Translate

Thursday, March 20, 2014

የአባ በላ ፍቅር እስከ መቃብር (ማህሌት ነጋ)

በማህሌት ነጋ

“ሃይለማሪም ደሳለኝ አብዩዝድ ነው። እንደውም ማታ ማታ (በህወሃቶች) ሳይገረፍ አይቀርም!” ብሎ ነበር ብርሃኑ ዳምጤ ከጥቂት ወራት በፊት በፓልቶክ ላይ።….
ESAT brings Aba Mela as a political analyst“ስለ አንድ ሰው ስንጽፍና ስንናገር ቢቻል አዎንታዊና መልካም ከሆኑ ነገሮች መጀመር ጥሩ ነው” ይሉ ነበር “የኔታ” በሚል ቅጽል ስም እንጠራቸው የነበሩ የዘጠናኛ ክፍል የአማርኛ አስተማሪያችን። ቀጭንና የዋህነት የተላበሰ ፊታቸው ላይ ችፍ ብሎ የማርክስን ግርማ ሞገስ ያጎናጸፋቸውን ገብስማ ሪዝ በእጃቸው እየዳበሱ ያስተማሩኝ ትዝ አለኝ።
ነገሩ የድሮ ትምህርት ቢሆንም የተማርኩትን በማሰብ እንደ አዞ ደንዳና ቆዳ ስለ ታደለው ብርሃኑ ዳምጤ ለመጻፍ ስነሳ ከልቅ አፉ ባሻገር ከማደንቅለት ባህሪው ብጀምር መልካም ነው ብዬ አሰብኩ።
ማንም በቀላሉ ሊክደው የማይችለው ሃቅ ብርሃኑ ዳምጤ (አባ መላ) የፍቅር ሰው ነው። ብርሃኑ ለፍቅር ሲል ብዙ መስዋእትነት ከመክፈል አልፎ በስደት ዘመኑ ሳይቀር እንደ ዘላን ብዙ ተንከራቷል። የሚገርመው ነፍስ ካወቀ ጀምሮ እስካሁን ያፈቀረው አንድ ብቻ ነው። ለፍቅረኛው ሲልም ብዙ ተሰቃይቷል፣ ወደ ፊትም መሰቃየቱ አይቀሬ መሆኑን ለመተንበይ ቀላል ነው።

