Translate

Wednesday, December 21, 2016

ሰበር መረጃ — የላክናቸው ሁሉ አይመለሱም የሰሜን ዕዝ ስምሪት ማዘዣ!


በልኡል አለም 
በሕወሃት ኮማንድ ፖስት ቁጥጥር ስር የወደቀው የሰሜኑ እዝ ወደ ሰሜን እና ደቡብ ጎንደር የላካቸው በወታደራዊ ደህንነት እና በወታደራዊ ምህንድስና የተሰማሩ አባላቶቹ መገደላቸውንና መሰወራቸውን ለኮማንድ ፓስቱ በላከው ሪፖርት ለማወቅ ተችሎአል። በሪፓርቱ መሰረት፣

Monday, December 12, 2016

ወያኔ የመከላከያ ሰራዊቱ ወደ አርበኞች ግንቦት 7 እየተቀላቀሉ መሆኑን አመነ።

(ዘርይሁን ሹመቴ)
የወያኔን አገዛዝ በመክዳት ወደ ትጥቅ ትግሉ እየተቀላቀሉ የሚገኙ የመከላከያ ሰራዊት ቁጥር እየጨመረ እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ። በቅርቡ በሰሜን ጎንደር ለነጻነት እየተዋደቁ ያሉትን ጀግኖች የአማራ ተወላጆችን ለመጨረስ ወያኔ ከላካቸው ወታደሮች አብዛኞቹ ወደ አርበኞች ግንቦት ግንባር መቀላቀላቸው ይታወቃል።በቆራጥነት ቤተሰባቸውን ጥለው በየጫካው የሽምቅ ውጊያ በማድረግ ወያኔን እያርበደበዱ ያሉትን የአማራ ታጋዮችን ትጥቅ ለማስፈታት የሚልካቸው ወታደሮች ከነሙሉ ትጥቃቸው ወያኔን እራሱን ለመውጋት ከህዝቡ ጎን ለመቆም ግንባሩን ተቀላቅለዋል።

Thursday, December 8, 2016

አርበኞች ግንቦት 7 የወያኔን ሰራዊት በሁመራ አዲስ አለም ዲንሻ አብደራፊ በካበታና በሰሜን ጎንደር አርበደበደ።

አባይ ሚዲያ ዜና
የአርበኞች ግንቦት የፖለቲካ ጉዳዮች ዋና ሃላፊና የግንባሩ ቃለ አቀባይ የሆኑት አቶ መንግስቱ ወልደስላሴ በወያኔ አገዛዝ ጋር ከፍተኛ ውጊያ እየተደረገ እንደሆነ ተናገሩ። እንደ ቃለ አቀባዩ ገለጻ የአርበኞች ግንቦት ወታደሮች በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በጥልቀት ሰርገው ገብተዋል። የፓለቲካ ጉዳዮች ዋና ሃላፊውም በማከልም እነዚህ ሰርገው የገቡት ወታደሮች ከወያኔ ጦር ጋር የሚያደርጉትን ውጊያ አጠናክረው እንደቀጠሉ ይናገራሉ።

Wednesday, November 30, 2016

ሰበር ዜና — ፕ/ር መረራ ጉዲና ታፍነዋል

ክንፉ አሰፋ
30 ኖቬምበር 2016 – የመድረክና የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ መሪ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ዛሬ ረቡእ ማምሻውን በደህንነት ሃይሎች ታፍነው መወሰዳቸውን ለማረጋገጥ ችለናል።
Dr. Merera Gudina
ዶ/ር መረራ ጉዲና
በዛሬው እለትፕ/ር መረራ ጉዲና መኖርያ ቤት በደህንነቶች እና ከባድ መሳርያ በጣጠቁ የአጋዚ አባላት ተከብቦ መዋሉን የአይን እማኞች ገልጸዋል። ብእር ብቻ ለያዘ አንድ ሰላማዊ ሰው ይህን ሁሉ ሃይል ማሰማራት ስርዓቱ ምን ያህል እንደተብረከረከ የሚያሳይ መሁኑን እማኞቹ ጨምረው ገልጸዋል።

በአውሮፓ ህብረት ጥሪ ተደርጎላቸው ሃገሪቱ ስላለችበት መስቀለኛ መንገድ ገለጻ አድርገዋል። ከዚያም በሆላንድ፣ በጀርመን እና በስዊዘርላንድ ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን ጋር ስለ ሃገሪቱ ሁነታ መወያየታቸው ይታወሳል።

Tuesday, November 29, 2016

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ: “አገራዊ ንቅናቄው የድርጅቶች እንጅ የብሄር ውክልና የለውም”


በቅርቡ በ4 የፖለቲካ ድርጅቶች የተመሰረተው የኢትዮጵያ አገራዊ ንቅናቄ ትናንት እሁድ በስቶክሆልም ከተማ የተሳካ ስብሰባ ማድረጉን ገልጿል። የአርበኞች ግንቦት7 መሪ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር መሪ አቶ ሌንጮ ለታ እንዲሁም የአፋር ህዝብ ፓርቲ መሪ ዶ/ር ኮንቴ ሙሳ በስብሰባው ላይ የተገኙ ሲሆን፣ ስብሰባው በስቶክሆልም /ስዊድን የንቅናቄው አስተባባሪ አቶ ዘለሌ ጸጋ ስላሴ ንግግር ተከፍቷል። ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ባቀረቡት ሰፊ ንግግር፣ ሁሉም የንቅናቄው አባል ድርጅቶች ኢትዮጵያን እንደ አንድ ሉአላዊ አገር የሚቀበሉ መሆናቸውን እና ችግሮቻቸውን በዲሞክራሲያዊ መንገድ ለመፍታት ዲሞክራሲያዊ ስርዓት መመስረት እንዳለበት ስምምነት ላይ የደረሱ በመሆኑ ተቀራርበው ለመስራት ውሳኔ ላይ እንዲደርሱ እንዳደረጋቸው ገልጸዋል። 

Monday, November 28, 2016

አርበኞች ግንቦት 7 በግጨው እና ማይለሚን በተባሉ ቦታዎች ባካሄደው ውጊያ በሕወሃት ጦር ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል

የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ሰራዊት በወያኔ የመከላከያ ሰራዊት ላይ የሚያደርሰውን ጥቃት አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)
Patriotic Ginbot 7 fighters in action
ኢትዮጵያንና ኢትዮጲያዊነትን ለማዳን ብሎም የተጨቆነውን ህዝባችንን በጫንቃው ላይ የተጫነበትን የባርነት ቀንበር አሽቀንጥሮ በመጣል ህዝብ ቀና ብሎ እንዲሄድና የዴሞክራሲ ተጠቃሚ እንዲሆን መራራና እልህ አስጨራሽ የትጥቅ ትግል እያካሄደ የሚገኘው ጀግናው የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ከወያኔው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ኮማንድ ፖስት ግብረ ሃይልና መከላከያ ሰራዊት ጋር ባደረገው ተከታታይ የማጥቃት እርምጃ የወያኔን ሹማምንቶች አንገት ያስደፋ አንፀባራቂ ድል ማስመዝገቡን አርበኛ ታጋይ ሪፖርተራችን ከስፍራ ባደረሰን መረጃ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ሰበር ዜና: አርበኞች ግንቦት7 በወያኔ ላይ በከፈተው ጦርነት የበላይነት ተቀዳጀ።

ኢትዮጵያንና ኢትዮጲያዊነትን ለማዳን ብሎም የተጨቆነውን ህዝባችንን በጫንቃው ላይ የተጫነበትን የባርነት ቀንበር አሽቀንጥሮ በመጣል ህዝብ ቀና ብሎ እንዲሄድና የዴሞክራሲ ተጠቃሚ እንዲሆን መራራና እልህ አስጨራሽ የትጥቅ ትግል እያካሄደ የሚገኘው ጀግናው የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ከወያኔው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ኮማንድ ፖስት ግብረ ሃይልና መከላከያ ሰራዊት ጋር ባደረገው ተከታታይ የማጥቃት እርምጃ የወያኔን ሹማምንቶች አንገት ያስደፋ አንፀባራቂ ድል ማስመዝገቡን አርበኛ ታጋይ ሪፖርተራችን ከስፍራ ባደረሰን መረጃ ለማወቅ ተችሏል፡፡

ከፍተን ብናየው? ሻአቢያና ኦነግ መስተፋቅር!

