Translate

Saturday, January 26, 2013

ድምጻችን ይሰማ የሚል ቲ-ሸርት ያደረጉ ሙስሊሞች ከስታዲየም ተባረሩ


ድምጻችን ይሰማ የሚል ቲ-ሸርት ያደረጉ ሙስሊሞች ከስታዲየም ተባረሩ


በትላንትናው ጨዋታ ላይ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ለመደገፍ የታደሙት በደቡብ አፍሪካ የሚገኙት የሙስሊሙ ማህበረሰቦች ድምጻችን ይሰማ እና እንዲሁም መሪዎቻችን ይለቀቁ የሚሉ ቲሸርቶችን ለብሰው በመታየታቸው በሰኩሪቲ ፖሊስ እየተለቀሙ ከስታዲየም ግቢ እንዲወጠ ተደርገዋል ። አብዛኞቹን ለጥያቄ እንፈልጋችኋለን በማለት የወሰዷቸው ሲሆን ሌሎቹን ደግሞ ይህንን ለብሳችሁ እዚግ ስታዲየም ውስጥ መቆም አትችሉም በማለት አስረግጠው ነግረረዋቸዋል ።ከደቡብ አፍሪካ የማለዳ ታይምስ ዘጋቢ እንደአቀረበው ሪፖርት ከሆነ ማንኛውም የተቃውሞ የሚያሰሙ ነገሮችን በመንግስት ሃይሎች እና በኢትዮጵያ ኤምባሲ ትብብር ህብረተሰቡን ለመቆጣጠር እና መብቱ እንደተጋፉት ገልጾአል ። ይህ ለምን ሆነ በማለት የማለዳ ታይምስ ዝግጅት ክፍል አስተባባሪ ላቀረበላቸው ጥያቄ መልስ ለመስጠት ቢቆጠቡም በድጋሚ እናንተ ይህንን የማገድ ስልጣን የላችሁም ይህ ትእዛዝ ሊመጣ የሚችለው ከፊፋ አስተዳደር በደቡብ አፍሪካ ስፖርት ፌደሬሽን ስር ብቻ ሊሆን ይገባዋል እንጂ በሃገሪቱ መንግስታቶች የሚሰጥ ላይሆን ይገባዋል ብሎ ሲያነጋግራቸው  ይህ ያንተ ጉዳይ አይደለም በማለት የጥበቃ ክፍሎቹ ሲመልሱ በማስከተልም ከሙስና ጋር የተያያዘ ስራ እየሰራችሁ እንጂ ይህ ህገ ወጥ እንደሆነ ልባችሁ ያውቃቸዋል ሲላቸው ከስታዲየሙ ለማባረር እንደሞከሩ እና ከዚያም በጥበቃዎቹ ዋና ሃላፊ ጋር በመነጋገር ጉዳዩን ትኩረት እንዲሰጥበት እና እንደዚህ አይነት ነገሮች በግዴለሽነት ሊታዩ እንደማይገባ እና በአለም አቀፍ ህግ ሊያስቀጣቸው እንደሚችል ጠቅሶ ተመልሶ ወደ ስታዲየሙ ለመቀላቀል መብቃቱን ሪፖርተራችን ከስፍራው ያደረሰን ዘገባ ያመለክታል ። ከጨዋታም በኋላ የኢትዮጵያን ሽንፈት በስታዲየም የሰሙ ወገኖች እንደተናገሩት ከሆነ ይህ ጉዳይ እልባት ካላገኘ በሚቀጥለው ከናይጀሪያ ጋር ለሚደረገው ጨዋታ ሁሉንም ነገር ያዩታል እንዲያውም ከጨዋታ ውጭ ሊሆኑም ይችላሉ ስለዚህ የሰው ልጅ የሚፈልገውን ለማድርግ የሚችልበትን ነገር መንፈግ የለባቸውም በሃገራችን የነፈጉንን ነጽነት በሰው አገር አይሞክሩት ሲሉ ገልጠዋል ። አንዳንዶቹም በመሸነፋቸው ደስ ብሎናል ሲሉም ቁጭታቸውን ገልጸዋል ። በሌላም በኩል በትላንትናው እለት የሞአ አንበሳው ምልክት የያዘውን እና ልሙጡን ባንዲራ ይዘው እንዳይገቡ ከመከለከሉም ውጭ በስታዲየሙ ውስጥ በልሙጡ ባንዲራ ማስታወቂያ የተሰራባቸው ሬክላሞች እንዲነሱ መደረጉን የዝግጅት ክፍላችን ሪፖርተር ከስፍራው ዘግቦአል ።
385176_202985146507804_1933869717_n554299_202985126507806_1643529397_n542414_202985096507809_10217403_n
maleda times | January 26, 2013 at 3:19 am | Categories: AMHARIC NEWS | URL: http://wp.me/p2gxmh-1no

No comments:

Post a Comment