Translate

Tuesday, December 1, 2015

አማራ እንደምን አደርክ (ኄኖክ የሺጥላ – ግጥም)


Henoke Yeshitila's pottery
ኄኖክ የሺጥላ
ኄኖክ የሺጥላ
ስለ ስቃይህ ባወራ አማራ ይሉኛል ብዬ
የልቤን የልቦና ቃል ፣ በይሉኝታ ጨርቅ አፍኘ
ታሪክ ተማርኩ ብዬ
አንድነት እንዳልንድ ብዬ
የፍቅር የመቻቻሉ ፣ ባህል ይፈርሳል ብዬ
ትግሬ እንዳይቀየም ፣ እንዳይከፋው የኔ ነገር
አማራ ይሙት አልኩኝ ፣ ምስኪን ዘመዴ ይቀበር !

እንደምን ነይ አያ ሞገስ
እንደምን ነህ አነቃንቀው
ለሴ ፣ ጥቢኛ ያጎረስከኝ
ጎንደር ጃን ተከል ዋርካው ስር
ስለ ሀገር የመከርከኝ
ደብረ ብርሃን ስላሴ ፣ ደብቀህ ፣ አቅፈህ ያኖርከኝ
ዳሞት እና ደጀን አፋፍ
በፍቅር አቅፈህ የሳምከኝ
መንዝ እና ይፋት-ቀወት ፣ ጠመንጃ ተኩስ ያስተማርከኝ
ላይ እና ታች አርማጮሆ ፣ ከሞት ከእሳት ያዳንከኝ
እንደምን ነህ ጃና-ሞራ
እንደምን ነህ አንተ አማራ !
እኔማ
በስልጣኔ ዳንኪራ
የነብሴ ክር ረግባ
እንዲህ ብል እንዲህ ቢሉኝስ
ብዬ ነገር ሳንቆላጵስ
አስበላሁህ ወንድምዬ
አዋረድኩህ አካልዬ
የዘመንጊንጥ በጀርባዬ ፣ በምላሴ ስር አዝዬ !
ትግሬ አትበሉ እያልኩ ፣ አስገደልኩህ ደጋግሜ
አጋሜ አትበሉ እያልኩ ፣ አሳረድኩህ ደጋግሜ
ስልጣኔ በፈጠረው ፣ በይሉኝታ አጥር ታጥሬ
አንድነት ፣ ሀገር ምናምን ፣ እያልኩ ቀበጣጥሬ
ዘሬን አስመነጠርኩት ፣ በአጉል ፍቅር ተወጥሬ !
እንደምን ነህ አማራው
ከስራ ሥራ የሌለህ
በዘርህ ኑሮ የተነፈግህ
ከሀገር ሀገር የሌለህ
ያም ይሄም የሚዝትብህ
ከታሪክ ታሪክ የሌለህ
የመጣውም የሄደውም ገዳይ በዳይ የሚልህ
እንደም ነህ አማራው
የነጻነት ገሞራው
የ አርበኛው ልጅ ባለ-አሻራው
ባላ ግርማው ፣ ባለ ጎራው !
እንደምን ነህ በደኖ
ገደሉ እና ድልድዩ
እንደምን ነህ ቤንሻንጉል
በትግሬ ሴራ አማራ ፣ የእናቴን ልጅ ገዳዩ
እንደምን ነህ አንተዬ
አማራ አልሞተም እያልኩ
ደሞ እንደገና እዬዬ !
ትግሬ አይገልም እያልኩ
ደሞ እንደ- አዲስ ወንድምዬ !
የኔን ነገር ተወው አያ
ላፍ እንጂ ለህሊና አልኖር
ለፎቅ ለመሬት ለቤት እንጂ
ለማንነቴ መቼ
ባንቀልባ ባንዳ አዝዬ ፣ ተዘቅዝቄ ተደፍቼ
አህያም እየተባልኩኝ
ሁለት ሚሊዮን ጎድዬ
አምስት ሚሊዮን ትግሬ ፣ ያሳዝነኛል አዬ !
እኔን ተወኝ ወንድምዬ
የኔን ነገር ተወው አያ
እውነትም እንደሚሉት ነው
መቼ ተሽዬ ካህያ
አማራ ከምል ብዬ ፣ አማራ ይሙት የምል
ሃያ አምስት ዓመት ነድጄ ፣ ለሰከንድ እንኳ የማልበስል
ተወው አያ !

No comments:

Post a Comment