አስፋ ጫቦ
Dallas Texas USAImage result for assefa chabo
እንደመግቢያ
ዛሬ ትንሽ መጻፍ የፈለኩት በኦሮሞ ነፃነት ግንባርና (ኦነግ) በኢሳይያስ አፈወርቂ መካከል ያለውን የቆየ ጥብቅ ትስስር በመጠኑ ለመፈተሽ ነው። መነሻ የሆነኝ እንግሊዝ አገር ሎንዶንና አሜሪካ፤ አትላንታ፣ ጆርጂያ የኦሮሞ “ምሁራንና ብሔርተኞች” ያደርጉት ስብሰባና የሰጡት መግለጫ ነው። ያ ራሱን ችሎ መነገር ያለበት ስለሚመስለኝ እመለስበታለሁ። የዚህኛው አላማ እዚያ ሰበሰባ ላይ ተካፋይ ከነበሩት “ነፃ አውጭዎች” አንዱን ኦነግን በጨረፍታ ለመታዘብ ነው።

Sunday, November 27, 2016

በሰሜን ጎንደር ከፍተኛ ጦርነት ሲካሄድ ዋለ

ኅዳር ፲፮ (አሥራ ስድስትቀን ፳፻ / ኢሳት ዜና :-በሰሜን ጎንደር ታች አርማጭሆ  ሳንጃ እና በጠገዴ ወረዳ ግጨው እንዲሁም ልዩ ስሙ ሃመረ በተባለ ቦታ ላይ የነጻነት ሃይሎች እና በገዢው ፓርቲ ወታደሮች መካከል ሲካሄድ በዋለው ጦርነት ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የህወሃት /ኢህአዴግ ወታደሮች መገደላቸው ታውቛል።

ከሁመራ ወደ ቀራቀር በሚወሰደው መንገድ ላይ ቁስቋም ማሪያም አካባቢ በሚገኝ ዳገት ላይ፣ በወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄ አባል በነበረውና ሊያዝ ሲል በማምለጥ ጫካ በገባው ጎቤ መልኬ በሚመራው የነጻነት ሃይሎች ጦርና በአገዛዙ ወታደሮች መካከል በተደረገው ከፍተኛ ውጊያ በርካታ ወታደሮች ሙትና ቁስለኛ ሆነዋል።

ህወሃት እጅ ላይ የንጹሃን ደም እየተንተከተከ ነው!! የምትኮሩ በዚህ ኩሩ

ሁሉም ደጅ እሳት አለ!!

tplf-and-blood

ህወሃት የታሪኩ ካስማና ማገር ከአስከሬን ጋር የተጣበቀ ስለመሆኑ የሚመሰክሩበት የሩቅ ሰዎች አይደሉም። አብረውት በበረሃ የነበሩ፣ አብረውት አመራር ሲሰጡ የኖሩ፣ “በሚያራምዱት አቋም” ከድል በፊትና በኋላ የተለዩት በተለያዩ ሚዲያ ላይ እንደመሰከሩት ህወሃት ደም ምሱ፣ አስከሬን ትራሱ ነው። በነዚሁ የቅርብ ሰዎቹ የተሰሙት ምስክርነቶች ስም፣ ቦታ፣ ጊዜ በመጥቀስ በወቀቱ እዚያው እንደነበሩ በማረጋገጥ እንጂ እንዲሁ በመላ አልነበረም። እነሱ ለአብነት ተነሱ እንጂ ሰለባዎችበየጊዜው አዳዲስ መረጃ ይዘው ብቅ ማለታቸው የተለመደ ነው። እዚህ ላይ ሌሎችም አይረሱም። ቅድሚያ ስለ ሌሎቹ።

Saturday, November 26, 2016

የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት በወያኔ ጦር ላይ በተለያዩ ቦታዎች በተደጋጋሚ ጥቃት በመፈፀም ከፍተኛ ጉዳት አደረሰ፡፡

የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ነበልባል የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ህዳር 10 ቀን 2009 ዓ.ም ለሊት ጎንደር ዳንሻ ከተማ ልዩ ስሙ አዲስ አለም በተባለ ቦታ ሰፍሮ ከሚገኝ የወያኔ መከላከያ ሰራዊት ላይ በፈፀመው ድንገተኛ ማጥቃት ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ አጥቅቶ ተሰውሯል፡፡ በወሰደው ድንገተኛ የማጥቃት እርምጃም 15 የወያኔ ቅጥረኛ ወታደሮችን በመግደል ቁጥራቸው ያልታወቀ ደግሞ ማቁሰሉን አርበኛ ታጋይ ሪፖርተራችን ከስፍራው ባደረሰን ዘገባ አስታውቋል፡፡

Thursday, November 24, 2016

የአርበኞች ግንቦት 7 ነበልባል ሰራዊት በዳንሻ፣ አዲስ አለም ጥቃት ሰንዝሮ መሰወሩን ንቅናቄው አስታወቀ

የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት በወያኔ ጦር ላይ በተለያዩ ቦታዎች በተደጋጋሚ ጥቃት መፈፀሙን በመቀጠል ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱ ታወቀ 
(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ) 
Patriotic Ginbot 7 fighters in action
የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ነበልባል የአርበኞች ግንቦት 7 ሰራዊት ህዳር 10 ቀን 2009 ዓ.ም ለሊት ጎንደር ዳንሻ ከተማ ልዩ ስሙ አዲስ አለም በተባለ ቦታ ሰፍሮ ከሚገኝ የወያኔ መከላከያ ሰራዊት ላይ በፈፀመው ድንገተኛ ማጥቃት ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ አጥቅቶ ተሰውሯል፡፡ በወሰደው ድንገተኛ የማጥቃት እርምጃም 15 የወያኔ ቅጥረኛ ወታደሮችን በመግደል ቁጥራቸው ያልታወቀ ደግሞ ማቁሰሉን አርበኛ ታጋይ ሪፖርተራችን ከስፍራው ባደረሰን ዘገባ አስታውቋል፡፡

የአርበኞች ገንቦት 7 ትላንት በጎንደር ዳንሻ ኣዲስ ኣለም ኣካባቢ ባድረገው ውጊያ ወደ 30 ሚድረሱ የወያኔ ወታደሮችን መግድሉን ምንጮቻችን ገልጸዋል።

Breaking News:-
የአርበኞች ግንቦት 7 ትላንት በጎንደር ዳንሻ ኣዲስ ኣለም ኣካባቢ ባድረገው ውጊያ ወደ 30 ሚድረሱ የወያኔ ወታደሮችን መግድሉን ምንጮቻችን ገልጸዋል።
የኣርበኞች ግንቦት 7 ሰሞኑን ተደጋጋ

Tuesday, November 22, 2016

ሰበር ዜና:-በጄኔራል ሲራጅ ፈርጌሳ የሽፋን ስእል በጄኔራል ሳሞራ የኑስ የበላይነት ቁጥጥር ስር የወደቀዉ የወታደራዊ ደህንነት የመከላከያ ሰራዊቱ ላይ አደገኛ እርምጃ በመዉሰድ አተኩሯል።

ልሁል አለም
world news
በመሆኑም ያለ ወታደራዊ ፍርድ ቤት ዉሳኔ ኮማንድ ፖስቱ በስዉር እንዲያጠቃ ትእዛዝ ተላልፎለት
የኮማንድ ፖስቱ ደህንነትን ተገን ያደረገዉ ዉሳኔ በ8 የመከላከያ አባላቱ ላይ እርምጃ እንዲወሰድ በማዘዙ
ትናንት በ11/03/2009 በመላዉ ሐገሪቱ የተነሳዉን ህዝባዊ እንቢተኝነት ይደግፋል ያደራጃል የተባለዉ የመካከለኛዉ እዝ ባልደረባ የም/መቶ አለቃ አለበል ትእዛዙ የዉሳኔዉ ሰለባ ሲሆን በተጨማሪ ከሰሜን እዝ ወታደራዊ መምሪያ ክፍል ወታደር ቅጣው ቢያድግልኝ ላይ እርምጃ ተወስዶባቸዋል።
ወታደር ቅጣዉ ቢያድግልኝ ሐሙስ ከሰሜኑ እዝ ክፍለ ጦር መምሪያ ትፈለጋለህ ተብሎ ከተወሰደ ወዲህ በጥይት ተደብድቦ መረሸኑን የአይን እማኝ የነበሩ አባላቶች በከፍተኛ ቁጭት ለምንጫችን የትናገሩ ሲሆን።

Monday, November 21, 2016

የሕወሃት ኮማንድ ፖስት በመከላከያ አባላት ላይ የግድያ እርምጃ እየወሰደ ነው

በልኡል አለም
Ambo Must Unite Ethiopians or Nothing Will & TPLF’s Killer Machine ...
 በጄኔራል ሲራጅ ፈርጌሳ የሽፋን ስእል ተሰጥቶት በጄኔራል ሳሞራ የኑስ የበላይነት ቁጥጥር ስር የወደቀዉ የወታደራዊ ደህንነት የመከላከያ ሰራዊቱ ላይ አደገኛ እርምጃ በመዉሰድ ላይ አተኩሯል።

