Translate

Sunday, March 23, 2014

የአንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን ምክር ቤት ስብሰባ በመንግስት ካድሬዎች በሀይል ተደናቀፈ

የአንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን ምክር ቤት ስብሰባ በመንግስት ካድሬዎች በሀይል ተደናቀፈ

Update:
ከ32 የሚበልጡ የአንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን ምክር ቤት አባላትና አመራሮች ንብረቶቻቸው ተቀምቶ ወደ ፖሊስ ጣቢያ እየተጋዙ ነው፡፡ የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራ እና ምክትል ኃላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ሺበሺ ከፓርቲው የተላኩ መሆኑን የሚያሳየውን ደብዳቤ ጨምሮ መታወቂያቸው ሳይቀር በካድሬዎቹ ተነጥቋል፡፡
————————-
የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራ እና ምክትል ኃላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ሺበሺ ደህንነታቸው አደጋ ላይ ነው፡፡
የሟቹን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር የአቶ መለስ ዜናዊ ምስል ያለበት ቲሸርት የለበሱ ከ10 የሚልቁ የመንግስት ካድሬዎች በወላይታ ሶዶ እየተደረገ የነበረውን አንድነት ፓርቲ የወላይታ ዞን ምክርቤት ስብሰባን በሀይል ማደናቀፋቸውን ከስፍራው ለፍኖተ ነጻነት የደረሰው ዘገባ አመለከተ፡፡

ካድሬዎቹ የስብሰባ አዳራሹን በሃይል በመስበር ከተሰብሳቢዎቹ ላይ የተለያዩ ሰነዶችን የቀሙ ሲሆን ድብደባ በመፈፀም ላይ ናቸው፡፡ በስብሰባ አዳራሹ ውስጥ የነበሩት የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራ እና ምክትል ኃላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ሺበሺ ደህንነታቸው አደጋላይ መሆኑን ለፍኖተ ነፃነት ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፣ ፍኖተ ነጻነት
ከታሰሩት የአንድነት አመራሮች መካከል፣
Andinet party leadershipAndinet party leadership in Southern Ethiopia

No comments:

Post a Comment