Translate

Wednesday, August 22, 2012

ተቃዋሚዎች ያለፈው የግፍ ስርአት ተመልሶ የማይመጣ መሆኑን በትግላችን የምናሳይበት ውቅት ላይ እንገኛለን ሲሉ ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ ገለጡ


ነሀሴ ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-የግንቦት 7 ንቅናቄ መሪ የሆኑት ኢኮኖሚስቱ ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ፣ የመለስ ዜናዊ ዜና እረፍት በግላቸው ስለፈጠረባቸው ስሜት እና በአገሪቱ ላይ ሊያመጣ ስለሚችለው መጥፎ ወይም ጥሩ አጋጣሚ ተናግረዋል
የተለያዩ ሀይሎች እጃቸው ላይ ያለውን ካርድ የሚጫወቱበት መንገድ የኢትዮጵያን እጣ ፋንታ እንደሚወስን ዶ/ር ብርሀኑ ተናግረዋል::

በኢትዮጵያ ውስጥ አሁን የሚታየውን የስልጣን ክፍተት ተከትሎ አገሪቱ ወደ መጥፎ ጎዳና እንዳታመራ ግንቦት7 ምን አማራጮችን ያቀርባል ለተባሉት ፣ ድርጅታቸው ሲመሰረት ጀምሮ አማራጮችን ግልጽ ማድረጉን ገልጠዋል::
ድርጅታቸው ግንቦት7፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የስልጣን ክፍተት ቢፈጠር መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ አስተባብሮ አመራር ለመስጠት ተቋማዊ ብቃቱ ምን ይመስላል ለተባሉት ዶ/ር ብርሀኑ ሲመልሱ፣ ግንቦት7 በአለፉት 4 አመታት ድርጅታዊ ብቃቱን ማጎልበቱን በሙሉ ልብ ተናግረዋል::
____________________________________________________________________________________________________________________________________
ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.
ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide

No comments:

Post a Comment