 በመሆኑም ያለ ወታደራዊ ፍርድ ቤት ዉሳኔ ኮማንድ ፖስቱ በስዉር እንዲያጠቃ ትእዛዝ ተላልፎለት የኮማንድ ፖስቱ ደህንነትን ተገን ያደረገዉ ዉሳኔ በ8 የመከላከያ አባላቱ ላይ እርምጃ እንዲወሰድ በማዘዙ፣ ትናንት በ11/03/2009 በመላዉ ሐገሪቱ የተነሳዉን ህዝባዊ እንቢተኝነት ይደግፋል ያደራጃል የተባለዉ የመካከለኛዉ እዝ ባልደረባ የም/መቶ አለቃ አለበል ትእዛዙ የዉሳኔዉ ሰለባ ሲሆን በተጨማሪ ከሰሜን እዝ ወታደራዊ መምሪያ ክፍል ወታደር ቅጣው ቢያድግልኝ ላይ እርምጃ ተወስዶባቸዋል።

Friday, November 18, 2016

ጎሠኛነት በባዶ ሜዳ (ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም)

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

Mesfin Woldemariam በተለያዩ የኢትዮጵያ አንገብጋቢ ጉዳዮች ላይ ሁሉ የሚደረገው ውይይትና ክርክር እንደተጠናቀቀ ተቆትሮ የአማራና የኦሮሞ ጎሠኛነት ትልቁ አንገብጋቢ ጉዳይ እየሆነ ነው፤ (ስለኢትዮጵያ ለማያውቅ ሰው በኢትዮጵያ ውስጥ ከጠሩና ከጸዱ አማራና ኦሮሞዎች በቀር በአገሪቱ ውስጥ ሌላ ሰው ያለ አይመስልም!) ጎሠኛነት ጉዳያችን ያልሆነው ኢትዮጵያውያን የዳር ተመልካች መሆኑ እየሰለቸን ነው፤ ምንም እንኳን አማራና ኦሮሞ የተባሎት ጎሣዎች በብዛት ከሁሉም ቢበልጡም ከሰማንያ በላይ የሚሆኑ ጎሣዎች እንደሌሉና በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ቃል እንደሌላቸው ተደርጎ የሚጎነጎነው የሚስዮናውያንና የስለላ ድርጅቶች ታሪክ ለኢትዮጵያውያን ባዕድ ነው፡፡

Thursday, November 17, 2016

የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮች በቃፍታ ሁመራ ከሕወሃት ሰራዊት ጋር እየተፋለሙ ነው

Patriotic Ginbot 7 fighters attacked TPLF
የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮች ከሕወሃት ሰራዊት ጋር ከፍተኛ ውጊያ ሲያደርጉ ውለው ከርሰሌት በምትባል ቦታ የሚገኘውን የአደባይ ተራራን ተቆጣጥረዋል።

Monday, November 14, 2016

ኢትዮጵያን የሚጠቅማት ”እኛ” እና “እነሱ” ሳይሆን “እኛ” ብቻ ነዉ (ኤፍሬም ማዴቦ)

ኤፍሬም ማዴቦ
Ephrem Madebo with Patriotic Ginbot 7 fightersእንደኔ አንዴ ሲቆጥቡት አንዴ ሲደብቁት በድንገት ዕድሜያቸዉ ወደ ሃምሳዎቹ የገባ ሰዎች አንድ የምንጋራዉ እምነት አለ- እሱም የኢትዮጵያ ፖለቲከኞች አንድ ነገር መጀመር እንጂ መጨረስ አያዉቁበትም የሚል እምነት ነዉ። በፍጹም ሊፈረድብን አይገባም። ከልጅነት ወደ አዋቂነት የደረስነዉ ጥንስስ ሲጠነሰስ እንጂ እንጄራዉን ሳናይ ነዉ። ፓርቲ ሲፈጠር እንጂ ዉጤቱን ሳናይ ነዉ። የፖለቲካ ህብረቶች ተፈጥረዉ ፈረሱ ሲባል ነዉ እንጂ እንዲህ አደረጉ ሲባል ሰምተንም አይተንም አናዉቅም። ባጠቃላይ የፖለቲካ ትግል ሲባል ነዉ እንጂ ድል ሲባል ሰምተን አናዉቅም። ድል የረጂም ግዜ ትግል ዉጤት እንደሆነ ይገባናል፥ ሆኖም ግን ዛሬ የሚረግጡን ሰዎች በረሃ ገብተዉ አዲስ አበባን እሲኪቆጣጠሩ ድረስ የወሰደባቸዉን ግዜ ሁላችንም የምናስታዉሰዉ ይመስለኛል። እኔ ይህንን ሁሉ ጉድ በአይኑ እያየ ያደገ ትዉልድ አካል ነኝ። ግን ይህንን ዕድሜ ልኬን ሲደጋገም ያየሁትን የአገሬን በሽታ መድሐኒት እፈልግለታለሁ እንጂ “ከመሳሳት እራሴን ላድናት” እኔን ምን አገባኝ የ”እነሱ” ጉዳይ ነው ብዬ እጆቼን አጣጥፌ አልቀመጥም። ጉዳዩ የኔ ነዉ . . .. ጉዳዩ የኛ ነዉ። “እነሱም” “እኛም” አንድ ላይ “እኛ” ነን። ሰዉ የመሆኔ ትልቁ ሚስጢር የሚነግረኝ በአካባቢዬ ካሉ ሰዎች ዉጭ መኖር የማልችል ማህበራዊ ፍጡር መሆኔን ነዉ። አንዳንዶቻችን መሳሳትን እንደ ጦር እንፈራለን፥ መሳሳትን ፈርተን እጃችንን አጣጥፈን ከምንቀመጥ እየተሳሳትንና ከስህተታችን እየተማርን የምንሰራዉ ስራ ነዉ አገራችንን ነጻ የሚያወጣት። ስለዚህ በእኔ እምነት ምንም ይሁን ምን ከኢትዮጵያ ፖለቲከኞች የሚጠበቅ ምንም ነገር የለም ብለን እጅና እግራችንን አጣጥፈን መቀመጡ የበሽታ ምልክት ነዉ እንጂ የጤንነት አይመስለኝም።

Thursday, November 10, 2016

“አዲስ አበባ ሆይ! አስር ጋሽ ቆፍጣናው እና ሁለት እያዩ ፈንገሶች ይኑሩሽ!!”

ኤርሚያስ ለገሰ
Ethiopian comedian, Eyayu Fungusእሁድ አመሻሽ:: በፈረንጆቹ አቆጣጠር ታህሳስ 06 ቀን 2016:: የአሜሪካን ክረምት የገባ የማይመስል ብርሃናማ ቀን ነበር። የዋሽንግተን ዲሲና አከባቢዋ ነዋሪ የሆንን ኢትዮጵያውያን በኮሎምቢያና 16ኛው ጎዳና መገጣጠሚያ ላይ በሚገኘው (ኮሎምቢያ ሃይት የትምህርት ማዕከል) የማይቀርበት ቀጠሮ ይዘናል። ወደ አደራሹ የምንሄደው የጣይቱ የባህልና የትምህርት ማዕከል ከሌሎች አገር ወዳጆች ጋር በመሆን ከኢትዮጵያ ያስመጡትን ቴያትር ለማየት ነበር። አብሬአቸው የምሄደው የቅርብ ወዳጆቼ የቴያትሩ ደራሲ እና ተዋንያን ጋር የቀረበ ግንኙነት ያላቸው በመሆኑ፤ ዘወትር ስለ ቴያትሩ ሲነግሩኝ የማዳምጣቸው ጆሮዬን እንደ ጥንቸል አቁሜ ነበር። በተለያየ ጊዜ ወግ ቢጤ ስንጭር ወደ ስደት ከመምጣታቸው በፊት ከአምስት ጊዜ ያላነሰ ተመላልሰው ቴአትሩን እንደተመለከቱት ሲያጫውቱኝና ከድራማው እየቀነጨቡ አባባሎችን ሲያጎኑት እኔ ቴያትሩን ባለመመልከቴ መንፈሳዊ ቅናት ያድርብኝ ነበር። “ማነው እያዩ ፈንገስ?…..ማነው ጋሼ ቆፍጣናው?” እያልኩ እራሴን እጠይቅ ነበር። በእያዩ ፈንገስ ፌስታል ውስጥ የተዶለተው ሰምና ወርቅ ምን እንደሆነ ለማወቅ መሻቱ ነበረኝ። “ሜዳ ጠፋ ተብሎ ተራራ የሚናድበት ሃገር” አይነት ፍርድና ቅጣት እየተሰጠ እንደሆነ በቴያትር ሲገለጥ ለማየት ፍላጎት ያሳድራል።

Monday, October 31, 2016

Sunday, October 30, 2016

ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ያደረጉት ጥሪ በመከላከያ ሰራዊቱ ዘንድ ከፍተኛ ተደማጭነትን እያገኘ መምጣቱ ታወቀ!

