Translate

Wednesday, June 8, 2016

አልሸባብ የገደላቸውን የኢትዮጵያ ወታደሮችን ፎቶ ግራፎች ለቀቀ

የልዑል ዓለሜ ዘገባ
በሶማሌያ የሚገኙ የኢትዮጵያ ወታደሮች በተለይም የ44ተኛ ክፍለ ጦር እየተዳከመ መምጣቱን ምንጮች እየገለጹ ይገኛሉ::
ኢትዮጵያዊያን ወታደሮች በአልሸባብ በአሰቃቂ ሁኔታ እየተገደሉ የሚገኙበት ኢል ቡር ( El bur ) የተባለዉ አካባቢ ሲሆን ከመከላከያ ሰራዊቱ መካከል አንዱ የላከልን መረጃ እንደሚያመላክተዉ ሰላም የማስከበሩ ሂደት በወያኔያዊያን አመራሮች ወደ ሰራዊት ማስጨረሱ ሁናቴ መሸጋገሩን ነዉ::
” የአልሸባብ አፈ ቀላጤ የሆነ አሊ መሃመድ ራጌ Ali Mahmud Rage የተባለ ግለሰብ በስፍራዉ ለሚገኙ መከላከያ ሰራዊት አዛዦች እና ወታደሮች በተለያየ መንገድ ማስጠንቀቂያ እየሰጠ የጥቃት አደጋ መፈጸሙን ከተያያዘዉ ሰንበትበት ብሏል! የሚል መልእክት ያሳለፈዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባል… የጥይት ድምጽ በተሰማበት ስፍራ ሁሉ በአፋጣኝ እየተወሰድን የምንማገድበት ሁኔታ እየተባባሰ ከመምጣቱ በላይ የ44ተኛ ክፍለ ጦር እየተመናመነ መጥቷል ሲል በምሬት አሳስቧል።
አል ሸባብ የኢትዮጵያ መከላከያ አባል የሆነ ኮማንደርን ጨምሮ ብዛት ያልቸዉ ወታደሮችን መግደሉን በተለያየ ወቅት የሚለፍፍ ሲሆን በሳለፍነዉ ሳምንት ዉስጥ ሁለት የመከላከያ ሰራዊት አባላትን በሞት ፍርድ መቅጣቱንም ከስፍራዉ አንድ የወያኔ ከፍተኛ አመራር ተናግረዋል ።


alsbehah2

No comments:

Post a Comment