Translate

Sunday, January 20, 2013

እንደ መከላከያ ሁሉ ኢትዮ ቴሌኮምም



እንደ መከላከያ ሁሉ ኢትዮ ቴሌኮምም

ዘረኛው የወያኔ መንግስት ዘረኝነቱን በሚያጠናክርለት ና የራሱን ጀሌዎች ብቻ የስርአቱ ተጠቃሚ በማድረግ የአንድ ብሄር የበላይነቱን ይዞ አሁንም እንደቀጠለ መሆኑን የሚያሳይ ሌላ መረጃ ሰሙኑን የግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ የጥናት ክፍል ይፋ አድርጓል ። ቀደም ሲልም  በየካቲት 2002 በመከላከያ ሰራዊት በአዛዥነት ቦታዎች ያለውን የብሄር ተዋጽኦ ማጋለጣችን ይታወሳል።
ወያኔ በኢትዮ ቴሌኮም ውስጥ ለረጅም ግዜ በየዘርፉ ልምድ ያላቸውን ባለሙያዎች አባሮና አፈናቅሎ ታማኝ ያላቸውን የህወሃት ታጋዮችን “ከሲቪል ሰርቪስ ኮሌጅ ያስመረታቸውን ምርቶች እና ከመቀሌ ኢንስቲዩት ቴክኖሎጅ ” በአብዛኛው ከአንድ ዘር በማምጣት መድቦ ኮርፕሬሽኑ የጀሮ መጥቢያ የስላላ ተቋምና የፓርቲው መሳሪያ በማድረግ የዜጎችን ሉዓላዊነት በመዳፈር ሀገራችንን በዚህ ዘመን የመረጃ ርሃብተኛ አድርጓታል።
በዚሁ ጥናት ሌላው አሳዛኙ ጉዳይ ከእያንዳንዱ 3.3 ሚሊዮን የኦሮሞ ተወላጅ ዉስጥ በኢትዮ ቴሌኮም ከፍተኛ አመራር ቦታ የተሰጠዉ አንድ የኦሮሞ ተወላጅ ብቻ ሲሆን ትግራይን ስንመለከት ግን ከእያንዳንዱ 194 ሺ የትግራይ ተወላጅ ዉስጥ ቢያንስ አንድ ሰዉ በኢትዮ ቴሌኮም ከፍተኛ አመራር ቦታ ላይ ተቀምጧል። ይህ የስራ አመዳደብ የትምህርት ችሎታንና ልምድን ተከትሎ የተሰራ ነዉ ቢባል እንኳን የላቀ የትምህርት ደረጃና የስራ ልምድ ያላቸዉ የኦሮሞ ተወላጆች ቁጥር ተመሳሳይ የትምህርት ደረጃና የስራ ልምድ ካላቸዉ የትግራይ ተወላጆች ቁጥር በአስር እጥፍ መብለጡ ምንም ጥርጥር የለዉም።

ሌላው መራራ ሀቅ 66.2 በመቶ የሚሆነዉን የኢትዮጵያ ህዝብ ከሚያቅፉት ከኦሮሚያና ከአማራ ክልል N1 በሚባለዉ ከፍተኛ የአመራር አርከን ዉስጥ በአመራር ቦታ የተቀመጡ ዜጎች ብዛት አራት ብቻ ነዉ (ሁለት ከኦሮሚያ ሁለት ከአማራ)። ከጠቅላላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ዉስጥ 5.4 በመቶዉ ብቻ ከሚኖርበት ከትግራይ ክልል ግን ስምንት ሰዎች ኤን አንድ በሚባለዉ ከፍተኛ የአመራር ቦታ ላይ ተቀምጠዋል።
ሌላው ወያኔዎች ለወደፊቱ የአለም ቴክኖሎጂ ሲያድግ ህወሃቶች የተቀረውን የሀገራችንን ህዝብ አድልሆ በማድረግ አንድን ዘር በኢኮኖሚና ቴክኖሎጂ የማሳደግ ስውር አጀንዳም ይዘው እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ጥናቶች በተደጋጋሚ እያሳዩን ነው። ስለዚህ ይህንን የማስቆምና ዜጎች በሀገራቸው እንደዜጋ የሁሉም መብቶች እኩል ተጠቃሚ ለማድረግ አስፈላጊውን መሰዋእትነት በመክፈል ተግባራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ሁላችንም እንገባ ዘንድ የግድ ነው።
ወያኔ/ህወሃት ለደረሰብኝ በደል ካሣ አሁን ተራዬን ሌሎችን የመበደል መብቴ ነው ብሎ የሚያደርገውን የአንድ ዘር የበላይነትንና ጨቋኝነቱን በድርጊቱ እንዲህ እየነገረን፤ በግልባጩ ግን ነጋ ጠባ የሚነገረን እኩል መሆናችንን ነው። ይህ ግን ሀሰት መሆኑን ጥናቱ አረጋግጦልናል። በቀድሞ ሥርዓት የተበደለ በአዲሱ ሥርዓት በዳይ ሆኖ ቢገኝ ጥፋቱን አቅልሎ ማየት፤ የሥርዓት ለውጥ የበዳይና ተበዳይ ቦታ መለዋወጥ አድርጎ ከመገንዘብ የሚመጣ እጅግ አደገኛ የሆነ አመለካከት ነው እና የሀገራችን ህዝብ ይህንን አረመኔ ዘረኛ ስርአት ብሄራዊ አደጋ ውስጥ ሳያስገባን ልንታገለው ጊዜው አሁን ነው።
ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ ከእነዚህና ሌሎች እውነታዎች በመነሳት አሁን ግዜው የፍልሚያ ነው የሚለው፤ የቻለ በግንባር ያልቻለ በደጀንነት ይሰለፍ፣ ጠጠር ይወርውር ጠጠር ያቀብል! የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! ሀገራችን ኢትዮጵያን ከሀገር በቀሉ ወራሪ ዘረኛ መንግስት የማዳን ጥሪ ጊዜው አሁን ነውና የምንችለውን ሁሉ በማድረግ የዜግነት ግዴታችንን እንወጣ! እኩልነት የሰፈነባት ኢትዮጵያን ለመገንባት የረጅሙ ጉዞ ምእራፍ አሁን ነው እና የአንድ ዘር የበላይ ዘረኝነት ፓሊሲን እንዋጋ!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!

No comments:

Post a Comment