Translate

Tuesday, April 19, 2016

የወያኔ መንግስት የጋምቤላ ወገኖቻችንን መገደል ሆን ተብሎ የተቀነባበረ ነው ተባለ


በትናንትናዉ እለት የደቡብ ሱዳንና የኢትዮጵያ ወታደራዊ ከፍተኛ አመራሮች ተወያይተዋል!!
ዉይይቱ እጅግ የሱዳናዊያን ብቻ ነበር የሚመስለዉ ያሉት ዉስጥ አዋቂ መረጃችን….
ተቆርቋሪነታቸዉ ለሱዳናዊያን የሙርሌ ብሔር ወንጀለኞች የሆኑ ሁለት ወታደራዊ አመራሮች በተለየ መልኩ በድንበር ማስጠበቁ እና የድንበር ማካለሉ ስራን አስረግጠዉ አስቀምጠዋል


” እንደዚህ ያሉ የብሔር ግጭቶች በሰሜኑ የሱዳን ድንበርና ኢትዮጵያ መካከልም ይፈጠራል ያሉት የኛዎቹ የመከላከያ ጀኔራል ጉዶች ድንበር እስኪካለል ድረስ የሰሜን ሱዳናና የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት አባላት አብረዉ በጥምረት እየሰሩ እንደሆነና የደቡብ ሱዳኑም ያንኑ እንዲያደርግ ሐሳብ አቅርበዋል” 
የጋምቤላ ወገኖቻችንን ከ10 ቀበሌዎች በላይ ዘልቀዉ በመግባት የገደሉ አካላት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ወይም ወንጀለኞቹ በሕግ ቁጥጥር ስር እንዲዉሉ እንዲሁም ታፍነዉ በተወሰዱት 103 ሕጻናት ዙሪያ እና የደቡብ ሱዳኑ መንግስት ካሳ እንዲከፍል በመጠየቅ በኩል ያልተሳተፈዉ የወያኔ መንግስት ነገሩን ሆን ብሎ እንዲፈጸም ያደረገ መሆኑን ከስብሰባዉ መንፈስ ለመረዳት ተችሏል።
በመጀመሪያ ደረጃ ጋንቤላን በፌደራል መንግስት እጠቀልላለዉ ያለዉ ህወሃት የክልሉን መከላከያ ሰራዊት በመበረዝ ከቦርደር ላይ እንዲነሱ በማድረግና በምትካቸዉ ምንም አይነት ሰራዊት ሳያመጣ መሰንበቱ! እንዲሁም በሁለቱ ብሔሮች መካከል የተፈጠረዉ ግጭት አዲስ እንዳልሆነና በማንኛዉም ወቅት እንዲህ ያለ አደጋ ሊከሰት እንደሚችል መረጃ እያለዉ ጉዳዩን በቸልተኝነት ያለፈዉ የድንበር ማካለሉን ጉዳይ ከጋምበላ ወደ ጎንደር ለመዉሰድ የታለመ ሳይሆን እንዳልቀረ ተንታኞች እየገለጹ ነዉ።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የሙርሌ ብሔረሰብ ታጣቂ የተባሉት ወታደራዊ አቋም ያላቸዉና ልዩ ስልጠና የወሰዱ የደቡብ ሱዳን ወታደርዊ ዩኒፎርም እንዲሁም አንዳንዶቹ የኢትዮጵያን መከላከያ የደንብ ልብስ የለበሱ ሲሆኑ ግድያዉን ከፈጸሙ በኃላ የኢትዮጵያ መከላከያ ፈጽሞ ያለመኖሩን የተገነዘቡት የጋንቤላ ህዝቦች በመተባበር የሙርሲ ብሔር የተባሉትን ነፍሰ ገዳዮች በማሳደድ የመልሶ ማጥቃት እንደፈጸሙ ምንጫችን አረጋግጠዋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
( ጉድሽ ወያኔ )

No comments:

Post a Comment