Translate

Monday, May 26, 2014

አቶ ስብሃት ነጋ – የእንደራደር ጥያቄዎን በታማኒ ተግባር ይጀምሩት!

ከአቢቹ ነጋ

ከዚህ በፊት የግንቦት ሰባት ድርጅት የንደራደር ጥያቄ ከኢትዮጵይ መንግሥት አንደደረሰው በአፅኖት አውርቶናል። ብዙ ሕዝብ የግንቦት ሰባትን ዜና በማድቤት የተፈበረከ እራስን የመካቢያ ወሬ አድርጎት አንደነበር አይዘነጋም። እኔ ግን ዜናውን አንደወረድ መቀበል ብቻ ሳይሆን ደስተኛም ነበርሁ። ኢትዮጵያን አግዚአብሔር አንደሚጠብቃትም ያመንሁበት ወቅት ነበር ማለት ይቻላል። የዋህ ላገር ቅን አሳቢ ስለሆንህ እንጅ ከእባብ የርግብ አንቁላል እንዴት ትጠብቃለህ ብባልም የባብ መርዝም መዳህኒት ሊሆን እንደሚችል ይታወቅ ብያለሁ።TPLF power broker, Sibehat Nega
ከሁልም ያስደስተኝ ግን ግንቦት ሰባት ጥያቄውን በሕዝባዊ መግለጫው ያስተናገደበት ዘዴ ነበር። አንዳንድ ሰዎች ድርጅቱ በኢሃዴግ ተጠይቆ ከሆነ ጉዳዩን በምስጢር ይዞ ማካሄድ ነበረበት ብለዋል። የሕዝብን ጉዳይ ይፋ ማድረጉ የሚአስመሰግነው እንጅ ሊአስወቅሰው አይገባም። ከሁሉም በጣም የሚአስደስተው ደግሞ ድርጅቱ ከመንግሥት ጋር በጠረጴዛ ዙሪያ ለመወያየትና ለመደራደር ዝግጁ መሆኑን ጠቅሶ ለድርድሩ ታማኒነት መንግሥት በቅድሚያ ማድረግ ያለበትን ነገሮች ይፋ ማድረጉ ነበር። በመሰረቱ ይህ ከፍተኛ የሆነ ያገር ጉዳይ ለህዝብ ምስጥር የሚሆንበት ምክንያት ውሃ የሚቋጥር አይሆንም። ድርድሩ ቢጀመር ግን ሂደቱን የሚአደናቅፉ ሁኔታውች አንዳይከሰቱ ሲባል በምስጢር ሊያዙ የሚችሉ ጉዳዮች ግን ይኖራሉ። በዚህ ድርጊቱ ግንቦት ሰባት የመንግሥትን ሀቀኝነት ፈትሾታል ቢባል ማጋነን አይሆንም።

