Translate

Tuesday, March 26, 2013

በአረመኔው የወያኔ አገዛዝ በግፍ እስር ቤት የታጎሩት ሙስሊም ኢትዮጵያዊያን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከፍተኛ ችግር ላይ መውደቃቸው ታወቀ


በአረመኔው የወያኔ አገዛዝ በግፍ እስር ቤት የታጎሩት ሙስሊም ኢትዮጵያዊያን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ከፍተኛ ችግር ላይ መውደቃቸው ታወቀ

ድምጻችን ይሰማ የሚል መፈክር አንግበው ላለፉት አስራ ሶስት ወራት አፋኙን የወያኔ አገዛዝ መቆሚያና መቀመጫ በማሳጣታቸው በጭካኔ እስር ቤት የተጣሉት ሙስሊም ኢትዮጵያዊያን ከፍተኛ ችግር ላይ መውደቃቸውን ዘጋቢያችን ከአዲስ አበባ ባስተላለፈልን ሪፖርት ገለጸ፣ ፣ እንደዘጋቢያችን ሪፖርት በዘረኛውና አረመኔው የወያኔ አገዛዝ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ታፍሰውና ማእከላዊ እስር ቤት ውስጥ በግፍ ታስረው የሚገኙት ሙስሊም የዩኒቨርሰቲ ተማሪዎች ፣ ቤተሰቦቻቸው ያሉበትን ቦታ ባለማወቃቸው በቀለብ እና በልብስ እጦት እየተቸገሩ ነው ብሏል።
ዘጋቢያችን እንደገለጠው በአቃቂ እስር ቤት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሙስሊም ተማሪዎችና መምህራን እስር ቤቱን አጨናንቀው እንደሚገኙ ለማወቅ የተቻለ ሲሆን ፣ ከነኝህ ታሳሪዎች ውስጥ እጂግ በርካቶቹ ቶርቸር ( አሰቃቂ ድብደባ) ተፈጽሞባቸዋል። ይህም አልበቃ ብሎ ተማሪዎቹ በአሁኑ ጊዜ የረባ ምግብ አጥተው በመሰቃየት ላይ እንደሚገኙና ልብሶቻቸው በላያቸው ላይ እያለቁባቸው ለእርዛት እየተዳረጉ እንደሆነም ታውቋል።

አሁንም ጭካኔአዊ አሰራው አለማብቃቱና የተለያዩ ታማሪዎች በየጊዜው እየተያዙ መሆኑን የገለጸው ዘጋቢያችን በማእከላዊ እስር ቤቶች ውስጥ ታስረው ከሚገኙት መካከል የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ተማሪ የሆኑት ኑርየ ካሲም እና ካሊድ ሙሀመድ፣ የጅማ ዩኒቨርስቲዎቹ ያሲን ፈይሞ፣ ሙሀመድ አሚን ከድር፣ እና ጁነዲን ሁሴን፣ የሚዛን ተፈሪው አብዱላኪም አህመድ፣ የወሎ ዩኒቨርስቲዎቹ ጣሂር ሙሀመድ ፣ ሙሀመድ አብዱራሂም እና ሰኢድ ሙሀዲን፣ የጎንደር ዩኒቨርስቲዎቹ ሰኢድ አብርሀም ፣ኦማር ሙሀመድ፣ እና ሊና ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲው አብዱላዚዝ ሰኢድ እንዲሁም የአዋሳ ዩኒቨርስቲዎቹ አብደላ ሙሀመድ ይገኙበታል ብሏል።
የሙስሊም ጉዳይ አምደኛ የነበረው ሶሎሞን ከበደ፣ የከሚሴው ዳኢ ጀማል ከበደ፣ የሻሸመኔው ዳኢ አብዱረዛቅ ሼህ አህመድ፣ የከሚሴው ዳኢ ኢክርሀም አብዱ፣ የሀረርጌው ሁሴን ሮባ፣ የድሬዳዋው ሙሀመድ ሀሰን፣ የከምሴው ሁሴን አሊ እና አደም አህመድ አሊ በማእከላዊ እስር ቤት ከታሰሩትና ከፍተኛ ስቃይ ከደረሰባቸው መካከል ይገኙበታል።
የወያኔ ኢህአዴግ ፈረስ የሆነው ሀይለማርያም ደሳለኝ የሙስሊሙን እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር እርምጃ እንወስዳለን በማለት ሰሞኑን በባህርዳር በመካሄድ ላይ ባለው የወያኔ ኢህአዴግ ጉባኤ ላይ መዛቱንም ተያይዞ የደረሰን ዘገባ አመልክቷል።

No comments:

Post a Comment