Translate

Tuesday, October 22, 2013

ትእምት የህወሓት ንብረት እንጂ የትግራይ ህዝብ ሃብት እንዳልሆነ የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ኣባልና የማረት ሓላፊ ኣቶ ተክለወይኒ ኣሰፋ ተናገሩ

! ……. የገዢዎቻችን ነገር ……….!
ኣንድ
በ1993 ዓም የህወሓት ክፍፍል መለስ የነ ስየ/ተወልደ ቡድን ለማሸነፍ በህወሓት ሰነፎች (የራሳቸው ነፃ ሓሳብ ያልነበራቸው) የፓርቲው ሰዎች ኣሰባስቦ ‘እኔን መርጠዋል’ ብሎ በህወሓት ሊቀመንበርነቱና የጠቅላይ ሚኒስተር ስልጣኑ ይዞ እንደሚቆይ ኣሳወቀ። ኣቶ ኣባይ ወልዱም ይሄንን ‘የመለስ ራእይ’ (ሰነፎች ማሰባሰብ፣ ጎበዞች ማባረር) እየተገበረ ይገኛል።
ሰነፎቹ ስልጣን ተረካቢዎች ኣሁን የጠበቁት የህዝብ ድጋፍ ባለ ማግኘታቸው ግራ ተጋብተው የሚናገሩትን ነገር እስካለማወቅ ደርሰዋል። በተለይ ኣዜብ መስፍንና ኣባይ ወልዱ (እንዲሁም ስብሓት ነጋ) ለሚናገሩት ነገር ‘ይቅር’ እንበላቸው። ብቁ ፖለቲከኞች ኣለመሆናቸው እየነገሩን ነው። ጭንቀታቸው በኣደባብይ ሲናገሩ ያሳዝናሉ።
ሁለት
የህወሓት መሪዎች ከስልጣን መውረድ የማይፈልጉበት ምክንያት (1) እስካሁን የሰሩት ጥፋት እንዳይጋለጥ ይሰጋሉ። (2) የትእምትን ሃብት ማጣት ኣይፈልጉም። (3) ፓርቲው ስልጣን ከለቀቀ ልክ እንደ የድሮ የደርግ ባለስልጣናት በጠላትነት ተፈርጀው ከሀገር የሚባረሩ ይመስላቸዋል።
‘ትእምት ግን የማን ነው?’ ብለን ስንጠይቅ መልሱ ‘የህወሓት መሪዎች’ የሚል እንደሚሆን ግልፅ ነው። ባለፈው የህወሓት ማእከላዊ ኮሚቴ ኣባልና የማረት ሓላፊ ኣቶ ተክለወይኒ ኣሰፋ ትእምት የህወሓት ንብረት እንጂ የትግራይ ህዝብ ሃብት እንዳልሆነ መናገሩ የሚገልፅ post ኣድርጌ ነበር። (መረጃው ያገኘሁት ከፌስቡክ ጓደኛየ ነበር)። መቼና የት እንደተናገረው መጥቀስ እንዳለብኝ ከጓደኞቼ ኣስተያየት ደርሶኛል።
ከተሰጡኝ ኣስተያየቶች በመነሳት ለማጣራት ስሞክር ተክለወይኒ ኣሰፋ ይሄን የተናገረው ባለፈው ዓመት ሮብ ሚያዝያ 10, 2004 ዓም ሲሆን ቦታው በMIT የስብሰባ ኣዳራሽ እንደነበር ለመረዳት ችያለሁ። ‘ለምን ያን እንዲናገር (ኣምኖ እንዲቀበል) ተገደደ?’ የሚለውን ጥያቄ መመለስ ተገቢ ነው፣ ምክንያቱም ብዙ ግዜ (ወይ ሁልግዜ) የህወሓት መሪዎች ትእምት የግል ሃብታቸው መሆኑ እያወቁ ለፖለቲካ ፍጆታ ሲባል ግን ‘ትእምት የህዝብ ነው’ ይሉን ነበር።
