Translate

Monday, June 5, 2017

ሰበር ዜና – በሰሜን ጎንደር ዋግ ሃምራ ወያኔ ጥቃት ደረሰበት

በልኡል አለሜ (ግንቦት 28/2009)
TPLF security members killed in Gondar
የህወሃት ወታደራዊ ደህንነቶች ባቀረቡት መረጃ መሰረት በምእራብ አቅጣጫ በሰሜን ጎንደር ዋግ ሃምራ፣ እንዲሁም ደባርቅ፣ ዳባትና፣ እንፍራዝ አካባቢዎች ላይ ወታደራዊ አሰሳና ጥቅት ለማድረግ ታስቦ የነበረ ቢሆንም ኦፐሬሽኑ ትናንት ሙሉ ለሙሉ ተሰርዟል!

በዋግ ሐምራ ድንበር ዘለል ጥቃት ለመፈጸም ተንቀሳቅሶ የነበርዉ 105 የሚጠጋ በልዩ ሐይል እና በ24 ተኛ ክ/ጦር አመራሮች የተዋቀረዉ ኮማንድ ሙሉ ለሙሉ ተበትኖአል!
በህወሃት አየር ሐይል በረራ ክንፎች ጭምር የጠፉ ወታደሮችን ለመፈለግ ጥረት ቢደረግም የተገኘ ፍንጭ እንደሌለ ታውቋል፣ በተለየ መልኩ የተደረገዉን የጥቃት ዉጥን ስኬታማ ለማድረግ RF23 (handheld transceiver) የሬዲዮ መገናኛዎች AK47፣ C39፣ FG32፣ MP44 የእጅ መሳሪያዎች የደረሱበት አልታወቀም።
የምንጫችን መረጃ እንደሚያመለክተዉ የህወሃት አሳሽ ቡድን ወታደሮቹ ባጠቃላይ ከነያዙት ትጥቅ መደመሰሳቸዉን ወይም መሰወራቸዉን ለማረጋገጥ ባለመቻሉ አሰሳዉን አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን አሰሳዉን የሰሜኑ እዝ የአየር ሐይል ጀቶች ዝቅ ብለዉ በመብረር ህወሃታዊ ድንጋጤያቸዉን አድምቀዉታል።

No comments:

Post a Comment