Translate

Thursday, May 16, 2013

ልቅ የሆነ የሙስና ግንኙነት…


melaku_fenta
ልቅ የሆነ የሙስና ግንኙነት… (ትንሽ ወግ)
አቶ መላኩ ፈንታ መንግስት የሚያውቀው በሽታ አለብኝ እና በዋስ ልፈታ፤ አሉ አሉ፤…
እኔ ደግሞ እንዲህ አልኩ፤
ምን ነካዎ አቶ መላኩ፤ መንግስት በሚያውቀው በሽታዎ ነውኮ ዘብጥያ የወረዱት፤ እርግጥ ነው ይህንን በሽታ ከየትም አላመጡትም፤ ከመንግስትዎ ጋር ባደረጉት ጥንቃቄ የጎደለው እና ልቅ የሆነ የሙስና ግንኙነት እንደሆነ ይታወቃል፡፡ እርግጥ ነው መንግስታችን ራሱም የዚህ በሽታ ተጠቂ መሆኑ እሙን ነው፡፡ እርግጥ ነው በማራዘሚያ ብዛት እንጂ ሁሉም ባለስልጣኖቸች የዚህ ህመም ሰለባ መሆናቸውም ግልጽ ነው፡፡
ታድያ መንግስት የሚያውቀው በሽታ ስላለብኝ ማሩኝ ከማለት በሽታውን ያመጣሁት ከእነርሱ ነውና ሁሉም ይምጡ ማለት አይሻልዎትም ነበር… ሃሃ (በቅንፍም የምር ግን ምንድነው መንግስት የሚያውቀው በሽታ…)

አቶ ገብረዋህድ ገብረ መድን በቤተሰቦቼ ላይ ኢሰብአዊ ድርጊት ተፈጽሞባቸዋል… ሀገሪቱ ምን አይነት ሀገር እየሆነች ነው… ብለዋል አሉ፡፡
እኔ ደግሞ እንዲህ አልኩ፤
አቶ ገብረዋህድ ቆየችኮ እርስዎ በስልጣን ነጠላ ሰረዝ በዶላር ነጠላ ሰረዝ በፓውንድ እና በብር የሞቀ ቤትዎ ሆነው የውጪው ቅዝቃዜ አልታወቅዎትም እንጂ “ሀገሪቱ ምን አይነት ሀገር እየሆነች ነው…” የሚለውን ጥያቄ እኮ እነ አቶ አንዷለም አራቄ መጠየቅ ከጀመሩ ቆዩ፣ ሀገሪቷ ምን አይነት ሀገር እየሆነች ነው የሚለውን ጥያቄ እነ አቶ በቀለ ገርባ ጠይቀው ማንም መልስ አልሰጣቸውም፡፡
በቅርቡ እንኳ አቡበከር በቴሌቪዥን እጁን በካቴና ታስሮ ፖሊሶች ሲሳሳቁበት በአደባባ እያየን ሁላችንም በአንድ ድምጽ ሀገሪቷ ወዴት እየሄደች ነው… ብለን ጠይቀን ነበር፡፡ ግን እርስዎም ሆኑ ጓደኞችዎ ድምፃችን አልሰማችሁም፡፡
እነ ርዮት አለሙ እነ እስክንድር ነጋ እነ ውብሸት ታዬ በፍትህ እጦት እና በኢሰብአዊ አያያዝ ተማረው “ሀገሪቷ ምን አይነት በያይነቱ ሆነች…” ብለው ከጠየቁ ቆዩኮ… ታድያ ያኔ የት ነበሩ… (በቅንፍም ይቺን ነገር ሁሉም ባለስልጣን በየተራ ይያት ብለን እንመርቃለን)
ፀረ ሙስና ኮሚሽን ሌሎችንም ሙሰኞች አጋልጡ ብሎ ስልክ ቁጥሩን ሰጥቶናል፡፡ አሉ
እኔ ደግሞ እንዲህ አልኩ፤
እኔ የምልህ ፀረ ሙስናዬ የምን ቁጥ ቁጥ ነው ብዬ… አጠቃላይ ኢህአዴግን በሙስና ብልግና ብጠቁም ለማሰር የሚያስችል ሰፊ ቃሊቲ አለህ… ከሆነ ዛሬውኑ እደውላለሁ…!
Abe Tokchaw

No comments:

Post a Comment