MIT (Mekelle Institute of Technology) ሲቋቋም ዓላማው የክልሉ ጎበዝ ተማሪዎች ተመጠው እዛው ተምረው ገዢውን ፓርቲ በታማኝነት እንዲያገለግሉ ታስቦ ነበር። ቁስ ነገር በመስጠት ጎበዝ ልጆችን ባርያ ኣድርጎ ለመግዛት፣ ይህንን ካልተቻለ ደግሞ ስርዓቱ እንዳይቃወሙ ለማድረግ ነ ው። ህወሓቶች ጎበዝ ተማሪዎችን (ወይ ሙሁራን ባጠቃላይ) ይፈራሉ። ምክንያቱም እነሱ በደምብ የሚያውቁት በሓሳብ ማሸነፍ ሳይሆን ተኩሶ መግደል ነው። ኣሁን የቸገራቸው ይሄንን ነው፤ (ውድድሩ በጠመንጃ ሳይሆን በሓሳብ መሆኑ)።
የMIT ተማሪዎች ግን ህወሓቶች እንደጠበቁት (ስለበሉ ስለጠጡ) ‘ታማኝ ኣገልጋዮች’ መሆን ኣልቻሉም። ጥያቄዎች ማንሳት፣ መብት መጠየቅ፣ መቃወም … ምናምን ጀመሩ። ማስተካከል እንዳለባቸው ተነገራቸው። ኣልተሳካም። ህወሓቶች በጉዳዩ ተሰብስበው ተወያዩ። ‘እነዚህ ተማሪዎች በራሳችን ገንዘብ ኣስተምረን ለኛ ጠላቶች እየፈጠርን ነን።’ (MIT fund የሚደረገው ከትእምት ነበር)። እንደዉጤቱም ‘ጠላቶች’ ለመፍጠር ገንዘባቸው ማባከን እንደሌለባቸው ተስማምተው የMIT ቡጀት ተዘግቶ ተቋሙ ወደ መቐለ ዩኒቨርስቲ እንዲጠቃለል (በጀቱ ከፌደራል መንግስት እንዲሆን ተወሰነ)።
ይሄን ዉሳኔ የMIT ማህበረሰብ ተቃወመው (በወቅቱ ስለ ጉዳዩ ፅፌ ነበር)። ብዙ ችግር ተፈጠረ። የህወሓት መሪዎች የMIT ማህበረሰብ (ተማሪዎችና ኣስተማሪዎች) እየሰበሰቡ ማነጋገር ተያያዙት ። ከነዚህ መሪዎች ኣንዱ ተክለወይኒ ኣሰፋ ነበር። እሱ ተማሪዎቹን ሰብስቦ በበጀት እጥረት ምክንያት MIT fund ማድረግ እንደማይችሉና የመቐለ ዩኒቨርስቲ ኣካል መሆን እንዳለበት ይነግሯቸዋል። ሰመረ የተባለ ተማሪ እጁን በማውጣት ‘ትእምት የትግራይ ህዝብ ሃብት ነው ትሉናላቹ ግን በትክክል የህዝብ ከሆነ ለምን ለህዝብ በሚጠቅም መልኩ ኣታውሉትም?’ ብሎ ይጠይቃል። ተክለወይኒም በጣም ተናዶ “ማን ኣለህ ዉሸታም! ትእምት (EFFORT) የህወሓት ነው፤ ህዝብ ደሞ ማነው?” (“መን ኢሉካ ሓሳዊ! ትእምት ናይ ህወሓት እዩ። ታይ እዩ ህዝቢ ኸ?” ብሎ መለሰለት።
ተክለወይኒ እንዲህ መናገሩ ምን ኣዲስ ነገር ኣለው? ኣዲስ ነገር ኣይደለም። ምናልባት ኣዲስ ከሆነ ግን በራሳቸው ኣንደበት በህዝብ ፊት መናገራቸው ብቻ ነው እንጂ የህወሓት መሆኑማ ማንም ሰው ያውቃል። ኣሁን ኣሁን እኮ ግን ትእምት የህወሓት ኣባላት መሆኑ ቀርተዋል። ትእምት የሁሉም ኣባላት ኣይደለም። ትእምት የተወሰኑ የህወሓት መሪዎች የግል ሃብት ነው። የጥቂት ሰዎች ነው።
ሦስት