ታዲያ ብርሃኑ “ሆዴ! ያላንቺ ማን አለኝ!” እያለ በፍቅር የሚያቆላምጣት አይኗ የሚያማልሉ፣ አፍንጫዋ ሰልካካ፣ ጸጉሯ የሃር ነዶ የሚመስሉ የቆንጆ ቆንጆ የሆነች ኮረዳ እንዳትመስላችሁ። በተቃራኒው፣ አፍንጫም፣ አይንም የሌላት ትልቅና ወደፊት የተገፋ ጆንያ የሚመስል ግንባር ብቻ ያላት መሆኗን ጠንቅቆ ያውቃል። ያለባት አንድ ትልቅ ችግር የመኖ ነገር አይሆንላትም። በቀላሉ አትጠረቃም። ቢሆንም ነፍሱ እስኪወጣ ይወዳታል።
በፍቅር “ሆዴ! ሆዴ! ” የሚላትም ሌላ ሳትሆን በስተርጅና አክሮባት የምታሰራው ሆዱን ነው።
“ሆድ፣ ሆዴ! ያላንቺ ማን አለኝ!” እያለ ዘውትር በፍቀር የሚዳብሳት ፍቅረኛ። የሚያቃጥል ፣ የሚያንቀዠቅዥ፣ ህሊና የሚያስት ፣የሚያክለበልብ፣ ቀልብ የሚያሳጣ ከሁሉም በላይ የሚያዋርድ የሆድ ፍቅር ቢባል ማጋነን እንደማይሆን እርግጠኛ ነኝ።
የታደለ ለነጻነት፣ ለፍትህ፣ ለእኩልነት፣ ለሰላም መስዋእትነት ሲከፍል፣ በየእስር ቤቱ ሲሰቃይ የቁብና የእድር ዳኛ ለመሆን ብቃት የሌለው አጭቤ ግን በሆድ ፍቅር ተቃጥሎ የሆድ ማንዴላ ሆኖ እንደ ረከሰ ሴተኛ አዳሪ በየአደባባዩ ከንቱ ስብእናውን በስሙኒ እየቸረቸር ለከፈሉት ሁሉ እየደነሰ ይኖራል። ኑሮ ካሉት…መሆኑ ነው።
ታዲያ ሰሞኑን ከተቃዋሚ ጎራ አመለጥኩ እያለ እያለከለከ ቤን (ሆድፈርስት) እና ሰለሞን ቅንድቡ በተባሉ እርካሽ የሆድ ውጠራ የትግል አጋሮቹ በኩል የለመደውን ቱሪናፋ ሲቸረችር አያቴን አስታወሰኝ። አፈሩ ይቅለላትና አያቴ የአባ መላ አይንቱን የመለፍለፍ ልክፍት ያለበትን ቅል ስታይ “አሻሮ የበላ አሻሮ ያገሳል” ነበር የምትለው።
እውነት ለመናገር ነገሩ ሁሉ ብርሃኑ መኖ ፍለጋ መጣ መኖ ፍለጋ ተመለሰ ወይንም ተገለባበጠ መሆኑን ስለምናውቅ እራሱን ማግዘፍ ያልተሳካለት ምስኪን ሆድ ወዳድ ምን ቢናገር ሊያስከፋን አይችልም። በነገራችን ላይ አባ መላ የሚለው ስም ስለሚያንስበት ከዚህ በኋላ አባ በላ በሚል የማእረግ እድገት እዲሰጠው ፍቃዳችሁ ይሁን።
አንድ ምስክር እንዳለው አባ በላ መብላት የሚያቆመው ሲጠግብ ሳይሆን ሲደክመው ብቻ ነው። ታዲያ አባ በላ በመፈረካከስ ላይ ካለው ከወያኔ መንደር አምልጬ መጣሁ ብሎ እያለከለ እንደመጣ መጀመሪያ ያቀረበው ጥያቄ የመኖ ነበር። “ይከፈለኝ” አለ። ለከፋዮቹ ችግር የሆነው ምን ሰርቶ ምን እንደሚከፈለው ማጣራት ነበር። ከፓርክንግ ሎት ምንተፋ ባሻገር ሙያ የለው፣ ትምህርት የለው፣ እውቀት የለው፣ አመል የለው፣ ግብረገብ የሌው፣ ግራ የሚያጋባ ጉዳይ ነበር።
የመጣው ባዶ እጁን ግን ደግሞ ትግስት የሌለው ቀዥቃዣ ቢሆንም “ሆደ ሰፊ” መሆኑ የታወቀ ጉዳይ ነው። ይከፈለኝ ሚስጥር ይዤ መጥቻለሁ፣ የወያኔ ሰላዮች በአሜሪካና በአውሮፓ ስምዝርዝርና አድራሻ አለኝ አለ። በርግጥ ለዚህ ጠቃሚ መረጃ ክትፎ ምናምን ተገዝቶለት መረጃውም ለሚመለከታቸው የአሜሪካና አውሮፓ መንግስታት መመራቱን ሰምቻለሁ።
በኢሳት ላይ ካልወጣሁ፣ መድረክ ካልሰጣችሁኝ አለ። የሚገርመው ግን በኢሳት ላይ ቃለምልልስ ለማድረግ እንኳን ይከፈለኝ አለ። ኢሳቶችም ለዚህ አንከፍለም አሉት። ምንም እንኳን መጀመሪያ ይከፈለኝ ሲል የቀረበው በስካይፕ ቢሆንም ቢያንስ ለትራንስፖርት ይከፈለኝ አለ።። የሆድ ነገር፣ የሆድ ፍቀር፣ የሆድ ትግል ነው ነገሩ ሁሉ።
የተቃዋሚው ጎራ አስቸጋሪ ትግል እንጂ መኖና አረቄ እንደሌለው ሲገባው ነገሩ ሁሉ ሊጥመው አልቻለም። እርሱ ሃሳቡ ሁሉ በቀላሉ የማትረካውን ፍቅረኛውን “ሆዴን!” ሞልቶና ሸንግሎ ማሳደር ነው።
ያም ሆነ ይህ ስለ አባ በላ ብዙ መጻፍ አያስፈልግም። ጓዙን ጠቅልሎ፣ ሆዱን ታቅፎ እያለከለ በመጣበት መንገድ ሄዶ የድሮ ጌቶቹ እግር ስር እያለቀሰ ማሩኝ ቢልም እኛ ድምጹን ቀርጸን ስላስቀረን ይሂድ ተውት። ድሮም ቢሆን ጅብ በጨለማ እንጂ በብርሃን ኑሮ አይሳካለትም።
ያልተማረው ተንታኝ አባ በላ እንደ ጀብድ የሚቆጥረው ስራ ፈቶ ፓልቶክ ላይ ተጥዶ የቆጥ ያባጡን መቀባጠሩን ነው። ለማንኛውም አባ በላ መንግስት የለም ወያኔ አልቆለታል እያለ ከዘፈናቸው ዘፈኖች መሃል አለፍ አለፍ እያልን እናዳምጥ። ወጪት ሰባሪ የሆነው አባ በላ ጌቶቹን የሚያጋልጡ በርካታ ዘፈኖች ስለዘፈነ ቀስ በቀስ እያወጣን እንዝናናባቸዋለን። እነዚህን ከታች ለናሙና የመረጥኳቸውን የውስጥ አዋቂው የአባ በላን ንግግሮች (ዘፈኖች) በጥሞና ይከታተሉ።

