Translate

Friday, July 7, 2017

እፉኝቶቹን ተሸክመን የመጓዝ ግዴታ የለብንም (መስቀሉ አየለ)

Ethiopian historical art workመስቀሉ አየለ
አጼ ኃይለስላሴ በአንድ ወቅት ኒውዮርክ በሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ጽህፈት ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተው ነበር። ወቅቱ የፓን አፍሪካኒዝም ስሜት ጣራ የነካበት፤ ባሪያ ፈንጋዮቹ አፍሪካን ጥለው መፈርጠጥ የጀመሩበት፣ አፍሪካውያን በንስሮቹ ባለራእይ ወጣት መሪዎች ኩዋሚ ንክሩሁማን፣ ጁሊየስ ነሬሬ፣ ጆሞ ኬንያታ ወዘተ መመራት የጀመሩበት፣ ለሶስት ሺህ ዘመን የአፍሪካ ሳይሆን የመካከለኛው ምስራቅ አካል ሆና ታሪኳን፣ ወግ፣ ባህል፣ ቋንቋና ሃይማኖቷን ጭምር ከቤተ እስራኤል ስትዋረስ የኖረችው አገራችን ለመጀመሪያ ግዜ ፊቷን ወደ ጎረቤት አፍሪካውያን የመለሰችበት እና ይልቁንም በባርነት ለኖሩት አፍሪካውያን የነጻነት ቀንዲል በመሆን የአፍሪካ ህብረትን በመናገሻዋ ያኖረችበት በዚህም እስከ ካረቢያን ያሉ አንድ በሁኔታው የተደመመ የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጠኛ ንጉሱን እንዲህ ሲል ጠየቃቸው፤ “ለመሆኑ ኢትዮጵያዊነት ምንድን ነው? ” እርሳቸውም ቆፍጠን ባለ አነጋገር “ኢትዮጵያዊነት ኩራትና ትህትና ነው” አሉት።

ጋዜጠኛውም ቢሆን የዋዛ አልነበረምና “ይቅርታ ያድርጉልኝ ጃንሆይ ይሄ ሃምብልነስ እና ፕራውድነስ የሚሉት ነገር እራስ በርሱ የሚጣረስ ማንነት አይመስልዎትም ወይ” የሚል ጥያቄ ያስከትላል። ንጉሱም እንዲህ አሉ፤ “አየኽ አንድ በጣም ተራ የምትለው ገበሬ ቤት በእንግድነት ብትሄድ ያለውን እራት አብልቶ፣ እግርህን አጥቦ፤ ያጠበውን እግርህን ስሞ፣ አልጋውን ላንተ ለቆ እርሱ ግን መሬት ላይ ይተኛል። በዚያው ልክ በሚስቱና በርስቱ ላይ ብትመጣበት ደግሞ በግንባርህ ላይ ጥይት ይቆጥርለሃል፤ ስለዚህ አይጋጭም፤ ነገር ግን ይሄንን ነገር ለመረዳት አንተ ራስ ህ ኢትዮጵያዊ መሆን አለብህ” ነበር ያሉት።
የዘመኑ ጭንጋፎች ነፍጠኛ የሚሉት እንዲህ አይነቱን ስነ ልቦና ነው። ጻድቁ ፕሮፌሰር አስራት “ነፍጠኛ ነኝ፤ ሃኪም ነኝ፤ አውሮፕላንም አበራለሁ” ሲሉ ገና በጠዋቱ አፈፍ ብለው የተነሱት የዘፈን ዳርዳሩ ስለገባቸው እንደነበር ዛሬ ላይ ቆሞ ወለል ብሎ የማይታየው የለም። ወንጀል ሆኖ ዋጋውን በህይወት ያስከፈላቸው ይሄው በውስጣቸው የተጻፈው ኪዳን ነበር።ክርስቶስ በደሙ ዋጋ ቤተክርስቲያንን እንዳነጻት ሁሉ ይህ በነፍጠኛው ደም የተጻፈው ኪዳን አገሪቱን ከነሙሉ ታሪኩዋና መንፈሳዊ እሴቷ ጠብቆ ለማቆየት የተከፈለው ዋጋ ነው። የዚህች አገር እጣ ፋንታም የሚያሳስበው፣ እዳዋም ከትከሻው የማይወርደው ይኼው የባለቤትነት ውርስ ነው።ምንም እንኳን ዛሬ ከውጭ ከመጣ ወራሪ መንጋ ጋር እያበሩ ይኽችን አገር ሲያደሙ የኖሩት የባንዳ ልጆች የቀዝቃዛውን ጦርነት ማለቅ ተከትሎ የደፈረሰው የታሪክ ወንዝ አምጥቶ አራት ኪሎ አምጥቶ ስለደፋቸው አገሪቷን ለመበቀል ከመቸውም ግዜ በላይ የተሻለ እድል ማግኘታቸው እሙን ቢሆንም ቅሉ ከነሱ የረጅም ግዜ ክፉ ምኞት በላይ ትልቁ ማነቆ የሆነው ግን ዛሬም ድረስ ከክህደት ታሪካቸው ባለመማር እነዚህ የእፉኝንት ልጆች በግድ ኢትዮጵያዊ አድርገን የመቀጠላችን ኩነት ነው።
ለመሆኑ ኢትዮኦጵያዊነት ለዚህ ትውልድ ምንድን ነው?
ኢትዮጵያዊነት እንጀራ መብላት ከሆነ ዛሬ አበሻ በተሰደደበት አገር የጤፍ እንጀራውም ተሰዶ ከቤጂንግ እስከ ሳንፍራንሲስኮ ከኖርዌይ እስከ ደቡብ አፍሪካ የውጭው አገር ዜጋም እየለመደው ነው። አገርኛ ቋንቋ መናገር ከሆነ ኢትዮጵያ ውስጥ ተወልደው ያደጉ ብዙ አርመኖች፣ ግሪኮችና የዛሬ ኤርትራውያን ኢትዮጵያዊ ሆነው አልቀጠሉም። ይልቁንም ኢትዮጵያ ብትሞት ሌላ አገር አላቸውና። ኢትዮጵያ ውስጥ ትንሽ ህንጻ ማቆም የኢትዮጵያዊነት መለያ ቢሆን ቢሆን ኖሮ ጣሊያን የተሻለ ኢትዮጵያዊ ይሆን ነበረ። ኢትዮጵያዊነት ማለት የዚህችን አገር ህመም መታመም ነው። በደስታዋ መስከር ነው። ለክብሯ መሰዋት ነው። በስሟ ማህሌት መቆም፣ጸሎተ እጣን ማሳረግ ነው። በዚህ ስሌት ከሄድን የተከዜ ማዶ ተውሳኮች እጣ ፋንታ ግልጽ ነው። በዚህች አገር ወርድና ቁመና ስር ሊገቡ የማይቻላቸውን እኒህን ጋንግሪኖች ይዞ በታሪክ ስም መገዝገዙ ሊበቃን ይገባል።ኖረው ቀርቶ ሞተው እንኳን መቃብራቸው ላይ የሚበቅለው እሾን ምን ያህል ጋሬጣ እየሆነ እረፍት እንደሚነሳ መለስ ዜናዊ ከተባለ ልቡሳነ ስጋ ያየነው ሃቅ ነው። ታሪክ ማለት እንደነዚህ ካሉ የደደቢት ተውሳኮች ጋር “አብሮ መኖር” ከሆነ ታሪክ ገደል አባቱ ይግባ።

No comments:

Post a Comment