ናትናኤል ኃይለማርያም
4814177_7
የአርበኞች ግንቦት ሰባትሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሀኑ  ለመከላከያ ሰራዊት አባላት፣የፌደራለ እና የክልል ፖሊስ አባላት፤ለአጋዚ ልዩ ጦር አባላት እና ለሌሎች ስርአቱ ታጣቂዎች ያደረጉት  ጥሪ  በሰራዊቱ ዉስጥ ከፍተኛ መነጋገሪያ  ከመሆኑም በተጨማሪ ሰራዊቱ ከህዝብ ጋር ለመቆም የመጨረሻ ዉሳኔ ላይ እንዲደርስ ያደረገዉ ጥሪ ነዉ ሲሉ እነዚሁ ምንጮች ጠቅሰዋል።የተደረገዉን ጥሪ መቀበላቸዉን ለማመላከት ሀሳባቸዉን የገለጹት የሰራዊቱ አባላት እንዳሉት “ መከላከያዉ የህዝብ ሳይሆን የህዉሀት ቡድን አገልጋይ እየሆነ መምጣቱን ሙሉ በሙሉ ያወቁበት ደረጃ ላይ መድረሳቸዉን እና ሊቀመንበሩ እንዳሉት ሰራዊቱ የቁም እስረኛ ሲሆን በተለይ ህዝባዊ እምቢተኝነቱ ከተጀመረ ጀምሮ ምን እንደሚያደርግ እና ወዴት እንደሚሄድ የጠራ አቅጣጫ ባለማግኘቱ እና ባለበት ከፍተኛ ጫና የተነሳ አማራጭ በማጣት በሰራዊቱ ዉስጥ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

Saturday, October 15, 2016

የአርበኞችግንቦት 7 ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መግለጫ


የአርበኞችግንቦት 7 ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መግለጫ
October 14, 2016
ጥቅምት 1 ቀን 2009 ዓ.ም.
የአርበኞች ግንቦት 7 ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባውን ከመስከረም 28 እስከ ጥቅምት 1 ቀን 2009 ዓ.ም. አካሂዶ በወቅቱ የአገራችን ሁኔታዎች ተነጋግሮ ውሳኔዎችን አሳልፏል፤ ሠራዊቱንም አነጋግሯል።
ሥራ አስፈፃሚው የአገራችን ፓለቲካዊ ሁኔታዎች በፍጥነት እየተለዋወጡ መሆኑና ተከታታይነት ያለው ወቅታዊና ውጤታማ አመራር መስጠት የሚገባ መሆኑ አጽንዖት ሰጥቶበታል። እንደ ሥራ አስፈፃሚው እምነት፣ በአገራችን የተለያዩ አካባቢዎች የተቀሰቀሰው ሕዝባዊ እምቢተኝነት በህወሓት የአገዛዝ ዘመን ደርሶ ወደማያውቅበት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል። ሕዝብ ለሚያቀርባቸ ጥያቄዎች ሁሉ ምላሹ ጥይት፣ እስርና ጉልበት የሆነው የህወሓት አገዛዝ በሚሰጣቸው ፋሽታዊ ምላሾች ሳቢያ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎቻችንተሰውተዋል፤ በአስር ሺዎች የሚገመቱት ደግሞ ለእስር ተዳርገዋል። በዚህም ምክንያት ለውጥ ፈላጊው ሕዝብ ሕዝባዊ እምቢተኝነት ከሕዝባዊ አመጽ ጋር ለማቀናጀት ተገዷል፤ ሰላማዊ ዜጎች ራሳቸውን ለመከላከል መሣሪያ ለማንሳት ተገደዋል። ለፖለቲካ ችግሮች ፖለቲካዊ መፍትሄ ከመስጠት ይልቅ ችግሩን በኃይል እወጣዋለሁ ብሎ እየሄደበት ያለው መንገድ ፈጽሞ እንዳይሳካ ማድረግና ይልቁንም ውድቀቱን የሚያፋጥን እንዲሆን ማድረግ የንቅናቄዓችን የጊዜው አብይ ተግባር መሆኑን ሥራ አስፈፃሚው አምኖበታል።ይህን እውን ለማድረግድርጅታችን የሕዝቡን ትግል በአግባቡ ማቀናጀትና መምራት ቀዳሚ ሥራው እንደሆነ የአርበኞች ግንቦት 7 ሥራ አስፈፃሚ ስምምነት ላይ ደርሷል።

Friday, October 14, 2016

ከሰሞኑ አስደናቂ የፕሮፖጋንዳ ዘመቻዎች ሁለቱ !

Tadesse Biru Kersmo
ከሰሞኑ አስደናቂ የፕሮፖጋንዳ ዘመቻዎች ሁለቱ !
1. በ1997 ምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የአመጽ አማራጮችን ሁሉ ይቃወም የነበረው ሰላማዊ ታጋይ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ አሁን የአመጽ ጥሪ ማቅረቡ በንጽጽር እየቀረበ ትናንት “ሰላምን በመስበክ ሲያሞኘን የነበረ ሰው ዛሬ ይኸው በይፋ ጦርነት አወጀብን” እያሉን ነው። በህወሓት ፕሮፖጋንዲስቶች ትንተና መሠረት፣ ይህ የአቋም ለውጥ የመጣው ስልጣን ፈላጊ ስለሆነ ነው።
ፕ/ር ብርሃኑ ከመነሻው የትጥቅ ትግል አማራጭን አለመስወዱ፤ ለሰላማዊ ትግል እድል መስጠቱ፤ በሰላማዊ መንገድ ታግሎ ለውጥ ለማምጣት በሙሉ እምነትና ጉልበት መንቀሳቀሱ ያስመሰግነዋል እንጂ እንዴት ሊያስወስቅሰው ይችላል? ትንሽ የማሰላሰል ችሎታ ያለው ሰው “ለመሆኑ በ 1997 ምን ሆነ? ከ 1997 በኋላ የዚህን ሰው አቋም የሚያስቀይር ነገር ምን ተፈፀመ?” ብሎ አይጠይቅም ብለው ለማመን እንዴት ቻሉ?
ምርጫ 97 ለፕ/ር ብርሃኑ ያረጋገጠለት ህወሓት በሰላማዊ ምርጫ ስልጣን እንደማይለቅ ነው። ባይሆን “በ97ስ እንዴት በምርጫ ይለቃል ብሎ አመነ?” ቢባል እንኳን ትንሽ ወግ ያለው ጥያቄ በሆነ። ይኸ ጥያቄም ብዙ ጊዜ ተጠይቆ መልስ ሰጥቶበታል “ወያኔ በሰላም ለመልቀቅ ተፈጥሮው አይፈቅድለትም ከሚል ነቢባዊ ውሳኔ በተግባር ተፈትኖ የሚሰጥ ውሳኔ ይሻላል” ዓይነት ምላሽ ሲሰጥ ብዙ ጊዜ ሰምቸዋለሁ።
ይኸ ጉዳይ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ታህሳስ 4 ቀን 2002 ዓ. ም. (December 10, 2009) የኖቤል የሰላም ሽልማት ሲቀበሉ ያደረጉት ንግግር ያስታውሰኛል። እንዲህ ብለው ነበር።
“እውነቱን በመቀበል እንጀምር − ብጥብጥ ያለበት ቅራኔን በእኛ እድሜ ማስቀረት አንችልም። ለወደፊቱም ሕዝቦች − በግልም ሆነ በጋራ − ኃይልን መጠቀም አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን ከሞራል አንፃርም ተገቢ የሚሆንበት ሁኔታ ይኖራል። ... አንሳሳት! ክፋት በዓለም ላይ አለ። በሰላማዊ ትግል ሂትለርን መግታት አይቻልም ነበር። ... አንዳንዴ ጉልበት መጠቀም ያስፈልጋል ማለት ከሃቅ የራቀ ምፀት አይደለም፤ ይልቁንስ ታሪክን በቅጡ መረዳት፤ የሰውን ልጅ ድክመቶችን ማወቅ እና የምክንያታዊነት ውስንነትን መገንዘብ ነው። ... ሰላም ተመራጭ መሆኑ መታመኑ ብቻውን ሰላምን ለማስገኘት አይበቃም።”

Wednesday, October 12, 2016

ለመለስ የተፃፈ ደብዳቤና የመለስ መልስ

ፍቃዱ ጌታቸው ለመለስ ወለላዬ ለመለስ መልስ

meles-z


ከፍቃዱ ጌታቸው ለመለስ
እንደምን አለህ ጋሼ እንደምን ነህ መለስ
ትመጣለህ ስንል ቀረህ ሳትመለስ
እኛማ ይሔውልህ
ባንተ ሌጋሲና ባንተ ትልቅ ራዕይ
በየአደባባዩ እንላለን ዋይ ዋይ
ዛሬም ጀነራልህ ተኩስ ነው ትዕዛዙ
ወገን ያጋድማል የግፍ አፈሙዙ
ለምንድን ነው ስንል ስምክን አስቀድመው
ከክርስቶስ በላይ ምስልህን አትመው
ቅዱስ መጽሐፍ ይመስል
ባንተ ራዕይና በሌጋሲህ ምለው
ቢረፈርፉንም አላለቅንምና
ደብዳቤ ላክንልህ ከሞት የተረፍነው!

