Translate

Wednesday, June 8, 2016

በዲምክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አዘጋጅነት ቅዳሜ ጁን 4 – 2016 በኖርዌይ ኦስሎ ከተማ የአርበኞች ግንቦት7 ታላቅ ህዝባዊ ስብስባ እና የገቢማሰባስቢያ ዝግጅት በተሳካ ሁኔታ ተካሄደ

በሕዝባዊ ስብሰባው ላይ ቁጥራቸው በብዙ መቶወች የሚጠጉ የንቅናቄው አባሎችና ደጋፊወች ለድርጅቱና ለመሪያችው አጋነታቸውን ለማሳየት ከኦስሎ እና ከመላው ኖርዌይ እዲሁም ከተለያዩ አገራት ተገኝተዋል በተለይም ክስቶኮልም የመጡ የድርጅቱ አባሎች ና ደጋፊወች ለዝግጅቱ ታላርትልቅ ድምቀት ስተውታል !!
የእለቱ የክብር እንግዶች
• የአርበኞች ግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት እና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀምበር አርበኛ ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ
• ፕ/ር ጌታቸው በጋሻው ከቪዥን ኢትዮጵያ
• ዶ/ር ሙሉአለም አዳም በኖርወዌይ አርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር
• ወ/ሮ ብዙአየሁ ጽጌ
Patriotic Ginbot 7 Public Meeting in Osloየእለቱ እንግዶች በተገኙበትሕዝባዊ ስብሠባው በኖሬጅያውያን የሰአተ አቆጣጠር ከቀኑ 16:15ተጀምሮ እስከ ምሽቱ 00:00 ሰዓት የተካሄደ ሲሆን የዲሞክራሲያዊ ለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ አቢ አማረ የለቱን ፕሮግራም በማስተዋወቅ ለዝግጁት ታዳሚውች እንኮን ደህና መጣችሁ በማለት ለዝግጅቱ መሳካት ክተለያየ ቦታ እርቀት ሳይገድባቸው ረጅም መንገድ ተጉዘው ለተገኙ እንግዶቻችን በድርጅታቸው ስምና ታላቅ ምስጋ ና አክብሮት ክአቀረቡ ቡሀላ የለቱ ፕሮገራም የመክፈቻ ንግግር በማድረገ አስጀምረዋል አያይዘውም በኢትዮጵያ ውስጥ በመላ የሀገራችን ህዝቦች በወያኔ አረመናዊ ስርአት በጭካኔ በግፍ ለተገደሉ እና በተለያዩ አስር ቤቶች በፖለቲካ ኣስተሳስባችው ምክንያት ያለወንጀላች የሚስቃዩ ውድ ኢትዮጵያዊን ወገኖቻችን በማስብ እንዲሁም አስቃቂ የኣካል ጉዳት ለተፈጸባቸው ኢትዮጵያዊን የአንድ ደቂቃ የህሊና ጸሎት በማስደረግ ስብሰባውን አስጀምረውታል::

