Translate

Thursday, July 20, 2017

አዲስ አበባ ወይብላ ማሪያም አካባቢ የሚገኙ ሱቆች ተዘግተው የሚያሳይ ፎቶ | ሽሮሜዳም በውስን ተዘጋግቶ ነበር

(ዘ-ሐበሻ) ሕወሓት መራሹ መንግስት በሕዝብ ላይ የጣለውን አግባብ ያልሆነ ግብር በመቃወም ነጋዴዎች ሱቆቻቸውን መዝጋታቸውና በአዲስ አበባ የተለያዩ ቦታዎች የሥራ ማቆም አድማ መደረጉን መዘገባችን አይዘነጋም:: በአዲስ አበባ ወይ ብላ ማርያም አካባቢ ሱቆች ተዘጋግተው የሚያሳዩ ፎቶዎች ደርሰውናል:: በሌላ በኩል በሽሮሜዳ አካባቢም በመጠኑ ሱቆችን የመዝጋት ተቃውሞ ተጀምሮ እንደነበር ምንጮች ገልጸው አንዳንድ ለሥርዓቱ ያደሩ ነጋዴዎች ሱቆቻቸውን መክፈታቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል:: እንደ ነዋሪዎች ገለጻ ከስርዓቱ ጋር ንክኪ ያላቸው እነዚህ ነጋዴዎች ከሕዝቡ ጋር የማይተባበሩ ሲሆን ሊደርስባቸው ለሚችለው ነገር ኃላፊነቱ የነሱ ነው ብለዋል::






No comments:

Post a Comment