Translate

Thursday, April 28, 2016

ሰበር መረጃ…. ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች የነጻነት ሀይሎችን ተቀላቀሉ!

የትግራይ ነጻ አዉጪ ቡድን የመከላከያ ሚኒስቴር አመራሮች የደረሳቸዉን መረጃ ተገን በማድረግ 11.250 ( አስራ አንድ ሺ ሁለት መቶ ሐምሳ ) የሚጠጉ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በ5 ወራት ጊዜ ዉስጥ ከየመን ከሱዳናና ከሊቢያ ወደ ኤርትራ በመጓዝ አርበኞች ግንቦት 7ን ተቀላቅለዋል!!
ይላል… በሶስቱም ሐገራት የኢትዮጵያ ኢንባሲዎች ላይ የተሰመየዉ የመረጃ ቃል አቀባይ።
ምንጫችን እንደጠቀሱት የወያኔ ባለስልጣናት ከፍተኛ ድንጋጤ ላይ ወድቀዋል! 
በተለይም የመንና ሊቢያ የሚገኙ ብዛት ያላቸዉ ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰን በግፈኛዉ አጋዚ ከምንገደልና የወያኔ የግፍ እስር ቤቶች ዉስጥ ከምንማቅቅ ብሎም ማእበል ከሚበላን በረሐ ሄደን መስዋትነት በመክፈል ሐገራችን ነጻ ብናወጣ እንመርጣለን በሚል ዉሳኔ! ከሊቢያዋ ቶብሩክ ( TOBRUK ) እና አካባቢዉ በመነሳት የሐኒሽ ደሴቶችን በጀልባ በማቋረጥና የሱዳንን ድንበር በመጣስ ወደ አርበኞቹ ተቀላቅለዋል ።
ወታደራዊ ደህንነቱ ከፈተኛ ስጋት ላይ ከመዉደቁ የተነሳ ለሐገር መከላከያ ያቀረበዉን መረጃዎች ተንተርሶ የመንና ሊቢያ የሚገኙ ስደተኞችን ወደ ሐገር ቤት የመመለሱ ስራ ልዩ ትኩረት እንዲሰጠው ተወስኖ ወያኔያዊያን ባለስልጣን ያስመረሩትን ወጣት ትዉልድ ለማታታለልና ወደ ሐገር ለመመለስ የትራንስፖርት ወጪዎችንና የጉዞ ሰነድ ዝግጅቶችን በመበጅት ስራ ላይ ተጠምደዋ።
ይህን በተመለከተ ከአርበኞች ግንቦት 7 ወይም ከሌሎች የነጻነት ሐይሎች የተገኘ ፍንጭ ባይኖርም ከትግራዩ ነጻ አዉጪ ቡድን በኩል ግን እዉነታዉን የሚያረጋግጡ ድርጊቶች እየተስተዋሉ ይገኛሉ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
( ጉድሽ ወያኔ )
 

No comments:

Post a Comment