Translate

Saturday, March 16, 2013

የ« ሪፖርተር» አዘጋጅ አማረ አረጋዊ ማላገጥህን አቁም!


Image
(ከኢየሩሳሌም አርአያ)
አማረ አረጋዊን የማውቀው ጋዜጣውን ሲጀምር ነው፤ አብሬው ለሶስት አመት ሰርቻለው። …አማረ የግል ጥቅሙ እስካልተነካ ድረስ በአገርና ሕዝብ ላይ የፈለገ ነገር ቢፈፀም ደንታ አይሰጠውም። <ፍትሕ> እና <ፍኖተ ነፃነት> ጋዜጦች ከህትመት ውጭ ሲደረጉ « የፕሬስ ነፃነት ይከበር» ብሎ አንድ መስመር በርዕሰ አንቀፅ አልፃፈም፤ እንዲያውም የ<ፍኖተ ነፃነት> አዘጋጆች ስለጉዳዩ አማረን ሲያናግሩት በረከትና ሽመልስ ከሚሰጡት መልስ ጋር የሚመሳሰል ምላሽ በማመናጨቅ ጭምር ነበር የሰጠው። በአንፃሩ የእርሱ ጋዜጣ ገፁ ሲቀነስ፥ ያዙኝ-ልቀቁኝ እያለ ስለ ፕሬስ ነፃነት ይደሰኩራል። የህሊና እስረኛ የሆነው እስክንድር ነጋን እስር ለፕሬስ ነፃነት የሚከፈል ዋጋ መሆኑን አማረ ሊናገር አይፈቅድም። ለነገሩ አማረ – ለእስክንድር ያለውን አመለካከት በጣም አውቃለሁ!! ነሃሴ 13 1997ዓ.ም ቦሌ ከአማረ ጋ ተገናኝተን ያለኝን (ስለ እስክንድርና ሲሳይ ያለውን ጥላቻ) እራሱም የሚዘነጋው አይመስለኝም። ..አሁንማ ቴሌቪዥን ሊጀምር ስለሆነ ከእንግዲህ « በኢትዮጲያ ነፃነት ተረጋገጠ…» እያለ አማረ እንደሚለፈልፍ አያጠራጥርም። …ሌላው « ፍትህ የለም፤ ሙስና ተንሰራፋ…» እያለ በሚለቀልቅበት ብዕሩ መልሶ « እነ እከሌ በሽብርተኝነት ተከሰው..» በማለት የ4ኪሎው መንግስት በውሸት የሚፈበርከውን «ክስ» ተብዬ «ትክክል» አድርጎ ለማቅረብና ለቀድሞ ጓዶቹ «መስዋዕት» ሲሆን በተደጋጋሚ ይታያል።
በተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ እየደረሰ ያለውን እንግልት፡እስርና ግድያ… አይቶ እንዳላየ በመሆን «ተቃዋሚን ያየህ ወዲህ በለኝ» እያለ በነአንዱዋለም አራጌ፡ በቀለ ገርባና ሌሎች ላይ ለማላገጥ..እግረ መንገዱን ደግሞ ገዢው ፓርቲ ብቻ አገሪቱን መምራት እንዳለበትና « መንገድም ህይወትም ሕወሓት ብቻ ነው » እያለ ሊሰብክ ይፍጨረጨራል። በጣም የሚያሳፍረው « ሕዝብ…እንዲህ አለ..» እያለ የሚዘላብደው ነገር ነው። መቼና የት ቦታ ነው « ሕዝብ ኢህአዴግ ይሻለኛል..» ያለው?.ለሚለው ምንም .አይጠቅስም፤ ..ሌላው ስለሙስሊሙ ሕገ መንግስታዊ የመብት ጥያቄ ትክክለኛነት ሊዘግብ ቀርቶ..ከዚህ በተቃራኒ « በሽብርተኝነት የተጠረጠሩ…» ወዘተ.እያለ የአለቆቹን የውሸት ድርሰት ተቀብሎ ሌሎችን ሊያደናግር ይቃጣዋል፤ በሙስሊም ወገኖቻችን ላይ በየቀኑ ስለሚፈፀመው ስቃይና የመብት ረገጣ ደንታ ስለማይሰጠው – ተፅፎ ስለሚሰጠው የሽብርተኝነት ድርሰት ያላዝናል። በዚህ ሳያበቃ « በድሬዳዋ በተናሳ ግጭት አንድ ታዳጊ ከመሞቱ በቀር የከፋ ጉዳት አልደረሰም» ሲል ያለሃፍረት በህፃን ልጅ ደም ያላግጣል። ስንት ሰው መሞት ነበረበት?..
አማረ፥ ወገናዊነትህንና አቋምህን ለጊዜው ልተውና አንድ ጥያቄ ብቻ ልጠይቅህ፤ ሁለት ልጆች እንዳሉህ አውቃለው፤ እስቲ አንዱ ልጅህን በድሬዳዋ በተገደለው ልጅ ቦታ አድርገህ ውሰደው፤ የተገደለው ያነተ ልጅ ቢሆንና እንዲህ ያለ ዘገባ ቢቀርብ ምን ይሰማሃል?…ከሶስት አመት በፊት ልጅህን ከትምህርት ቤት ልትወስድ ቆመህ ተደበደብክ፤ አንተ በደረሰብህ አደጋ ልጅህ የሚሰማው ስሜት ምን አንደሆነ ግልፅ ነው፤ ያንተ ልጅ የተሰማው ስሜት አይነት ፥ እስክንድር ከት/ቤት ሲያመጣው በነበረው ልጁ ላይ የፈጠረው መሪር የሃዘን የተለየ አይደለም!! ነገር ግን የአንተ «ሕሊና» ይህንን ማየት አይፈልግም! ማመዛዘን አልፈጠረበትም!!…ፖሊስ ከፎቅ ላይ ወርውሮ የገደለውን ወጣት « በመለስ ሞት አዝኖ ራሱን አጠፋ» ብለህ የድራማው አካል ሆነህ ስትተውን፤ በአንፃሩ ስለ የኔሰው ገብሬ አንድ መስመር ትንፍሽ አላልክም።..አማረ ያንተን ማንነት ዲሲ የሚገኘው ወንድምህ ( ድሙ) ጭምር በግልፅ የሚመሰክረው ነው። ዛሬ ጀመርኩ እንጂ አልጨረስኩም። ብዙ ስላንተ የምላቸው አሉኝ። በቀጣይ እመለስባቸዋለሁ።..

No comments:

Post a Comment