ሃይለማሪያም ደሳለኝ “አብዩዝድ” ነው

Ethiopian PM Hailemariam Desalegn on Al Jazeeraሃይለማሪያምን ተዉት፣ እኔ ለሃይለማሪያም ማዘን ጀምሪያለሁ። እኔ እንደውም ከሳውዲ ከተመለሱት ሰዎች አንዱ ይመስለኛል። ምክንያቱም የት ጠፋ ይሄ ሰውዬ። በሳውዳአረዲያ ነበረ ማለት ነው። እና ሰሞኑን እንሰማለን ማለቴ ነው። አንዱ abused የሆነ ሰው ነው ማለቴ ነው። እርሱ እኮ ሰልፍ ሊወጣለት የሚገባው ሰው
ነው። ግን ጥሪ ለምን እንደማያቀርብ አይገባኝም። አለ አይደለም እንደዚህ abused እደረጋለሁ፣ እንደውም ማታ ማታም ሊገረፍ ይችላል። ምክንያቱም በጣም
ተደነባብሯል።
የሚያወራው ነገር ሁሉ ግራ የሚያጋባ ነገር ነው። እርሱን ተዉት እንደ መሪም አትቁጠሩት። እሱ እንደ ሰው ህሊና ቢኖረው immediately resign ማድረግ
አለበት። እውነቴን ነው፣ ከልቤ ነው። መናቄ አይደለም። ምክንያቱም authority ሲባል de facto power ሊኖረው ይገባል። ዝምብሎ መቀለጃ ስትሆን፣ you have to resign። ብዙ ስራ አለ ለሱ የሚሆን። ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ የኮብል ስቶን ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት አለ። አንዱን ሊመራ ይችላል። በደቡብ የሚካሄደውን የኮብል ድንጋይ ምንጣፍ ቢከታተል ይሻለዋል። ምን አጨቃጨቀው ከነዚህ ሰዎች ጋር።