በመኾኒ በሺዎች የሚቆጠሩ መኖርያ ቤቶች እንደሚፈርሱ በመንግስት ኣካላት ከተነገረ በኋላ ኗሪዎቹ ኣማራጭ መጠልያ እንዲዘጋጅላቸው ቢጠይቁም መፍትሔ እንዳላገኙ ጠቅሼ ነበር። ከዚህ በመነሳት “ቤቶቹ የሚፈርሱት በምን ምክንያት ነው?” የሚል ነገር ተነስተዋል። የሚፈርስበት ምክንያት “ሕገ ወጥ ግንባታ” ተብሎ ነው።
በመኾኒ ወደ 7 ሺ የሚጠጉ ቤቶች ‘ሕገ ወጥ’ ከሆኑ ‘ሕጋዊ የሆነ ቤት የለም’ ልንል ነው። ግን ይህን ሁሉ ቤት ‘በሕገውጥ መንገድ’ ሲገነባ (ለብዙ ዓመትም ኑሮበታል) ኣስተዳዳሪዎቹ (የመንግስት ተወካዮቹ ) የት ነበሩ? እስኪገነባ ድረስ ዝም ብለው እያዩ ነበር ወይስ ከተገነቡ በኃላ፣ ኣገልግሎት መስጠት ከጀመሩ በኋላ ነው ‘ሕገወጥ’ የሆኑት? ‘ሕገወጥ’ ቤት ከተገነባ ከጅምሩ ነው መቆም የነበረበት። ራሳቸው ይፈቅዳሉ፣ ይሰጣሉ፣ በኋላ ያፈርሳሉ። ይህንን ተግባር በነዋሪዎቹ የሚፈጥረው የስነ ልቦና ችግር ቀላል ኣይደለም። እንደዚህ ዓይነት ችግር ከመልካም ኣስተዳደር እጦት የሚመነጭ ነው።
የህወሓት መሪዎች ያዳላሉ። ምሳሌ ልስጣቹ፡ ከተወሰኑ ዓመታት በፊት በመቐለ ከተማ የመኖርያ ቤቶች ግንባታ ጉድ ነበር። ብዙ የከተማው ነዋሪዎች ‘ሰራዋት’ ተብሎ በሚጠራ ኣከባቢ (የከተማው ኣስተዳደር ፍቃድ ኣግኝተው፣ ማንም ሳይከለክላቸው) በሺዎች የሚቆጠሩ ቤቶች ተገነቡ። ኣገልግሎት መስጠት ጀመሩ።
በተመሳሳይ መልኩ (በተመሳሳይ ግዜና ሁኔታ) ግን ለየት ባለ ቦታና ለየት ባሉ ሰዎች ሌላ ዓይነት ቤቶች (ቪላዎች) ይገነቡ ነበር። እነዚህ ለየት ባለ ቦታ የተገነቡ ቪላዎች Hill Top Hotel ኣከባቢ በሚገኝ ‘ልዩ መንደር’ ነው። ‘ልዩ መንደር’ ያልኩበት ምክንያት እዛ ኣከባቢ ቤት መስራት የሚፈቀድለት ሰው የህወሓት ከፍተኛ ባለስልጣን መሆን ኣለበት። ሌላ ተራ ሰው እዛ ኣከባቢ ቤት መስራት ኣይፈቀድለትም። በወቅጡ የነበረ “ጥሕሎ” የተሰኘ መፅሔት “ኣፓርታይድ መንደር” ብሎ ሰይሞታል። እስካሁንም “ኣፓርታይድ መንደር” ተብሎ ይጠራል። ባለስልጣናቱ ለብቻቸው ተለይተው የሚኖሩበት ሠፈር ስለሆነ ነው።
ሁለቱም የ’ሰራዋት’ (የሰላማዊ ሰው)ና ‘ኣፓርታይድ መንደር’ (የባለስልጣናቱ) የቤት ግንባታዎች ማንሳት ለምን ኣስፈለገ? በሰራዋት የተገነቡ ቤቶች ሁሉም በግፍ (በዶዘሮች) እንዲፈርሱ ሲደረግ የባለስልጣናቱ (ኣፓርታይድ መንደር) ግን ማንም ሳይነካው እስከኣሁን ድረስ ኣለ። የተራ ህዝብ ፈረሰ (ሕገወጥ ተባለ) የራሳቸው (የባለስልጣናቱ) ግን ‘ሕጋዊ ሆነ’ (ምክንያቱም እነሱ ኮ ከሕግ በላይ ናቸው)።
ወይ ኣድልዎ!  Abraha Desta

No comments:

Post a Comment