ህወሃት “አስከሬን ልግዛችሁ” አለ!

የኦሮሚያ 2.4 ቢሊዮን ብር የት ገባ?

blood birr

በሙት መንፈስ አገር እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በይስሙላነት ባስቀመጠው ፕሬዚዳንት አማካኝነት ፓርላማ ብሎ በሰየመው የራሱ ስብስብ በኢትዮጵያ ያለ አንዳች ልዩነት ለገደላቸው ወገኖች አስከሬን መግዣ ብር ሰይሜአለሁ ብሏል፡፡ ከዚህ በፊት በኦሮሚያ ላፈሰሰው መድቤአለሁ ያለው 2.4 ቢሊዮን ብር እስካሁን የት እንደገባ አይታወቅም፡፡

“ህወሃት በእስረኞች ላይ አጥንት የሚያመነምን መርዝ ይጠቀማል” እማኝ

"የባዮሎጂካል መሣሪያ ጥቃት ነው፤ ቤተሰብ ለልጆቻችሁ ድረሱ"

bio-bone

በኢትዮጵያ እስረኞች አጥንትን ቀስ በቀስ በሚያፈርስ መርዝ እየተጠቁ መሆኑን ታውቁ ኖሮዋል?
ከጥቂት ዓመታት በፊት የግንቦት ሰባት መሪዎች እና አባላት መታሰራቸው ይታወሳል። ብዙዎቹ ቃሊቲ የሚገኘው እስር ቤት ነበሩ። በእስር ቤት እያሉ በደረሰባቸው ያልታወቀ ሕመም ምክኒያት ሕይወታቸውን ያጡ መሪዎችም ነበሩ።ታዲያ አንዴ ከሜክሲኮ ወደ ሃያሁለት በታክሲ ተሳፍሬ ስሔድ በግምት የሃያ ዓመት ዕድሜ ያለው ልጅ ታክሲው ውስጥ ገብቶ አጠገቤ ተቀመጠ።

Tuesday, October 11, 2016

ኢንጂነር ይልቃል ታሰሩ

(ዘ-ሐበሻ) የሰማያዊ ፓርቲን እስከባለፈው ሳምንት ድረስ ሲመሩ የቆዩት ኢንጂነር ይልቃል መታሰራቸው ተሰማ:: ከርሳቸው ጋር አብረው ሌሎች የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች መታሰራቸው ተሰምቷል::
መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አውጥቻለሁ; እየታደስኩኝም ነው ባለ ማግስት ተቃዋሚዎችን እየጠራረገ ማሰሩን ተያይዞታል::
hiber-radio-interview-with-eng-yilkal-getnet.jpg
ከኢንጂነር ይልቃል በተጨማሪ አቶ ወረታው ዋሴ; ወይንሸት ሞላ እና ብሌን መስፍን እንዲሁም እያስጴድ ተስፋዬ በተለያዩ ቦታዎች በደህንነቶች ተይዘው መታሰራቸውን የዘ-ሐበሻ ምንጮች አስታውቀዋል::
ሰማያዊ ፓርቲ ባለፈው ሳምንት ባደረገው ጉባኤ ኢንጂነር ይልቃልን ከሊቀመንበርነት ማንሳቱ ይታወሳል::

Monday, October 10, 2016

ህወሃት/ኢህአዴግ ዕድሜዬ ከ6 ወር አይበልጥም አለ

"ህወሃት የመቀበሪያ ጉድጓዱን በጥልቅ የቆፈረበት አዋጅ ነው"

soilders

ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም የሚገዛው ህወሃት ላለፉት 25ዓመታት መብት በገፍ ሲሰጥ የቆየ ይመስል ህገመንግሥታዊ መብቶችን የሚገፍ ያስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጇል። አዋጁ ለስድስት ወር ይቆያል ማለቱ የህወሃት ዕድሜ ከስድስት ወር እንደማይቆይ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል፡፡

Thursday, October 6, 2016

አዲስ አበባ ተቆላልፋለች – ፖሊስ እና ሰራዊቱ በሕዝብ ላይ አልተኩስም ብለዋል (ወቅታዊ ሪፖርታዥ)

ክንፉ አሰፋ 
መግቢያ የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ብሄራዊ እርቅ እና ድርድር እንዲደረግ ጥሪ ማድረጉ ይታወሳል። አምስቱ የሕወሃት ቁንጮዎች ትእቢት የተሞላበት ምላሽ ነው የሰጡት። ከድርድር ይልቅ ከሕዝብ ጋር ጦርነት መግጠምን መርጠዋል።

Soldiers in Addis Ababa, Ethiopia አብዛኛው የፖሊስ እና የሃገር መከላከያ ሰራዊቱ “ሕዝብ ላይ አልተኩስም” ማለታቸው የህወሃት አመራርን ጭንቅ ውስጥ አስገብተውታል።

 አዲስ አበባ ተቆላልፋለች። በአራቱም አቅጣጫ በኩል የሚገባም የሚወጣም የለም።  መንገዶች በሙሉ ተዘጋግተዋል።  ስልክ እና ኢንተርኔት ጠፍቷል።

 በአዲስ አበባ ዙርያ ባሉ ከተሞች ሰኞ መስከረም 23 ቀን የተጀመረውን ሕዝባዊ አመጽ ለማዳፈን በህወሃት የተወሰደው የአፈሳ እርምጃ አመጹን አላቆመውም። ሰኞ ማምሻውን በሺዎች የሚቆጠሩ ዘጎች ታፍሰው ወዳልታወቀ ስፍራ በወሰዳቸው ሳብያ አመጹ በዛሬው እለት ተባብሶ ቀጥሏል።  የአካባቢ ፖሊሶችም ከሕዝብ ጋር በመሆን በአመመጹ እየተሳተፉ በመሆኑ የስራአቱን ቁንጮዎች ጭንቀት ውስጥ ከቷቸዋል።

Tuesday, October 4, 2016

በሕዝብ አቆጣጠር አሁን ሁሉም ነገር አበቃ ህወሃት - ቄጤማና ቅጠል የያዘን ህዝብ ረሸነ


irreecha74
irreecha55
ዛሬ ጨለሞ ዋለ። ዛሬ አገር ማቅ ለበሰች። ዛሬ የሆነውን ማመን ይከብዳል። ቄጤማና ቅጠል ይዘው የወጡ ሰላማዊ ዜጎች በጅምላ ተረሸኑ። “Down! Down! Woyane … Down! Down TPLF! …” በማለት ቁጣውን የገለጸ ሕዝብ እገዛሃለሁ በሚለው የትግራይ ህዝብ ተገንጣይ ቡድን (በህወሃት) ተጨፈጨፈ። ከአየርና ከምድር ጭስና ጥይት የተረጨበት ህዝብ፣ የሚገባበት ጠፍቶት የውሃ ራት ሆነ። ሞተ። ቆሰለ። በውሃ ተበላ።

“አሁን ደም ተቃብተናል፤ ዕርቅ የለም፤ ሌላ ሳይከተል ልቀቁልን”፤ “ከህወሃት ጋር ድርድርና እርቅ ብሎ ነገር የለም” የሕዝብ ምላሽ ሃይለማርያም ውረድ ተባለ!


irreecha79
ኦሮሚያ ብቻ ሳትሆን ድፍን አገርን ማቅ ያለበሰው የጅምላ ጭፍጨፋ እያደር አጥንት የሚያደቅ መረጃ እየወጣበት ነው። ህወሃት የእርቅ መንገዶችን በሙሉ አሟጦ የቀበረበት ይህ “ይቅርታ የሌለው ወንጀል” እስካሁን የ678 ንጹሃንን ህይወት አጥፍቷል። የትዳር ጓደኛውን አስከሬን በግል ተሽከርካሪ ጭኖ እያነባ ወደ ቤተሰቡ የወሰደ አለ። ገንዘብ ተዋጥቶለት የሚስቱን አስከሬን ጭኖ ወደ ሱሉልታ የተጓዘ መኖሩ ተሰምቷል። እናትና ልጅ ባንድነት ቀብራቸው ተከናውኗል። በአንድ ቀን ሁለት ወይም ከዚያ በላይ ወገኖች ከቤተሰባቸው ጎድለዋል። አስከሬን አሁን ድረስ እየተቆፈረ እየወጣ ነው። ሃይቅ ላይ የተንሳፈፉ አስከሬኖች እየተለቀሙ ነው። ህዝብ ቁጣው ገንፍሎ በተለያዩ ስፍራዎች እምቢተኛነቱን እየገለጸ ነው። ህወሃት ግን አሁንም ይዋሻል።