ስለሆነም የግንቦት ሰባት መግላጫ ቀለም ሳይደርቅ የመንግሥት መገናኛ ምኒስተር የማስተባበያ መግለጫ ወዲአው አወጣ። ማስተባበያውም በይዘቱ ቀላልና ተራ ሲሆን ድርጅቱን ኮንኖ ከመንግሥት ለተቃዋሚዎች ያቀረበው የንደራደር ጥያቄ አለመኖሩን አበሰረ። ልክ ተራ ሰዎች እንዳሉት መንግሥትም ግንቦት ሰባት እራሱን ለመኮፈስ የተጠቀመበት ባዶ ፕሮፖጋንዳ ነው አለ። መንግሥት የፖለቲካ ክስረትና ታማኒነት የጎደልው መሆኑን በራሱ አወጀ። መግለጫው መሰረተቢስ ቢሆን አንኳን መንግሥት ራሱን ከፍ አድርጎ በማየት የእንደራደር ጥያቄውን በኩራት ሊቀበለው በተገባ ነበር። በዚህም መንግሥት ከአጥቂነት ወደተከላካይነት ራሱን ዝቅ አድርጎ ታይቱዋል።
ያለእሳት ጭስ አይኖርም እንዲሉ ሰሞኑን በጀርመን የአማርኛ ራዲዎ ላይ በተደረገ ውይይት አቶ ስብሃት የንደራደር ጥያቄን በማያሻማ ሁኔታ ተናግረዋል። ኢትዮጵያን የገጠማት ዘርፈ ብዙ ችግር ለመፍታት ሕውሓትና ኢሓዴግ ከተቃዋሚወችና ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋረ ለድርድርና ለውይይት ራሱን ማዘጋጀት እንዳለበት ባጽንኦት ገልጸዋል። እባብ ያየ በልጥ ይደነግጣል አንዲሉ በተቃዋሚ ጎራ የሚገኙ ሰዋች የአቶ ስብሃትን ጥሪ በከፍተኛ የጥርጣሬ ዓይን ተመልክተውታል። በተልይም የሕውሓትን የጀርባ አጥንት ከምስረታ ጀምሮ ስልጣን አስከያዘበት ገዜ ያለውን በሓሪ ለሚአውቁ ሁሉ ማመን ተስንዋቸዋል። ሆኖም ሌባ ይመጣል ተብሎ ሳይተኛ አይታደርም እንዲሉ የድርጅቱ ችግር አንዳለ ቢሆንም በወቅታዊ የፖለቲካ ሁኔታዎች አስጋዳጅነት ይህ አይሆንም ማለት አይቻልም። እንደዚህ ጸሓፊ ግንዛቤ የፖለቲካ አስተያየት በወቅቱ ባለው የማህበራዊ፣ ኢኮነሚያዊ፣ ፖለቲካያዊ ጭብጥ ሀኔታና ገምግሞ መሰረታዊ አቋምን ማንጸባረቅ ግድ ይላል። በዚህ ላይ ስምምነት ከተገኘ ፖለቲካ ደግሞ መቻል በሚቻልበት ጊዜ የሚከናወን የኪነጥበብ ስራ (Politics is the Art of the Possible) ይሆናል ማለት ነው።
ወያኔ ኢሃዴግ ኢትዮጵያ አሁን ከፍተኛ አጣብቂኝና ብሎም መስቀለኛ መንገድ ላይ አንዳለች ተረድተዋል። ሁኔታው ባለበት ከቀጠለ አገር የሚባለው ነገርም ላይኖር ወደሚቻልበት አዝማሚያ አየተጓዘ መሆኑን ይገነዘባሉ። ሃያ ሶስት ዓመት ሙሉ በሕጋዊም ሆነ በሕገወት መንገድ የተካበተው ሃብት፤ ንብረትና እንገነባለን የተባለው የትግራይ ሪፑብሊክም እውን ወደማይሆንበት ደረጃ እደተደረሰና የሁሉም መጥፊያ መቃረቡን ከነሱ የበለጠ የሚረዳ አይኖርም። አርባ ዓመት ሙሉ ፖለቲካ ጸንሰው፤ ወልደው፤ አሳድገውና ተግብረው ፤ አኝከውና ተመግበው ያደጉ የህውሃት ሰዎች ይህን መጻኢ ችግር አይርዱም ብሎ የሚአስብ ተቃዋሚ ካለ የፖለቲካ ድርቅ የመታው በቻ ነው።
