Translate

Thursday, November 19, 2015

ወንጌል እና ሰይጣን፣ ትግሬ እና ብርቱካን ( ሄኖክ የሺጥላ )

ወንጌል እና ሰይጣን፣ ትግሬ እና ብርቱካን ( ሄኖክ የሺጥላ )
የብርቱካን አሊ ልጅ አብዱ በራ’ብ እንዳልሞተ ወያኔ ነገረን ። በዛ ላይ ቢቢሲ ደሞ እንደ ኢሳት እንደዋሸ ተነገረን ። ይሁን !
እንበልና የብርቱካን ልጅ በራብ አልሞተም ፣ ቀጥሎም የብርቱካን ልጅ በቁንጣን ነው የሞተው እንበል ፣ እንደውም እንደ ወያኔ ባለ ስልጣን ልጆች ሰክሮ መንገድ ላይ ውስኪ እየደፋ ሲሄድ የደፋው ውስኪ አዳልጦት ነው የሞተው እንበል ፣ ከፍ ሲል ለቢቢሲ ጋዜጠኛ ያሳየችው ቅጠል የተሸፈነ የልጇ የአብዱ መቃብር ሳይሆን የእህል ማስቀመጫ ጎተራ ነው እንበል ፣ እነዚህ ሁሉ እውነት ሆኑ እንበል ፣ ከዚያስ ?
እርግጥ ነው ፣ ነገሩን በጥልቀት ከተመለከትነው የብርቱካን ልጅ የሞተው በራብ አይደለም ፣ ራብ ነብሱን ከስጋው የለየው የመጨረሻው ጉዳይ ይሆን ይሆናል እንጂ ፣ የብርቱካን ልጅ የሞተው ፣ እኛ ወንድነታችንን የተቀማን ግዜ ነው ፣ ብርቱካን ልጆቿን የቀበረችው የወለደቻቸው ቀን ነው ፣ እርግጥ ልጇን አፈር ያለበሰችው ዛሬ ነው ፣ መቃብሩ የተቆፈረው ግን ወያኔ ስልጣን ላይ ሲወጣ ነው ። ረሃቡ ሞትን ያስከተለ አንድ ምክንያት ሊሆን ይችላል እንጂ የብርቱካን ልጅ ረሃብ ባይኖርም አያድግም ! ሰው አይሆንም ! ሃገሩን አይጠቅምም ! ባገሩ አይጠቀምም !

የብርቱካን ልጅ አድጎ ቢሆን ኖሮ ዛሬ ረሃብ ነብሱን ከቀማው የተለየ ነገር አይጠብቀውም ነበር ። ወይ የባህር ውሃ ይበላዋል ፣ ወይ የሱማሊያ ወታደር ሆኖ የፈንጅ ማምከኛ ይሆናል ፣ አልያም በየ አረብ ሃገራቱ እንደ አሸዋ ይበተናል ።
ብርቱካን ( በዘንድሮ አስተሳሰብ ትግሬ ባለመሆኗ ብቻ ) አይርባትም ፣ ሊርባት አይችልም ፣ አይጠማትም ፣ ሊጠማት አይችልም ፣ አይቸግራትም ፣ ሊቸግራት አይችልም ። እንደውም ከቆመችው ብርቱካን ፣ ልጇ አብዱ የተሻለ እረፍት ያገኛል ። ብርቱካን እድለኛ እናት አይደለችም ፣ ምክንያቱም ወንድ ልጅ ወልዳ አላሳደገችም ፣ ቀየዋ ወንድ አልወለደም ። ስለዚህ እናቱን ሲንቁበት ፣ እህቱን ሲደፍሩበት ፣ ሃገሩን ሲቀሙት ፣ ዝም ያለ ትውልድ ፣ የ አልቃሻ እና ሆደ ባሻ ወንድ ዘመን እናት ነች ። ስለዚህ አይደልም ልጇ አብዱ ብርቱካን ራሷ ሙታለች !
እኔ ትግሬ ነኝ ወያኔን ግን አልደግፍም ባይ መጻጉ ፣ ልበ እባብ አፈ ቀላጤዎች ፣ እንደዚህ አይነት ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ባንድ ኢትዮጵያዊ እናት ላይ ሲፈጸም < ልክ አይደለም አላሉም !> ፣ ትናንት ወያኔ ወንዝ ውስጥ ወርውሮን ከሞት ተርፈን በህንድ አርገን ፣ በእንትን አርገን አማሪካ ገባን የሚሉት ሳይቀሩ ፣ ደማቸውን ቆጥረው ፣ ማንነታቸውን ቆንጥረው ፣ ስለዚህ ጉዳይ አንዳች ነገር ሲተነፍሱ አታዩም ። የድህረ ገጽ ባለቤቶቹም ፣ ከሞተ 15 ዓመት የሆነውን ሰው ታሪክ አንስተው < ክንፈን መለስ ገደለው > አከሌ በደለው ይሉናል ፣ ለምን መሰሪዎች ስለሆኑ ! ለምን የብርቱካን መሞት ለነሱ ምናቸውም ስላልሆነ ፣ ለምን ብርቱካን መሞት ስላለባት !
መደምደሚያ
አብዛኛውን ጊዜ ስለ ትግሬ መክፋት ሳወራ ወገቡን ይዞ የሚከራከረው አማራ ይገርመኛል ። ቢያንስ ስለ ብርቱካን ስትሉ ዝም በሉ !
ግራህን ሲመታ ቀኝህን ስጣቸው የሚለው ትምህርት የተሰበከበት ሀገር ሰዎች ፣ ስለ ማንነታቸው ምን እንደሚያረጉ ማን አያውቅምና !
የ ሴፕቴምበር 11ን’ አደጋ ተከትሎ አማሪካኖች ለኢራቅ ግራ ጉንጫቸውን ሰጡ እንዴ ? ታዲያ የኛ ክርስቶሳዊነት ምንጩ ምን ይሆን ?
የጋራ ሀገር ሳይኖር የጋራ ፍቅር የሚባል ነገር የለም ። የብርቱካን ልጅ በራብ ሞቶ ፣ የ አዜብ መስፍን ልጅ ጠግቦ የሚያድርበት አንዳችም ሰማያዊ ምክንያት ስለሌለው ግራዬን ሲመቱኝ ፣ የሚዞር ቀኝ ጉንጭ የለኝም ! ለሰይጣን ወንጌል የምናስተምር ባንሆን እላለሁ !

No comments:

Post a Comment