በሰበታ፣ ዓለም ገና፣ በፉሪና አየር ጤና የሕዝብ ቁጣ ገነፈለ – የትግራይ ነጻ አውጪ ወታደሮች እየተኮሱ ነው

(ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ ዙሪያ ባሉት በሰበታ፣ ዓለም ገና፣ በፉሪና አየር ጤና ሕዝብ ግልብጥ ብሎ አደባባይ በመውጣት በመንግስት ላይ ተቃውሞውን በማሰማት ላይ መሆኑ ተሰማ:: ለዘ-ሐበሻ የመጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት በነዚህ ከተሞች የንግድ እንቅስቃሴዎች ቆመዋል::: ሕዝቡን ለመበተን የትግራይ ነጻ አውጪ ወታደሮች እየተኮሱ መሆኑ ተሰምቷል::
14591847_1848685248699812_7965544009936441995_n
በቅድሚያ በፉሪ የጀመረው ተቃውሞ ወደ አየር ጤና የተዛመተ ሲሆን ዓለም ገና እና ሰበታም በሕዝብ ተቃውሞ እየተደበላለቁ ይገኛሉ::
ከፉሪ እስከ ጆሞ ድረስ የፌደራል እና የኦሮሚያ ክልላዊ ፖሊስን ዩኒፎርም የለበሱ የትግራይ ነጻ አውጪ ወታደሮች እንደወረሩት ሲሰማ ሕዝቡን ለመበተንም ተኩስ ከፍተዋል::
በፉሪ ሱቆች እና ካፌዎች በአጠቃላይ ንግድ እንቅስቃሴ መቆሙም ተዘግቧል:: ጆሞ አካባቢ ልጆቻቸውን የሚያስረምሩ ወላጆች ወደ ትምህርት ቤት በመሄድ ልጆቻቸውን እያወጡ ሲሆን በነዚህ አካባቢዎች ትራንስፖርት መቆሙም ታውቋል::

Saturday, October 1, 2016

“ኦጋዴን፤ የኢትዮጵያ [የህወሃት] ድብቅ ኃፍረት”

“አንዳችሁንም አናስተርፍም፤ እንጨርሳችኋልን” የህወሃት ነፍጠኞች

Ogaden 15
ሰዎችን እንደ እህል በዘር ጆንያ እየሠፈረ በፈለገበት ሣጥን ውስጥ ማስገባት ዓላማው የሆነው የትግራይ ሕዝብ ነጻአውጪ ግምባር (ህወሃት)፤ በኦሮሞ ተቃውሞ #oromoprotest እና በአማራ ተጋድሎ #amhararesistance የተነሳውሕዝባዊ እምቢተኝነት ዕንቅልፍ ስለነሳው በተለይም ደግሞ የሁለቱ በኅብረት መቆም ኅልውናው ላይ አደጋ ስለጣለበት ሶማሊና አፋር ክልል መንጎዳጎድ ጀምሯል፡፡

Thursday, September 29, 2016

የህወሃት መከላከያ ሰራዊት እጁን እየሰጠ ወደ ኤርትራ እየገባ ይገኛል

በልኡል አለም ሰበር መረጃ ! !
Ethiopian Soldiers ከምእራብ ትግራይ ወደ ኡምሃጅር የተወረወረ የህወሃት መከላከያ ሰራዊት የግንባር ጦር በገጠመዉ ድንገተኛ የተኩስ ልዉዉጥ ምክንያት እጁን እየሰጠ ወደ ኤርትራ እየገባ ይገኛል። ከሰሜኑ እዝ ከመከላከያ አባላቱ ዉስጥ ያፈተለከዉ መረጃ እንደሚጠቁመዉ ከሆነ የመዋጋት ፍላጎት የሌላቸዉ የህወሃት ወታደሮች በትናንትናዉ እለት ወደ አል-ፉሽቓ (Al fushqa) ሱዳን ድንበር በኩል አምርተዉ ለነጻነት ታጋዮች እጃቸዉን መስጠታቸዉ ታዉቋል። ብዛት ያላቸዉ ቀላልና ከባድ የጦር መሳሪያዎች በምርኮ መግባታቸዉንና የህወሃት መከላከያ ሰራዊት አባላትም መቀላቀላቸዉን የገለጸልን ምንጫችን በምርኮ የሚገቡትን ወገኖች የኤርትራ ወታደሮች ወደ መደበኛ ማረፊያ ማዘዋወራቸዉን ምንጮች አረጋግጥጠዋል፡፡ 
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !

Thursday, September 22, 2016

በአልሞ ተኳሽ እና በመሬት ስርቆት የታወቀው ህወሓት ለኢትዮጵያ አደጋ ተጠያቂ ነው – አክሎግ ቢራራ (ዶር)

አክሎግ ቢራራ (ዶር)
“እኛ ጠንካራ ለመሆን የምንችለው በመተባበር ብቻ ነው፤ በተጻራሪው፤ እኛ ደካማ የምንሆነው በመከፋፈል ነው።” ጀሪ ሮሊንግ፤ የቀድሞው የጋና ፕሬዝደንት
Ethiopia's killing squadዛሬ ግብጾች ስለ ኢትዮጵያ ያወጡትን ዘገባ ስሰማ ከዚህ በፊት ስለ ተሃድሶ ግድብ በተከታታይ ያቀረብኳቸውን ትንተናዎችና ማስጠንቀቂያዎች አስታወሰኝ። በአጭሩ ያሳሰብኩት ህወሓት/ኢህአዴግ የኢትዮጵያን ሕዝብ ከፋፍሎና አፍኖ ይህን ለዚህ ግድብ ዋስትና ሊሰጥ አይችልም የሚል ነው። መጀመሪያ፤ ህወሓት ለራሱ የበላይነት በማሰብ ብቻ፤ ታላቋን ትግራይን ለመፍጠር ባለው ህልም ብቻ፤ ኢትዮጵያን በፈጠራ የሕዝብ ስርጭት ከፋፈላት፤ መተከልን ወደ ቤን ሻንጉል፤ ብዙ የጎንደርና የወሎ አማራ መሬቶችን ምንም ውይይት ሳይደረግ፤ ፓርላማው ሳያውቅ ወደ ታላቋ ትግራይ ቀላቀለ። የትግራይ ወሰን በአንድ ጊዜ ሱዳንን አካለለ፤ ወደ ደቡብ ሄዶ ቤን ሻንጉል ደረሰ። ታላቁን የተሃድሶ ግድብ ለአደጋ በሚያመች ሁኔታ ወደ ወዳጁ ሰሜን ሱዳን አስጠጋው። የግድቡ የውሃ ፈሰስ ለሱዳኖች እንዲጠቅም አደረገ፤ አደጋውን ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲሸከም ወሰነ።

ብራቮ ሸገሮች፣ ብራቮ ጋዜጠኛ ሕይወት ፍሬ ስብሐት!!

በፍቅር ወርቁ
Addis Ababa University, Ethiopiaመንግሥት ከሰኞ ጀምሮ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራንና የአስተዳደር ሠራተኞች ጋር የጀመረውን ውይይት በተመለከተ እየሰጣችሁን ያለው መረጃ እጅግ ሚዛናዊና የተብራራ ነው። የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን በሚያሳዝን ሁኔታ ስብሰባው በእጅጉ የተሳካና ያለ ምንም እንከን/ተቃውሞ እየተካሄደ እንዳለ ነው የዘገቡትና እየዘገቡት ያለው …።
ለአብነት ያህል ከሸገር ሬዲዮ ወጪ በመንግሥት ስር የሚገኙትም ሆነ የግሎቹ ኤፍ ኤም ሬዲዮኖች በስብሰባው የመጀመሪያ ቀን መንግሥት ለስብሰባው አጀንዳ ይሆን ዘንድ ባሰራጨው ሰነድ ላይ ፈጽሞ ለእኛ የማይመጥንና አገሪቱ ካለችበት ወቅታዊ ፖለቲካዊ ትኩሳትን ከግምት ውስጥ ያስገባ ባለመሆኑ በሚል- በተቃውሞ ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የስብሰባው ተሳታፊ ምሁራን አዳራሹን ለቀው እንደወጡ የዘገበው የሸገር ሬዲዮ ብቻ ነው። በአጠቃላይ ከጅማሬው ቀን ጀምሮ የስብሰባውን ድባብ በሚዛናዊ መልኩ መረጃዎችን ለሕዝብ እያቀረባችሁ ነውና ሸገሮች ምስጋና እና አድናቆት ይገባችኋል። ለዚህ ለዛሬው የቁጭት ስሜት ለተቀላቀለበት አስተያየቴ ምክንያት የሆነኝ ግን፤

