Translate

Thursday, October 3, 2013

በጣሊያን ጀልባ ሰጥሞ ከ90 የሚበልጡ አፍሪካውያን ስደተኞች ህይወት አለፈ

 በመቶዎች የሚቆጠሩ አፍሪካውያን ስደተኞችን ይዛ ወደ ላምቤዱሳ ደሴት በማቅናት ላይ የነበረች አንዲት ጀልባ  እሳት  ተቀስቅሶባት  በመስጠሟ 92 ሰዎች ሞቱ ።
በጀልባዋ ላይ የተቀሰቀሰውን እሳት ለማምለጥ ስደተኞቹ ወደ ባህር መዝለላቸውና  ጀልባዋም መስጠሟ  ተነግሯል ። 150 የሚጠጉ ሰዎችን ህይወት ማትረፍ  እንደተቻለ ፖሊስ አስታውቋል ።
200  የሚሆኑ  ስደቶች  ግን እስካሁን  የደረሱበት  ያልታወቀ ሲሆን ፥  የሟቾች ቁጥርም አሁን ከተጠቀሰው  በላይ  ሊሆን  እንደሚችል ተገምቷል ።
ከስደተኞቹ መካከል  የሚበዙት  ኤርትራውያንና  ሶማሊያውያን ሲሆኑ ፥ አንድ ህፃንና  አንድ ነፍሰ ጡር ሴትም  ይገኝተውበታል ።
በአሁኑ ወቅት  የሜዲትራኒያን ባህር የተረጋጋ ሁኔታ ያለው በመሆኑ  በየእለቱ አፍሪካውያን ስደተኞችን የያዙ ጀልባዎች በደቡባዊ የጣሊያን  የባህር ዳርቻ  እንደሚደርሱ  ነው የሚነገረው ።
ሆኖም ስደተኞቹን የሚጭኑት ጀልባዎች ጤንነት አሳሳቢ በመሆኑ  አሳዛኝ ክስተት በአከባቢው  እየተደጋገመ መጥቷል ።
የመንግስታቱ  ድርጅት  የስደተኞች ጉዳይ ደርጅት እንደሚለው  በዚያ  አከባቢ  ችግር ባለባቸው ጀልባዎች በመሰፈራቸው በየዓመቱ በተንሹ 1  ሺህ 500 የሚሆኑ  ስደተኞች ባህር ላይ  የቀራሉ ።

ምንጭ ፦  ቢቢሲ

No comments:

Post a Comment