Translate

Monday, March 14, 2016

ዜና መረጃ — ህወሃት አሉኝ የሚላቸዉ ጄኔራሎቹን አጣጣለ

በልኡል አለም
በ11/03/2016 በመከላከያ ሚኒስቴር ቅጥር ግቢ ዉስጥ በተደረገ ድንገተኛ ስብሰባ ላይ የተገኙ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ጄኔራሎች እራሳቸዉን ከኤርትራ ጄኔራሎች ብቃት ጋር በማወዳደር መናቆራቸዉን ምንጮች እየገለጹ ይገኛሉ።
general samora yenus
በሚኒስቴር ጀኔራል ሲራጅ ፈጀታ የዉስጥ ደንብና ምክክር የተጠራዉ ይህ ድንገተኛ ስብሰባ አሉ የሚባሉ የወያኔ ጄኔራሎችን ያካተተ ሲሆን የምክክር መድረኩ ባስገራሚ መልኩ ይዘቱን ቀይሯል። ይህዉም የኤርትራ ጄኔራሎችን ብቃት በተመለከተ ጠቅለል ያለ መረጃ ያቀረቡት ጠ/ሚኒስቴር ጄኔራል ሲራጅ ፈጀታ ለሻቢያ ስራዊት የመጀመሪያዉን ጥይት ከተኮሱ ከነ ሃሚድ ኢድሪስ አዉት ጀምሮ እስከ አሁኑ የጸጥታ ሐላፊ የበላይ ጠባቂ ከሜጄር ጄኔራል ፊሊፖስ ወልደዮሓንስ እንዲሁም እስከ እታች ለመዉረድ የሞከረ ሲሆን በንግግሩ መደምደሚያ ላይ ኤርትራን ለመዉጋት ብንነሳ እነዚህ የሻቢያ መኮንኖች ምን ያህል ይከላከላሉ የሚል እሳቤ ነበርዉ።