ሳሞራ ዘረኛ ነው

Samora Muhammad Yunis is the Chief of Staff of the Ethiopian National Defence Forcesአሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ስትመለከት structurally እከሌ ሚኒስትር ነው ይሉሃል ምክትሉ ደግሞ ሌላ ሰው ነው። ዋነው ሰውዬ አይደለም አለቃው፣ ምክትሉ ነው አለቃው። እኔ በቅርብ ቦታውን አልጠቅስልህም የመከላከያ ሚኒስትሩ እዚህ መጥተው ነበር፣ ዋሺንግተን ዲሲ። አብሯቸው ኢታማዦር ሹሙ ሳሞራ ነበር።
የውጭ አገር ሰዎች ሁሉ ያሉበት ዲነር ነው። ሌሎችም ባለስልጣኖች ነበሩ። እኔም ነበርኩ። ኢታማዦር ሹሙ መከላከያ ሚኒስቴሩን ይሰድበዋል፣ በዘሩ። ፈረጆች ባሉበት እኮ ነው። ቀለድኩ ነው የሚለው። እንዲህ አይነት ቀልድ አለ እንዴ። በወታደራዊ ስርአት ውስጥ መከላከያ ሚኒስቴር ማለት ትልቅ power ነው ያለው።
አንተ አስር አለቃ ሆነህ ሃምሳ አለቃው ሲመጣ ቆመህ ነው ሰላምታ የምተሰጠው… አንድ ኤታማዦር ሹም፣ምንም ልምድ የሌለው ጎሬላ ነው። በጣም ጨዋ ሰው
ነው መከላከያ ሚኒስቴሩ፣ እኔ ስለማውቀው ነው። በጣም ነው የተናደደው (አቶ ሲራጅ ፈርጌሳ)። ደሞ እኮ አስተርጉሞ ለፈረንጆች ሊነግራቸው ይፈልጋል። ጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዘናዊ አሉ ብሎ ነው የሚያወራው። የዚህን ሰውዬ ብሄረሰብን እንደ ሌባ አድርጎ ነው ይሚቆጥረው።…እኔ እንደዛን ቀን ደሜ ፈልቶ አያውቅም።
ብዙ ሰዎችም የሚያውቁት በብዙ ነገር ነው፣ የኢትዮጵያ ህዝብ አንዱ መቼም የሚፋረደው እሱን (ሳሞራን) ነው። በመከላከያ ውስጥ የተጠላ ሰው ነው። ይሄንን ሰውዬ ሲያዋርደው ስታይ really በዚያን ለት ዲነሩ አንዳለ ነው የተበላሸው…። አንተ ሚኒስቴር ስለሆንክ አይደለም ዘበኛው (ህወሃት ከሆነ) ሊኒቅህ ይችላል።…አንድ ስርአት structural problem ካለብት ሚኒስቴሩን ሹፌር የሚያዘው ከሆነ…አሁን እዚህ ዋሺንግተን ኤምባሲ አንድ ሰለሞን የሚባል ሃያ አመት የሚያውደለድል አለ። ምን እንደሚሰራ አይታወቅም፣ ።።ሰላይ ነው ልጁ መሰለኝ…ሰላሳ አምባሳደር ይቀያየራል። እርሱን የሚነካው የለም። ሾፌር ነው መደበኛ ስራው። ግን he is powerful than the ambassador, even ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ የበለጠ። እንደዚህ አንደዚህ አይነት ሰዎች ናቸው እዚህ የሚመደቡት።….