Thursday, September 1, 2016

የሕወሃት ብጥብጥ እና ሽሽት- ከውስጥ አዋቂ ምንጭ (ክንፉ አሰፋ)

ክንፉ አሰፋ
Ethiopia, TPLF officialsሕዝባዊ አመጹ ያመጣውን ቀውስ ተከትሎ በህወሃት ከፍተኛ አመራር ውስጥ ከፍተኛ መበጣበጥ እና የርስ-በርስ ፍጥጫ መከሰቱን ከታመነ የውስጥ አዋቂ ምንጭ መረጃ ደርሶናል። 
“Whoever sows injustice will reap calamity.”
“አመራሩ ክፉኛ ከመከፋፈሉ የተነሳም የርስበርሱ ችግራቸው ላይ ተወጥረዋል።” ይላል መረጃው። ቀንደኞቹ የህወሃት አባላት ስርዓቱ እንዳበቃለት ስለተገነዘቡ ንብረት እና ልጆቻቸውን በማሸሽ ላይ ናቸው።
ሕዝቡ ሁሉ እንደተፋቸው በግልጽ እየነገራቸው ስለተገነዘቡ፤ የህወሃት የደህንነት አባላት ሕዝቡን ተተው የራሳቸውን ሰራዊት እና ፌደራል ፖሊስ አባላት እንዲሰልሉ ተነግሯቸዋል። “ተጠርጣሪ” የኦህዴድ እና ብአዴን አባላት በነዚህ ሰላዮች ስለተከበቡ በፍርሃት መወጠራቸውን ከራሳቸው አንደበት እየተሰማ ነው።

Wednesday, August 31, 2016

ሰበር ዜና! የትግራይ ወጣቶች በተጠንቀቅ እንዲቆሙ ትእዛዝ ተሰጠ


የትግራይ ወጣቶች በተጠንቀቅ እንዲቆሙ ትእዛዝ ተሰጠ 
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አባይ ወልዱ እና ከፍተኛ የህወሓት ሹማምንቶች እምነት የሚጣልባቸው የፓርቲው ወጣት አባላትን ስብስበው ጠንካራ ትእዛዝ አስተላለፉ::

አገዛዙ በዐማራ ሕዝብ ላይ ይፋ ጦርነት አውጇል፤ በባሕር ዳር የሰባታሚት ማረሚያ ቤት ዐማሮች በጅምላ ተቀብረዋል


ዐማራ ዛሬ (ነሃሴ 25 ቀን 2008 ዓ.ም) 
Muluken Tesfaw #AmharaResistance
አገዛዙ በዐማራ ሕዝብ ላይ ይፋ ጦርነት አውጇል፤ በባሕር ዳር የሰባታሚት ማረሚያ ቤት ዐማሮች በጅምላ ተቀብረዋል
• የአብራጂራ ሕዝብ የመከላከያ ታንክ ላይ ሰንደቅ ዓላማ ተከለ 
• የዐማራ ተጋድሎ ከእለት ወደ እለት እየጨመረ ሒዷል፤ የጋይንት፣ የቋሪትና ግምጃ ቤት አካባቢዎች ከጠላት ቀጣና የጸዱ ናቸው 
• የትግሬ መከላከያ ሠራዊት በወገራ አውራጃ ሕጻናትና አቅመ ደካሞች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ፈጽሟል
• የደባርቅ፣ የመተማ፣ ሸኽዲና ሽንፋ ከተሞች በቃጠሎ ታፍነው ውለዋል
• በቡሬ ትንሳኤ ሆቴል ግቢ 2 አስከሬን ተደብቆ ተገኘ
• በወንበርማ ሽንዲ ወረዳ የዐማራ ተጋድሎ ሁለተኛ ቀኑን አስቆጥሯል
• በእጅባራ ሕዝብና መከላከያ ተፋጠዋል

ሕወሃት የትግራይ ልዩ ሃይል አባላትን የአማራ ልዩ ሃይልን የደንብ ልብስ አልብሶ አማራውን እንዲጨፈጭፉ አሰማርቷል - See more at: http://ecadforum.com/Amharic/archives/16861/#sthash.4zGhse80.dpuf

Ethiopia, special force members in the Amhara region
በማኅበራዊ ገጾች እየተሰራጩ ያሉ ታማኝነት ያላቸው መረጃዎች እንደሚያመለክቱት “የአማራ ልዩ ሃይል አቋም ይዟል” ተቃውሞ በማሰማት ላይ ባሉ ወገኖቹ ላይ አልተኩስም ብሏል። ሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ሕወሃት) ይህ ነገር እጅግ አስደንግጦታል።

Tuesday, August 23, 2016

በቂሊንጦ ወህኒ ቤት ታስረው የሚገኙ እስረኞች የሶስት ቀን ብሄራዊ ሃዘን እንዲታወጅ ጠየቁ


ኢሳት (ነሃሴ 17 ፥ 2008) 
በተለያዩ ክልሎች ለዴሞክራሲ፣ ፍትህና ነጻነት ሲሉ ህይወታቸውን ያጡ ወገኖችን ለማስታወስ ኢትዮጵያውያን ከነሃሴ 19 እስከ 21 ፣ 2008 የሚቆይ የሶስት ቀን ብሄራዊ ሃዘን እንዲታወጅ በቂሊንጦ ወህኒ ቤት ታስረው የሚገኙ እስረኞች ጠየቁ። 
በአቶ በቀለ ገርባ፣ ደጀኔ ጣፋ፣ አዲሱ ቡላላ፣ ጉርሜሳ አያኖ፣ ዮናታን ተስፋዬ፣ ፍቅረማሪያም አስማማው፣ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ እና ብርሃኑ ተክለ ያሬድ በጋራ ተጽፎ ለኢሳት የደረሰው ደብዳቤ፣ “ብሄራዊ የሃዘን ቀን የሚታወጀው የዲሞክራሲና የፍትህ ጥያቄ አንግበው የተሰው ወገኖቻችንን በልባችን ውስጥ ህያው ሆነው እንደሚኖሩ ለማረጋገጥና እነሱም የወደቁለትን አላማ በትግላችን እንደምናሳካው ቃል ለመግባት እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸውም አጋርነታችንን ለማሳየት ነው” ሲል ያስረዳል። 

Sunday, August 21, 2016

ህወሃት በሕዝብ ላይ የደገሰው በዶ/ር ደብረጽዮን አንደበት

ህወሃት በሕዝብ ላይ የደገሰው በዶ/ር ደብረጽዮን አንደበት

(ክንፉ አሰፋ)
haile tplf debretsion
ባለፈው ሳምንት ጌታቸው ረዳ ከአልጃዚራ ቴሌቭዥን ጋዜጠኛ ጋር ተጋፍጦ ነበር። አንድ ጥያቄ ቀረበለት። “በራሳችሁ የምትተማማኑ ከሆነ ለምን የተባበሩት መንግስታት ታዛቢዎች እንዳይገቡ ከለከላችሁ?”
ሚኒስትር ጌታቸውም። “የተባበሩት መንግስታት አያስፈልገንም። እኛው ራሳችን ከህዝቡ ጋር እንነጋገራለን።” ሲል ነበር የድፍረት መልስ የሰጠው።

አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ቃለምልልስ ሰጠ “ከባለፉት 9 ወራት ብቻ ከ1 ሺህ በላይ ኦሮሞዎች በኢትዮጵያ ተገድለዋል – ወደዚያ አልመለስም”

 አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ በሪዮ ኦሎምፒክ በማራቶን ውድድር የብር ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ ካመጣ በኋላ እጁን ወደላይ በማጣመር መንግስትን የተቃወመው ባለፉት 9 ወራት ብቻ ከ1 ሺህ በላይ ኦሮሞዎች በመንግስት ጸጥታ ኃይሎች በመገደላቸውና በርካቶችም በመታሰራቸው ነው አለ:: አትሌቱ በቃለምልልሱ ላይ እንዳለው ወደ ኢትዮጵያ ቢመለስ ለህይወቱ አስጊ በመሆኑ ወደ ኢትዮጵያ እንደማይመለስ አስታውቋል:: ቃለምልልሱን በቭዲዮ ይመልከቱት::

Saturday, August 13, 2016

ስለ ወያኔ መውደቅ ሳስብ(ሄኖክ የሺጥላ)

ስለ ወያኔ መውደቅ ሳስብ ፥ አይኖቼ በደስታ እንባ ይሞላሉ ። እንባውን የፈጠረው ይቺን ቀን ማየት ያልቻሉትን ብዙዎች ስለማስብ ነው ። ዛሬ ጎንደር ላይም ሆነ ኦሮሚያ ላይ የተነሳው ትግል ፥ ባንድም ይሁን በሌላ መልኩ የዛሬው ደረጃ ላይ ከመድረሱ በፊት አእላፋት ህይወታቸውን ገብረውበታል ። እልፎች ታስረዋል ፥ ህልቆዎች ከስራ ፥ ከሃገር ተባረዋል ፥ ቆጥረን የማንጨርሳቸው ሊህቃኖች ተንገላተዋል ፥ ታድርደዋል ። ህፃናቶች ተገለዋል ፥ እናቶች ፀጉራቸውን ተላጭተው አሸባሪ ተብለው ታስረዋል ። ብዙዎች በርሃ ወርደዋል ፥ እጅግ ብዙዎች ሞተውለታል ፥ ብዙዎችም ሞተውበታል!