ሁላችንም ከምንጠፋ ተወያይተን ችግራችንን አንፍታ ብለው ቢአስቡ የሚደንቅ ካለመሆኑም በላይ ባብዛኛው ተጠቃሚ የሚሆኑት በስልጣን ላይ ያሉት ፖለቲከኞች ናቸው። ምክንያቱም በስልጣን፤ በሃብት፤ በምቾትና በብልጽግና የካበቱት እነርሱ ብቻ ስለሆኑ በሕይወትም ኪሳራ የሚደርሰው በመጀመሪያ በነሱ ላይ አንደሚሆን ጥርጥር የለውም። ተቃዋሚውማ አሁን ካጣው በበለጠ ሊአጣው የሚችል የሃብት፤ የሕይወት፤ የንብረትና የኖሮ ኪሳራ ይኖራል የሚል እምነት አይኖርም። ተቃዋሚው ማጣት የማይፈልገው ነገር ቢኖር ሉአላዊነትዋ የተጠበቀች አንዲት አገርን ነው ። ይህ ደግሞ የሁላችንም ክስረትና መጥፊያ ስለሆነ ሁላችንም የድርሻችንን ማድረግ የተጠበቅብናል።
ስለዚህ አቶ ስብሃት ደጉን ነገር አስበዋልና እንቀበላቸው ። ለዚህ ምክንያቱ ብዙም ቢሆን ግለሰቡ የሕውሓት መስራች፤ የድርጅቱ አንጋፋ መሪ፤ የሕውሓት ዋና አማካሪና ተድማጭ በሎም ፈላጭ ቆራጭ በመሆናቸው ድርጅታቸውን በቀላሉ ያሳምናሎ በሎ መገመት ይቻላል። በተጫማሪ ትግራይና ሕዝብዋ በሕውሃት ላይ ፊቱን ካዞረ ቆይትዋል። መሰረታዊ የፖለቲካ አምባቸውን ማጣታቸውብዙ ተወርቶለታል። ለአረና ትግራይ ንቅናቄና አስተምህሮት ምስጋና ይግባውና።
እንደአብነት ለመጥቀስ ያህል ባለፉት ወራት የትግራይን ሕዝብ ድጋፍ ለመጠየቅና ለመቀሰቀስ አንጋፋዎቹ የሕውሃት መስራቾች ስብሃት ነጋ፤ አባይ ጽሐየ፤ ስዩም መስፍንና ዓባይ ወልዱ በተለያዩ አውራጃወችና ወረዳዎች ተዘዋውረው ሕዝቡን ለመቀስቀስ ሞከረዋል። በሁሉም ቦታ በሚባል ደረጃ የገጠማቸው ተቃውሞና ጥያቄ አንድወጥ ነበር። ከሕዝቡ የተሰጣቸው መለእክት መልክተኞችንና ድርጅታቸውን ከማሰደንገጡም ባሻገር አከርካሪአቸው ተሰብሮ በመጡበት አንዲመለሱ አንዳደረጋቸው በቅርብ የሚከታተለው አብርሃ በላይ ከመቀሌ ነግሮናል።
የትግራይ ህዝብ መሰረታዊ የሆኑ ጥያቄውችን አንስቶ አስታንግድዋቸዋል። ከጥያቄዎች ውስጥ በዋናነት የሚጠቀሱት ሕውሃት በትግራይ ሕዝብ ስም አየነገደ ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር አጣልቶና አጋጭቶ ደም እንዲቃባ መደረጉ፤ ኢትዮጵያን የመሰለ ታሪካዊ ሃገር ታሪክ አልባና ወደብ አልባ መሆንዋ፤ የሃገሪቱ መሬትና ግዛት እየተቆረሰ ለባእዳን ሃገሮች የጅመንሻ መደረጉ፤ ይህ ድርጊት በቀደሙት መንግሥታት ተደርጎ የማያውቅ አሳፋሪና አዋራጅ ስራ በትግራይ ሕዝብ ስም መፈጸሙ ያበሳጨው ለመሆኑ በማያሻማ ሁኔታ ተነግሩዋቸዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ ተጋብቶ ተዋልዶ አንዳልኖረ ሁሉ በክልልና በቋንቋ ለያይታችሁ አርስበርሱ ለማበላት ማንኛውንም መሰናዶና ዝግጅት በትግራይ ሕዝብ ስም እይፈጸማችሁ ይገኛል።
