Translate

Wednesday, September 3, 2014

ግንቦት 7 ንቅንቄ ቅዳሜ ኦገስት 30, እሁድ ኦገስት 31, እና ሰኞ ሴፕቴምበር 1, 2014 በመላው አለም ያደረጋቸው ህዝባዊ ስብሰባዎች ማሳካቱን ገልጿል።

ግንቦት 7 ንቅንቄ ቅዳሜ ኦገስት 30, እሁድ ኦገስት 31, እና ሰኞ ሴፕቴምበር 1, 2014 በመላው አለም ያደረጋቸው ህዝባዊ ስብሰባዎች ማሳካቱን ገልጿል።
በአለም 26 ከተሞችና በኖርዝ አሜሪካ በሚገኙ 6 ታላላቅ ከተሞች የተደረጉት ውይይቶች በርካታ ኢትዮጵያኖች በቦታው በመገኘት ድጋፋቸውን ያሳዩበትና የገለጹበት ሲሆን፣ ዝግጅቱ በአትላንታ፣ ቦስተን፣ቴክሳስ፣ በዋሽንግተን ዲሲ እንዲሁም በካናዳ ቶሮንቶና ካልጋሪ ተካሂዷል።
DcWashington Dc

በነዚህ ስብሰባዎች ሁሉ የግንቦት 7 ዋና ጸሃፊ የታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌ ስራዎች ሲታወሱና ሲዘከሩ ውለዋል። በሁሉም ስብሰባዎች ወያኔን ማስወገድ በሚቻልበት ስልቶችና ትብብሮች ላይ ሰፊ ውይይቶች ተደርጎባቸዋል። በታላላቁ ከተሞች ቁጥሩ በርካታ ህዝብ በተገኘበት በዚሁ ስብሰባ ማህበረሰቡ የተሰማውን ቁጭት በመለወጥ ትግሉን በማገዝና በመቀላቀል የወያኔን እድሜ ማሳጠር ወቅቱ የሚፈልገው ምላሽ መሆኑን ተሰብሳቢዎች አስምረውበታል።
oslo

Norway

ታጋይ አንዳርጋቸው ጽጌ ትግሉን ዳር ላይ አድርሶታል ከዚህ በኋላ ፍሬውን ማየት እንደሚፈልጉ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ሲገልጹ፣ ለዚህ ደግሞ ወጣቱ ትውልድ ከአበው የወረሰውን የእምቢተኝነት እና አልገዛም ባይነትን በመድገም መሰዋእትነት በመሆን ኢትዮጵያን ከአምባገነኖች ነጻ ለማውጣት የነጻነት ሃይሉን በመቀላቀል ኢትዮጵያዊ ግዴታውን መወጣት ይኖርበታል ሲሉ የመድረክ ተናጋሪዎች ተመሳሳይ የሆነ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

coloradoColorado
በዚህ ላንቺ ነው ኢትዮጵያ በተባለው የግንቦት 7 ዘመቻ በርካታ የገንዘብ ድጋፍ የተሰበሰበ ሲሆን ቁጥራቸው ቀላል የማይባል የአባላት ድጋፍ እና ትግሉን ለመቀላቀሉን የቆረጡ ምዝገባዎች መካሄዳቸውን አረጋግጠናል።


    10665667_1478626519055764_5970644406129423890_n

    No comments:

    Post a Comment