Translate

Sunday, July 9, 2017

ባንዳነት ጌጥ የሆነላቸው (መስቀሉ አየለ)

መስቀሉ አየለ
ቡልጋሪያ የምትባል የምስራቅ አውሮፓ ክፍል አለች። ለአራት መቶ አመት ያህል በቱርክ የእሳት ሰንሰለት ተጠፍንጋ የኖረች አገር ናት። የኦቶማን ቱርክን ጦር ቀጥቅጦ ወደ መቃብር የገፋላት የሩሲያ ጦር ነበር። ቡልጋዎች ይህን የነጻነት ቀን በያመቱ ሲያከብሩ የክብር እንግዳው የሚመጣው ከሩሲያ ነበር። ባለፈው አመት ግን ይኽ አልሆነም። በሶፊያ፣ ቡልጋሪያ የሚገኘው የ አሜሪካን አምባሳደር ተቆጣ አሉ፤ ተቆጥቶም አልቀረም ይልቁንም የክብር እንግዳው ከቱርክ መሆን አለበት ብሎ ቀጭን ትእዛዛ ያስተላለፈው ለአገሪቱ ፕሬዝዳንት ነበር።በጌታና የሎሌ ግንኙነት ወቅት ፕሮቶኮል ትርጉም የለውም።Unpatriotic act
የናዚ ጀርመን ጦር አውሮፓን እንዳይወር በወቅቱ የነበሩት መራሄ መንግስትታ ለሂትለር እጅ መንሻ የመስዋእት ጠቦት አድርገው የሰጡት ፖላንድን ነበር። ክፋቱ ሂትለር እርሷን በልቶ አለማቆሙ ነው እንጂ። ፖላንድን ከናዚ ጦር ነጻ ለማውጣት ስድስት መቶ አምሳ ሺህ የሩሲያ ጦር ነበር ያለቀው። በታሪኩ አሰቃቂ በተባለለት አስቸጋሪ የበረዶ ላይ ከበባ ዋጋ ለከፈሉትና ድፍን አውሮፓን ከናዚዝምና ከፋሽዝም ለታደጉት የሩሲያ ወታደሮች መታሰቢያ በፖላንድ ዋርሳው የቆሙትን ሃውልቶች ዛሬ ከአሜሪካ በላይ አሜሪካዊነት በሚሰማቸው የፖላንድ መሪዎች መፈራረስ በመጀመራቸው የሩሲያ መንግስት የወታደሮቹን አጽም በክብር ወደ አገሩ መልሶ ለማሳረፍ ቃል ገብቷል።ዛሬ ፖላንድ ማለት በምስራቅ አውሮፓ ውስጥ ያለች አንዱዋ የአሜሪካን ላፕዶግ መሆኗን በብዙ አጋጣሚ እያስመሰከረች ያለችበት ሁኔታ ነው ያለው።

በኛም አገር ለአገራቸው በጎ የዋሉ፤ ለማንነታቸው ዋጋ የሰጡና እራሳቸውን የተቀደሰ መስዋእት አድርገው ህዝባቸውን የታደጉ አባቶቻችን አጽመ እርስታቸው የሚያርፈው አዲስ አበባ በሚገኘው ዮሴፍ ቤተክርስቲያን እንደነበረ ይታወቃል። አርከበ እቁባይ የተባለ የባንዳ ልጅ የመናገሻውን ቢሮ በያዘ ሰሞን “የኒህን የነፍጠኞች ምናምንቴ አውጥተኽ ጣልልኝ!” ብሎ ባዘዘው መሰረት የዚያ ሁሉ የአርበኛ አጽም ነበር ድፍን አዲሳቤ በኣይኑ ብረት ቆሞ እያየ በቡልዶዘር ተጠራርጎ የፈረሰው። ከላይ በሌሎች አገሮች ተሞክሮ እንዳየነው ባንዳ ሁሉ ስነ ባህሪያቸው አንድ ነው። ሰሞኑንም የፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ፣ መልአከ ብርሃናት አድማሱ ጀንበሬና ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሤን አጽም አንሡ መባላችን ያው ከላይ በፖላንድ ካየነው እውነት ልዩነት የለውም። እንዲህ በማንነቱ የሚሸማቀቅ፣ የገዛ ታሪኩን የሚያዋርድና ገንዘብ ባየበት ሁሉ እንደ ሴተኛ አዳሪ የሚገለፍጥ የወያኔ አይነት ባህሪ ለምን የምእራባውያንን ልቦና እንደሚያማልል ግልጽ ነው። ዘመኑ የባንዳ ነው።

No comments:

Post a Comment