ከዚህ ወዲህ የቀረቡት አስተያየቶች እጅግ አስደንጋጭ የንበሩ ሲሆን… በሰሜኑ እዝ የጠ/ላይ መምሪያ አዛዥ እንዳስቀመጡት
“እስካሁን የተጠቀሱት የሻቢያ ጄኔራሎች በዉጊያዉ ላይ ጉልህ አስተዋጾ አያደርጉም ባይባልም ጠላት ግን አይናቅም ! ! በመሆኑም ዋነኞቹ እና ቀንደኞቹ ግን አልተጠቀሱም ለምሳሌ በባድሜ ጦርነት ወቅት የአሰብን እራስ ገዝ ሲጠብቅና ሲያጠቃ የነበረዉ በቡሬ ግንባር መሬት ወርዶ ሲያርመሰምሰን የኖረዉ ግንባር 71 የሚባለዉን የኢትዮ-ኤርትራን ድንበር ቆርሶ አስገራሚዉን ምሽግ የገነባዉ በ70ዎቹ የእድሜ ክልል ዉስጥ የሚገኘዉ ሜጀር ጄኔራል ዳንኤል አብረሃ በምን መልኩ ነዉ የታየዉ!!! የኛ ጄኔራሎች በተንጣለለ መኖሪያ ቤት ዉስጥ በከተማ ይኖራሉ የኤርትራ ሰራዊት ጄነራሎች አስቸጋሪዉን የሬንጀር ኮርስ የበረሃ ጉዞ 50 ኪ/ሜ ከወታደሮቻቸዉ ጋር ያሳልፋሉ መመሪያ ይሰጣሉ በኮምፒተር ከመታገዝ አልፈዉ መሬት እየሰነጠቁ የጦር ምህንድስናዉን ይጠልፋሉ! የትኛዉ የኛ ሰራዊት አዛዥ ነዉ ኤርትራን ለመዉጋት የሚዘልቀዉን ጦራችንን ከጎኑ ሆኖ አይዞህ የሚለዉ ሳሞራ የኑስ ነዉ! ወይስ እርሶ ክቡር ሚኒስቴር አቶ ሲራጅ!”
በማለት ያንጓጠጠ ሲሆን ከእርሱ በመቀጠል ተቀማጭነቱ አዲስ አበባ ቤተ መንግስት የሆነ የቤተ መንግስቱ የክፍለ ጦር መምሪያና የብርጌድ ሃላፊ በበኩሉ፣
“እኔም በዚህ ሐሳብ እስማማለዉ በተለይም ወታደራዊ ፖለቲካ ሳይንስ አወራረዳችን ዜሮ በመቶ ነዉ ቢባል አያሳፍርም ለምሳሌ የኤርትራዉን ወታደራዊ ፖለቲካ ብንመለከት ጄኔራል ስብሓት ኤፍሬምን መዉሰድ በቂ ነዉ እርሱ የረገጠበት ቦታ ላይ እኛ ምን ያህል ዘልቀን ገብተናል በእርሱ አንጻር የሚገኙ የእኛ ጀኔራሎች የፖለቲካዉ አመራሮች እነማን ናቸዉ! ዉጊያ ተጀመር ይባል ከጀመርን ደግሞ እንድንገባ የተነደፈዉ በአሰብ በኩል ያለዉ አንዱ መንገድ ነዉ! ከዚያ ዉጪ በአማሐጅር ጀርባ አድርገን በባረንቱ ቆርጠን እስከ ተሰኔ ሊሆን ይችላል ነዉ የሚባለዉ!! ሁለቱም መንገድ ያዋጣናል የሚል እምነት የለኝም ” በማለት አስተያየታቸዉን ከሰጡ ወዲያ ሌላኛዉ ተናጋሪ በተመሳሳይ መልኩ፣
“በአሰብ በኩል ሻቢያን ለመዉጋት የታሰበዉ እቅድ ዋና ፍሬ ነገሩ ተቃዋሚዎቻችን ናቸዉ ዛሬ እነርሱ እኛ ከመጣንበት አይነት ስፍራ በረሃዉን ተሸክመዉ ይገኛሉ ከዚህ ቀደም ባደረግነዉ ዉጊያ በአሰብ በኩል ግንባር 71 ላይ የሰፈርዉን የሻቢያ ሰራዊት ምሽግ ለመምታት የአየር ሐይላችን ያደረገው ሙከራ ትዝብት ዉስጥ ጥሎናል እንኳን ያንን ምሽግ መምታቱ ይቅርና ሶጃ የተባለ የመንገድ ስራ ድርጅት የሰራዉን በኢትዮ-ኤርትራ መንገድ ላይ የተገነቡ ድልድዮችን ማፍረስ እንክዋን ተስኖን ነበር። ዛሬ አሰብ በነ ሳኡዲ አረቢያ መዳፍ ዉስጥ ነች ወደ አሰብ የምናደርገዉ ግስጋሴ ከጅምሩ አደጋ ይገጥመዋል ከሳዉዲ አሰብ የሚወረወሩት አሜሪካን ሰራሽ የጦር መርከቦች ከበዛ 60 ደቂቃ ካነሰ 42 ደቂቃ ዉስጥ አሰብ ይደርሳሉ የጦር ጀቶቹ ከ15 እስከ 20 ደቂቃ አሰብን ይጎበኛሉ ወደድንም ጠላንም በአሰብ በኩል ያሉትን እነ አርበኞች ግንቦት 7ን ለማጥቃት ስንነሳ በአሰብ ወደብ ላይ የሚገኙት የጸረ ሽብር ጥምር ሐይሎች ከሸባሪዎቹ እንደ አንዱ ነዉ የሚቆጥሩን! በተለይም አሁን ባሉን ጄነራሎች የመዋጋት ብቃት የለንም!”
በማለት እጅግ አንገት የሚያስደፋ ትችቶችን በማቅረብ ስብሰባዉ በከንቱ በኤርትራ ጄኔራሎች ብቃት የበላይነት የተካሄደ እና ለ3 ሰአታት የዘለቀ ሲሆን በመጨረሻም ዉጊያዉ የማይቀር ነገር ግን አለም አቀፍ ትኩረትን ወደኛ እንዲያዘነብል በማድረግ በኩል ስራ እንዲሰራ ተወስኖ አስቸኳይ እርምጃ እንዲወሰድ መመሪያ ተላልፏል።

No comments:

Post a Comment