መልካም አስትዳደር ጨርሶ ጠፋ። እናነተው ቀማኛ አናነተው ዳኛ ሆናችሁ ሕዝቡ ሕግን አጥቶ ቶጉላላ። መንግሥት ዘራፊና ነጣቂ፤ ጉቦኛ፤ የልማት ደንቃራ፤ የሃይማኖት ጸር፤ ሕዝብ በሰላም በቤቱ ማደር አልችል አለ፤ ስራአጥነት በረከተ፤ አገርም ልትፈርስ አፋፍላይ ቆማለች በማለት እንደነገራቸውና ለነዚህ ጉዳዮች መልስ ይዛችሁ የምትመጡ ከሆነ አንቀበላችሁአለን ብሎ አንዳሰናበታቸው ተነግሩዋል። በሌሎች ክፍላተሃገራትም የገጠማቸው ተቃውሞ ከዚህ ቢበልጥ አንጅ ያላነሰ መሆኑን ስብሃትና ጓደኞች አበጥረው ያውቃሉ። ሕውሓትና ኢሃዴግ ማስተዳደር እየተሳነቸው መምጣቱም ተነግርዋል። ያአማረ አረጋዊን ሪፖርተር ጋዜጣ ርዕሰ ዓንቀጾችና ክቡር ምኒስተር በሚል የሚጽፈውን በተጨባጭ ሁኔታ ላይ የተመረኮዘ አሽሙር ነክ ጽሁፍ ላነበበ የመንግሥትን ክሽፈት መረዳት ይችላል። የሕውሓት ዋና አፈቀላጤ የኢትዮጵያ ፈርስቱ (ቤን) ከሁለት ወራት በፊት በቁጣ መልክ ያበሰረው እውነታ በቂ መስክር ነው። ከለጋሽ አገሮች የሚደርስባቸው ፖለቲካዊና የኢኮኖሚያዊ ጫናም በቀላሉ የሚታይ አይደለም። በመካከለኛው አፍሪካ ሬፑብሊክ፤ በሱዳንና በደቡብ ሱዳን ያለው ቀውስ፤ በኮንጎና በናይጀሪያ ያለው የርስበርስ ግጭት፤ በሶማሊያ ያለው ትርምስ፤ በየአሃጉሩና ሃገራቱ የሚነሳው የሃይማኖት ግጭት ሕውሓት/ኢሃዴግን አያስደነግጠውም፤ አያሳስበውም የሚል ፖለቲከኛ ካለ የፖለቲካ ሃሁ ያልቆጠረ ብቻ ነው። ሌላው ቢቀር ለራሱ ህልውና ሲል ኢሃዴግ ለድርድር አይመጣም ማለት አይቻልም።
አቶ ስብሃት በማያሻም መልኩ ሃላፊነቱን ወሰድው የድርድሩን ስራ ለመጀመር መድፈራቸውና መፈለጋቸው ብቻ በራሱ ሊአስመሰግናቸው ይገባል። ላለፈ ክረምት ቤት አይሰራም አንዲሉ ከዚህ በፊት የተሰሩ ስሕተቶችን በማመንዥግ የሚገኝ ትሩፋት አይኖርም። መታወቅ ያለበት ሑላችንም ያንድ አገር ልጆች ነን። ችግሮችን በመወያየትና በመቻቻል ለመፍታት መሞከር የስልጣኔ ምልክት ብቻ ሳይሆን ታላቅነታችንንም የመናስመክርበት አጋጣሚ ይሆናልና እንጠቀምበት። እንግዲህ አቶ ስብሃት ኢንሴንቲቩን መውሰደ አችላለአሁ በማለታቸው ብቻ ያምበሳውን ድርሻ አንደያዙ ይወቁት። ለድርደር ዝግጁ መሆናቸውን ደግሞ ታማኒነት ያለው ሰራ በቅድሚያ በመሰራት እንዲአሳምኑን በጉጉት እንጠብቃለን። ካላደረጉት የሚአፍሩት አቶ ስብሃትና ኢሃዴግ በቻ ናቸው። አገርም በክስረት ጎዳናዋ ትቀጥላለች።

No comments:

Post a Comment