አዜብ መስፍን አጭበርባሪ ናት

Azeb Mesfin, the wife of Meles Zenawiባክህ ተው አዜብ ምናምን ይለኛል። በሶስት መቶ ብር፣ በሁለት መቶ ብር ነው የምኖረው ምናምን ትላለች። ያልጠየቋትን ትለፈልፋለች። በሁለት መቶ ብር ነው እንዴ አሜሪካ በየግዜው የምትመጣው። ምን አይነት የምን ገንዘብ ነው? እኔ እሱ አይደለም፣ ስለሱ ችግር የለብኝም።…ይሄንን የሚገዛ ሰው ካለ ይግዛ stupid ሰው ካለ እንጂ አራት ሺ ብር ደሞዝተኛ የ100ሺ ብር ቦርሳ የምትገዛ ሴትዮ “አራት ሺ ብር ምናምን” ትላለች። በቃ ይሄው ነው።
First of all, የምትሰጣቸው ኮሜንቶች backfire የሚያደርግ ነው። መለስ መንጃ ፍቃድ የለውም፣ ባንክ አካውንት የለውም …ምን ማለት ነው? ቤተሰቡን take care የማያደርግ ፍጡር ምን አይነት መሪ ነው? እንዴት ነው መንጃ ፈቃድ የሌለው መሪ የሚኖረው በአለም ላይ?…እንዴት ነው ባንክ አካውንት የሌለው መሪ የሚኖረው? ይሄ irresponsibility ነው። ቤለሰብህን handle ማድረግ አለብህ…. መታወቂያ ሊኖርህ ይገባል። መታወቂያ የሌለው መሪ ነው እንዴ ሲመራ የነበረው። ምንድን ነው የሚያወሩት?…ስለገንዘብ የማያውቅ መሪ ነው?… እንዴት ነው ስለገንዘብ የማያውቅ ሰው ስለሃገር ኢኮኖሚ ሲወስን የነበርው? ይሄ ጥሩ ነገር አይደለም። ለማን ተይ እንዳላሏት አልገባኝም።
እሷ ገንዘብ የሚመስላት በቼክ የሚሰጥ ነው። How about የቤተ መንግስት ኦዲት የማይደረገው ገንዘብ…እማይወራረድ ገንዘብ አለ፣በሚሊዮን የሚቆጠር። ገንዘብ ሚኒስቴር የማያውቀው። እሱ ገንዘብ አልመሰላትም እንዴ?….How about ኤፈርት? የኤፈርት ስራ አስኪያጅ አይደለችም እንዴ?… ስለዚህ እንደዚህ አይነት ነገር ያመኛል። እንደዚህ አይነት childish የሆነ ፉገራ። እንደ ሃገር ደግሞ ሊያመን ይገባል።…አውቃለሁ የዚህ የዶክተር ጌታቸውም ጠበቃ እርሷ ነች። I know that, አጭበርባሪ ነች። የኢህአዴግ ዘጠነኛ ጉባኤ አድርባይነትን ተዋጉ ብሎናል ይሄ ሩም በአር ያነት እራሱን አስቀድሞ በአድር ባይነት ላይ ዘመቻ አውጇል።

