዳን ከነበሩ ኢትዮጵያዉያን ጠይቃቹ ተረዱ። ሰዎችን በሙስና ይዞ ሎሌ ሚያረገው ህወሃት፤ እነዚህንም ኢትና አሽሮች ባሰራቸዉ አሳፋሪ ወንጀል ዛሬም ከርቀት ሆኖ ይቆጣጠራቸዋል።አንዳንዶቹ ንሰሃ አርገዉ ቤተ-ክርስቲያን ወይም ተዉበት አርገዉ መስጊድ ቢገቡም፤ የካድሬነት ስራ ይሰጣቸዋል። ስለ ቤተ ክርስቲያኑ ባላዉቅም ስለ መስጊዱ ትንሽ ልበል…

ኢትና አሸሮች ምን ያደርጋሉ?
ስርዓቱን ሊነካ የሚችል ስራ ለመስራት ስብሰባ ቢጠራ ስብሰባዉን ንግግር በማስረዘም ማበላሸት፣ከተሰብሳቢዉ ጋር ችግር በመፍጠር ስብሰባዉን የጭቅጭቅ ማድረግ፣ሰላማዊ ሰልፍ ሲጠራ ቢቻል ሰላማዊ ሰልፉን ማስቀረት ካልሆነ ሰላማዊ ሰልፉ ደካማ እንዲሆን ማድረግ፣ሚስጥርን ለህወሃት አሳልፎ መስጠት፣ “እኔ ከዚህ ዘር ስለሆንኩኝ ነዉ የማልታመነዉ” በማለት ማለቃቀስ፣ በህዝብ ዘንድ የማይደገፍ ሐሳብ ሲሰነዘር ደካማዉን ሐሳብ በመደገፍ ተክቢርን ማዥጎድ ጎድ፣ ፊትና (መከፋፈል) መጣ ብሎ በማልቀስ የሰዉን ልብ በልቶ አቅጣጫ ማስቀየር፣ስርዓቱን በጽኑ የሚቃወሙ ግለሰቦችንና ሚዲያዎችን ስም ማጥፋትና ተዓማኒነትን ማሳጣት ወዘተ የገኙበታል።
ኢትና አሸሮች ዲያስፖራ ባሉ ቡድኖች በቦርድ-በሃላፊነት ተመርጦ ለመስራት የማያቅማሙ ሲሆኑ በተለያዩ ኮሚኒቲዎች በሃላፊነትም ይሰራሉ፤ አንዳንድ የኑሮን እንቅፋቶች ህወሃት ሰለሚያነሳላቸዉ ከሌላዉ የበለጠ ግዜን መለገስ ብቻ ሳይሆን ዳጎስ ያለ ገንዘብን አዉጥቶ በመርዳት የሰዉን አፍ ለማዘጋት ይሞክራሉ። ሰዎችን በጥቅም ለመደለል የሚያረጉት ሙከራ የላቀ ነዉ፤ በመንግስትና በዲያስፖራዉም መሃከል ድልድይ በመሆን ባመራር ደረጃ ላይ ላሉ ወገኖች በኢንቨስትመንት ስም መሬት በማሰጠትና ሌሎችንም ለሙስና የሚመቹ ጉዳዮችንም ያስፈጽማሉ።
ምክር፥ ዉድ ኢትና አሸሮች! ዉድ የሆነዉን ህይወት ለህወሃት አሳልፎ ሰጥቶ የቁም እስረኛ ከመሆን የትላንቱ ታሪካቹ የትላንት ነዉና ዛሬ የናንተን የበደል ገፈት የቀመሱ እህቶችን ይቅርታ ጠይቃቹ፤ አምላክቹን ጥልቅ በሆነ ንሰሃ (ተዉባ) ተማጸኑትና እራሳ ሁን ከህወሃት ቀንበር ነጻ አዉጡ።
ምክር፥በኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞች የእምነት ማእከላትና ማህበራት ዉስጥ ተሸጉጣቹ የሙስሊምን ሰላማዊ ትግል እንቀለብሳለን ብላቹ የምታምኑ ከሆነ ከንቱዎች ናቹ። የሰሞኑም ግርግራቹ አልሰራም(ያዲሳባዉም ጭምር)፤ እናንተ ለሰራቹት የኢትና አሸር ሐጢዓት ይቅርታ ጠይቁ እንጂ ድምጻችን ይሰማ” የሚለዉ ጀግና ትዉልድም ሆነ መሪዎቹ ከማፍያዉ ህወሃት የላቁ በመሆናቸዉ ይቅርታ አይጠይቁም። ግዜዉ ሳይረፍድ የህወሃትን ሲህር (መተት) ከላያቹ ላይ ገፋቹ ጣሉና ከጀግናዉ ትዉልድ ጋር አብራቹ ጀግኑ።
ዉዱ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! እነዚህ ኢትና አሸር የምንላቸዉ ንዑሳንን ሴራ ለማሳየት በጃችን ያለዉን የድምጽና የቪዲዮ መረጃ ብንለቀዉ “ለካስ አልቀናል” ብሎ ብዙሓኑ ይደናገጣል። ተወደደም ተጠላም  ለህዝብ በነጻ (ሊላሂ) እንሰራለን የሚሉ የዲያስፖራ ቅምጥሎች ይህን ሰላምዊ ትግል ለማዳከም እንዳልዳከሩት የለም…ግን ዉድቀት ታትማባቸዉለች አሸናፊ አይሆኑምና ልብ ያለዉ ልብ ይበል!
ሳዲቅ አህመድ

No comments:

Post a Comment