Translate

Saturday, June 11, 2016

በጀርመን አ.ግንቦት 7 የተሳካ ስብሰባ እያደረገ ነው | ሕወሓቶች በር ላይ የተቃውሞ ሰልፍ ወጥተዋል

አርበኞች ግንቦት 7ን ለመደገፍ አዳራሽ ውስጥ የሚገኘው ህዝብ
አርበኞች ግንቦት 7ን ለመደገፍ አዳራሽ ውስጥ የሚገኘው ህዝብ
                                   አርበኞች ግንቦት 7ን ለመደገፍ አዳራሽ ውስጥ የሚገኘው ህዝብ
(ዘ-ሐበሻ) የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር በተገኙበት በጀርመን በርሊን ከተማ በመካሄድ ላይ ባለው የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ላይ ሕዝብ አዳራሹን ሞልቶ እየተመለሰና ከውጭ ሆኖ እየተከታተለ መሆኑን የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ከበርሊን ዘገቡ:: ባልተለመደ መልኩ የሕወሓት ኢምባሲ ሰራተኞችና ለትምህርት ወደዚያው የተላኩ የባለስልጣናት ዘመዶች “አርበኞች ግንቦት 7 የ እናት ጡት ነካሽ ነው” የሚሉና ሌሎችንም መፈክሮችን ይዘው ከአዳራሹ ፊት ለፊት ተቃውሞ እያሰሙ ነው::

አርበኞች ግንቦት 7 የጠራው የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በተሳካ ሁኔታ እየተካሄዱ ነው ያሉት እነዚሁ የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ከውጭ የሕወሓት ሰዎች የትግራይ ክልልን ባንዲራ ይዘው በመቃወም ላይ ናቸው ብለዋል:: ‘የኢትዮጵያ ሕዳሴ በሕዝቦቿ እውን ይሆናል’; “አዲሲቷ ኢትዮጱያልማትን እንጂ ጦርነትን እና ሽብርን አትሻም” የሚሉና ሌሎችንም መፈክሮችን የያዙት እንዚሁ 15 የማይሞሉት ሰልፈኞች አርበኞች ግንቢት 7ን ለመደገፍ በሄደው ሕዝብ ድምፃቸው እንደተዋጠ ከስፍራው የደረሱን መረጃዎች ጠቁመዋል::
የበሊኑን ስብሰባ እንዳለቀ ተጨማሪ መረጃዎችን ይዘን እንመለሳለን::
ግንቦት 7ን ለመቃወም ከውጭ የቆሙት የሕወሓት ኢምባሲ ሰራተኞችን እና የባለስልጣናት ዘመዶች
ግንቦት 7ን ለመቃወም ከውጭ የቆሙት የሕወሓት ኢምባሲ ሰራተኞችን እና የባለስልጣናት ዘመዶች
                          ግንቦት 7ን ለመቃወም ከውጭ የቆሙት የሕወሓት ኢምባሲ ሰራተኞችን እና የባለስልጣናት ዘመዶች

No comments:

Post a Comment