የአቋም ለውጥ

ታዲያ ዛሬ አባ በላ ግርማ ብሩ አሞሌ ጨውና ብር ሲያሳየው እንደልማዱ ከሻቢያ አምልጨ ተመለስኩ እያለ ልፈፋ ጀመረ። አይ አባ በላ! በኢሳት ላይ በግንባር ሲቀርብ ሲሳይ አጌና “ከወያኔ ካምፕ ምን አስወጣህ?” ብሎ ሲጠይቀው ደረቱን ነፋ አድርጎ “ህሊናዬ እንቅልፍ ነሳኝ” አለ።
በረጅም አረፍተ ነገርም እንዲህም አለ፣ “በየግዜው የምናያቸው ነገሮች እየተሻሻሉ መምጣትን ሳይሆን እጅግ በሚያሳዝን ሁናቴ በአገሪቱ ኢኮኖሚ፣ ፖለቲካ፣ ማህበራዊ ህይወት ውስጥ በተለይ ዲሞክራሲን ፍትህን፣ የመልካም አስተዳደር ችግር፣ የሰብአዊ መብት ጥሰት ህሊናህ ሊሸከመው ከሚችለው በላይ እየሆነ ሲመጣ ፣አገሪቱ የጥቂቶች ሆና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ባእድ ሆነው፣ ወጣቶች ሌት ተቀን ከዛች አገር እግራችን ይውጣ በሚል አገራቸውን እስከሚጠሉበት፣ ሴት እህቶቻችን በየአረብ አገሩ በሚሸጡበት፣ ጋዜጠኞች በመጻፋቸው እድሜ ልክ በሚፈረድበት፣ የኑሮ ውድነት በአለም ደረጃ ፍጹም ልትሸከመው በማትችል ደረጃ፣ ዛሬ ኢትዮጵያዊ ውስጥ የመንግስት ሰራተኛ እንዴት አድርጎ እንደሚኖር ሁሉ የማያውቅበት ሁናቴ ሲፈጠር ያንን ጉዳይ እንዲታረም ባለን ‘አክሴስ’ ሃላፊዎቹን ሁሉ እንትን ማድረግ እንሞክር ነበር።….ስር አቱ እርስበርስ መናበብም አልቻለም።….በጣም እሮሮ ያለብት ስርአት በመሆኑ ከዚህ መንግስት ጋር ሆነህ ለማስተካከል የምታደርገው ጥረት ዝም ብሎ ግዜ ማጥፋት ስለሚሆን እንደውም በሚሰራው ስተትና ወንጀል ላይ ታሪካዊ ሃላፊነት ይኖራል የሚል እንትን ስላለኝ ካለብኝ የዜግነትና የሞራል ጉዳይ አንጻር ጥያቄው አገር የማስቀደም፣ ህዝብን የማስቀደም ጉዳይ ስልሆነና የግል ጉዳይ ስላልሆነ የግዴታ ይህንን ስርአት በማንኛው መልክ ለማስተካከል ወይንም ለመለወጥ ከሚታገሉ ጎራ ዲሞክራሲያዊ ሃይል ጋር አብሮ መስራቱ ለአገር ይጠቅማል የሚል እምነት ላይ ደርሻለሁ። እና አሁን ሲሪየስ አቋም ነው ያለኝ።….”
“መቼም ይሄ በረጅሙ “በጄጄጄ!” የሚያስብል ጉዳይ ቢሆንም አያቴ “ጦጣ መንና ጫካ ገባች” የምትለው ተረቷን አስታወሰኝ።
አባ በላም ዝም ብሎ ህሊናዬ እንቅልፍ ነሳኝ የሚል ጨዋታ ጀመረ እንጂ አፈጣጠሩ ለህሊና ሳይሆን ለሆድ ስለሆነ ብዙ በአደባባይ መለፍለፉን ትቶ ሆዱን እየጠቀጠቀ ቢኖር ይመረጣል። እኔን ከአባ በላ በላይ የሚያሳዝኑኝ “የጨነቀው እርጉዝ ያገባል” እንዲሉ እርኩስ ጥንባቸውን ያወጣ ሆድ አደር ድጋሚ መቀጠራቸው ነው። ሳሞራ ዘረኛ፣ ሃይለማሪያም እርባና ቢስ አሻንጉሊት፣ አዜብ አጭበርባሪና ሙሰኛ፣ ስብሃት ሰካራምና ሴሰኛ፣ ብርሃነ ገ/ክርስቶስ ሌባ፣አባይ ወልዱን መሃይም፣ ቴድሮስ አድሃኖም ህጻንና እንጭጭ፣ ሽመልስ ከማል የማይረባ አድርባይ፣ አባ ዱላ ላንቲካ፣ ግርማ ብሩ እግር አጣቢ፣ በረከት ሴሰኛ….እያለ ፓልቶክ ላይ እንዳልጨፈጨፋቸው ዛሬ ሻቢያን ለመዋጋት ተመልሼ መጣሁ እያለ ያጃጅላቸዋል።…
አባ በላ ጠመዝማዛ መንገድ በከንቱ ተጓዘ እንጂ እውነታው እንዲህ ነው። የእርሱ ፍቅር እስከ መቃብር እንደነ ሰብለወንጌል የፍቅር ታሪክ የሚያማልል አይደለም። አባ በላ የሚያፈቅረው አብሮት የተወለደውን ሆድ ስለሆነ ጥቂት ቆይቶ አብሮት ይቀበራር። እኛም የሆድ ፍቅር እስከ መቃብር የሚለውን ታሪኩን ጽፈን የቀብሩ ስነስርአት ላይ እናስነብብለታለን። ምስኪን የሆድ አርበኛ! ስለ ህሊና ሳትናገር ዝም ብለህ የሰጡህን መኖ ጠቅጥቅ። መልካም መኖ ይሁንልህ ብለናል!

No comments:

Post a Comment