በመቀጠልም የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ ሊቀመንበር አቶ ዳንኤል አበበ ፕሮግራሙን እንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ካደረጉ በኃላ በፕሮግራሙ ላይ በመገኘት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ለማበርከት ከተለያዩ ሐገሮች ለመጡት አባላት እና ደጋፊዎች ያላቸውን አክብሮት እና ምስጋና አቅርበዋል። በእለቱ ለተገኙት የክብር እንግዶችም እጅግ ጠቃሚ እና ትምሕርት አዘል ንግሮችን አድርገው እንዳለቀ ዶ/ር ሙሉ አለም አዳም ፕሮግራሙን መሪ መድረኩ አስጀምረውታል።
በዝግጅቱም ላይ በእንግድነት ከተጋበዙት የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ፕሮፈሰር ብርሀኑ ነጋ ከኤርትራ በረሃ፣ ፕሮፈሰር ጌታቸው በጋሻው በተጨማሪም የኢሳት ጋዜጠኞች ገሊላ መኮንን አምስተርዳም እና መታሰቢያ ቀፀላ ለንደን እንግድነት ተገኝተዋል። በዚህም ዝግጅት ፕሮፈሰር ጌታቸው ስለ ኢትዮጵያ ያለውን የኢኮኖሚ ትንተና በሰፊው ገልፀዋል።
Patriotic Ginbot 7 Public Meeting in Osloፕሮግራሙን በሰፊው ሲጠበቅ የነበረው የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ፕሮፈሰር ብርሀኑ ንግግር በመቀጠል በአገሩቱ ውስጥ እየተደረገ ያለውን ትግል ሰፊ እና ጥልቅ ማብራሪያ አቅርበው በደቡብ አፍሪካ እንዲሁም በተለያዮ አለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኞች አስከፊው ስደትና መከራ በወያኔ መንግስት በመሸሽ እያደረሰባቸው ባለው ስቃይ ለዚ አስከፊ ስደት የዳረጉን የወያኔን የግፍ አገዛዝ ጫፍ መድረሱንም ጭምር ያሳየ ምልክት ነው በድርጊታቸውም በቃ ልንላቸው ይገባል ትግሉን መደገፍ ማጠናከር እንደሚገባ ገልፀዋል።
በቀጣዮም ፕሮግራም ታዳሚው ያልተጠበቀው ለተሳታፊውም በዓነቱ እንግዳ የሆነ ነገር በመከሰቱ ህዝቡን ያስደሰተ ክስተት ተከሰተ። በዝግጅቱም ላይ ከተሳታፊዎች ፊታቸውን በከፊል በመሸፈን ዝግጅቱን ሲከታትርሉ የነበሩት ግለሰብ ማንነታቸው በመድረክ ላይ በመወጣት ተሳታፊ ያስደመመ ያስደተና የአንድነት መንፈስን የበለጠ ያጠናከረ ክስተት በአንዳርጋቸው ፅጌ እህት ወ/ሮ ብዙነሽ ፅጌ ያልተጠበቁ እንግዳ ሆነው ተገኝተዋል ። ወ/ሮ ብዙነሽ ጽጌ ግጥም በማቅረብ ተሳታፊው በእንባ ፥ በቁጭት ስሜት ያንገበበ መልዕክት ያለው ግጥም አስተልፈዋል። የተወሰን ደቂቃ የምሳና ሻይ እረፍት በማድረግ በቀጥታ ወደ ልዩ ታሪካዊ የጨረታ ዝግጅት ነበር የታለፈው በጨረታውና የገቢ ማሰባሰቢያ የቀረበው ፎቶ የታጋይ አርበኛ ፕሮፈሰር ብርሀኑ ነጋ ፣ አርበኛ ታጋይ መዓዛ ፅጌ እና አንዳርጋቸው ፅጌ በ አንድ ላይ ያጠቃለለ ነበር። ለጨረታው ቀርቦ የነበረው ከፍተኛ ዋጋ በ ወ/ሮ ብዙ አየሁ ፅጌ አሸንፈዋል። በጨረታውም ያሸነፉትን የሶስቱ ታጋይ አርበኞች ፎቶ መልሰው ለአዘጋጁ አስረክበዋል አዘጋጁም ከረጅም ርቀት ተጉዘው ከስዊድን አገር ለመጡ አገር ወዳድ አርበኞች አስረክበዋል።
Patriotic Ginbot 7 Public Meeting in Oslo
 በፕሮግራሙ ላይ ከመቼውም ጊዜ በላይ ኢትዮጵያዊነት ነግሶ የታየበት ነበር ። በቀሪ ልዩ ዕጣ የወጣላቸው በልዮ ስሙ ኦታ አካባቢ ነዋሪ የሆኑ የትግሉ አጋር በዕጣው የወጣላቸውን የኮምፒተር ዕጣ ለ አርበኞች ግንቦት 7 አባልት እና ደጋፊ ለትግሉ ይጠቅማል በማለት በስጦታ መልክ ለግሰዋል። ሌላም ሌላም ስጦታዎች የተካተቱበት እና ለትግል ሜዳ ለተሰማሩት አጋር ጋዶች የሚሆን በ አንድ ግለሰብ 1000 ቲሸርት በስጦታ ተለግሰዋል። በማጠቃለያውም በ ኖርዌዳን ክሮነር 800,162 /ስምንት መቶ ሺህ አንድ መቶ ስልሳ ሁለት ሳንትም/ ተሰብስቦዋል ። የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ በተካሄደው የአርበኞች ግንቦት 7 ገቢ ማሰባሰቢያ በደመቀ ሁኔታ እንዲሳካ ላደረጋችሁ የነጻነት ታጋዮች ሁሉ ድርጅቱ የተሰማውን ትልቅ አድናቆት በምስጋና ሲገልጽ በተለይ ከስዊድን እንዲሁም ከሰሜንና ከተለያየ የአውሮፓ ክፍል የመጣችሁ፣ ከበርገን፣ ከትሮንድሃየም፣ ከክርስትያንሳንድ፣ ስታቫንገር እንዲሁም ከተለያየ የኖርዌይ ቦታ የመጣችሁ፣ በማያያዝም የከረንት አፌር ፓል ቶክ ሩም እንዲሁም ኢካዴፍ ከፍተኛ አድናቆት እና ምስጋና ስናቀርብ በማያያዝ የፍጻሜ የትግሉ ለሚጠይቀው መስዋእትነት ከአፍ ባለፈ በተግባር ስላሳያችሁት አጋርነት የነጻነት ታጋዮች ሁሉ ድርጅቱ የአክብሮት ምስጋናውን ያቀርባል፣ በተለይ የዘረኛው የጥጵልፍ አቃጣሪ ቡችሎች ፕሮጋራማችንን ለማስተጓጎን ያደረጉትን ያልተሳካ ሙከራ ከነሱ ውስጥ በመሆን እንቅስቃሴያቸውም ስታቀብሉን ለነበር የውስጥ አርበኞች ከፍተኛ አድናቆት እና ምስጋና እናቀርባለን፣
በስተመጨረሻ ከአገር ቤት በመደወል የገንዘብ ድጋፍ ላደረጋችሁንም ከፍተኛ ምስጋናችንን እናቀርባለን!!
ኢትዮጵያችን በክብር ለዘላለም ትኖራለች
ዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ !

No comments:

Post a Comment