በደብረማርቆስ ንግድ ቆሟል | አልሞ ተኳሾች ብዙ ሰው አቁስለዋል

በደብረማርቆስ ንግድ ቆሟል | አልሞ ተኳሾች ብዙ ሰው አቁስለዋል
(ዘ-ሐበሻ) በጎጃም ደብረማርቆስ የተነሳውን ሕዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር አልሞ ተኳሽ (ስናይፐር) ፖሊሶችን መጠቀሙ ተሰማ:: እነዚህ አልሞ ተኳሾችም ያቆሰሏቸው ስዎች ቁጥር ከ20 እንደሚበልጥ ዘ-ሐበሻ በስልክ ያነጋገረቻቸው የደብረማርቆስ ነዋሪዎች ገልጸዋል::

በወልቃይት ጠገዴና ቃብቲያ ሁመራ ህዝብ ላይ የታቀደው ድቡቁ የህወሓት ሴራ ሲጋለጥ

A Quest for Identity and Geographic Restoration of Wolkait-Tegede, Gondar, Amhara, Ethiopia.
በቅድሚያ ይህንን ድብቅ የወያኔ ሴራ የሚያጋልጠውን ሰነድ ከነትርጉሙ የላኩልንን ወገኖች ከልብ እናመሰግናለን።

Friday, August 12, 2016

በጎጃም መንግስት ፈረሰ እየተባለ ነው

Alemnew Mekonnen
የአማራውን ሕዝብ “ልፋጫም” ብሎ የተሳደበዉና ሕወሃት ጉልበት ብቻ አመራር ላይ የተቀመጠው አለምነህ መኮንን ባረፈበት ሆቴል ድብደባ እንደተፈጸመበት መረጃዎች ይጠቁማሉ። አለመነህ በሕወሃት ታጣቂዎች ታጅቦ ሾልኮ ከአካባቢው ያመለጠ ሲሆን፣ ብዙዎች ሰዉዬው አይኑን በጨው አጥቦ በዚህ ወቅት ሕዝብ ፊት ለመቅረብ መድፈሩ አስገርሟቸዋል።
በጎጃም እነብሴ ሳር ምድር፣ቋሪት እና ሌሎች ደጋማ ቦታወች ያሉ አርሶ አደሮች መንግስት ፈርሷል የሚል ወሬ በመስማታቸው የቀበሌ ሊቀመንበር እና ፀሃፊወችን ቤታቸውን በድንጋይ እና በጥይት እንደደበደቡ እየተነገረ ነው። እስካሁን አራት የገጠር ሚሊሻወች የተገደሉ ሲሆን አቶ ቢያድጌ አለሙ የሚባል ሊቀመንበር መገደሉ ታውቋል።

የኢህአዴግ ከፍተኛ አመራሮች የመፍትሄ ያለህ እያሉ ነው


ነሃሴ  ፮ ( ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በተቃውሞ እየተናጡ ባሉት የአማራ እና የኦሮምያ ክልሎች ዙሪያ የኢህአዴግ ማዕከላዊ ኮሚቴ እና የክልል ስራ አስፈፃሚዎች እንዲሁም የፌደራል ባለስልጣናት የቪዲዩ ኮንፈረንስ  እያደረጉ ነው፤ ስብሰባው መፍትሄ ማመንጨት አልቻለም።

“ሲመረው የማይነሳ ህዝብ የለም ባለም፣” አለ አቦይ ስብሐት ነጋ! (ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
የኢትዮጵያውያን የጸደይ አብዮት በ2016 የክረምት ወቅት መጀመሩ ነውን? 
አንድ ህዝብ ታምቆ ፣ ታምቆ ማለት ተጨቁኖ  በዘመንታ አይቆይም ። ዩኒቨርሳል universal  ማለት ነው ።  አንድ ህዝብ እንደ ህዝብ መጠን  በዓለም ታሪክ  አንዳስቀመጡት አንደፈለጉት  የሚቀመጥ አይደለም። ሲመረው ይፈነዳል።  ይሄ ዓለም አቀፋዊ  እውነታ /universal  truth  ነው። ሲመረው የማይነሳ ህዝብ የለም ባለም።  በታሪክም /historically።  አሁንም።  ለወደፊትም ። (አዛውንቱ የእንጨት ሽበት ባለቤቱ አቦይ ስብሀት ነጋ፣ የዘ-ህወሀት ጭንቅላት፣ ንጉስ፣ የክርስትና አባት፣ ተጽእኖ ፈጣሪ እና የአለቆች ሁሉ አለቃ (ካቦ) እ.ኤ.አ በ2015 ከተናገረው የተወሰደ።)  (ለማዳመጥ እዚህ ይጫኑ ።)
በዘ-ህወሀት ላይ የፍርዱ ቀን ደረሰ ማለት ነውን?
Protests in Ethiopia
እ.ኤ.አ ታህሳስ 2015 “የኢትዮጵያውያን የጸደይ አብዮት በበጋው ወቅት መጀመሩ ነውን በሚል ርዕስ በኢትዮጵያ በመምጣት ላይ ስላለው የጸደይ አብዮት ትችት አቅርቤ ነበር፡፡“

Breaking News: A Breakthrough agreement between ODF and Patriotic G7

Memorandum of Understanding (MoU)
Oromo Democratic Front (ODF) and Patriotic Ginbot 7 (PG7)
lencho-leta-and-berhanu-nega
August 11, 2016

Thursday, August 11, 2016

በኢትዮጵያ ሕዝባዊ ተቃውሞዎችን ተክትሎ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ደኅንነት ሁኔት አስጊ መሆኑን ሪፕሪቭ ገለጸ

በኢትዮጵያ ሕዝባዊ ተቃውሞዎችን ተክትሎ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ደኅንነት ሁኔት አስጊ መሆኑን ሪፕሪቭ ገለጸ

ነሃሴ  ፬ ( አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከ100 በላይ ሰላማዊ ዜጎች መብታቸውን በሰላማዊ ሰልፍ መጠየቃቸውን ተክትሎ በኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይሎች መገደላቸውን ተክትሎ ላለፍት ሁለት ዓመታት ከየመን ታፍነው የተወሰዱት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የሞት ፍርድ ይፈረድባቸዋል የሚል ስጋት እንደፈጠረባቸው ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ሪፕሪቭ  አስታውቋል።

በኢትዮጵያ የሚካሄደውን ህዝባዊ ተቃውሞ የተለያዩ አለማቀፍ ሚዲያዎች ሽፋን እየሰጡት ነው።


ነሃሴ  ፭ ( አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ታላላቅ ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙሃንና የሰብዓዊ መብት ተቋማት በኢትዮጵያ በተለይ በኦሮሚያና አማራ ክልል ውስጥ የተካሄደውን የጅምላ ግድያ በስፋት አትኩሮት ሰጥተው ዘግበውታል። በዋና ከተማዋ አዲስ አበባን ጨምሮ መላውን ኦሮሚያ ክልል በጎንደርና አካባቢው በባህርዳር የተካሄዱት ሰላማዊ ሰልፎች በጸጥታ አስከባሪዎች በግድያ ምላሽ መሰጠቱን ቢቢሲ ዘግቧል። ሁለቱ ታላላቅ የአገሪቱ ብሔረሰቦች  አነስተኛ ቁጥር ባለው አንድ ብሄት በመሳሪያ ሃይል በግዳጅ መገዛታቸውንም ቢቢሲ የኢትዮጵያን ሕዝብ ቁጥር በመቶኛ ስሌት ቀመር ይዞ በመውጣት አሰነብቧል። 6.1% የሚሆኑት የትግራይ ብሔር ተወላጆች 34.4% የሚሆኑትን ኦሮሞችና 27% የሚሆኑት አማራዎች ያገለለ አስተዳደር መመስረታቸውን፣  የስልጣን፣ የሃብት፣ ወታደራዊና ደኅንነቱ በህወሃት ቁጥጥር ስር መውደቁን ቢቢሲ በመረጃ አስደግፎ ዘግቧል። የኦሮሚያ ክልልን የመሬት ቅርምትና የወልቃይት ሕዝብን የማንነት ጥያቄዎችም  ሰፊ ሽፋን አግኝተዋል።